Tuesday, February 3, 2015

የፓስተር ተከስተ ጌትነት የወሲብ ቅሌት በቪኦኤ

የዝሙትና የአፍቅሮ ንዋይ አንበሳ ያልሰበረውን መንፈሳዊ ሰው ማግኘት ከባድ እየሆነ ነው። በመጨረሻው ዘመን ላይ ሰይጣን እንደሚያገሳ አንበሳ እየዞረ ሰዎችን የሚሰብርበት ትልቁ መንጋጋው ትዕቢት፤ ዝሙትና ገንዘብን መውደድ ናቸው።
በየቤተ እምነቶቹ ትላልቅ የሚባሉት ሁሉ መንፈሳዊ አከርካሪያቸው የተሰበረው በነዚህ ወጥመዶች ነው። ጳውሎስም አለ፤ «ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤
እንደ ገና ስመጣ በእናንተ ዘንድ አምላኬ እንዲያዋርደኝ፥ አስቀድመውም ኃጢአት ከሠሩትና ስላደረጉት ርኵሰትና ዝሙት መዳራትም ንስሐ ካልገቡት ወገን ስለ ብዙዎች ምናልባት አዝናለሁ ብዬ እፈራለሁ»
2ኛ ቆሮ 12፤20-21