Showing posts with label ለጥያቄዎ መልስ. Show all posts
Showing posts with label ለጥያቄዎ መልስ. Show all posts

Monday, July 1, 2013

በጎልጉል ድረ ገጽ በቀረበው ''አንተ ማነህ?'' ጽሁፍ ላይ አቶ የኑስ (ዮናስ - በመጽሐፍ ቅዱስ) ላቀረቡት የግል ወቀሳ ጽሑፈ የተሰጠ ምላሽ


አቶ የኑስ (ዮናስ) የተባሉት - በመጽሐፍ ቅዱስ) ላቀረቡት የግል ወቀሳ፤
አቶ ዮናስ !!!
አሁንም

ስላም ይብዛልዎት እያልኩ ነገርን ነገር ያነሰዋልና ባላሰብኩት ነገር ላይ በሰነዘሩብኝ የሃሰት ክስ ላይ ተመስርቼ አንዳንድ የጋራ ጥያቂዎችን እንዳቀርብ ይፍቅዱልኝ???
1) የሙስሊሙ ጥያቄ በአገሪቱ ውስጥ በሙሉ መልካም አስተዳደር እንዲመጣ ነው ወይስ በእኛ ላይ ብቻ በደል ስለደረሰብን ትግላችን ለሙስሊሙ መብት ብቻ የሚል ነው?
2) በየቦታውና በየጊዜው በሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ዘዎትር የሚሰማው መፈክር 'መሪዎቻችን ይፈቱ' እንጂ በታሰሩ ጋዜጠኞች፤ ፖለቲከኞች፤የመብት ተከራካሪዎችና በአጠቃላይ ፍትህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ስትሉ ሰምቼ አላውቅምና ይህ ከምን የመጣ ነው?
3) ያስታውሱ እንደሆነ ''ሰማያዊ ፓርቲ'' ባዘጋጀው ሰልፍ ላይ አዘጋጆች ከተከሰሱበት ምክናያት አንዱ በሰልፉ ላይ አንዳንድ ሙስሊም ወገኖች ባቀረቡት ጠበብ ያለ ግለኛ መፈክር ምክንያት ነበር ታዲያ በቅንነት ለአንድ አገርና ሕዝብ በተሰለፈ ሁሉን አቀፍ ሰልፈኛ መካከል እንዲህ ዓይነቱ ሥራና ዝንባሌ የት የሚያደርሰን ይመስልዎታል?
4) ጥያቄዎቼ የሁላችንንም የወደፊት የጋራ ጉዳይ የሆነውንና አገርን ለመልካም አስተዳደር ለማብቃት ከሚደረገው አጠቃላይ እንቅስቃሴ አንጻር ሊኖረው የሚገባውን ፋይዳ ከወዲሁ ቆም ብለን ለማሰብ እንድንችል በማሰብ የተሰነዘሩ መሆናቸውን ከወዲሁ አስበው በቅንነት እንዲመልሱልኝ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት በትህትና እየጠየኩ ባለፈው እንደነካኩት እንደ ሃይማኖት ልዩነትና ክርክር አድርገው የሚቆጥሩት ከሆነ ግን ለፍላጎትዎ ማርኪያ የሚሆንዎን ጥሩና መሰረት ያለው ክርክር ወይም በመረጃ የተደገፈ ማስረጃ በክርስትናና በእስልምና መካከል አገሪቱ ባፈራቻቸው ምሑራን በአማርኛ በስፋት የሚቀርበውን ''Аnswering Islam ''  ድህረ ገጽ ቢከታተሉ ለችግርዎ የተሻለ መልስና ግንዛቤ ሊያገኙ ይችላሉና ትኩረትዎን ወደ እዚህ ድህረ ገጽ ቢያደርጉ ይሻልዎታል ማለት እወዳለሁ። ለአገራችን ጠቅላላ ችግር ብዙ የሚሠራ ሥራ ስላለ እኔን ለጊዜው ቢተውኝ??? አሁንም ጨዋ ሙስሊም ወገኖቼን እወዳለሁ። ክፋትን ተላብሰው ባልሆነ ነገር በመካፋፈል ለትውልድ መርዝ የሚረጩትንና እየረጩ ካሉ የእኛው ጉዶች ጋር ግን ምንጊዜም ስምምነት እንደሌለኝ ላሳውቅዎት እወዳለሁ። ደግሞም አንዳንዶች በመድረክ ላይ እየወጡ ''አላህ ወ-አክብር'' እንደሚሉት ዓይነት ማስመሰል ጨርሶ አላውቅበትምና በዚህ አይገምቱኝ። ደግሞም የእኔን እምነት መከተል አለባችሁ በማለት ከፍቅር ሌላ ሰይፍ አላነሳም። ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ስለሚጠፉ!!!

አሁንም ለጋራ የአገራችን ችግር
በጋራ አብረን በቅንነት እንሰለፍ!!!

ምድራዊ አገራችንን ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ያስባት!!!

አሁንም አክባሪዎ

በይስሃቅ በኩል የአብርሃም ዘር

ተናገር ነኝ

Sunday, May 20, 2012

ለጠያቂያችን የተሰጠ መልስ

ALEMIN HULU YEFETERE AND AMLAK WOLDEABE WOLDEMARIAMNEW"KIDUS EGZIABHER BICHA NEW.GIN,MUZLIMOCH ALLAH (AMLK)MILUT MANIN NEW???
ከላይ በፈረንጅኛው ፊደል የቀረበው የአማርኛው ንባብ ጥያቄ፤ በጡመራ ገጻችን ላይ ባለው «ይጠይቁ» ዐምድ ላይ የተላከልን ነው።
ንባቡን ወደፊደላችን ስንመልሰው፤ ይህንን ይሰጠናል።
«ዓለምን ሁሉ የፈጠረው አንድ አምላክ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ነው። ቅዱስ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ግን ሙስሊሞች አላህ(አምላክ) ሚሉት ማንን ነው?»
ጥሩ ጥያቄ ነው። ሙስሊሞች የሚያመልኩትን «የአላህ» ማንነት ከመመልከታችን በፊት እነሱ ብቻ ትክክለኛ እንደሆኑ ቆጥረው  እኛ የምናመልከውን እግዚአብሔርን በተመለከተ የሚሉንን ጥቂት ለማሳየት እንሞክራለን።
በእኛ ዘንድ የሚነገረውን አንድነት በሦስትነት ሳይከፋፈል፤ ሦስትነት በአንድነት ሳይጠቃለል፤ አንድም ሦስትም ብለን ማምለካችንን ሦስት አምላኰችን እንደምናመልክ አድርገው ይቆጥራሉ። ይህንንም «ሽርክ»شرك ይሉታል። ይህም ማለት «አጋሪ» ፤ ከአንድ በላይ  አምላኪ ማለት ነው። ከዚያም በተረፈ ጣዖት አምላኪ ማለት ነው። አላህ አንድ ገጽ፤ አንድ አካል፤አንድ ግብር ያለው እንጂ አንድም ሦስትም ሊሆን ስለማይችል ክርስቲያኖች የሚያመልኩት አላህን ሳይሆን «ፍጡርን ነው» ይላሉ። አንድና አንድ ብቻ (Oneness) ወይም توحيد ተውሂድ(ተዋህዶ) ያልተቀበለ ሁሉ አላህን አልገዛም ያለ ነው ይላሉ። (ተዋሕዶ ማለት አንድ ገጽ ማለት  እንደሆነ ልብ ይሏል?) توحيد ወይም Oneness ማለት ነውና። لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ «እሱን የሚመስል ማንም የለም፤ ሁሉን የሚሰማ፤ ሁሉን የሚያይ እሱ ብቻ አንድ ነው» ቁርዓን ሱረቱል Ashura 42፤11
( Fundamentals of Tawheed/Islamic monotheism/  Dr Abu Ameenah Bilal Philips)
ስለዚህ ተውሂድን( ተዋሕዶን) (Unification) ያልቀበሉ ሁሉ ከሀዲዎች ናችሁ ይሉናል።
በዚህም ተውሂድን ባለመቀበል የተነሳ ዛሬ በዓለም ላይ ያለው ኃጢአት ሁሉ የመጣው የሽርክና ውጤት ነው ይላሉ። ስለዚህ በእነሱ ዘንድ ክርስቲያኖች  ሽርክ አማኞች  ስለሆኑ የኃጢአቶች ሁሉ  ምንጮች ናቸው ማለት ነው። ይህ እንግዲህ እነሱ ክርስቲያኖችን የሚተነትኑበት መንገድ ነው። http://www.allaahuakbar.net/shirk/crime.htm/ይመልከቱ።
ክርስቲያኑን እንዴት እንደሚመለከቱት የብዙ ገጽ ትንታኔ ማቅረብ ቢቻልም ለማሳያነት ይህ በቂ ሆኖ ክርስቲያኖች እስልምናውን እንዴት እንደሚያየው ጥቂት ለመግለጽ እንሞክራለን።
አሊ ሲና የተባለ የቀድሞ የእምነቱ ተከታይ (Why I left Islam?)በተባለው ጽሁፉ እንዲህ ሲል ጽፏል። የእስልምና እምነት ተከታይ በዚህ ዘመን ከአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ መድረሱን ይገልጽና ታዲያ ይህ ሁሉ ህዝብ የሚሳሳት ይመስልሃል? ብሎ ይጠይቃል።