Friday, March 9, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እንዲከላከሉ ተወሰነባቸው!

 ሊቀ ትጉሃን ተሾመ ኃይለ ማርያም በ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሤራ በፖሊስ ተይዘው ወደ ነጌሌ ቦረና ተወሰዱ

በቆሞስ መልአከ ገነት አባ ሙሉጌታ ታዬ የክብረ መንግሥት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ላይ የተቃጣው የግድያ ሙከራ ከሸፈ

የካቲት 16 ቀን 2004 ዓ.ም በክብረ መንግሥት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚከበረውን የቅድስት ኪዳነ ምሕረት በዓለ ንግስ በመረበሽ ያስተጓጎሉት ሃያ አምስት የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና አፍቃሬ ማኅበረ ቅዱሳን ተከሳሾች ለመጋቢት 19 ቀን 2004 ዓ.ም ቀነ ቀጠሮ ቀርበው እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል፡፡ ዐቃቤ ሕግ አሥራ ሦስት ምሥክሮችን ያሰማ ሲሆን ክሱን በጽሑፍ፣ በሰውና በምስል ማስረጃ አጠናቅሮ አስረድቷል፡፡ በተጨማሪም ሰባት ምሥክሮች ቃለ መሐላ ከፈጸሙ በኋላ ዐቃቤ ሕጉ በቃኝ ሳይሉ ምክንያቱ በግልጽ ባልታወቀ ምክንያት ዳኛው አቶ ጉዩ እንዳይመሠክሩ አስቁመዋል ተብሏል፡፡  
በዚህም ሳቢያ ስምንት ቀንደኛ በጥባጮች በዚያው ዕለት 29/6/2004 ዓ.ም በነፃ አሰናብተዋቸዋል ተብሏል፡፡ ከነዚህ ስምንት ቀንደኛ መሪዎች ውስጥ መሪጌታ መዝገቡ ጌታነህ፣ ቄስ መኮንን ጉቴሳ (የአንድ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የታሪክ መምህር)፣ ወ/ሮ ሃይማኖት ጥላሁን፣ ወ/ሮ መቅደስ፣ ዲ/ን እንዳሻው፣ ዲ/ን ብንያም፣ ዮናስና ጌትነት የተባሉት መሆናቸው ታውቋል፡፡ በተለይም የእነዚህ ቀንደኛ በጥባጮች መለቀቅ፣ የከተማውን ኅብረተሰብ፣ የፍትሕና የፀጥታ አካላትን ማስቆጣቱ ተመልክቷል፡፡

Thursday, March 8, 2012

ትንቅንቅ!

 በእውነተኛ ራእይ ላይ የተመሠረተ፣

ርእስ- የመጨረሻው ትንቅንቅ
            ደራሲ- ሪክ ጆይነር
          ተርጓሚ ሰሎሞን አሰፋ
                                                            ናዝሬት፣ 2004 /
                          ክፍል ፩

የሲኦል ኃይላት እየተመሙ ናቸው

አጋንንታዊ ሠራዊቱ በዓይኔ ማየት እስኪሳነኝ ድረስ እጅግ ብዙ ሲሆኑ እያንዳንዳቸውም የተለያዩ ሰንደቅ ዓላማዎችን ተሸክሞ በተሰለፈ ክፍለ ጦር ስር ተከፋፍለው ተሰልፈው ነበር። ትላልቆቹ ክፍለ ጦሮች ትዕቢት፣ራስን ማጽደቅ፣ ስምን ማስጠራት፣ ራስ ወዳድነት፣ በጭፍን መፍረድና ቅናት የሚሉ ሰንደቅ ዓላማዎችን በያዘ ጦር ስር ተሰልፈው ነበር። በዓይኔ ማየት ከምችላቸው ከእነዚህም ሌላ እጅግ በርካታ ሌሎች ክፍለ ጦሮችም ተሰልፈው ነበር። ይሁንና ከገሃነም እየወጣ ከመጣው ከዚህ አስፈሪ መንጋ ፊት በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉት ግን እጅግ ኃያላን ይመስሉ ነበር። የዚህ ሠራዊት መሪ ደግሞ የወንድሞች ከሳሽ የሆነው ራሱ ሰይጣን ነበር።
ይህ መንጋ ሠራዊት የታጠቃቸው የጦር መሣሪያዎች በላያቸው ላይ ስሞቻቸው ተጽፎባቸው ነበር። ሰይፎቹም ዛቻ፣ ጦሮቹ ክህደት፣ ቀስቶቹ ሀሰት፣ ክስና ስም ማጥፋት ይባሉ ነበር። መራርነት፣ አለመቀባበል፣ ትዕግስት ማጣት፣ ይቅር አለማለት የተባሉ ስሞች ያሏቸው ጥቂት የአጋንንቱ ቡድን አባላትም ለዋናው ውጊያ ከዚህ ሠራዊት ፊት ቀድመው እንዲጓዙ ተልከው ነበር።

እነዚህ የአጋንንቱ ቡድን አባላት ቁጥራቸው አናሳ ቢሆንም ኃይላቸው ግን ከኋላቸው ተሰልፎ ከሚገሰግሰው በርካታ ክፍለ ጦር የሚተናነስ አልነበረም። ቁጥራቸው አናሳ የሆነው ደግሞ ለስልታዊ ምክንያት ብቻ ነበር። እነዚህ ጥቂት አጋንንታዊ ቡድኖች ልክ ዮሐንስ መጥምቁ ሕዝቡን በጥምቀት ለጌታ ለማዘጋጀት ብቻውን የተለየ ቅባት እንደተሰጠው ዓይነት እነዚህም ህዝቡን ለጥፋት ለማዘጋጀት «ብዙሃኑን ሕዝብ ለማጥመቅ» ልዩ አጋንንታዊ ኃይልን የለበሱ ነበሩ። አንዱ የመራርነት አጋንንት በሕዝብ ወገን ሁሉ ወይም ባህሎች ላይ እንኳን ሳይቀር መርዙን መርጨት ይችል ነበር። የርኩሰት አጋንንቱ ደግሞ ከአንድ የቴአትር፣ የፊልም ወይም የንግድ ምርት አስተዋዋቂ ተዋንያን ጋር ራሱን በማቆራኘት ቁጥሩ እጅግ በርካታ የሆነውን ሕዝብ እንደኤሌክትሪክ ያለ ኃይል እየላከ በመምታት ያፈዛቸውና ያደነዝዛቸው ነበር። ይሄ ሁሉ ደግሞ ቀጥሎ ለሚመጣው ለታላቁ የክፋት መንጋ መንገድ ጠርጎ ለማዘጋጀት ነበር።

Tuesday, March 6, 2012

ሰበር ዜና! «ዘመድኩን በቀለ የ5 ወራት እስር ተፈረደበት»

ለቀበጠች አማት ሲሦ በትር አላት


ሕገ ቤተክርስቲያንንና ሕገመንግሥትን በጫማው ረግጦ፣ ከሕግ በላይ ሆኖ በሕዝብና በቤተክርስቲያን ተወዳጅ የሆኑ ሰባክያነ ወንጌልና ዘማሪያንን አፉ እንዳመጣለት ተሃድሶና መናፍቅ እያለ ሲሳደብና ሲወራጭ የነበረው ዘመድኩን የ5 ወራት የእሥር ዋራንት ተቆረጠለት፡፡

ዛሬ የካቲት 27 ቀን 2004 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት የዋለው ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ካየ በኋላ ዘመድኩን ሕግን በመጣስ በተለይም በመጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ላይ ባደረሰው የሞራልና የስም ማጥፋት፣ እንዲሁም የዛቻ ወንጀል ፍርዱ ሊወሰንበት መቻሉ ታውቋል፡፡ ዐቃቤ ሕግ ፍርዱ አንሷል ቢልም፣ የዘመድኩን ጠበቃ የልጆች አባት፣ የብዙ ቤተሰብ አስተዳዳሪና ወላጅ እናቱ በቅርብ የሞቱበት መሆኑን አስረድቶ የፍርድ ማቅለያ ሃሣብ በማቅረቡ ሊቃለልለት እንደቻለ እማኞቻችን ገልጸዋል፡፡

ይሁ እንጂ 5 ወሩም ቢሆን እንደማይፈረድበት የገመተው ዘመድኩን፣ እጅግ መደንገጡንና ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩ ተባባሪ የውንብድና ጓደኞቹ ሲያለቅሱ እንደነበር ተስተውሏል፡፡ የዝግጅት ክፍላችን ዘመድኩንን እግዚአብሔር ያውጣህ እያለ፣ የ5 ወራት የእሥር ቤት ቆይታህ የትምህርት፣ የንስሐ እና የመስተካከል ቆይታ ያድርግልህ በማለት ለማኅበረ ቅዱሳን ጓደኞቹ "የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም" በሚል ተረት ይሰናበታቸዋል፡፡
እግዚአብሔር ለሁላችንም ማስተዋልን ያድለን!!!
አሜን!!!
ምንጭ ፣http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com/2012/03/blog-post_06.html