Showing posts with label በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን. Show all posts
Showing posts with label በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን. Show all posts
Friday, August 29, 2025
እንዳንጠፋ ድነታችንን በጸጋው ኃይል አጽንተን እንጠብቃለን!
በጌታችንንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ አንዴ ድነናል፣ በዚህ ድነት በመንፈስ እንመላለሳለን፣ ኃጢአትን አንፈፅምም!
“ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።”
— ገላትያ 5፥16
የሀልዎተ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መጋቢ ዘነበ ግርማ ድነታችን በሕይወት ዘመናችን በጽድቅና በቅድስና በመመላለስ ካልፈጸምነው ልንጠፋ እንችላለን ብሎ ያስተማረውን ትምህርት የሪል ስቴቱ ባለቤት ነብይ በላይ ሽፈራውና ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተው ለተመረጡት ሰዎች ብቻ እንጂ ለዓለሙ ሁሉ አይደለም ብሎ የሚያስተምረው አማን ሻሎም የተባሉት ነብይ ዘነበን ተቃውመው የሙግት ትምህርት ሲለፈልፉ ሰማሁ። አዘንኩም፣ ገረመኝም። ያዘንኩት እነዚህ ተቃዋሚዎች ከእነሱ በስተቀር የቃል እውቀት ማንም እንደሌለው አስበው መናገራቸው ሲሆን የገረመኝ ለከት የሌለው ባዶነታቸውን በአደባባይ ሲገልጹ አለማፈራቸው ነው።
የዘነበን፣ የበላይ፣ የአማን ሻሎም እና የተመሳሳይ ሰዎች አስተምህሮ በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ከመበርበራችን በፊት እንደመግቢያ የመጀመሪያውን ሰው የአዳምን ማንነት እንደማስረጃ እንመልከት።
አዳም እንዲኖር የተሰጠው ቦታ የት ነበር ብትባሉ በገነት እንደምትሉ እርግጠኛ ነን። የሰው ልጆች ከዚህ ምድር በሞት ሲለዩ ነፍሳቸው የት ትሄዳለች ብለን ብንጠይቃችሁ መልሳችሁ ምን ሊሆን ይችላል? በገነት ልትሉ እንደምትችሉ ብንገምት የተሳሳትን አይመስለንም። ምክንያቱም ከኢየሱስ ጋር ከተሰቀለው አንዱን ፍርደኛ ኢየሱስ እንደዚህ ሲል ሰምተነዋል።
“ኢየሱስም፦ እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ አለው።”
— ሉቃስ 23፥43
በፊትም አዳም የኖረበት፣ በኋላም በኢየሱስ ክርስቶስ ያመንን እኛ የምንኖርበት ቦታ ገነት መሆኑን እንረዳለን። አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እስኪፈጠሩ መኖሪያችን ዔድን ገነት ነው።
“ነገር ግን ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደ ተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 3፥13
እሺ! እውነቱ ይህ ከሆነ አዳምን ለዘላለም ይኖር ዘንድ እግዚአብሔር ከሰጠው መልካም ሥፍራ ከሆነው ገነት ያስወጣው ምንድነው? እግዚአብሔር አዳምን በገነት ማኖር ስላልፈለገ ነው እንዴ ከገነት የተባረረው? አይደለም! አዳም ከሚስቱ ጋር የእግዚአብሔርን ቃል በገዛ ምርጫቸው ስላፈረሱ ነው።
ባለመታዘዝና የተሰጣቸውን ትዕዛዝ በማፍረሳቸው፣ ከእግዚአብሔር ድምፅ ይልቅ የሰይጣንን ፈቃድ ለመፈፀም ፈቃደኛ ስለሆኑ ነው የተባረሩት። ሁሉን አዋቂ እግዚአብሔር አዳም እንደሚሳሳት አያውቅም ነበር? እግዚአብሔር አስቀድሞ ያውቃል! የእግዚአብሔር ሁሉን አዋቂነት የሰውን ልጆችን ነጻ ምርጫ አይጋፋም። ማወቅና መረዳት የምንችልበትን ነፍስያ ባህርይውን ያካፈለን ለዚህ ነው። በምርጫህ ወደህ፣ አምነህ ታመልከዋለህ፣ አልፈልግህም ብለኸው ለኃጢአት ብትገዛ ከኃጢአት የሚታጨደውን ደመወዝ በምርጫህ ትቀበላለህ።
ስለሆነም አዳም በበደለ ጊዜ ዐመጽና ኃጢአት ከእግዚአብሔር አምላካዊ ባህርይ ጋር በገነት አብሮ መኖር ስለማይችል አዳም ከቅዱሱ ከእግዚአብሔር ፊት ተባረረ። የመጀመሪያው አዳም ሕይወት የተጠናቀቀው በዚህ የእውነት ፍርድ ነው።
የመጀመሪያው አዳም ከተጠናቀቀበት ፍርድ ነጻ ለመውጣት ዋጋ ከፍሎ ወደ አዳነው ወደ ሁለተኛው አዳም እንምጣ!
ሁለተኛው አዳም የመጀመሪያው አዳምንና ልጆቹን ለማዳን ከኃጢአት የነጻ፣ ለእግዚአብሔር አልታዘዝም ከሚል ዐመጽ የተለየ ንጹህ ነበር። ለዚህም የማዳን ሥራ ራሱ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ መጣ። “ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።”
— ዮሐንስ 1፥14
እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ሆኖ ሳለ በቃሉ ብቻ አዳምን ወደገነት መመለስ እየቻለ ለምን ሰው መሆን አስፈለገው? ብለን ስንጠይቅ መልሳችን እግዚአብሔር በጽድቅ ፈራጅ፣ በእውነትም ፍትህ ሰጪ ስለሆነ ነው የሚል ይሆናል። ዳዊት በመዝሙሩ እንዳለው።
“እርሱም ዓለምን በጽድቅ ይፈርዳታል፥ አሕዛብንም በቅንነት ይዳኛቸዋል።”
— መዝሙር 9፥8
ለኃጢአት ዋጋ ፍርድ ሳይሰጥ ጽድቅ የለም። ከእግዚአብሔርም ጋር እርቅ አይኖርም። የስርየት መስዋእቱም ደም ነበር። ለዚህ ነበር እግዚአብሔር ራሱ ሰው የሆነውና ስለአዳም ኃጢአት የደም መስዋእት የከፈለው።
ፊልጵስዩስ 2፣6-8
"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።"
አዳም ለኃጢአት ሲታዘዝ ተባረረ። ኢየሱስ ለጽድቅ ሲታዘዝ ሕይወት ሆነልን።
እስከዚህ ድረስ መግቢያ ይሆነን ዘንድ ስለወደቀው የመጀመሪያው አዳምና የዘላለም ሕይወት ስለሆነው ስለሁለተኛው አዳም፣ ኢየሱስ ቤዛነት ይሄንን ያህል ካልን ስለእነዘነበ ግርማ፣ በላይ ሸፈራውና አማን ሻሎም የክርክር ጉዳይ እንግባ።
ነብይ ዘነበ ግርማ ስለድነት በተናገረበት አንቀጽ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ በነጻ የተሰጠንን ዋጋ መጠበቅ አለብን፣ ከኃጢአት ካልጠበቅነው የዘላለም ሞት ያገኘናል፣ የተሰጠንን ድነት ልናጣ እንችላለን የሚል ይዘት የነበረው አስተምህሮ አቅርቦ ነበር። በላይ ሽፈራውና አማን ሻሎም የተባሉት ሰዎች ደግሞ በተቃውሞ የሰጡት መልስ የተሰጠንን ድነት እኛ መጠበቅ አይጠበቅብንም። አንዴ ድነናል፣ ይሄንን ድነት የትኛውም ኃጢአት አያጠፋብንም፣ የሚጠፋ ከሆነ ለዘላለም አልዳንም ማለት ነው ሲሉ የሚያግዛቸውን ጥቅስ በማቅረብ እውነቱ በነሱ ዘንድ ብቻ እንዳለ ለማስረዳት ታግለዋል።
እዚህ ላይ እኛ ጥያቄ እናንሳ! ከላይ በመግቢያችን ለማብራራት የሞከርነው የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እዚህ ላይ ይነሳል። የመጀመሪያው ሰው፣ አዳም ገነት የገባው ለጊዜው ነበር እንዴ? አይደለም! እግዚአብሔር ሰውኛ ድራማ ስለማይጫወት አዳም የተፈጠረው ከእርሱ ጋር ለዘላለም እንዲኖር እንጂ አዳም የበለሲቱን ፍሬ እስኪበላ ድረስ ለጊዜያዊ ማቆያነት አልነበረም። አዳም የተፈጠረበትን ዘላለማዊ ሕይወት የተሰጠውንና ከእግዚአብሔር ጋር ከመኖር ይልቅ የጠላቱን ድምፅ ሰምቶ ሞትን በራሱ ላይ ስላመጣ እግዚአብሔር ጻድቅ ሆኖ ሳለ ዐመጸኛ እንዴት ከእርሱ ጋር ኅብረት ሊያደርግ ስለማይችል በፍርድ ቀንበር ስር ወደቀ። ዐመጸኛ ከእግዚአብሔር ፍርድ ሊያመልጥ አይችልም። የመጀመሪያው አዳም እምቢተኛ ሲሆን ሁለተኛው አዳም የመጣው ደግሞ የአባቱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ነው።
“ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና።”
— ዮሐንስ 6፥38
በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ የዘላለም ሕይወት በማመን ያገኘ ሰው፣ ዐመጸኛ ሆኖ የዲያብሎስን ድምፅ ቢሰማ ሊሆን ይችላል? አትጠራጠር፣ የዘላለም ሞት ይፈረድበታል! ኢየሱስ ሞት ዋጋ ያለው በሁለት መንገድ ነው። አንደኛው ዋጋ ኢየሱስ የተወደደ የእግዚአብሔር መስዋእት ሆኖ ከአዳም ኃጢአት መዳንህን ባመንክበት ቅጽበት ስርየት ሆኖልህ የእግዚአብሔር ልጅ ትሆናለህ።
“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።”
— ሮሜ 8፥15
ልጅ በቅዱሱ በአባቱ ፊት ምን መሆን ይጠበቅበታል? ይሄ ሁለተኛው የኢየሱስ የሞት ዋጋ በእግዚአብሔር ፊት ልጆቹ ሆነን የምንመላለስበት ጉልበታችን ነው። ጸጋ ይባላል።
“ነገር ግን እንደ ክርስቶስ ስጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን።” ኤፌሶን 4፥7
ይህ ጸጋ በእምነት የዳንነውና የእግዚአብሔር ልጆች የሆንነው እኛን ምን ያደርግልናል?
“ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤”
— ቲቶ 2፥12-13
በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ አምኖ የዳነ ሰው በጽድቅ መኖር ግዴታው ነው። የተሰጠው ድነት በነጻ ነው ማለት ዋጋ አልተከፈለበትም ማለት አይደለም።
“በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።”
— ማቴዎስ 7፥21
አዎ፣ በሥራችን አልዳንም። ይህ ማለት ግን ሥራ የለብንም ማለት አይደለም።
በላይ ሽፈራውና አማን ሻሎም ይሄንን ቃል አይወዱትም። በእምነት አገኘነው ያሉትን ድነት ለሥጋ ፈቃዳቸው የሚከለክል ቃል ስለሆነ አይጠቅሱትም። አንዴ የተሰጠን ድነት በእኛ ስራ አይጠበቅም ይላሉ። ባንሰራም ያገኘነው ድነት አይጠፋብንም ብለው ይጮሃሉ። የሚጠፋ ከሆነ ቀድሞውኑ አልተሰጠንም ነበር እያሉ ስጦታቸውን ለፈለጉት የዐመጽ ተግባር እንደማስረጃ እንዲቆጠርላቸው ይታገላሉ። የተሰጠህን ነጻ ውድ ስጦታ ካልጠበከው ስጦታው ቀድሞውኑ አልነበረም ማለት ነው እንዴ?
ስጦታው የማይጠፋ ነው። የማይጠፋው የሰማይ ስጦታ ስለሆነ ነው። ነገር ግን የሰው ልጅ አጥፊ ልምምድ ስላለው ሊያጠፋው ይችላል። ምሳሌው የገነቱን አዳም አስብ።
“እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።” ያዕቆብ 2፥17 ዐመፀኞች ለተሰጣቸው ድነት ሥራ ስለሌላቸው ዐመጽነታቸውን የሚደግፍ ጥቅስ ይደረድራሉ። አዳም በሄዋን፣ ሄዋንም በእባብ እባብም በዐመጽ ምክንታቸው ስር ቢደበቁም ከፍርድ አላመለጡም።
የዚህ ዘመን ወንጌላውያን የተባሉት አብዛኛዎቹ መንፈሳዊ መረዳት የላቸውም። ብዙ አንብበው፣ ብዙ የቲዎሎጂ ትምህርት ቢኖራቸውም ብዙ አነበቡ እንጂ ከመንፈሳዊ እውቀት የተለዩ ዝናብ የሌለባቸው ዳመናዎች ናቸው። ዳዊት ፋሲል የሚባልም ግብዝ ሰው በተሳልቆና እውቀት በሚመስል የፌዝ ንግግር የገነት በር ቁልፍ በእጄ ነውና፣ በኔ በኩል ግቡ በሚመስል መልኩ ብዙ ያወራል።
አማን ሻሎም የተባለው ሌላኛው ግብዝ ሰው ራሱን ብዙ ባነበበው መጽሐፎች ውስጥ ደብቆ አዋቂ መስሎ ለመታየት ብዙ ጊዜውን ይጨርሳል። ይጋጋጣል። የተከራካሪዎቹን አፍ ዝም ስላሰኘ በእውቀት የበለጣቸው ይመስለዋል። ከነዚህ ደካማ እውቀቶቹ መካከል አንዱ ኢየሱስ የሞተው ለኛ ለጥቂቶች ነው የሚለውን የጆን ካልቪንን Limited Atonement ወይም Particular Redemption መዳን የሆነው ለተወሰኑት ብቻ ወይም የተመረጡ ብቻ ነው የሚል አስተምህሮ አስፋፊ ነው። ይህ ትምህርት የመጨረሻው የክህደት ጫፍ ነው። እግዚአብሔርን ጨካኝ፣ ፈራጅ አድርጎ የሚከስ ነው። እግዚአብሔር ኢየሱስን የላከው የተወሰኑ ሰዎች ብቻ ለማዳን ከሆነ ከመዳን ውጪ ያሉት ሰዎች ለሲኦል ማገዶነት እግዚአብሔር ያዘጋጃቸው ናቸው ማለቱ ነው። እንዳይድኑ ተደርገው የተፈጠሩ ሰዎችን እግዚአብሔር በእሳት እያቃጠለ ለመደሰት ያዘጋጃቸው ናቸው ማለት እግዚአብሔር ፍቅር አይደለም ማለቱ ነው።። እነዚህ ሰዎች ከዘላለም እሳት ውጪ ለመዳን ምርጫም፣ እድልም የሌላቸው ናቸው ማለት ነው። ይህ ትምህርት ደግሞ ይሄንን የእግዚአብሔር ቃል በቀጥታ ይቃወማል።
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
— ዮሐንስ 3፥16
እግዚአብሔር አብ አንድያ ልጁን ወደዓለም የላከው የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ ለማዳን ብቻ ነው የሚለው አማን ሻሎም Mouthpiece of Satan የሰይጣን አፍ አገልጋይ ነው።
በዚህ ቃል ውስጥ ጥቂቶች፣ የተመረጡ፣ የተወሰኑ፣ የተለዩ...የሚል ቃል ይታያችኋል?
“ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ።”
— ዮሐንስ 1፥7
"ሁሉ" ማለት በግሪክኛ πάντες ፓንቴስ ማለት ሁሉ፣ all, everyone እያንዳንዱ ማለት እንጂ የተወሰኑ፣ የተለዩ ማለት አይደለም። በላይ ሽፈራው አግብቶ የፈታ፣ ዳግመኛ ያገባና ሌላም፣ ሌላም የሚወራበት፣ በሪል ስቴት ገንዘብ ብዙዎች ያለቀሱበት፣ አማን ሻሎም በሱስ የተጠመደ፣ ቀለበት አስሮ የከዳ፣ ሌላም፣ ሌላም ሆነው ሳለ በእግዚአብሔር ፊት በጽድቅ መመላለስ ሲያቅታቸውና ለምኞታቸው ልጓም ማስገባት ሲሳናቸው፣ ለኃጢአታቸው አርነት የሚሰጥ ጥቅስ በማቅረብ የስህተት ደጋፊዎቻቸውን ለማሰባሰብ ይሯሯጣሉ።
ማጠቃለያ፣
የዳንነው በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ በነጻ ነው። በነጻ የተሰጠን ሕይወት ዋጋ ተከፍሎበታል። የከፈለልንን ስለምንወደው ትእዛዛቱን እንጠብቃለን። ትእዛዛቱን የምንጠብቀው ስለምንወደው እንጂ ለመዳን አይደለም።
“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16
ያ አጽናኝ ከኃጢአት ይጠብቀናል። ተሳስተን ኃጢአት ብናደርግ ስንኳን የንስሐ እድል አለን።
“በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።”
— 1ኛ ዮሐንስ 1፥9
ድነናል፣ ድነታችንን እንጠብቃለን። እንደዴማስ ኢየሱስን ትተን ለዓለም ኃጢአት ባሪያ አንሆንም።
Saturday, December 21, 2024
ታቦትም ጽላትም ዛሬ የሉም!
ታቦትና ጽላት ዛሬ የሉም!
በዚህ ርዕስ ላይ ብዙ ጊዜ ፅፈናል። አብዛኛው ሰው የሚያምነው የነገሩትን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተፃፈውን ባለመሆኑ ዛሬም ስለታቦትና ጽላት ሲከራከር ይውላል። ስለታቦትና ጽላት ምንነትና እንዴትነት ከመናገራችን በፊት አንድ ነገር በመጠየቅ ልጀምር። አንድ ሰው ናይሮቢ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነው ቢላችሁ መልሳችሁ ምን ሊሆን ይችላል? በእርግጠኝነት መልስ ከመስጠታችሁ በፊት ፊቱን በደንብ ታዩታላችሁ፣ ፈገግ ልትሉ ትችላላችሁ፣ ምን እያልክ ነው ብላችሁ መልሳችሁ ልትጠይቁት ትችላላችሁ። ከመቼ ወዲህ? ልትሉትም ትችላላችሁ። ምክንያቱም ናይሮቢ ከኬንያ ዋና ከተማነት ተዛውሮ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆኖ የተቆጠረበትና ሊሆን የሚችልበት እድል ስለሌለ ጠያቂያችሁ እያሾፈ ወይም እየቀለደ እንደሆነ መገመታችሁ የሚጠበቅ ነው። አብዛኛው ሕዝብ የሚረዳው እውነት ናይሮቢ የኬንያ ዋና ከተማ እንጂ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አለመሆኑን ነው። አሁን ባለንበት ሁኔታ ይሄ የተረጋገጠ እውነት ነው።
እንደዚሁ ሁሉ ከእስራኤል ውጪ ታቦትና ጽላት ነበረኝ ወይም አለኝ የሚል ሁሉ ናይሮቢ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነው ብሎ የሚናገርን ሰው ይመስላል። ምክንያቱም እነዚህን ነገሮች እየነገራችሁና እንደሆነ እየመሰከረላችሁ መሆኑ ነውና።
እኔ እግዚአብሔር በምድር ላይ ከአህዛብ መካከል ከመረጣቸው ከእስራኤል 12ቱ ነገድ አንዱ ነኝ፣ በኮሬብ ተራራ የኪዳኑ ፅላት ሲሰጥ ነበርኩ፣ ከ40 ዓመት በኋላ ርስት ምድርን ዘመዶቼ በኢያሱ እጅ ሲወርሱ ድርሻ መሬት አግኝቻለሁ፣ ኢየሩሳሌም የንጉሡ ከተማ ከተማዬ ነበረች፣ ሥርዓተ ቤተ መቅደሱ ሲፈፀም እስከናቡከደነጾር ውድመትና ዘረፋ ድረስ እዚያው ሳከናውን ነበርኩ። ወገኖቼ ለ70 ዓመት በባርነት ባቢሎን ሲወርዱ ነበርኩ። በሄሮድስ ዘመን ቤተመቅደሱ ተሰርቶ ሥርዓተ ታቦቱ ባይፈፀምም እየሄድኩ እጸልይ ነበር። በአጭር ቃል እኔ ከተመረጡት ከእስራኤል ወገን እንጂ ከአህዛብ አይደለሁም እያላችሁ ነው። ከዚህ ሰው ጋር ስለታቦትና ጽላት አሰራርና ሥርዓት ጋር መነጋገር የምትችሉት በመጀመሪያ በዚህ ጉዳይ ላይ መግባባት ስትችሉ ብቻ ነው። የታቦትና የጽላት ሥርዓት እንኳን የካም ነገድ እንደሆነ በሚነገርለት በአፍሪካ ይቅርና የሴማውያን ድንኳን መገኛ በሆነችው በኢየሩሳሌምም ዛሬ የለም። ባልተመረጥክበት፣ የተለየ ኪዳን ባልተቀበልክበት፣ የመቅደሱ አገልግሎት በሌለበት ሁኔታ ራስህን በራስህ ስትመርጥ ማድረግ የምንችለው ነገር ጤንነትህን በመጠራጠር ወደምታምንበት ፀበል ሂድ እንልሃለን እንጂ ላንተ ታቦትና ጽላት የምንደፋበት ምንም ምክንያት ሊኖረን አይችልም።ምክንያቱም እኛ በመንፈስ ቅዱስ የታተምን ጤነኞች ስለሆንን ለበኣል መሰዊያና ለማመለኪያ አጸድ የምናፈነድድበት ዜሮ ምክንያት የለንም። እነዚህ ሰዎች ተረፈ ምናሴ ናቸው። ምናሴ የተባለ የይሁዳ ንጉሥ እንዲሁ አድርጎ ነበር።
"ያዘዝኋቸውንም ሁሉ፥ ባሪያዬም ሙሴ ያዘዛቸውን ሕግ ሁሉ ቢያደርጉ ቢጠብቁም ለአባቶቻቸው ከሰጠኋት ምድር የእስራኤልን እግር እንደ ገና አላቅበዘብዝም ባለው ቤት የሠራውን የማምለኪያ ዐፀድን የተቀረጸውን ምስል አቆመ። ነገር ግን አልሰሙም፤ እግዚአብሔርም ከእስራኤል ልጆች ፊት ካጠፋቸው ከአሕዛብ ይልቅ ክፉ ይሠሩ ዘንድ ምናሴ አሳታቸው።" (2ኛ ነገ 21፣8-9)
ሊቁ የተረት አባት ዘበነ ለማ በአንድ ወቅት "ያለማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም" ብሎ ያስተምር ነበር። ከወገኖቹ በኩል ወቀሳ ሲበዛበት እንደዚህ ብሎ የማስተማር ጩኸቱን ቢቀንስም በትምህርቱ የተበከሉት ግን ዛሬም ድረስ "ያለማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም" የሚለው ስሁት ትምህርት ስር እንደሰደደ አለ። የተረት ሊቁ ዘቤ ለማ ታቦትና ጽላት የወረስነው ከሙሴ ሥርዓት ነው የሚለው ጩኸቱ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። የታቦት ቁመቱ፣ ርዝመቱ፣ ክብደቱ፣ አሸካከሙ፣ አቀማመጡ፣ ጽላቱ ላይ ምን ተጻፈ፣ ማን ጻፈ፣ ወዘተ የሚለው ጥያቄ ለደፋሩ ዘቤ ጉዳዩ አይደለም። የመናገር እድልና ሥፍራ ስላገኘ የስህተት መርዙን መርጨት ለሱ የተሟላ እውቀት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ በግልጽ ቋንቋ የዘበነ ለማን አስተምህሮ የሚቃወም ትምህርት ሲሰጥ ሰምቸዋለሁ። ትምህርቱ የተሟላ ባይሆንም በትክክል ያንፀባረቀው አቋም ግን ይበል የሚያሰኝ ነው። የኦሪቱ ታቦትና ጽላት ዛሬ የለንም ብሏል። ይሄ ናይሮቢ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አይደለም ብሎ ሀቁን እንደመመስከር ይቆጠራል። ነገር ግን የተጓደለው ነገር ቢኖር በቤተመቅደሱ ውስጥ መስዋእት እንሰዋበታለን በማለት የተናገረው የተሟላ መልስ አይደለም። ሲጀመር እሱ ከኦሪቱ ኪዳን ጋር በተመሳሳይ ስም ጽላት መባል የለበትም። በሌሎች አብያተክርስቲያናት እንደሚደረገው ለምሳሌ በግብጽ ኦርቶዶክስ ጠረጴዛ፣ መሰዊያ ተብሎ ይጠራል። ከዚያ ባለፈ ተሸክመውት መንደር ለመንደር አይወጡም፣ ገብርኤል ጡጦስ፣ ጣንጦስ፣ ኤፈራንጦስ እያሉ ሕዝቡን በጻድቅ ስም አያደነዝዙበትም። በእልልታና በጩኸት አያሰግዱትም፣ ይቀስፍሃል፣ ይሰነጥቅሃል እያሉ አያስፈራሩበትም። አይሸጥም፣ አይለወጥም። የኢትዮጵያው ግን ምናሴ በእግዚአብሔር ቤት ከፈፀመው አምልኮ ጋር ተመሳሳይ ነው። በዚህ ዘመን የተሰረቀው ታቦት በተለይም ብዙ ዘመን የቆየው ከተገኘ ብዙ ዋጋ እንደሚያወጣ ይታወቃል።
ስናጠቃልል፣
ኢትዮጵያ እስራኤል አይደለችም፣ ሆናም አታውቅም። ኪዳን አልተሰጣትም፣ ታቦትም ጽላትም የእርሷ አልነበረም። የአህዛብ ሀገር ነበረች። ክርስትና እንዴት እንደገባ ራሷ በምትተርክበት ታሪክ በፍሬምናጦስ በኩል አብርሃና አፅብሃ የመጀመሪያውን ክርስትና መንግሥታዊ ሃይማኖት አድርጋ ተቀበለች። ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በኦፊሴል መናገር ያለባት የኦሪቱ ታቦትና ጽላት የለኝም፣ አሁን ያለው መሰዊያ ወይም መስዋእት ማቅረቢያ ጠረጴዛ እንጂ የተለየ አምልኮ፣ ስግደትና ምስጋና የሚቀርብለት ነገር አይደለም ብላ ማወጅ አለባት። መሰዊያ የቀረበበትን ማክበር እያለች 365 ቀን በሙሉ ሕዝቡን ማሰገድ ትክክል አይደለም። ሕዝቡ መስዋእቱን ከመብላት ይልቅ የመስዋዕቱን መክተፊያ ይዞ በመውጣት ሕዝቡን በእልልታ፣ በዝማሬ፣ በቅኔና በስግደት ማሳሳት ወንጀልም፣ ኃጢአትም፣ ክህደትም ነው። ሕዝቡ የእግዚአብሔር ታቦት ይህ ነው ብሎ ያምናል። ለዚህ ታቦት ሲል ለመግደልም፣ ለመሞትም አይመለስም። እንደእውነቱ ከሆነ የሕዝቡን አእምሮ በዚህ መልኩ ቀፍድዶ በማሰር ወደሞት ከመንዳት የባሰ ከዚህ በላይ ጥፋት የለም። እውነቱ ግን እግዚአብሔር አብ ለኛ የሰጠን መዳኛችን፣ ጽላታችን፣ አምልኮና ስግደታችን በኢየሱስ በኩል እንጂ በቁሳቁስና ሰዎች ባዘጋጇቸው ምናምንቴ ሥርዓቶች በኩል አይደለም። ዓይናችንን ከኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነቅለን ወደሌላ ወደማንም ለመዳን አናማትርም። ሌላ መንገድ በጭራሽ የለምና ነው።
የታቦት፣ የጽላት፣ የተክልዬ፣ የአቦዬ፣ የሳምርዬ፣ የክርስቶፎሎስ፣ የአርሳዲ፣ የፈለቀች፣ የዘነበች፣ የአርሴማ፣ የንፍሮ፣ የዳቦ፣ የአፈር፣ የአመድ የሚባል የመዳኛ ዘዴ እና 20 እና 30 ትውልድህን የሚያስምር መንገድም፣ ኪዳንም ከሰማይ በታች ሌላ ስም በጭራሽ የለም።
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6 የተባልነው ይህንን ነው። የምንድነው፣ የዳንነው በዚህ ስም ብቻ ነው።
Tuesday, December 17, 2024
ኪዳነ ምሕረት ኢየሱስ ነው!
ኪዳነ ምሕረት ኢየሱስ ክርስቶሰ ነው!
ከዚህ በላይ የሚታየው ስእል የጣኦት አምላኪዎች እንጂ የሌላ የማንም ስእል አይደለም። በጣኦት አምላኪዎቹ ልብ ሰይጣን ያስቀመጠው ትርጉም እንደምንገምተው ልጅ እግሩ ሰው የኢየሱስ፣ ሽማግሌው ደግሞ የአብ መሆኑ ነው። በእግዚአብሔር መንግስት ሦስት ምስሎች በአኀዝ የሚቀመጡበት ወይም በወጣትና በሽማግሌ የሚመሰልበት መለኮታዊ ማንነት የለም። ከእግዚአብሔር ያልሆነ የሰው ልብ ያመነጨው ስእል ሁሉ ከተመለከ፣ ከተወደሰ እሱ ጣኦት ነው የሚባለው። “እንዳትረክሱ፥ የተቀረጸውን ምስል የማናቸውንም ነገር ምሳሌ፥ በወንድ ወይም በሴት መልክ የተሠራውን፥”
(ዘዳግም 4፥16)
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ምሕረትና ይቅርታ የአዳም ልጆች እንዲያገኙ ለማንም ኪዳን አልሰጡም። መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጆች የምሕረትን ኪዳን ሞታችንን ከሞተልን ከኢየሱስ በቀር ለፍጡራን እንደሰጡ አንድም ቦታ ተጽፎ አናገኝም። “ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።” ነው የተባለው።
(ይሁዳ 1፥25) እውነቱ ይህ ከሆነ የመዳን ኪዳን ያገኘነው እንዴት ነው?
ኪዳነ ምሕረት ማለት የምሕረት፣ የይቅርታ፣ የሥርየት ቃል ድምዳሜ ወይም ፍጻሜ ማለት ነው። ምሕረት የማይገባው ጥፋተኛ፣ በምሕረት አድራጊው እቅድ ከእዳ፣ ከበደል፣ ከወንጀል ነጻ አድርጌሃለሁና የነጻነትህን አዋጅ በዚህ ደብዳቤ አረጋግጬልሃለሁ ብሎ የሚሰጠው የአርነት ሰነድ ነው። የዚህ ፅሑፍ ዓላማ ወደሆነው ዝርዝር ጉዳይ ከመግባታችን በፊት ራሱ "ኪዳን" የሚለው ቃል ምንን ያመለክታል የሚለውን ለመመልከት እንሞክር!
ውል በሁለት ተዋዋይ ወገኖች መካከል በቃል ወይም በፅሑፍ የሚደረግ አሳሪ ሕግ ነው። በውሉ ላይ ተዋዋይ ወገኖችን መብትና ጥቅም በማካተት የሚደርሱበት ስምምነት ሲሆን መሠረታዊው የውል አስፈላጊነት ጥቅምንና መብትን ለማስከበር መርህ አድርጎ የሚነሳ ቢሆንም ውል ሁልጊዜ አዋጭ ወይም ዘላቂ ላይሆን ይችላል። ውል በዓለማችን ላይ እየተሠራበት ያለው የተዋዋይ ወገኖች አሳሪ ስምምነት ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ ኪዳን በጣም የተለየ ነው። የእግዚአብሔር ኪዳን ወይም (Covenant) በእግዚአብሔርና በሰው ልጆች መካከል የሚደረግ የአቻ ስምምነት አይደለም። ኪዳን ማለት በጥሬ ትርጉሙ ውል:ስምምነት ቢሆንም ኪዳኑ በምድር ላይ ሰዎች እንደሚያደርጉት በሁለት እኩል ተዋዋይ ወገኖች መካከል እንደተደረገው አይደለም። በውል ሰጪ(በእግዚአብሔር) እና በውል ተቀባይ (በሰው ልጆች) መካከል የተደረገው ኪዳን እግዚአብሔር መብትና ጥቅሙን ለማስከበር ወይም ከሰው ልጆች የሚያገኘው የተለየ መብት እንዲጠበቅለት የተደረገ ኪዳን ሳይሆን እግዚአብሔር በባህርይው ፍቅር ስለሆነ የጠፋውን የሰው ልጅ ለማዳን፣ በክንዱ ተጠብቆ እንዲኖር ሲል እግዚአብሔር ፍቅሩን የገለፀበት መንገድ ነው። ሌላውን ወገን የሚጠቅም ኪዳን ማድረግ የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር የሚገባው ኪዳን አምላክነቱን አስገድዶ ለመጫን ሳይሆን ጌትነቱን ለተቀበሉት ሁሉ ከአምላክነቱ በረከት እንዲትረፈረፍላቸው ከፍቅሩ የተነሣ የሚደረግ ኪዳን ነው።
“በጭንቃቸው ሁሉ እርሱ ተጨነቀ፥ የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤ በፍቅሩና በርኅራኄውም ተቤዣቸው፥ በቀደመውም ዘመን ሁሉ አንሥቶ ተሸከማቸው።” (ኢሳ 63፥9)
እግዚአብሔር አዳምን የፈጠረው ማንንም ሳያማክር ከአምላካዊ ክብሩ ሕያውነት እንዲካፈልና በዘላለማዊ ፍቅሩ እንዲኖር ነው።
“ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። (1ኛ ዮሐ 4፥10)
ለአዳም የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ያሟላለት በአዳም ጥያቄ አልነበረም። እንዲያውም አዳም የተፈጠረው የአምላክን ባሕርይ ተካፋይ እንዲሆን፣ ክብሩ በሱ እንዲታይ በአርአያውና በምሳሌው ነው። እግዚአብሔር ከፈጠረውና ገዢ እንዲሆን በፍጥረቱ ላይ ካሰለጠነው ከአዳም ጋር የገባው ኪዳን ከሰጠሁህ እልፍ አእላፍ ፍጥረት መካከል ይሄን አንዱ ከበላህ ሞትን ትሞታለህና እንዳትበላው የሚል ትእዛዝ ነበር። አዳም ሞትን የሞተው ባልተነገረውና በማያውቀው ነገር ሳይሆን ራሱ ሞትን በመምረጡና የእግዚአብሔርን ድምጽ በመጣሱ የተነሳ ነው። ይህ የመጀመሪያ ኪዳን የፈረሰው ውል ተቀባዩ ውሉን በማፍረሱ ስለሆነ ውሉ የሚያስከትለው ቅጣት በአፍራሹና በልጆቹ ላይ ሞት ተግባራዊ ሆኗል።
ከአዳም ውል አፍራሽነት በኋላ እግዚአብሔር ከአዳም ልጆች ጋር የገባው ሌላኛው ኪዳን ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ በኮሬብ ተራራ ነው። ልቅሷችሁንና ጩኸታችሁን ሰምቻለሁ ከባርነት አወጣችኋለሁ፣ ወተትና ማር የምታፈስ ሀገር አወርሳችኋለሁ ብሎ በታላቅ ድንቅና ተአምራት ከግብጽ ከወጡት እስራኤላውያን ጋር ያደረገው ኪዳን ኮሬብ ላይ ተገልጿል።
(ዘጸ19፣4—5) ❝በግብፃውያን ያደረግሁትን፥ በንስርም ክንፍ እንደተሸከምኋችሁ፥ ወደ እኔም እንዳመጣኋችሁ አይታችኋል። አሁንም ቃሌን በእውነት ብትሰሙ ኪዳኔንም ብትጠብቁ፥ ምድር ሁሉ የእኔ ናትና ከአሕዛብ ሁሉ የተመረጠ ርስት ትሆኑልኛላችሁ፤❞ ብሏል። ይህ ኪዳን ዘላለማዊው ኪዳን እስኪፈጸም ድረስ በምድራዊ ርስት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከሌሎች ለይቶ የሚያቆይበት የኪዳን ሕግ ተሰጥቶ ነበር።
እግዚአብሔር ከመረጠው፣ ራሱ ከሚመራው፣ የተሻለ ሀገር አወርስሃለሁ ካለው ከዚህ ሕዝብ ጋር ኪዳን አደረገ። ይህ ኪዳን እግዚአብሔር የመረጠው ሕዝብ ከአህዛብ የሚለይበት፣ ደግሞም ከእግዚአብሔር ጋር በድምፅና በመልእክት የሚገናኝበት የሕግ ኪዳን ነበር። በአድርግና አታድርግ የተሠጠው የኪዳኑ ስምምነት በተጻፈው የጽሌ ሠሌዳ ላይ እንዲህ የሚል ተፅፎበት እንመለከታለን።
1/ ከኔ በስተቀር ሌሎች አማልክት አታምልክ፣ 2/ የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ አትጥራ፣
3/ የሰንበትን ቀን አክብር፣ 4/ እናትና አባትህን አክብር፣ 5/ አትግደል፣ 6/ አታመንዝር፣
7/ አትስረቅ፣ 8/ በሀሰት አትመስክር፣
9/ የባልንጀራህን ገንዘብ አትመኝ፣
10/ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ የሚል የኪዳን ሕግ ነበረ። ይህ ኪዳን ይጠበቅ ዘንድ የሚከናወንበት መንገድ የኃጢአት፣ የደኅንነት፣ የሚቃጠል መስዋዕት በማቅረብና ትዕዛዛትን በመጠበቅ ነበር።
“እንዲህም ይሆናል፤ ይህችን ፍርድ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳንና ምሕረት ለአንተ ይጠብቅልሃል፤”
( ዘዳግ 7፥12)
ይህ ሕግና ትዕዛዛቱ ምድራዊ ሥርየትን ያስገኝለታል እንጂ አዳም ትቶ ወደወጣበት ገነት መልሶ የሚያስገባ አልነበረም። ይህንን በእግዚአብሔር ቁጣ የተዘጋውን የገነት በር መልሶ በመክፈት አዳምንና ልጆቹን ማስገባት የሚችል ከሰው ልጆች አንድም ሰው ስላልነበረ በሌዊ ወገን በሚሾሙ ካህናት በኩል ደም በመርጨት ጊዜያዊ ሥርየትን እያገኙ እስከአማናዊ የተሻለ ኪዳን ድረስ ለመቆየት ችለዋል። ምክንያቱም ሰው በጥፋት ሥራው የተረገመ በመሆኑና ምድርም በተረገመው ሰው ምክንያት የተረገመች በመሆኗ ከሰው ልጆች መካከል ከእርግማን ነጻ የሆነ ሰው ስላልነበረ ዘላለማዊ ድነት ማስገኘት የሚችል አንድም ጻድቅ አልነበረምና ነው።
“አዳምንም አለው፦ የሚስትህን ቃል ሰምተሃልና፥ ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍም በልተሃልና ምድር ከአንተ የተነሣ የተረገመች ትሁን፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ በድካም ከእርስዋ ትበላለህ፤”
(ዘፍ 3፥1)
እግዚአብሔር ሌሎች ንዑሳን ኪዳናት ከወደዳቸው ጋር ኪዳን አድርጓል። ከኖኅ ጋር በቀስተ ደመና (ዘፍ9፣11-12)፣ ከሙሴ ጋር (ዘጸ34፣27)፣ ከአብርሃም ርስቱን ሲሰጠው(ዘፍ15፣28)፣ የቁልፈታቸው ግርዛት እንዲወድቅ (17፣11)፣ ከይስሐቅ (ዘፍ17፣19)፣ ከያዕቆብ (ዘፍ35፣10-15)፣ ከዳዊት ጋር (ኤር33፣17) ኪዳን አድርጓል። ይህ ኪዳን በዘመናቸው እግዚአብሔርን ለታዘዙበትና ለፈፀሙበት ፍቅር የተነገረላቸው የመኖር ኪዳን እንጂ የአዳምን በደል የሚሽር ወይም ለሰው ልጆች የዘላለም ሕይወትን የሚያስገኝ ኪዳን አልነበረም።
“የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ብትጠብቅ፥ በመንገዱም ብትሄድ፥ እግዚአብሔር እንደ ማለልህ ለእርሱ የተቀደሰ ሕዝብ አድርጎ ያቆምሃል።” (ዘዳ 28፥9)
እግዚአብሔር የምወደው ልጄ... ያለው ከሰማይ ከወረደው በስተቀር ወደሰማይ የወጣ የለም የተባለለት ባለሙሉ ሥልጣን ዘላለማዊ ሊቀካህን፣ በደሙ በሰማያዊቷ መቅደስ የገባ ኢየሱስ ብቻ ነው። ሞትን አሸንፎ በሞት የተሸነፉትን ሁሉ ከምርኮ ነፃ ማውጣት የቻለ ከኢየሱስ በቀር ማንም የለም። ይህንንም ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን መልዕክቱ እንዲህ ሲል አስረግጦ ይነግረናል።
(ኤፌሶን 4፣8-10) ስለዚህ፦ ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ ይላል። ወደ ምድር ታችኛ ክፍል ደግሞ ወረደ ማለት ካልሆነ፥ ይህ ወጣ ማለትስ ምን ማለት ነው? ይህ የወረደው ሁሉን ይሞላ ዘንድ ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ደግሞ ያው ነው።
ይህ ኪዳን፣ አዲስ ኪዳን፣ የሕይወት ኪዳን ይባላል። አብ በአዳም ልጆች ላይ የነበረውን ቁጣ ያበረደበት፣ የተወደደ መስዋዕት፣ በደሙ በኩል ዘላለማዊ የማዳን ሥርየት የተፈፀመበት ኪዳን ይህ ነው። “እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።”
( ዮሐ 6፥47 )
ከዚህ ኪዳን ውጪ እግዚአብሔር ሌላ ኪዳን የለውም።
“ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤” (ሮሜ 5፥10)
ከዚህ የምሕረትና የይቅርታ ኪዳን ውጪ እግዚአብሔር የተቀበለውና ደስ የተሰኘበት ሌላ ኪዳን የለም ብቻ ሳይሆን ይሄንን ኪዳን ማሟላት የሚችል ከሰው ልጆች መካከል አንድም ሰው አልነበረም። ቢኖርማ ኖሮ ኢየሱስ ሰው ሆኖ መወለድ ባላስፈለገው ነበር። ስለዚህ ለሰው ልጆች የተሰጠ የምሕረት ኪዳን ኢየሱስ ብቻ ነው። ሌላ ኪዳነ ምሕረት የለም! ይህንን ኪዳን የሚተካ፣ ማዳን የሚችል፣ አብ የወደደው መስዋእትና የምወደው ልጄ ያለው ከኢየሱስ በቀር ማንም ስለሌለ ኪዳነምሕረት በማለት በቅድስት ማርያም በኩል ዘላለማዊ ድነት አገኛለሁ በሚል ተስፋ ወደ ማርያም የሚለምን ሁሉ ከሕይወት ኪዳን የጎደለ፣ እግዚአብሔር የሰጠውን የመዳን ኪዳን ያቃለለ ሰው ነው። ድንግል ማርያም ቅድስትና ብፅእት እንጂ እግዚአብሔር አብ የምሕረቴን ኪዳን በሷ በኩል አድርጌአለሁ ብሎ ኪዳን የሰጠበት ሁኔታ የለም።አንዳንዶች በማርያም ጉዳይ ስለጥንተ አብሶ (የቀደመ በደል) እያነሱ ጉንጭ አልፋ ክርክር ሲያደርጉ ይታያሉ። ይሄ የማይረባ ክርክር ነው። ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ኢየሱስ መምጣት ድረስ ለሰው ልጆች ሁሉ ገነት ተዘግታበት ይኖር ነበር። በገነት የሌለ ሰው ሁሉ በደለኛ ነው። በሕይወት አኗኗሩ ጻድቅና ንፁህ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ከገነት ውጪ ስላለ በደለኛ ነው። በአጭሩ በኪሩብ የምትጠበቀው ገነት የተዘጋበት የሰው ልጅ ሁሉ በደለኛ ነው።
እንዲያውም ብፅእት ማርያም ራሷ ነፍሷ ጌታን እንደምታከብር፣ መድኃኒቷም እንደሆነ እንደዚህ በማለት መስክራለች። “ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤” (ሉቃስ 1፥47)
እግዚአብሔር የብሉይን (አሮጌውን) ኪዳን ከተመረጡት ከእስራኤላውያን ጋር፣ አዲሱን ኪዳን በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ካመኑት ጋር የሕይወትን ኪዳን አድርጓል። ሌላ ከማንም ጋር የማዳን፣ የሕይወት ኪዳን አላደረገም።
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
(ዮሐ 14፥6) ኪዳነ ምሕረት ኢየሱስ ነው!
Saturday, November 9, 2024
ስለሸኮናው ድፍንና ቅድ ክርክር መነሻው ከኦርቶዶክስ አጠቃላይ የወንጌል እውቀት ችግር የሚመነጭ ነው!
አባ በርናባስ የተባሉ ሊቀጳጳስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮና በምእመናኖቹም ቅቡል የሆኑና እንደጽዩፍ የሚቆጠሩ የአህያና ተመሳሳይ እንስሳትን ጉዳይ አንስተው በሐዲስ ኪዳን ትምህርት ክልክል እንዳይደሉ ለማብራራት ሞከረዋል። ምሁርና ሊቅ ነኝ ባይ መንጋው የአቡኑን ትምህርት ለመቃወም ከዳር ዳር ለመጮህ አንካሳ ዶሮ አልቀደመውም። ከአፉ ለሚወጣው መራር ቃላት ግድ የሌለው መንጋ ስለአህያ ሥጋ ርኩሰት ለመናገር የቸኮለው የጽድቅ ጉዳይ አንገብግቦት ሳይሆን እንደፈሪሳውያን ሕጋችን ተነካ ከሚል አጉል ተመጻዳቂነት የመነጨ ነው። ሀገሪቱ ካለችበት ወቅታዊ ችግርና ኦርቶዶክስ እንደቤተ ክርስቲያን በውስጧ ሌባና ማጅራት መቺ አመራር፣ በውጪ ደግሞ በሰሜን የትግራይ፣ በመሐል የኦሮሚያ፣ በጎጃም የቅባት ወዘተ ሲኖዶስ እየተባለ ሊበታትናት ጎራ የለየበትን ችግር ከመፍታት ይልቅ የአህያ ሥጋ ይጣፍጣል! ወይስ ይመራል! ብሎ ለመከራከር መራኮቱ የሚያሳየን ቤተ ክርስቲያኒቱ በአዚም፣ በድንዛዜ ውስጥ እንዳለች አመላካች ይመስለኛል። ከዚህ ድንዛዜ የሚያወጣ ያልተጠበቀ መለኮታዊ ኃይል ካልደረሰላት በስተቀር ቤተክርስቲያኒቱ እንደሥጋ ደዌ በሽታ እየፈራረሰች ማለቋን የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ያየ ያስተውላል። የዚህ ታሪክ ጸሐፊ ከ10 ዓመት በፊት ስለቤተ ክርስቲያኒቱ አደጋ በሰፊው ጽፎ ነበር። ይህንን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ!
1/ለውጥ አንድ
2/ለውጥ ሁለት
3/ለውጥ ሦስት
4/ለውጥ ዐራት
5/ለውጥ አምሥት
ወደተነሳንበት ርዕስ እንመለስ!
ለመሆኑ አህያ፣ ፈረስ ወይም አሳማ፣ ሸኮናው ድፍን፣ሸኮናው ቅድ፣ የሚያመሰኳ፣ የማያመሰኳ ይበላል፣ አይበላም ያለው ማነው? ኢትዮጵያ በሲና ተራራ ላይ ኪዳን የተገባላት የኪዳን ሀገር ናት ወይ? ብለን እንጠይቅ። መልሳችን አይደለችም ይሆናል። ኢትዮጵያ ከግብፅ፣ ከሱዳን፣ ከየመን ወይም ከሶሪያ የተለየች የኪዳን ሀገር አልነበረችም፣ አይደለችምም። ሙሴ የሕጉን ኪዳን በሲና ተራራ ላይ ከተቀበለበት አንስቶ በሰሎሞን ቤተመቅደሱ እስከታነፀበት ድረስ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ለ500 አመታት ያህል በጣኦትና በፀሐይ አምልኮ ስር እንደነበረች ታሪክ ይነግረናል። ታዲያ ባልኖረችበትና በሌለችበት ረጅም የእንቅልፏ ዘመን ውስጥ ልክ የብሉይ ኪዳንን ሕግ ተቀብላ ስትተዳደርበት የነበረች አድርጋ ስለሸኮና ድፍንና ቅድ የኦሪት ሕግ ለማውራት የሚጠይቃት የተለመደ ድፍረቷን እንጂ እውቀቷን አይደለም። ሲጀመር ከእግዚአብሔር ለኢትዮጵያ የተሰጠ የኪዳን ሕግ የለም። ሕግ ሁሉ ለእስራኤል ብቻ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሚነግረን እውነት ይህንኑ ነው።
“ነገር ግን እናንተን፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ፤ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ። እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ።”
— ዘሌዋውያን 20፥24
ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር በዚህ ኪዳን ውስጥ ነበረች? ኧረ በጭራሽ! በተረትና እንቆቅልሽ PHD ሲኖርህ እንደዘቤ ደፋሩ የሌለህን እውቀትና ማስረጃ በ"ተረቴን መልሱ፣ አፌን በዳቦ አብሱ" ዘዴ ይሆንን ጎጋ ምእመን ታስጨበጭባለህ። ከየት እንደተማረው ባይነግረንም ከዘበነ ለማ በስተቀር የኦሪት ሕግ ለኢትዮጵያ መሰጠቱን ታሪክ አያውቀውም።
ንጉሡ ዳዊትም በመዝሙር እስራኤልን ለርስቱ የተመረጠ ሕዝብ እንደነበረ እንዲህ እያለ ሲዘምር እናገኘዋለን። ዳዊት የኢትዮጵያ ንጉሥ ሆኖ ያውቃል እንዴ? ዳዊት ለርስቱ እግዚአብሔር የመረጠው ሕዝብ ንጉሥ እንጂ የአህዛብ ንጉሥ አልነበረም። አህዛብ ግን ከእግሩ በታች ተቀጥቅጠው የተገዙ ባሪያዎች ነበሩ። መዝ 47፣3-4
አሕዛብን ከእኛ በታች፥ ወገኖችንም ከእግራችን በታች አስገዛልን። ለርስቱ እኛን መረጠን፥ የወደደውን የያዕቆብን ውበት።
ኦርቶዶክስ ወንጌል ገና አልገባትም ስንል በማስረጃ ነው። እሷ ግን 2000 አመቴ ነው ብላ እድሜዋን በመቁጠር የእውቀት ሁሉ ጫፍ እንደደረሰች ልትነግረን ትፈልጋለች። እኛ ደግሞ ድንጋይ ውሃ ውስጥ ለሺህ አመታት ስለኖረ ዋና ይችላል ማለት አይደለም እንላታለን። እድሜ ጥሩ ቢሆንም በራሱ ምሉዕና ባለእውቀት ያደርጋል ማለት አይደለም። የግእዝን ብሂል ስላጠኑ ብቻ የእውቀት ጫፍ የደረሱ የሚመስላቸው የተረት አባቶች ከእውነት እንደተፋቱ ዛሬም አሉ።
የዚህ ፅሑፍ አቅራቢ አህያም። አሳማም፣ አንበጣም አይበላም። የማይበላው የተጠቀሱት ፍጥረታት እንደብሉይ ኪዳን ሕግ አትብሉ ስለተባለ ወይም በሐዲስ ኪዳን አስተምህሮ ርኩሳን እንደሆነ እንደተቆጠሩ ስለተማረ ሳይሆን የመብላቱ ባህልና ልምድ ስለሌለው ነው። እኔ አልበላም ማለት የሚበላ ሰው ቢኖር ረክሷል በሚል ኢ-ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ከማነወር ነጻ ሰው ስለሆነ ነው።
ወንጌል እንደሚነግረን “የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና።”
ሮሜ 14፥3
የኦርቶዶክስ መምህራን ነን ባይ ከእውቀት የተፋቱ የተረት አባቶች በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተምታታ መልስ ሲሰጡ ተዉ እንጂ ብሎ የሚከለክላቸው የለም። ተሳስታችኋል ብሎ የሚያርማቸው ስለሌለ እንደፈለጉት እየተረጎሙ ስለ ሸኮና ቅድ፣ ሸኮና ድፍን፣ የሚያመሰኳ፣ የማያመሰኳ እያሉ ያልተሰጣቸውን ሕግ እየጠቀሱ የረከሰና ያልረከሰ ሕዝብ እያሉ ራሳቸውን ከጻድቃን ጎራ፣ የሚበላውን እንደኃጢአተኛ ፈርጀው ፍርድ ሲሰጡ ድንቁርናቸው አይሰቀጥጣቸውም። በሐዲስ ኪዳን ከልማድና ከወግ ካልሆነ በስተቀር የማይበላ ነገር የለም።
1ኛ ጢሞ 4:4-5
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፥ ከምስጋናም ጋር ቢቀበሉት የሚጣል ምንም የለም፤ በእግዚአብሔር ቃልና በጸሎት የተቀደሰ ነውና።
በዘንዶና በፀሐይ ታመልክ የነበረችው የአህዛብ ሀገር ኢትዮጵያ ያልተሰጣትን ሕግ እየጠቀሰች ቅድና ድፍን የምትለው ተረት ተረት ለእስራኤል የተነገረውን ቃል ወደራሷ እየተረጎመች ካልሆነ በስተቀር በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ውስጥ አህዛብ ማነው? ሕዝብስ? ብለን እንጠይቃታለን።
“አሁንም ቃሌን በእውነት ብትሰሙ ኪዳኔንም ብትጠብቁ፥ ምድር ሁሉ የእኔ ናትና ከአሕዛብ ሁሉ የተመረጠ ርስት ትሆኑልኛላችሁ፤”
— ዘጸአት 19፥5
ከእስራኤል ውጪ ያለው ሁሉ አህዛብ ይባላል። አህዛብ ደግሞ የኦሪቱ ሕግ የኪዳን ሕዝብ አካል አይደለም። ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሌላት የኪዳን ሕግ የሚበላና የማይበላ እያለች ስለኮሼር kosher” (כָּשֵׁר) ሕግ መናገር አትችልም። ከተናገረችም ከድንቁርና የተነሳ ነው። ከእስራኤል ውጪ የነበረው አህዛብ ይባላል። የአህዛብ ሀገር ኢትዮጵያ ስለሕግ ማውራት አትችልም።
ከሕጉ ውጪ የነበርነውን እኛን አህዛቦችን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕጉን ትእዛዛት ሁሉ ፈፅሞ በሐዲስ ኪዳን ሕግ እንደአዲስ ወለደን።
ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ፣
“እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤”
— ሮሜ 9፥4 ካለ በኋላ ከሕግ መሰጠት ውጪ የነበርነውን እኛ አህዛብን ወደአዲሱ የድነት ሕግ እንዴት እንደገባን እንዲህ እያለ ይነግረናል። "የምሕረቱ ዕቃዎችም ከአይሁድ ብቻ አይደሉም፥ ነገር ግን ከአሕዛብ ደግሞ የጠራን እኛ ነን። እንዲሁ ደግሞ በሆሴዕ፦ ሕዝቤ ያልሆነውን ሕዝቤ ብዬ፥ ያልተወደደችውንም የተወደደችው ብዬ እጠራለሁ፤ እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም በተባለላቸውም ስፍራ በዚያ የሕያው እግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉ ይላል። (ሮሜ9፣24-26)
ሕግን የተከተሉ እስራኤሎች ሕግን በመከተላቸው በእምነት ከሚገኘው ጽድቅ ጎደሉ። እኛ አህዛብ ደግሞ በሕግ ከነበረው ሥርዓት ውጪ ስለነበርን በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ በማመን ከሚገኘው ጽድቅ የእምነት ተካፋይ ሆንን።
"እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው፤ እስራኤል ግን የጽድቅን ሕግ እየተከተሉ ወደ ሕግ አልደረሱም።" ሮሜ9፣30-31
ማጠቃለያ፣
ስለሕግ አፈጻጸም ዛሬ ማንም የመናገር መብት የለውም። ፊተኛውን አስረጅቶ ዛሬ በአዲስ ኪዳን ሕግ ውስጥ ነን። የቀደመችቱ ሕግ፣ ሕጉን ያፈረሰ ምን ይሁን ትላለች? በድንጋይ ተወግሮ ይገደል! ኦርቶዶክስ የቀድሞውን ሕግ በግድ እየተገብራለሁ ካለች ስንት ሰው ደብድባ ልትገድል ነው? አባ ባርናባስ ያስተማሩት እንደወንጌል ሕግ ስህተት ባይኖርባቸውም እንደኦሪት ሕግ አስፈጻሚዋ ኦርቶዶክስ አንድ ቀን የማደር መብት ሊያገኙ አይገባም ነበር። ሕጉ ይገደሉ ስለሚል። ዘቤ ለማ ምትክ አልባው የተረት አባት phd በተረት holder፣ ሄኖክ ኃይሌ በተረቱ ብዛት ምእመናን በባዶ ሜዳ ያሰከሩት ዲያቆን፣ መምህራነ ኮኑ በበደወሉ፣ ፊደላተ ዘኈለቁ ኵሉ የተባለላቸው ተረት ጠምጣሚ ሁሉ በማይመለከታቸውና በማያውቁት የኦሪት ሕግ በግድ ነው የሚጮሁት እውነቱን ስለሚያውቁ ሳይሆን ድንቁርናቸውን እንደባለእውቀት ትውልዱ ስላጸደቀላቸው ነው።
የእግዚአብሔር መንግስት አሳማ በመብላት አትጠፋም፣ ባለመብላትም አትገኝም። “የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።”
— ሮሜ 14፥17
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፥ ከምስጋናም ጋር ቢቀበሉት የሚጣል ምንም የለም፤ በእግዚአብሔር ቃልና በጸሎት የተቀደሰ ነውና።
1ኛ ጢሞ4፣4-5 ስለዚህ በመብላትና ባለመብላት ራሷን ጻድቅ የምታስመስለው ኦርቶዶክስ ከ2000 ዓመት በኋላም ወንጌል ገና አልገባትም። በግሌ አሳማም፣ አህያም አልበላም። አልበላም አልኩ እንጂ የሚበሉት ተኮንነዋል፣ ረክሰዋልም ማለቴ አይደለም። የሚበሉትን አናረክስም፣ የማይበሉትንም ብሉ ብለን አንሰብክም። ወንጌል ስለመብልና መጠጥ አይደለችምና። አባ በርናባስ ያስተማሩት ምንም ስህተት ባይኖርበትም በመንጋ ለሚነዳ ምእመን ይህንን ማስተማር እንደወንጀል ስለሚቆጠር ስለመብልና መጠጡ ትተው መጀመሪያ ስለወንጌል የመዳን ቃል ይስበኩ። ኦርቶዶክሶች ወንጌልን በግእዝም፣በአማርኛም በልዩ ልዩ ቋንቋ ያነቧታል እንጂ አልተረዷትም! የዘሌዋውያን ሕግ እንኳን በኢትዮጵያ በዛሬይቱ እስራኤል የለም። የሌለውን ሕግ እንዴት አድርጋ ነው ኦርቶዶክስ የምትተገብረው? ዘቤ መልስልኝ። ሕጉ ካልተፈጸመ መውገሪያ ድንጋይህን ይዘሃል ወይ? ለነገሩ አንተ ራስህ የቤተክርስቲያኒቱ መርግ ነህ።
Monday, July 8, 2024
ታቦትና ጽላት ዛሬ የሉም!
ዛሬ ታቦትና ጽላት የሉም!
ሐዋርያው ጳውሎስ ለተሰሎንቄ ሰዎች በላከው መልእክቱ "ከሚመጣው ቁጣ ትድኑ ዘንድ ራሳችሁን ከጣዖት ወደእግዚአብሔር ዘወር እንዳላችሁ" እያለ የነበሩበትን ከንቱ አምልኮ አራግፈው በመተው እንዴት እንደተመለሱ ሲያስታውሳቸው እናነባለን። ይህንንም አስረግጦ ሲያስረዳ ልትተዉት የሚገባውን እየነገርን፣ ለእግዚአብሔር መታዘዝን እያስረዳናችሁ እንጂ በማባበል ወይም በማቆላመጥ እንዳልነበረ እናንተው ምስክሮቻችን ናችሁ ይላቸዋል።
"እንደምታውቁ፥ እያቈላመጥን ከቶ አልተናገርንም፥ እግዚአብሔርም እንደሚመሰክር እያመካኘን በመጎምጀት አልሠራንም፤ የክርስቶስም ሐዋርያት እንደ መሆናችን ልንከብድባችሁ ስንችል፥ ከእናንተ ቢሆን ወይም ከሌሎች ክብርን ከሰው አልፈለግንም።" (1ኛ ተሰ2:5—6)
ይህንን ቃል ዛሬም ያለማቆላመጥ፣ ክብርና ምስጋናን ባለመፈለግ በግልጽ ቋንቋ መናገር ይገባናል። ይኼውም በዚህ ዘመን ከሰማይ በታች ለተለየ ወገን፣ ዘር፣ ትውልድ ወይም በአጠቃላይ የሰው ልጅ ለተባለ የተሰጠ የቀደመችውን የእስራኤላውያን ዓይነት የታቦትና የጽላት ሕግ የለም። አዎ በዚህ ዘመን ትውልድ የሚንበረከክለት፣ የሚሰግድለት፣ ምሥጋናና ውዳሴ የሚቀርብለት፣ እልልታና እምቢልታ የሚነፋለት ታቦትም፣ ጽላትም የለንም!
ይልቅስ ዓይናችሁን ሕግን ሁሉ ወደፈጸመው፣ ሕግ ያስከተለው እዳና በደላችንን ቀራንዮ ላይ በሞቱ ጠርቆ ወዳስወገደው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልከቱ። (ቆላስ2:15)
ሕግ ካስከተለው ሞት ሕይወት ወደሰጠን ሕያው ታቦታችን ኢየሱስ ተመልከቱ። ይኼን በግልጽ / baldly/ መናገር እውነትን መግለጥ እንጂ ሃይማኖታዊ ስብከት አይደለም።
(2ኛ ቆሮ3:3)
ምክንያቱም፣
1/ ታቦትም፣ ጽላትም የተሰጠው ከአህዛብ ለተለየው ለእስራኤል ከሥጋ ነው። (ዘዳ7:6)
2/ ለታቦትም ሆነ ለጽላት የተሰጠ መለኪያ፣ መስፈሪያና ሕግ ዛሬ ላይ የለም። (ዘጸ 25:10—23)
3/ ሙሴ በሰበረው ላይም ይሁን ዳግመኛ በቀረጸው ጽላት ላይ 10ቱን ትዕዛዛት በጣቱ የጻፈው እግዚአብሔር ራሱ ነው። (ዘጸ31:18) (ዘዳ10:4)
በእነዚህ ዋና መመዘኛዎች የተነሳ ዛሬ ላይ ታቦትም፣ ጽላትም የለም ብሎ ደምድሞ መናገር ይቻላል። እኛ አለን ብለው የሚከራከሩን ካሉ መልሳችን እሱ ወደእግዚአብሔር የሚደረግን አምልኮ የሚጋርዱ የማመለኪያ አፀዶች ናቸው እንላቸዋለን። (ዘዳ16:21—22) እስራኤሎችም ወደ እግዚአብሔር የሚደረግን አምልኮ የሚያጋሯቸው የማምለኪያ አፀዶችን እየተከተሉ እግዚአብሔርን ያስቀኑ ነበር። የማምለኪያ ቅርጾች፣ ምስሎች፣ ስዕሎች፣ ስግደት የሚቀርብላቸው የሰዎችና የመላእክት ስሞች በሙሉ ከአህዛብ የተወረሱ ሲሆኑ ለእግዚአብሔር ብቻ የሚቀርብን ምሥጋናና ውዳሴ በመጋረድ እነሱም እንዲካፈሉ (share) እንዲያደርጉ በሰይጣን የተፈበረኩ ጣዖታት ናቸው። ለጣዖት አምልኮው መሸፈኛ የሚቀርበው ሞገት እግዚአብሔር ያከበራቸው ስለሆኑ ነው የሚል ቢሆንም ስግደት፣ ምሥጋና፣ ውዳሴ፣ እልልታ፣ ሽብሸባ፣ ቅኔና ዝማሬን አካፍላችሁ ብትሰጡልኝ እኔ በነሱ በኩል እንደደረሰኝ እቆጥርላችኋለሁ ያለበት ጊዜ የለም። አንዳንድ መፍቀሬ ጣዖታት ሰዎች በጻድቅ ስም የተቀበለ የጻድቁን ዋጋ ያገኛል እያሉ አምልኮ አፀዳቸውን ለመከላከል ሲጋጋጡ ይታያሉ። ለምሳሌ ሐዋርያው ጳውሎስ የታመነ የእግዚአብሔር ሰው ነበረ ብሎ ማመን ያላየሁትን ጳውሎስ ምስልና ሐውልት ሰርቼ፣ ታቦትና ጽላት ቀርጬ እንድሰግድለት፣ እንድንበረከክለት፣ የዝማሬ፣ የቅኔ ጎርፍ እንዳፈስለት ሊያደርገኝ አይችልም። ምንጩ ያልታወቀው የጳውሎስ ምስል ለክርስቲያን ምኑ ነው? የጳውሎስስ ጽላት መነሻው ከየት ነው?
እስራኤሎችን ሲያስቸግር ከነበረው ከማመልከያ አፀድ የሰይጣን መንፈስ የተቀዳ ነው። እግዚአብሔር በእገሌና በእግሊት በኩል የምታቀርቡት ምስጋናና ውዳሴ በተዘዋዋሪ ይደርሰኛልና ቀጥሉበት ሊል የሚችልበት አምላካዊ ባህርይ የለውም። ይልቁንም “እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም። ”ኢሳ 42፥8 ሲለን እናገኘዋለን።
እነዚህ በገበያ ላይ የሚሸጡ የጂፕሰም ምስሎች፣ ቅርጾችና የቀለም ስዕሎችን ግማሽ ክርስቲያኖች እየገዙ ስግደት፣ ጸሎትና ማዕጠንት የሚያቀርቡላቸው ከአምልኮ እግዚአብሔር ጋር የሚያገናኛቸው ምንም ነገር የላቸውም። በአምልኮ ሽፋን የከፍታ ወንበር ላይ የተሰቀሉ ጣዖታት ናቸው።
በሰማይ ሚካኤልና መላእክቱ ከዘንዶው ጋር እንደተዋጉና ዘንዶውም እንዳልቻላቸው የሚናገረውን የዮሐንስ ራእይ 12:7 መነሻ በማድረግ ጣሊያናዊው ሰዓሊ ጉዊዶ ሬኒ (Guido Reni) በ1635 የሳለውን ስዕል ከገበያ ገዝተው ክርስቲያኖች የሚሰግዱለት፣ በየጥንታውያኑ አብያተ ክርስቲያናት በሱቲ፣ በተንቆጠቆጠ ጨርቅና መብራት በከበረ ቦታ ተቀምጦ፣ ስግደት እየተቀበለ፣ በእጣን እየታጠነ ውዳሴ የሚጎርፍለት ጣዖትን ከማምለክ ውጪ ሌላ ምን ስም ሊሰጠው ይችላል? ጉዊዶ ሬኒ የሰዓሊነት እውቀቱ ያመነጨው እንጂ ከዘንዶው ጋር ስንት የወደቁ መላእክት እንደነበሩና ከሚካኤል ጋር ስንት መላእክት እንደተሰለፉ የሚያውቀው አንዳች ነገር የለም። የወደቀው ባለጡንቻ ወጠምሻው ጥቁር ሰው ሰይጣን መሆኑ ነው? ጥቁር የሆነ ነገርን ሁሉ የሰይጣን መለያ አድርጎ የሰጠው ማነው? የብርሃንን መልአክ ለመምሰል ራሱን መለወጥ የሚችልን ፍጥረት ሁልጊዜም ጥቁር እንደሆነ ማሰብ የእውቀት ጉድለት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ እሱም ስዕሉ ወግ ደርሶት በየቤተመቅደሱና ክርስቲያን መሳይ አላዋቂዎች ቤት በክብር ተሰቅሎ እሱም በወደቀበት ስግደትን ይቀበላል። ያ ወደል ወጠምሻ ሰው ወደስዕሉ የሚደረገውን አምልኮ የሚስማማበት ይመስለኛል።
ማጠቃለያ፣
በአዲስ ኪዳን ለእስራኤል ብቻ ተለይቶ የተሰጠው የኪዳኑ ታቦት ዛሬ የለም። "ሥጋና ደሙ የምንፈትትበት ነው" የሚለው ለክህደት የሚቀርብ ምክንያት አምልኮን ከእግዚአብሔር ውጪ ለሌላ በማጋራት ከሚያስከትለው የዘላለም ሞት አያስጥልም። እንደጠረጴዛ እንገለገልበታለን እንጂ እያልክ በፈጠራ ስዕል አሽሞንሙነህ፣ ተሸክመኸው ውጣና ሕዝብን በእልልታና በሆታ፣ እያስጎነበስክ በስግደትና በከንቱ አምልኮ ወደሞት እርድ ንዳው የሚል ፈቃድ የሰጠህ ማነው?
ስዕል፣ ምስልና ቅርጽ በየመቅደሱ፣ በየዐውደ በራፉ አስቀምጠህ እያሰገድክበት የገንዘብ መሰብሰቢያ አዚም አድርገህ እንድትጠቀም በልብልህ ላይ ከሰይጣን ውጪ ይሄንን ረቂቅ ተንኮል ያቀበለህ ማንም የለም።
ለዚህ ዓይን ያወጣ፣ ከአምልኮ እግዚአብሔር የራቀ ተግባርህ ዋጋ ትከፍልበታለህ። እግዚአብሔር ያጸዳዋል፣ ቆሻሻውን ይጠርገዋል። የኤልዛቤልን ግልሙትና ገፎ እርቃኗን ያስቀረዋል። እግዚአብሔር ከነክርፏቷ የተሸከማት እድሜ ለንስሐ ነበር፣ አሁን ግን ራሱ ወርዶ የገማውን አስወግዶ፣ አዲስ አድርጎ ይሰራዋል!
Monday, June 10, 2024
ካህን ማነው?
ካህን ማነው?
ካህን የሚለው ግስ ስርወ ቃሉ ዕብራይስጥ ሲሆን ኮሄን כהן (kohen) ከሚለው ቃል የመጣ ነው። አጭር ትርጉሙ "አገልጋይ" ማለት ሲሆን አቅራቢ፣ ሠራተኛ፣ የሚራዳ ማለትንም ያመለክታል። በቅዱስ መጽሐፋችን የመጀመሪያው ካህን የሳሌም ንጉሥ የነበረው፣ ትውልድና ዘር ያልተቆጠረለት መልከጼዴቅ ነበር። (ዘፍ 14:18) እሱም የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነበር። (ዕብ6:20) የመልከጼዴቅ ክህነት በኢየሱስ ክርስቶስ ምሣሌነት የተነገረበት ምክንያት የካህንነት ሹመቱ በነገድ አልተቆጠረም። የኦሪቱ የክህነት ሥልጣን ከሌዊ ነገድ በመወለድ የሚገኝ ቢሆንም ኢየሱስ ግን ሊቀካህን የሆነው ከይሁዳ ነገድ ነው። የኦሪቱ ክህነት ያለመሃላ የሚፀና ቢሆንም የኢየሱስ ክህነት እንደመልከ ጼዴቅ ክህነት በእግዚአብሔር በመሃላ የተረጋገጠ ነው። (ዕብ 7:20—21)
የዚህ ክህነት ዋና ምስጢር በአዲስ ኪዳን ከኢየሱስ በስተቀር በመሃላ እንደመልከ ጼዴቅ ለዘላለም ካህን ነህ ተብሎ የሚሾም ሌላ ካህን የለም ማለትን ያመለክታል። የኢየሱስ የካህንነት ምስጢር ራሱ መስዋእት፣ ራሱ መስዋእት አቅራቢ፣ በአብ የተወደደ መስዋእት ሆኖ በደሙ የዘላለም የኃጢአት ማስተሰሪያ መስዋእት ሆኖልን ስለእኛ ጸንቶ መቆሙን ያረጋግጥልናል።
“እርሱም እንደነዚያ ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ዕለት ዕለት መሥዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤ ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎአልና።” (ዕብ 7፥27)
የዚህ በመሃላ የተሾመው ሊቀካህን መስዋእት ወደእሱ የሚመጡትን ነፍሳት ሁሉ የሚቤዥ አንዴ የቀረበ፣ ሕያው የሥርየት መስዋእት ነው።
“ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።”(ዕብ 7፥25)
ስለመልከጼዴቅ ከብሉይ ኪዳን የምናነበው ቃል ከአብርሃም ጋር ተገናኝቶ ከመባረኩ በስተቀር በፊት የት እንደነበረ፣ በኋላም ወዴት እንደሄደ የተነገረ ምንም ታሪክ የለም። ይህንን ታሪክ ኢየሱስ ራሱን በዘላለማዊ የማዳን የምልጃው ውስጥ መስዋእት ሆኖ ራሱን ሲገልጥ ብቻ ነው ለማየት የቻልነው። (ዕብራውያን ምዕራፍ 7ን ደግመው ያንብቡ)
ስለዘላለማዊ ሊቀካህን አገልግሎት ስንናገር ይሄንን ሥርዓት ኢየሱስ በራሱ መስዋእትነት የደመደመው ስለሆነ እኛ ክርስቲያኖች ከእንግዲህ ሌላ ምድራዊ ሊቀካህን ዛሬ የለንም። ምክንያቱም የሊቀካህን አገልግሎት በእግዚአብሔርና በሰው መካከል፣ መካከለኛ አገልጋይ ሆኖ ሥርየትን ማስገኘት ነበር። በኦሪቱ የነበረውን የደም መስዋእት በራሱ ሕያው ሞትና ትንሣኤ ላመኑበት ሁሉ ሥርየትን ስላስገኘ ለክርስቲያን የሚሞትና ቢሞትም ሥርየትን ማሰጠት የሚችል ሰው የለምና ነው። እንኳን ለሌላው የኃጢአት ሥርየት መሆን ይቅርና ራሱን ለማዳን የሚበቃ ማንነት ያለው ሰው በምድር ላይ በጭራሽ የለም። በዚህ ዘላለማዊ ሊቀካህን ሞትና ትንሣኤ ያመንን እኛ በሱ የዘላለም ሕይወትን አግኝተናል።
“እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።”ዮሐ 6፥47
ሌላኛው የክህነት አገልግሎት ያለመሃላ የተሾሙይ የአሮን ዘሮች ነበሩ።
በብሉይ ኪዳን የካህናት ወገን መሆን የሚቻለው ከያዕቆብ ልጆች ሥስተኛ በሆነው ከሌዊ ዘር በመወለድ ብቻ የሚገኝ የአገልግሎት ክብር ነበር።(ዘዳ10:8) ሌዊ ማለት በዕብራይስጥ የተባበረ፣ የተያያዘ፣ የተገናኘ ማለት ነው። ምናልባትም የስሙ ትርጓሜ ከመገናኛው ድንኳን አገልግሎት ጋር የተያያዘና በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል አገናኝ የሆኑበትን የክህነት አገልግሎት የሚያመለክት ስም ይሆናል። ሌዋውያን የመገናኛው ድንኳን አገልጋዮች ስለሆኑ ከ፲፩ዱ የእስራኤል ነገድ ጋር እንዳይቆጠሩ እግዚአብሔር አዘዘ።
(ዘኁ1:48—49) የሌዋውያን አገልግሎት የምስክሩን ድንኳን መጠበቅ (ዘኁ1:51) ሲንቀሳቀሱ መሸከም (ዘኁ1:53) በማረፊያቸው ደግሞ መትከል ሲሆን አሮንና ልጆቹ ደግሞ የመስዋዕቱን ሥርዓት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ማከነወን ነበር። (ዘጸ28:41) በኋለኛው ታሪክ እንደምናነበው ከሌዋውያኑ ወገን የሆኑት አሳፍና ወንድሞቹ ደግሞ በከበሮ፣ በጸናጽል፣ በመሰንቆ ይዘምሩ ነበር። (1ኛ ዜና 15:16—19)
ከክህነት አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ከሌዊ ወገን የሆኑ ካህናት በምስክሩ ድንኳን ውስጥ ልዩ፣ ልዩ የአገልግሎት ድርሻ ነበራቸው። ሕዝበ እስራኤል ሲንቀሳቀስ የመገናኛውን ድንኳን በታዘዘው መሠረት ነቅለው ለሸክም የሚያዘጋጁ፣ የተዘጋጀውን ንዋያተ ቅድሳት ደግሞ የሚሸከሙ፣ በሚያርፉበት ቦታ ደግሞ ከተሸከሙት ተቀብለው በሥርዓቱ ተክለው ለአገልግሎት የሚያዘጋጁ፣ በተተከለው ድንኳን ውስጥ የማስተሰርያ መስዋዕቱን የሚያከናውኑ፣ ተሸክመው ሲሄዱም ሆነ ሲያርፉ በመዝሙርና በመሰንቆ እያሸበሸቡ የሚያገለግሉ መዘምራን ነበሩ። በዚህ የመገናኛው ድንኳን አገልግሎት ውስጥ ከሌዊ ነገድ የተወለዱት ብቻ በአገልግሎት ተከፍለው በእግዚአብሔር የታዘዙትን አገልግሎት ሲፈፅሙ ኖረዋል። የዚህ ክህነት ባለሙሉ መብት ደግሞ በእግዚአብሔር የተመረጡት የእስራኤል ሕዝቦች ሲሆኑ ከእነርሱም መካከል የሌዊ ዘሮች ብቻ ነበሩ። ከሌዊ ዘሮችም ለድንኳኑ አገልግሎት የተለዩት የአሮን ልጆች ብቻ ናቸው። ስለዚህ፣
1/ በዚህ ዘመን እስራኤላውያን ብቻ ናቸው ለእግዚአብሔር የተመረጡ ሕዝቦች የሚል የአዲስ ኪዳን ትምህርት የለም። ስለዚህ ለተለየ ሕዝብ የተሰጠ የብሉይ ኪዳን የክህነት ሕግ በዚህ ዘመን የለም። አማኞች ሁሉ ካህናት ናቸው።
“መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።” ራእይ 5፥9-10
2/ ሌዊ በሌለበት ሌዊ፣ መስዋዕትና ሥርየት አቅራቢው ኢየሱስ በሆነበት ራሱን የተለየ ካህን የሚያደርግ ቢኖር እሱ ምድራዊ ሥርዓት ነው።
እኛ በኢየሱስ ሊቀካህንነት ያመንን ሁላችን ለርስቱ የተለየን በደሙ የተዋጀን ካህናት ነን።
“እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥9
3/ ሌላ የምድራዊ ሹመት ሊቀካህን ይሁን ካህናት የማያስፈልገን ምክንያት ሁሉም ሰዎች በሞት የሚሸነፉና በኃጢአት የወደቁ ወይም ሊወድቁ የሚችሉ ደካማ ፍጥረቶች ስለሆኑ ነው።
ዕብ 7፣22—23 እንዲሁ ኢየሱስ ለሚሻል ኪዳን ዋስ ሆኖአል። እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው።
ሥልጣነ ክህነት የሚባል መለኪያና መስፈሪያ የተዘጋጀለት የአገልግሎት መስፈርት በዚህ ዘመን አለ ቢሉ እሱ ከምድራዊ አስተምህሮ የመነጨ እንጂ ከሰማያዊ አገልግሎት ጋር ምንም ግንኙነት የለውም። በሰማይም፣ በምድርም ያለን ሊቀካህን አንድ ሲሆን እሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ዕብራውያን 8፣ 1—2 ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፥ እርስዋም በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ናት።
በሊቀካህናችን በኢየሱስ መስዋዕትነት ያመንንና የኃጢአትን ሥርየት ከአብ የተቀበልን፣ እኛ አማኞች ሁላችን በኢየሱስ የተሾመን ካህናት ነን።
“መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን።”
— ራእይ 1፥6
ማጠቃለያ፣
ካህን ማነው? ለሚለው ጥያቄ የማጠቃለያ መልሳችን በእስራኤል ዘሥጋ ዘመን ከ12ቱ ነገድ ለሌዊ ብቻ የተሰጠ ነበር። በአዲስ ኪዳን ዘመን በመልከ ጼዴቅ ሥርዓት የዘላለም ሊቀካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን በእሱ ያመን እኛን በደሙ ተቀድሰን የመንግሥቱ ካህናት፣ የሰማያዊት ኢየሩሳሌም አገልጋዮች ሆነናል።
" ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥ በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥ የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል"
(ዕብ 12:22—24)
Thursday, March 28, 2024
ጸጋ ምንድነው? What is Grace?
ይህ ፅሑፍ ከባለፈው ፅሑፋችን የቀጠለ ነው። በባለፈው ፅሑፋችን "የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግንብ ሳይሆን ሰው ራሱ ነው፣ በእግዚአብሔር የተቀደሰው" ካልን በኋላ የተቀደሰ ቤተ መቅደስ መሆን የሚቻለው እንዴት ነው? በሚለው ጥያቄ ላይ ተመርኩዘን ዛሬ ደግሞ በዚሁ ዙሪያ የተወሰነውን ሐተታ እናቀርባለን። መልካም ንባብ!
በጌታችን፣ በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ ሁሉ የኃጢአታቸውን ሥርየት አግኝተው የዘላለምን ሕይወት ይወርሱ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉ።
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” ዮሐ 3፥16
አብ በአንድያ ልጁ በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ልጆቹ እንድንሆንለት በመፈለጉ የተነሳ ከቀዳማዊው የአዳም ኃጢአት፣ ሥርየት ያገኘንበትን ሰማያዊ ስጦታ ልጅነትን ሰጥቶናል። በዚህም የተነሳ የዐመጻ ልጆች እንዳልነበርን ሁሉ (ዕብ 8:12) አባ፣ አባት ብለን የምንጠራበትን የልጅነት መንፈስ (ሮሜ 8:15) ካገኘን በኋላ ልጅነታችንን በመጠበቅ መኖር ያለብን እንዴት ነው? የሚለው ጉዳይ የግድ ሊታወቅ የሚገባው መንፈሳዊ እውቀት ነው።
በዚህ ምድር ላይ ለሚኖር ሰው ሁሉ የነፍስ የኃጢአት በሮቹ ሦስት ናቸው። አምነው ባልዳኑ ሰዎች ላይ ሦስቱም የኃጢአት በሮች ክፍት ስለሆኑ በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት እስኪያምኑ ድረስ በዚህ ፅሑፍ ስለጸጋ አስፈላጊነት ልንመክራቸው አንደፍርም።
*ሦስቱ የኃጢአት በሮች ምንድናቸው? እንዴትስ ይሰራሉ?
ሦስቱ የኃጢአት በሮች የተባሉት፣
1/ ሥጋ 2/ ዓለም 3/ የወደቀው መልአክ ናቸው።
ያመኑና የዳኑ ክርስቲያኖች በሙሉ እነዚህን የኃጢአት በሮች ምንነት ማወቅና ለመዝጋት የሚችሉበት አስፈላጊ ኃይላቸው ጸጋ /grace/ይባላል። የእግዚአብሔር ልጅ መሆን የቻልንበትን ድነት/ድኅነት/ ይሄንን ምድር ለቀን እስክንሄድ ድረስ አስጠብቀን መገኘት የግድ ነው። አንዴ ድኛለሁና ከእንግዲህ የፈለኩትን መሆን እችላለሁ አይባልም። ይሄንንም ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ እያለ መንፈሳዊ ማሳሰቢያ ይሰጠናል።
"እንግዲህ ለምኞቱ እንድትታዘዙ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አይንገሥ፤ ብልቶቻችሁንም የዓመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ፥ ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ፥ ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ።" (ሮሜ 6: 12—13)
ስለሆነም ከድነት በኋላ አማኝ ሁሉ ራሱን በጽድቅና በቅድስና መጠበቅ አለበት። ይሄን ከባድ የሚመስል ነገር ግን የመንፈሳዊ ብቃት ኃይል የሆነውና ጸጋ የተባለው የታላቅ ምስጢር እውቀት ያስፈልገዋል።
ጸጋ የሚገኘው እንዴት ነው? የሚለውን ከማየታችን በፊት ጸጋ የሚከላከላቸውን ሦስቱን የነፍስ የኃጢአት በሮችን ማወቅ አለብን። የኃጢአት በሮቹን ካወቅን በሚሰጠን ጸጋ እንዴት መዝጋት እንደምንችልና አስፈላጊ እንደሆነ በደንብ ይገባናል።
1/ ሥጋ፣
የለበስነው ሥጋ ፈራሽና በስባሽ ነው። በዳግም ትንሣኤ በአዲስ መልክ እስኪለወጥ ድረስ
“እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።”2ኛ ቆሮ 3፥18 "እንለወጣለን" የሚለውን የግሪኩ ቃል"μεταμορφούμεθα" ሜታሞርፌውሜታ ይለዋል።ይህም ከአንድ ከነበረበት ሁኔታ ወዳልነበረበት ሌላ ሁኔታ መለወጥ ማለት ነው። ለምሳሌ ቢራቢሮን ለመወጥ ይመለከቷል!
ነፍስ ወደተገኘችበት ወደሰማይ ስትወጣ ሥጋ የምትኖረው በዚህ ምድር ነው። ምክንያቱም ሥጋ የተሠራችው ከዚሁ የምድር አፈር ስለሆነ ነው። እግዚአብሔር ያበጀውን የምድር አፈር ሕይወት የሰጠው የሕይወትን እስትንፋስ እፍ ባለባት ጊዜ ነው። ሥጋ በራሱ ሕይወት የለውም። የሥጋ ሕይወቱ ነፍስ እስካለበት ድረስ ብቻ ነው። ከደቂቃዎች በፊት አንድ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ስታወራ የነበረች ሥጋ፣ ነፍስ ትቷት ቢወጣ በድን ሆና ትቀራለች። ነፍስ ከመለየቷ በፊትና ከተለየች በኋላ ሥጋ እዚያው ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ ይገኛል። ልዩነቱ ነፍስ ስለሌለበት ሥጋው ሕይወት የለውም። ነገር ግን ነፍስ እስካለችበት ድረስ ሥጋ ሕይወት ስለሚኖረው የተዋቀረችበት የዐራት ባህርያቷ መሻትና አደገኛ የማይስማሙ ፍላጎቶች አሏት። መሻቷንና ፍላጎቶቿን ማወቅና መቆጣጠር ያለበት ባለቤቷ የሆነው የዳነው ሰው ራሱ ሲሆን ይህም ኃይል የእግዚአብሔር ጸጋ ይባላል።
ሰው የነፍስና የሥጋ ውሁድ ሆኖ ድነቱን/መዳኑን/ መጠበቅ የሚችለው በመንፈሱ ነው። በኢየሱስ አምኖ የዳነ ሰው ሥጋውን መቆጣጠር የሚችለው ከእግዚአብሔር ጋር ባለው መንፈስ ሲሆን በየዕለት ግንኝነቱ የሚያግዘውንና የሚረዳው ጸጋ እንዲበዛለት ያደርጋል።
“እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።” ዕብ 4፥16
ምክንያቱም ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ እያለ አበክሮ የሚነግረን ራሳችንን ማሸነፍ የምንችልበት ይህ ጸጋ ከውድቀት ይታደገናልና ነው።
"ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።
ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም።" (ገላ 5:16—17)
ሥጋ ከምትበላውና ከምትጠጣው ሙቀት የተነሳ ወሲባዊ ፍላጎቷ ተቀስቅሶ ከትዳር በፊት ይሁን በኋላ ከተመኘኋት ጋር ላመንዝር ትላለች። የነፍስ መንፈሳዊ እውቀት ደግሞ “ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል።”
(1ኛ ቆሮ 6፥18) ብሎ ይቆጣጠራታል።
ሥጋ ልስረቅ፣ ልዋሽ፣ ላታልል፣ መሻቴን ሁሉ እንድፈፅም አትከልክሉኝ ትላለች። ጾም፣ ጸሎት አድካሚ ነው። ይሄ ሁሉ ለምኔ ነው? ልቀቁኝ፣ በአምሮቴ ልኑርበት ትላለች። ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ "“በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም።”
ሮሜ 8፥8 በማለት እቅጩን የነገረን። ለዚህም ነው፣ የሥጋን አምሮትና የመሻት በር ለመዝጋት ጸጋ የተባለው ኃይል የሚያስፈልገን። የእግዚአብሔር የበዛው ደግነቱ፣ በልጁ ሞት የዘላለምን ሕይወት ከሰጠን በኋላ የተፈጠርንበትን የሥጋ ፍላጎት መቆጣጠር የምንችልበትን ጸጋ የተባለውን ኃይልም አብሮ ሰጥቶናል።
ወሲብ ለሥጋ የተሰጠ የአምላክ ፈቃድ ነው። ነገር ግን ኃጢአት የሚሆነው አለቦታውና አለጊዜው ስንጠቀመው ነው። ቅድመ ይሁን ድኅረ ጋብቻ ወሲብ ሁሉ ዐመፅ ነው።
ምክንያቱም፣ “እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ።”ሮሜ 8፥13
“ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር፥ የወደደውን ያድርግ፤ ኃጢአት የለበትም፤ ይጋቡ።”1ኛ ቆሮ 7፥36
መብልና መጠጥ የሥጋ ባሕርያት ናቸው። ነገር ግን የምንበላውንና የምንጠጣውን መለየት፣ ሆዴ ይሙላ፣ ደረቴ ይቅላ ባለማለት ሥጋን ለመጎሰም በጾምና ጸሎት የምንጠመድበትን ኃይል ለማግኘት ጸጋ የተባለ ጉልበት ያስፈልገናል።
“መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤ ጌታም ለሥጋ ነው፤”1ኛ ቆሮ 6፥13
እዚህ ላይ በኢየሱስ አምነው ያልዳኑ ሰዎች ማለትም ሥጋና ነፍሳቸው ከእግዚአብሔር ባልሆነ መንፈስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ስለሆነ ከጸጋው ተለይተው ስለወደቁ ሁሉም ኃጢአቶች በነሱ ላይ አቅም ኖሮት የፈለገውን ይሰራል።
“ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና።”
(1ኛ ዮሐ 3፥8)
(...ይቀጥላል%)
Tuesday, March 12, 2024
እግዚአብሔር ሰው በሠራው ቤተ መቅደስ አይኖርም!
ይህ አባባል እግዚአብሔር ሰው በሠራው መቅደስ ዛሬ ይኖራል ብለው ለሚያምኑ ሰዎች ጆሮን ጭው የሚያደርግ ቃል ነው። ነገር ግን እውነቱ እግዚአብሔር ዛሬ ሰው በሠራው መቅደስ አለመኖሩ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር አዝዞት፣ ወርድና ቁመቱን ነግሮት የተሠራ ምድራዊ ቤተመቅደስ ዛሬ የለምና ነው። የቀደመችቱን የእስራኤል ቤተ መቅደስ ወርዱንና ቁመቱን፣ ስፋትና ርዝመቱን፣ ጽላቱንና ታቦቱን፣ ኤፉዱንና አልባሳተ ካህናቱን፣ መጋረጃዎቹንና ቀለማቱን፣ በአጠቃላይ የቤተ መቅደሱን ንዋያተ ቅድሳት የመረጠው እግዚአብሔር ራሱ ነበር እንጂ ምድራውያን ሰዎች አልነበሩም። ያቺ እግዚአብሔር ይገለጽባት የነበረችው ቤተ መቅደስ ዛሬ የለችም። በሙሴ የነበረው የመገናኛው ድንኳን እግዚአብሔር ራሱ ባዘዘው መሠረት የተሠራ ነው። (ዘጸ36:1) በሰሎሞን ዘመን ወደሕንጻ ቤተ መቅደስ ሲቀየር ለዳዊት ከወገቡ የሚወጣው ልጁ እንደሚሰራለት እግዚአብሔር ራሱ ተናግሮ ስለነበር እንጂ ሰሎሞን ከልቡ አንቅቶ የሰራው አልነበረም።
(2ኛ ዜና 6:9)
ይህ ሰሎሞን ያሠራው ቤተ መቅደስ የፈረሰበትን ታሪክ መጽሐፍ ቅዱሳችን ሲነግረን ሕዝቡ እንደአሳቡ፣ እንደፈቃዱና እንደትእዛዙ ባለመሄዱ የተነሳ የደረሰባቸውን መከራ እንዲህ ይተርክልናል። “ሴዴቅያስም በነገሠ በዘጠኝኛው ዓመት በአሥረኛው ወር ከወሩም በአሥረኛው ቀን የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆርና ሠራዊቱ ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም መጥተው ከበቡአት፤ በዙሪያዋም ዕርድ ሠሩባት።
(2ኛ ነገሥት ምዕራፍ 25ን ያንብቡ)
ቤተ መቅደሱ በናቡከደነጾር ፈርሶ፣ ንዋያተ ቅድሳቱ ተዘርፎ፣ ሕዝቦ ለባርነት ተግዞ ከተወሰደ በኋላ ኢየሩሳሌም ዳዋ ወርሷት ነበር።
“እናንተንም ከአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፥ ሰይፍንም አስመዝዝባችኋለሁ፤ ምድራችሁም የተፈታች ትሆናለች፥ ከተሞቻችሁም ባድማ ይሆናሉ።”
ዘሌ 26፥33 ያለው ቃል ተፈጽሟል።
ሁለተኛው ቤተ መቅደስ ተመልሶ የተሠራው በታላቁ ሄሮድስ ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሞቱ በተናገረበት አንቀጽ የ2ኛውንም ቤተ መቅደስ መፍረስ ሲተነብይ እንዲህ ብሎ ነበር። “ኢየሱስም መልሶ፦ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው።” ዮሐ 2፥19
አይሁዶችም ሲመልሱለት፣ "ወይቤልዎ ፡ አይሁድ ፡ በአርብዓ ፡ ወስድስቱ ፡ ዓመት ፡ ተሐንጸ ፡ ዝንቱ ፡ ቤተ ፡ መቅደስ ፡ ወአንተሰ ፡ በሠሉስ ፡ መዋዕል ፡ ታነሥኦ?"
ይህ ቤተ መቅደስ ለማነጽ 46 ዓመት ፈጀ፣ አንተ በሦስት ቀን መልሰህ ትሰራዋለህን? ብለው ጠይቀውታል። ዋናው መልእክቱ ለሰውነቱ ቤተ መቅደስ ቢሆንም ከሕንጻው ቤተ መቅደስም መፍረስ ትንቢት ነበር። ይህ በሄሮድስ የታነጸው ሁለተኛው ቤተ መቅደስ 46 ዓመት የፈጀ ሲሆን ሰሎሞን ካሰራው ቤተ መቅደስ የተለየ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ያዘዘው ቃል ሥርዓት የሚፈጸምበትና የሚከናወንበት ቤተ መቅደስ አልነበረም። ታቦቱ የለም። ታቦቱና ጽላቱ በሌለበት የእግዚአብሔር ክብር አይታይም ማለት ነው። የቤተመቅደሱ ሥርዓት የሌለበት፣ ታቦቱና ጽላቱ የማይገኝበት፣ እግዚአብሔርም በሁለቱ ኪሩብ መካከል በሚታየው የክብር ደመና መካከል ተገልጾ በአሮን የክህነት ማዕረግ ተሹመዋል የተባሉትንና በወቅቱ ሊቀካህናት የነበሩት ሐናንና ቀያፋን የሚያናግርበት ቤተ መቅደስ አልነበረም። የእግዚአብሔር ድምጽ የሚሰሙበት ቤተ መቅደስ ሆኖ ቢሆን ኖሮ ስለኢየሱስ ድምጽ ይመጣላቸው ነበር። ከዚያ ይልቅ በዚህ በሄሮድስ ቤተ መቅደስ አደባባይ የሕዝቡ የኃጢአት ሥርየትና የደኅንነት መስዋዕት ሳይሆን ይቀርብ የነበረው የገንዘብ ለዋጮችና የርግብ ሻጮች ገበታ ነበር። ገንዘብ ለዋጮቹ ለበዓል ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡትን ሰዎች ገንዘብ የሚመነዝሩ /money exchangers/ ሲሆኑ ርግብ ሻጮቹ ደግሞ ለበደል ሥርየት የሚሆኑ ርግቦችን ለሚመጡ ለእንግዶች የሚሸጡ የነጋዴዎች አደባባይ ሆኖ ነበር። ይህ ተግባር እግዚአብሔር አዝዞ በተሠራው በሰሎሞን ቤተ መቅደስ አደባባይ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ ከሕዝቡ ተለይቶ ይጥፋ የሚለውን ቅጣት ያስከትል ነበር። ኢየሱስም፣ በዚህ ድርጊታቸው በተበሳጭቶ “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል፥ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት አላቸው።”
(ማቴ 21፥13)
ይህ ቤተ መቅደስ እግዚአብሔር የማይከብርበት፣ ሥርዓተ መቅደሱ የማይፈጸምበት ስለነበረ መፍረስ ነበረበት። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ በተናገረው ቃል መሠረት ባረገ በዐርባኛው ዓመት፣ የሮማው ንጉሥ ጥጦስ በ70 ዓ/ ምህረት ገደማ ካፈረሰው በኋላ ላለፉት 2000 ዓመታት ቤተ መቅደስ የሚባል ታሪክ የለም። ከዚያ በኋላም እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስሩልኝ ያለው የተለየ ሕዝብና ሀገርም የለም። የቤተመቅደሱን ስፋትና ቁመት፣ የንዋያተ ቅድሳቱን ዝርዝርና ዓይነት የነገረው አንድም ሕዝብ ስለሌለ እግዚአብሔርን ለመገናኘት የምንሄድበት ቤተ መቅደስ በዓለም ላይ የትም ሀገር የለም። ልባቸው ያፈለቀውን፣ ኅሊናቸው ያሰበውን፣ ያላቸው የገንዘብ አቅም የፈቀደላቸውንና በሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ በተፈቀደ ዲዛይን በተሠራ ሕንጻ ውስጥ እግዚአብሔርን ይገባበት ዘንድ በወይራና በቅብዐ ሜሮን ግንቡን ረጭተው እግዚአብሔር ሆይ ቀድሰነዋልና ና ግባበት እያሉ ሲጣሩ ውለው ቢያድሩ በዚያ በሰዎች ሃሳብ ሕንጻ ውስጥ እግዚአብሔር የለም። እግዚአብሔር እንደዚያ አድርገው እንዲሰሩለት ያዘዘው ሕዝብና ሀገር ስለሌለ፣ ሰዎች በልባቸው መሻት በሰሩት ቤተ መቅደስ ውስጥ በተሽሞነሞነ ጥሪና ልመና የሚገባ አምላክ አለ ብለው የሚያስቡ ከሆነ ተሳስተዋል። የሚገባ ካለም ሌላ መንፈስ ይሆን ይሆናል እንጂ የሰማይ አምላክ አይደለም።
ሐዋርያት 17፣ 24—25
"ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤ እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም"።
አሁን ቤተ መቅደሱ አንተ ነህ። ይሄን አንተ ቤተ መቅደስ የሆነው ሰውነትህን አቆሽሸህ ስታበቃ ሕንጻውን ቀድሼዋለሁ ብትል ስህተትም፣ ክህደትም ነው። ለዚህም ነው፣ የቆሸሹ፣ ከኃጢአት ያልተመለሱ፣ ለመመለስም ፍላጎት የሌላቸው ዐመጸኞች ቤተ መቅደስ በሚሉት ሕንጻ ውስጥ ተሰግስገው መደበኛ ኑሮአቸውን የሚኖሩት። እግዚአብሔር እኔ ውስጥ የለም፣ እዚያ እኔ በሠራሁት ሕንጻ ውስጥ አምላኬ ስላለ ጥዋትና ማታ እየሄድኩ ኃጢአቴን ይቅር እንዲለኝ እነግረዋለሁ ብትል ሕንጻ ውስጥ ቁጭ ብሎ የአንተን ኃጢአት የሚሰማ የሰማይ አምላክ ስለሌለ መጀመሪያ ራስህን ቀድስ። ኢየሱስ ከኦሪቱ ቤተ መቅደስ አገልግሎት ይልቅ ወደበለጠው የአዲስ ኪዳን አገልግሎት የመጣው አንተን አማኙን ለመቀደስ እንጂ በድንጋይ የተሠራ ቤት ለመቀደስ አይደለም።
“ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።”
— ዮሐንስ 14፥23
እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ስለተባለ ቤተ መቅደሱ አንተ ራስህ ነህ። ቃሉን ጠብቅ፣ አብ ይወድሃል። ወልድም ይወድሃል። አንተም መኖሪያው ትሆናለህ። አንተ መኖሪያው ካልሆንክ የእግዚአብሔር መኖሪያ የሆነ ሌላ ሕንጻ የለም። ሕንጻው አንተ ነህ። ይሄንን ሕንጻ የሠራው ኢየሱስ ነው።
(በቀጣይ ፅሑፋችን "ሰው የእግዚአብሔር መኖሪያ ሕንጻ መሆን እንዴት ይችላል?") የሚለውን እንመለከታለን።
Wednesday, January 17, 2024
“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።” ሐዋ 4፥12
አዳም ከአምላኩ ትዕዛዝ በወጣ ጊዜ፣ ከሔዋን ጋር ከገነት ተባሮ አሜከላና እሾህ ወደምታበቅለው ምድር መጣሉን መጽሐፍ ቅዱሳችን ይነግረናል። ዘፍ 3:1—24
ይህ የአዳም በደል ከእሱ በተወለዱ ዘሮቹ በሙሉ በውርስ ሲተላለፍ ኖሯል። ከሰማይ ከወረደው ሁለተኛው አዳም/ ኢየሱስ/ በቀር ያለ ውርስ ኃጢአት የኖረ ማንም አልነበረም። የኢየሱስም ከሰማይ ወርዶ ሰው የመሆን ምስጢሩም የሚነሳው፣ የአዳም ዘር በሙሉ በሞት ፍርድ ሥር ያለ በመሆኑ ከሥጋ ለባሽ አንድም ሰው ዘሩን ነጻ ማድረግ ስለማይችል ነበር። ይህንንም ሐዋርያው ጳውሎስ አስረግጦ ሲያስረዳ ወደ ሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ እንደዚህ ብሎታል።
“ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤” ሮሜ 5፥12
ስለዚህም ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል "ወልድ" በሥጋ ሰብእ ከድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ከኃጢአት ብቻ በቀር አዳማዊ ባህርይን ተዋሕዶ ሰው ሆነ። አዳምንና ልጆቹን ከዘላለም ሞት ማዳን የሚችለው ከኃጢአት ነጻ መሆን የቻለ ብቻ ስለነበር ኢየሱስም የእግዚአብሔር በግ ሆኖ ለኃጢአተኞች ነጻ መውጣት የአብ መስዋእት ሆኖ ቀረበ።
“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።”ዮሐ 1፥29
ይህ የዓለምን ኃጢአትን የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ (ካልቪኒስቶች ለዓለሙ ሁሉ አልሞተም ይላሉ) መስቀል ላይ ውሎ የኃጢአት ሥርየት እርሱ መሆኑን አምነው፣ በስሙ ለተጠመቁና እስከመጨረሻው እምነታቸውን አጽንተው ለተጠበቁ በሙሉ እንጂ ለተወሰነ ዘር፣ ነገድ፣ ጎሣ፣ ብሔር ወይም ለተወሰነ ወገን የተፈፀመ ማዳን አልነበረም። ሐዋርያው ጳውሎስ ሞት ወደዓለም በአንዱ አዳም በኩል ለሁሉ እንደደረሰ ሕይወት ደግሞ በአንዱ በኢየሱስ በኩል ለተቀበሉት ሁሉ ሆነ በማለት ያስረዳናል።
“በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።”
ሮሜ 5፥17
እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ወደዓለም የላከውና ለመስቀል ሞት የታዘዘው የአዳም ዘር በሙሉ በእርሱ አምነው እንዲድኑበት እንጂ የተወሰነ ቡድን ወይም በምርጫ ለተለየ ወገን ለይቶ ለማዳን አይደለም።
በዚህ ዘመን ጆን ካልቪን የተባለ የ17ኛው ክ/ዘመን የተነሳ የአዲስ ሃይማኖት አስተማሪ ደቀመዛሙርት ነን የሚሉ በዚህ ዘመንም ኢትዮጵያ ውስጥ ሃይማኖታዊ ክሂዶትን አጠናክረው በመቀጠል ኢየሱስ የሞተልን ለእኛ ለተመረጥን፣ አስቀድሞ ለተለየንና ለተጠራን ብቻ እንጂ ለአዳም ልጆች ሁሉ ኃጢአት አይደለም እያሉ በታላቅ ድፍረት ሲናገሩ ይደመጣሉ። ብዙዎችንም እያሳቱ ይገኛሉ።
በመጥምቁ ዮሐንስ የተመሰከረልንና "የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ" ዮሐ 1:29 የሚለው ቃል በካልቪኒስቶች አስተምህሮ "ለኛ ለተመረጥነው እንጂ ለዓለሙ ሁሉ አይደለም" በሚለው መቀየር አለበት
እንደማለት ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ በአዳም አለመታዘዝ ሞት ለሁሉ እንደደረሰ፣ በአንዱ በኢየሱስ መታዘዝ ሕይወት ለሁሉ እንደበዛ እንዲህ በማለት ይነግረናል።
“በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።” ሮሜ 5፥19
ከእኛ ከኃጢአተኞቹ የሚጠበቀው እግዚአብሔር በልጁ ሞት እንዳዳነን፣ ሕይወትም እንደሰጠን ማመንና መቀበል ብቻ እንጂ ከእኛ በሆነ ሥራ አይደለም።
"ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም" ኤፌ 2:8—9
ነገር ግን ካልቪኒስቶች ሥራም፣ እምነትም፣ ማወቅም፣ መረዳትም፣ ማመንም ሳይጠበቅብን አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተመረጥነውና የተለየነው እኛ ብቻ /predestination/ የተሰጠን ስንድን ለሲኦል የተዘጋጁት ደግሞ ያልተመረጡና አስቀድሞ
የተፈረደባቸው ናቸው በማለት አምላካዊ ምህረቱን ለግላቸው በመውሰድ በሌሎች ላይ የፍርድ ቃል በድፍረት ሲናገሩ አይሰቀጥጣቸውም። ይህ አባባላቸው ኢየሱስ የተሰቀለው አስቀድሞ ለተመረጡና ለተወሰኑ ሰዎች እንጂ በእርሱ አምነው ለሚመጡ ለዓለሙ ሁሉ አይደለም ለማለት የሚረዳቸውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ ቦጭቀው ሲጠቀሙ ይህንን ይጠቅሳሉ።
“አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።”
ሮሜ 8፥30
ይሄንን ቃል ሲያብራሩ እኛ /ካልቪኒስቶቹ/ ራሳቸውን ማለታቸው ነው። አስቀድሞ እንድንድን የተወሰነልን ነን። ከእንግዲህ የትኛውንም ኃጢአት ብንሰራ አንጠፋም። አስቀድሞ በተሰወነልን መሠረት የጠራን አንዴ ልጆቹ አደረገን። አፅደቆም በሰማይ አከበረን ይላሉ።
ከዚህ ከእግዚአብሔር ቃል እውነት ፍፁም ተቃራኒ በሆነ ክህደት ውስጥ እንዲዘፈቁ ያደረጋቸው ሰይጣናዊ ትርጉም ሁለት መሰረታዊ ነገርን ከመሳት የመጣ ነው። እሱም፣
1/ የእግዚአብሔር ሁሉን አዋቂነት ወደሰውኛ እውቀት ማውረድና
2/ የእግዚአብሔርን ምሕረትና የይቅርታ ሚዛን አለመረዳት ናቸው።
እግዚአብሔር አምላክ የማያውቀውና የተሰወረበት ምን ምስጢር አለ? እግዚአብሔር ፍጥረትን ከፈጠረበትና ዓለማትን ከሚያሳልፍበት ሁሉን ቻይነቱ፣ የሉዓላዊነት ሥልጣን ውጪ የሆነና መሆን የሚቻለው አንዳችም ፍጥረት የለም። ይህም የእግዚአብሔር የሁሉን አዋቂነቱ /Omniscient/ እና የከሃሌ ኩሉነት /Omnipotent/ በራሱ አምላካዊ ባህርይው የሚገኝ ነው። ከዚህ ተነስተው እነዚህን ጥያቄዎች ብናነሳ የምናገኛቸው ትክክለኛ መልሶች ያሉት በእርሱ ዘንድ ብቻ ናቸው። የሰው ልጅ ከተፈጠረ ጀምሮ ስንት ሰው ተወልዷል፣ በፆታ ስንቱ ወንድ ስንቱስ ሴት ነው? ስንትስ ሰው ሞቷል፣ ስንት ሰውስ በሕይወት አለ? ስንቱ ገነት ገባ? ስንቱስ ሲዖል ወረደ? የሚሉትን ጥያቄዎች ብንጠይቅ ይህንን በትክክል የማወቅ ኃይሉ ያለው በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ነው። በዚህም እግዚአብሔርን ሁሉን አዋቂ አምላክ እንለዋለን።
“ፍጥረታችንን እርሱ ያውቃልና፤ አቤቱ፥ እኛ አፈር እንደ ሆንን አስብ።” መዝ 103፥14
“የጠለቀውንና የተሠወረውን ይገልጣል፤ በጨለማ ያለውን ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው።”ዳን 2፥22
የእግዚአብሔርን ሁሉን አዋቂነት ካልቪኒስቶቹ ራሳቸውን ከፀደቁት ጎራ ጨምረው እግዚአብሔር ዓለም ሳይፈጠር የፈረደባቸውንና በሰማይ ያፀደቃቸውን ስለሚያውቅ እኛን ከፀደቁት አድርጎ አስቀድሞ ወደፅድቁ ስለጨመረን ኩነኔ የሚባለው ነገር አይመለከተንም እያሉ በአስቀድሞ መወሰን/Predestination/ ውስጥ ራሳቸውን ያስቀምጣሉ።
እግዚአብሔር ሁሉንም አዋቂ ነው ማለት ጄምስን ኮንኜዋለሁ፣ ገብረማርያምን ደግሞ አፅድቄዋለሁ ብሎ አስቀድሞ ውሳኔ የሰጠበት ሰው የለም። እንደዚያ አስቀድሞ ከተወሰነ የኢየሱስ ሰው መሆን ለምን አስፈለገ? ለምንስ ተሰቀለ? እምነትስ ምን ሊጠቅመን? እምነትንስ በሥራ መግለፅ ምን ሊጨምር? አስቀድሞ ለፅድቅ የተወሰነ ሰው ስለኃጢአት የሚከፈል ዋጋስ ለምን አስፈለገው?ቢከፈልለትም ሆነ ባይከፈልለት አስቀድሞ የተወሰነለትን ከመቀበል የሚያግደው ነገር ምን አለ?የሚሉ ጥያቄዎችን ብናነሳ መሆን የሚገባቸው ትእይንቶች/ ትርኢቶች/ እንጂ በመሰረታዊ የሰው ልጆች የመዳን መንገድ ላይ ትርጉም የሌላቸው ሆኖ እንዲታዩ የሚያደርግ ነው። ውሳኔው ቀድሞ ስለተሰጠ መዳኑ አይቀርበትም። ቀራንዮ ላይ የተፈፀመው ስቅለት አስቀድሞ የተነገረለትን ለማሳየት የተደረገ ትርኢት ነው ማለት ነው።
ይህ የጆን ካልቪን ትምህርት አደገኛና የእግዚአብሔርን ፍፁም የሆነ ፍቅር በመሻር ሰው የሚፈረድበት በራሱ ምርጫ ሳይሆን ለሲዖል እሳት እንደማገዶ እንጨት አስቀድሞ አዘጋጅቶት የነበረውን ሰው ወደእሳት በመወርወር የሚደረግ ድምዳሜ እንጂ በማመኑ ወይም ባለማመኑ የሚደረግ ፍፃሜ አይደለም የሚል ክህደት ነው። ይህም እግዚአብሔር ሰው በምርጫው እንዲወስን ነባቢት፣ ለባዊትና ሕያዊት ነፍስ አልሰጠውም የሚል አምላክን እንደጨካኝ ገዢ የሚስል ሰይጣናዊ ትምህርት ነው። ዮሐንስ በራእዩ የጻፈልን ቃል፣
"ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ። እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።
አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ"ራእይ 22:11—13
የሚለው ቃል አስቀድሞ በተወሰነ ነገር ላይ ዝም ብሎ የተጻፈ እንጂ ፅድቅም፣ ርኩሰትም በማድረግ እንደሥራው የሚባል ክፍያ የለም እያሉን ነው ካልቪኒስቶቹ።
የጆን ካልቪን ክሂዶተ እምነትና አስቀድሞ የመወሰን /predestination/ ስህተቶች በ5 ነጥቦች የተመደቡ ናቸው።
1/ Total Depravity/ የሰው ልጅ ከውድቀት በኋላ በጭራሽ ጻድቅ መሆን አይችልም የሚል ነው።
ይህ የስህተት ትምህርት በአዳም ስህተት የተላለፈው ውድቀት የሰውን ልጅ ከነአካቴው የክፋት ሁሉ ባለቤት ነው ብሎ በሰው ጆሮ የሚያንቃጭል የሰይጣን ውንጀላ ሲሆን ሰው ሁሉ እኔን መስሏል የሚል ሰይጣናዊ ድምፀት ያለበት ክስ ነው። ከውድቀት በኋላ ለአዳም ልጆች ሁሉ የተላለፈውን ሞት የሚያስቀር የጽድቅ ሥራና ወደወጣበት ገነት የሚመልስ ማንነት በሥራው አያገኝም ማለት፣ ሰው በጎነት፣ ደግነት፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር መኖር፣ የጽድቅ ሥራ መፈፀም አይችልም ማለት
አይደለም። በመጽሐፍ ቅዱሳችን በዚህ ተግባር የተመሰከረላቸው ሰዎች ነበሩ። ለምሳሌ ሄኖክ፣ ኖኅ፣ አብርሃም፣ ሎጥ፣ ሳሙኤል፣ ኤልያስ፣ ኤልሳዕ፣ ዳንኤል፣ ሠለስቱ ደቂቅ ወዘተን መጥቀስ ይቻላል። ከዚህም የተነሳ የካልቪኒስቶች ስሁት ትምህርት በምድር ላይ የጽድቅ ስራን መሥራት በመቻልና በሥራ በመጽደቅ መካከል ያለውን ልዩነት አቅላቅለው እውነትን ደፍጥጠው ይክዳሉ።
2/ Unconditional Election /አስቀድሞ መመረጥ/ እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የሚድኑትን አስቀድሞ መርጧቸዋል።
ሲመርጣቸውም ምንም ዓይነት መስፈርትና መለኪያ አላደረገም። በቃ! ጻድቅ እንዲሆኑ ተፈጠሩ የሚል ነው። ኃጢአት፣ ሥርየት፣ እምነት፣ የሚባል ነገር ለፎርማሊቲ እንጂ ከተመረጡበት አያስቀራቸውም፣ አይጨምርላቸውም። የትኛውም ኃጢአት ከምርጫው አያስቀራቸውም የሚል ሲሆን እግዚአብሔር ለሲዖል መርጦ ያስቀራቸው አሉ በማለት ፍፁም ፍቅር የሆነውን የእግዚአብሔር ፍቅር ከሰው ልብ አውጥቶ የሚጥል ሰይጣናዊ ትምህርት ነው። ሲጀመር ሲዖል ለሰይጣንና ለመላእክቱ እንጂ ለሰው ልጅ አልተፈጠረም። ማቴ 25:41
3/ Limited Atonement የኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ላይ ሞት የተከናወነው ለእኛ አስቀድሞ ለተመረጥነው ብቻ ነው የሚል አስተምህሮ ነው።
ለዚህም እንዲረዳቸው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ። “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”ዮሐ 10፥11 ኢየሱስ ነፍሱን የሰጠው ለእኛ ለተመረጥነው በጎቹ ብቻ ነው የሚል ነው።
ሲጀመር ካልቪኒስቶች በ/Limited Atonement/ /ለበጎቹ ብቻ/ በሚለው አስተምህሮአቸው ውስጥ ሁለት ነገር ይስታሉ። አንደኛው በማይቀየር ማዳኑ ውስጥ አስቀድሞ በጎቹ ከተመረጡ ኢየሱስ ለምን መሰቀል አስፈለገው? ዝም ብሎ እነሱን እየለየ ወደገነት ማስገባት ተገቢ በሆነ ነበር። ሲቀጥል ካልቪኒስቶች የስህተት ትምህርታቸውን ተርጉመው የኢየሱስ በጎች እኛ ነን ያሉት ራሳቸው እንጂ ካልቪኒስቶች ብቻ የተመረጡ ናቸው የሚል ማረጋገጫ በመጽሐፍም፣ በመላእክትም የተመሰከረ አይደለም። ደግሞ የተነገረን እውነት የተለየ ወንጌል የሰበከ የተረገመ ይሁን የሚል ነው። ገላ 1:8
እኛ ግን እንዲህ ብለን እናምናለን።
“በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤” ገላ 3፥26 በኢየሱስ
አዳኝነት ያመነ፣ የተጠመቀና እምነቱን በሥራ የገለፀ አማኝ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ሆኗል ብለን እንናገራለን እንጂ ኢየሱስ የዓለም መድኃኒት የተባለበትን ሞትና ትንሣኤውን የካልቪኒስቶች ብቻ መድኃኒት ብለን ስለሁሉ የሞተበትን ምስጢር አንክድም።
4/ Irresistible Grace/ የካልቪኒስቶች ሌላው ስሁት አስተምሮአቸው አስቀድሞ በፀጋው የተጠሩት መቼም እንዳይጠፉ ሆነው የሚል ነው።
ለዚህም ደጋፊ እንዲሆናቸው ዮሐንስ በወንጌሉ የጻፈውን የራሳቸው ብቸኛ ማረጋገጫቸው አድርገው ያቀርባሉ።
“አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም”
ዮሐ 6፥37
የሚገርመው ነገር በ30 ጠገራ ብር ኢየሱስን የሸጠው ይሁዳ ከተጠሩት ሐዋርያት መካከል አልነበረም ወይ? ሲባሉ ከሐዋርያነት የተደመረው ሽያጩን እስኪፈፅም እንጂ በዘላለማዊ ጥሪ ውስጥ አልነበረም ይላሉ። ለያህዌ ስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ካልቪኒስቶች እግዚአብሔር በሰው ሕይወት ላይ ቁማር ይጫወታል፣ ያለምርጫህ ብትጠፋም ላንተ መጥፋት ግድ አይሰጠውም ወደሚል የአምላክን ባህርያዊ ፍቅር
ወደማስካድ ይወርዳሉ። እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ስለሆነ የሚጠፉትንና የሚድኑትን ያውቃል ማለት የሚጠፉትና የሚድኑት እግዚአብሔር አስቀድሞ ስለወሰነባቸው ሳይሆን ሰዎች በሚያደርጉት የራሳቸው ውሳኔ የተነሳ መሆኑን አይቀበሉም። አዳም ከገነት ከመባረሩ በፊት ፍጻሜውን እግዚአብሔር ያውቅ ነበር ማለት አትብላ ያለውን እፀ በለስ በግድ እንዲበላ ስለወሰነበት ነበር ብሎ ማቅረብ አደገኛ ክህደት ነው። ይህም የሰው ልጅ በራሱ ማሰብና መወሰን የማይችልና አስቀድሞ በተገጠመለት የውሳኔ ሶፍትዌር የሚንቀሳቀስ ቁስ ነው እንደማለት ነው። የተወሰነብህን ትኖራለህ እንጂ በእውቀትም፣ በእምነትም የምትጨምረውና የምትቀንሰው ነገር የለም ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱሳችን የሚነግረን አንዴ በተሰጠ ምርጫ የለሽ ውሳኔ ሳይሆን የምናምነው አምላክ አውቀን በዚሁ በእምነታችን ፀንተን ስንቆይ እንደሆነ በግልፅ ይነግረናል።
“የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤”
ዕብ 3፥14
እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ከወጡ በኋላ ወተትና ማር ወደምታፈሰው ምድር ሳይገቡ በምድረ በዳ የቀሩት
እግዚአብሔር በረሃ በልቷቸው እንዲቀሩ አስቀድሞ በወሰነባቸው ውሳኔ ሳይሆን ድንቅና ተአምራትን አድርጎ ከሰማይ መና፣ ቀን በደመና፣ ሌሊት በብርሃን ዓምድ እየመራቸው በነበረው አምላካቸው ላይ በማመፃቸው ነበር።
" ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን? አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን? ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ? ባለማመናቸውም ጠንቅ ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን" ዕብ3: 15—19
5/ PERSEVERANCE OF THE SAINTS ይህ ማለት አንዴ ከዳንክ ለዘላለም ድነሃል። በየትኛውም ኃጢአት ወይም በዓመጻ የሚጎድልህ ማንነት አይኖርህም ማለት ነው።
Once saved, always saved ይሉሃል። በካልቪኒስቶቹ ዘንድ በዕብራውያን 10:36 ላይ የተመለከተው በእምነት ፀንቶ፣ ፈቃዱን እያደረጉ መኖር ነገር እርባና የለውም።
“የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና።”
ዕብ 10፥36
አንዴ የዳነ፣ ለዘላለም የማይጠፋ ስለሆነ በካልቪኒስቶች ዘንድ የሐዋርያው ጴጥሮስ ምክር ምንም አያስቀርበትም።
“ስለዚህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ ይህን እየጠበቃችሁ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆናችሁ በሰላም በእርሱ እንድትገኙ ትጉ፥” 2ኛ ጴጥ 3፥14
የእግዚአብሔር ፈቃድ ብታደርግም፣ባታደርግም አንዴ ድነሃልና አትጠፋም፣ አትጨነቅ። ዮሐንስ በመልእክቱ የፃፈው ካልቪኒስቶችን አይመለከትም።
ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው የሚለው ቃል ቢኖርም አንዴ ስለዳንክ ችግር የለውም ይሉሃል።
“ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና።”1ኛ ዮሐ 3፥8
አንዴ ስለዳንክ በኃጢአት የተነሳ ከዲያብሎስ ብትሆንም አትጨነቅ፣ አትጠፋም እያሉ ለድፍረት ኃጢአት ያበረታቱሃል። ኃጢአት መስራት፣ አለመስራትህ የሚቀንስብህ ወይም የሚጨምርልህ ነገር የለም ይሉሃል።
“ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።”1ኛ ዮሐ 2፥17 ፈቃዱን ብታደርግ ጥሩ ነው። ሳትፈፅመው ብትቀርም ችግር አያስከትልብህም፣ አትጨናነቅ፣ አንተ ለዘላለም የተመረጥህ ነህና። ዮሐንስ በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዓላማ ውስጥ ለመኖር ፈቃዱን መፈፀም ተገቢ ነው ያለው የራሱ ግምት በመሆኑ ካልቪን ያሻሻለውንና አንዴ የዳነ፣ ለዘላለም ዳነ የሚለውን ትምህርት ተከተል ይሉሃል ከሃዲዎቹ!
ማጠቃለያ፣
ካልቪኒስቶቹ የሳቱት እውነት፣ የምሥራቹ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስ ቃል እንጂ የጆን ካልቪን ትርጉም፣ አባባል፣ አገላለፅ ወይም የአስተምህሮ አቋም አለመሆኑን አለማወቃቸው ነው። ካልቪን በአንድ ወቅት የተለየ የወንጌል አስተምህሮ ተገልጾልኛል ብሎ የራሱን ትርጉም ይዞ የመጣ ሰው እንጂ የምሥራቹ ቃል ምንጭ ስላልሆነ ካልቪኒስት ነኝ ብሎ እሱን መከተል አደገኛ ስህተት ነው። ማንም አማኝ የወንጌልን ትምህርት በብዙ መንገድ፣ ከብዙ ሰዎች ሊሰማ ወይም ሊያገኝ ይችላል።
ያ ማለት ግን የወንጌል እውነት እሱ ከሰማበት ቦታ ብቻ ይገኛል ማለት አይደለም። የየትኛውም ትምህርት ማረጋገጫና መመዘኛ መንፈስ ቅዱስና የምሥራቹ ቃል እውነት መሆኑን አለማወቃቸው ነው። ሉተር፣ ካልቪን፣ ዝዊንግሊ፣ ኤራስመስ፣ ኖክ፣ ዊክሊፍ፣ ኸስ፣ ሜላንክቶን ወይም ቲንዳል የእውነት ቃል ምንጭ ወይም የመጨረሻው የእውነት ማረጋገጫ ሊሆኑ እንደማይችሉ አለመረዳታቸው ነው። ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ይልቅ ግለሰቦቹ በሰጡት ትንታኔ ላይ በመመስረት ለማመን መሞከራቸው ነው ካልቪኒስት ሆነው ለመኖር የወሰኑት። እኛ ግን የተሰቀለልንና ከሞት ያዳነን የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይና ደቀመዛሙርት እንጂ የአጵሎስ ወይም የጳውሎስ አይደለንም። ከሰማይ በታች እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ስም ማነው? ከሰማይ በታች ሊድኑበት ለወደዱና ወደእርሱ ለመጡ በሙሉ የሚያድነው ስም ኢየሱስ ብቻ ነው። ከሰማይ በታች የተሰጠ የካልቪን አስተምህሮ፣ ለካልቪኒስቶች ሊኖር ይችላል። እኛን ክርስቶሳውያንን አይመለከትም። የካልቪን የሚባል አስተምህሮም፣ መምህርም የለንም።
Saturday, January 13, 2024
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዋና ችግር ጳጳሳት ናቸው!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዋና ችግር ራሳቸው ጳጳሳቱ ናቸው። ምክንያቶቹ፣
1/ አንድ ወጥ የሆነ የቀደምት አበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ የለውም። ተረት፣ ተረት፣ እንቆቅልሽና እንቶ ፈንቶውን ስህተት አርሞ በትክክለኛው የወንጌል ጎዳና ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ እንድትሄድ ማድረግ አልቻለም።
ዳንኤል 5፣ 24—28
ስለዚህም እነዚህ የእጅ ጣቶች ከእርሱ ዘንድ ተልከዋል፤ ይህም ጽሕፈት ተጽፎአል። የተጻፈውም ጽሕፈት፦ ማኔ ቴቄል ፋሬስ ይላል።
የነገሩም ፍቺ ይህ ነው፤ ማኔ ማለት፥ እግዚአብሔር መንግሥትህን ቈጠረው ፈጸመውም ማለት ነው። ፋሬስ ማለት፥ መንግሥትህ ተከፈለ፥ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎችም ተሰጠ ማለት ነው።
ከዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል አንፃር ቤተክርስቲያኒቱ መፈረካከሷ ገና ይቀጥላል።
2/የጳጳሳቱ ጉባዔ በቤተ ክርስቲያኒቱ ትልቁ የሥልጣን ማዕከል ነው። ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን በመንፈሳዊ ምሳሌነት፣ በእውቀት፣ በዘመናዊ አስተዳደርና መዋቅር መምራት አልቻለም። በዚህም የተነሳ ዘረኝነት፣ ሌብነት፣ ዘረፋ፣ ጉቦ፣ የፍትህ መጓደል፣ ጥንቆላና አስማተኝነት ከጳጳሳቱ ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ የዕለት ከዕለት ተግባር ነው። ከዚህ የተነሳ የሚከናወነው አምልኮተ እግዚአብሔር ከምእመናኑ የሚገኘውን ገንዘብ ለመሰብሰብና ጥቅም ማስገኛ ምንጭ ከማድረግ ባለፈ እግዚአብሔርን ከመፍራትና ለቃሉ ለመገዛት ካለ መንፈሳዊ ብቃት የተነሳ አይደለም።
3/ ቤተ ክርስቲያኒቱ የታሪክ፣ የቅርስ፣ የሥነ ፅሑፍ፣ የሰነድ ባለቤት ሆና ሳለ ይህንን ሁሉ አራግፋ በመጣል የገዢዎች ባለሟል፣ ትዕዛዝ ፈጻሚ እና የመከራ ጽዋ የምትጎነጭ እርስ በእርሷ የምትባላ ሆና እያየናት ነው።
ሲጠቃለል፣ ቤተክርስቲያኒቱ ጥቋቁር ጨርቅ በተሸፋፈኑ ጳጳሳት ከመፍረስ አትድንም። ወደቀደመ ክብሯ አትመለስም። ከተረት፣ ተረት እና ከፈጠራ የስህተት አስተምህሮ ወጥታ ወደእውነተኛ የወንጌል መንገድ ልትገባ አትችልም። ቢመርም እውነቱ እሱ ነው።
Tuesday, June 28, 2022
Wednesday, May 4, 2022
Monday, May 2, 2022
Saturday, April 16, 2022
ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር ማቴ ፳፩፣፱
«ሆሳዕና» ቃሉ ከሁለት አረማይክ ቃላት የተሰራ ሲሆን ትርጉም «እባክህ እርዳ፣ አሁን አድን» ማለት ነው። እብራይስጡም ይህንኑ ቃል ወርሶ «הושענא » ሆሻአና ሲል ይገኛል። አዎ «አሁን አድን፣ እባክህ እርዳን» ብሎ የአዳም ዘር ያጣውን ልጅነትና የደረሰበትን ሞት ለመላቀቅ የሚያሰማው የጩኸት ድምጽ ነው፣ «ሆሳዕና»!!!
ዳዊት ነቢይ በመንፈስ ቅዱስ ተመልክቶ ማዳኑን ሲጣራና አሁን ናልን ሲል ከዘመናት በፊት አድምጠነዋል። የውስጥ ዓይኖቹ ሩቅ አይተዋል። ማዳኑንም ሽተው እንዲህ ሲል ዘምሮለታል።
«አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና» መዝ ፻፲፰፣፳፭
ያ ማለት ደግሞ « אָנָּ֣א יְ֭הוָה הֹושִׁ֘יעָ֥ה נָּ֑א אָֽנָּ֥א יְ֝הוָ֗ה הַצְלִ֘יחָ֥ה נָּֽא » አና ያኽዌ ሆሳአና አና ያኽዌ ሆስሊኻ ና» የሚለው የእብራይስጡ ቃል ነው።
አበው የማዳኑን ነገር አስቀድመው አይተው በተስፋ «ሆሳዕና» እያሉ ዘምረዋል። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ በክርስቶስ ኢየሱስ እስኪገለጥ ዘወትር በእንባና በዝማሬ ወደ ተስፋው ፍጻሜ ድምጻቸውን ያሰሙ ነበር።
አዎ ንጉሥ ክርስቶስ ከዘጠና ዘጠኙ በጎች መካከል የጠፋውን አንዱን በግ ፍለጋ ንጉሥ ሆኖ ሳለ እንደንጉሥ ያይደለ በአህያ፣ ለዚያውም በውርንጫ ተቀምጦ «የአሁን አድን (ሆሳዕና)» ጩኸት ሊመልስ በጽዮን ከተማ ይመጣል፤ ይህንንም ዘካርያስ ከዘመረው ዘመናት ተቆጥረው ነበር።
«አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል» ዘካ ፱፣፱
ምንኛ ይደንቅ? ምንኛስ ይረቅ? ንጉሥ ስለመምጣቱ አስቀድመው የተናገሩለትና ከዘመናት በፊት ማዳኑን አይተው በእልልታ የዘመሩለት!!
ሰማያዊ ንጉሥ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለዘርዓ ብእሲ ከስጋችን ተዛምዶ ማዳኑን ሲጠብቁ፤ ከሩቅ አይተው ሲጣሩ፣ ሲዘምሩለትና አንድ ቀን ማዳኑ እንደሚሆን ተስፋ ሲያደርጉት የነበረው ሰዓቱ ደርሶ በመካከላቸው ሲገኝ ይጠብቁት የነበረው ዓይነት ሳይሆን ውበት የሌለውን ንጉሥ ለመቀበል የገዛ ወገኖቹ ተቸግረው ነበር።
አዎ የደም ግባት ብቻ ሳይሆን የንጉሥ ወግ የሌለው፣ በአህያ ለዚያውም በውርንጫ የሚመጣ ንጉሥ እንዴት ይቀበሉት?
«በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም» ኢሳ ፶፫፣፪
አባቶቻቸው ለዘመናት «ሆሳዕና፣ ማዳንህ አሁን ይሁን» ያሉለትና የዘመሩለት በዕለተ ቀጠሮው ማዳኑን ሊያሳይ ከጽዮን ደጃፍ ቀርቦ ሳለ የማያውቁት፣ ያልሰሙት፣ ትንቢቱን ያላነበቡት «ሆሳዕና» ሲሉ ትልልቆቹ ዕብራውያን ግን ዝም አሉ፣ ዝም በሉም አሉ!
«ነገር ግን የካህናት አለቆችና ጻፎች ያደረገውን ድንቃ ድንቅ በመቅደስም፣ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ እያሉ የሚጮኹትን ልጆች ባዩ ጊዜ፥ ተቈጥተው፣ እነዚህ የሚሉትን አትሰማምን? አሉት»
የማዳኑ ጌታም፣
«እሰማለሁ፤ ከሕፃናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ የሚለውን ቃል ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው» ማቴ ፳፩፣ ፲፭-፲፮
ኢየሱስ ክርስቶስ የእነዚህን ሕፃናት ዝማሬና ምስጋናን የሰማው ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም ማዳኑን ሊፈጽም በመጣ ጊዜ ነበር። ቤተ ፋጌ ከኢየሩሳሌም ከተማ ምሥራቃዊ አቅጣጫ በቢታንያና በደብረ ዘይት ተራራ መካከል የምትገኝ መንደር ነበረች። ቤተ ፋጌ ማለት በአረማይክ «ያልበሰለ በለስ ቤት» ማለት ነው። ርቀቱም ከኢየሩሳሌም የሰንበት ያህል ምዕራፍ ነበር።
ጌታ ኢየሱስም ከኢያሪኰ ከተማ ወደኢየሩሳሌም ሲወጣ ካረፈባት ከቤተ ፋጌ መንደር ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ልኰ ውርንጫይቱን ከታሰረችበት ፈትተው እንዲያመጡለት አዟል።
«ወደ ኢየሩሳሌምም ቀርበው ወደ ደብረ ዘይት ወደ ቤተ ፋጌ ሲደርሱ፥ ያንጊዜ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ላከ፥እንዲህም አላቸው፦ በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርስዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ» ማቴ ፳፩፤፪
ያን ጊዜም በቀደምት አበው የተነገረው ትንቢትና ዝማሬ ፍጻሜ አገኘ ማለት ነው።
«የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም። ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር» ማቴ ፳፩፣፱
ይሁን እንጂ ኢየሩሳሌም ለሆሳዕና አልተዘጋጀችም ነበር። ይልቁንም ቤተ መቅደሱ አካባቢ ስለማዳኑ ዝማሬ በማቅረብ ፋንታ የጦፈ የንግድ ገበያ ደርቶበት ነበር። ቤተመቅደሱ የጸሎት ሥፍራ መሆኑ ቀርቶ የሻጮችና የለዋጮች መድረክ ሆኖ ነበር። ያኔ ማዳኑ የቀረበላት ኢየሩሳሌም በመቅደሱ በራፍ ስትሸጥ፣ ስትለውጥ መድኃኒቱን ሆሳዕና እያለች መቀበልን እንዳልቻለች ሁሉ የዛሬዋ ቤተክርስቲያንስ ንግድና ሸቀጥ የሌለበትን «ሆሳዕና» እያከበረች ነው ወይ? ብለን ብንጠይቅ ራስን ማታለል ካልተጨመረበት በስተቀር፣ መሸጥ መሸቀጡ የሌለበትን «ሆሳዕና» የሚያከብር የለም ነው መልሱ። ዐውደ ምሕረቱ ሱቅ በደረቴ ያልሆነበትን ሥፍራ ማግኘት ከባድ ነው።
ኢየሱስ ማዳኑን ከመፈጸሙ በፊት እነዚህን ነጋዴዎች አስወግዷል። ገበታቸውን ገልብጧል። እየገረፈ አስወጥቷል። የወንበዴዎች ዋሻ የሆነውን የጸሎት ቤት ጠራርጓል። ዛሬስ ቤቱ ስንት ወንበዴ መሽጎበት ይሆን? ወንበዴዎቹ ይዘምራሉ፣ ሆሳዕና ይላሉ፣ የዘንባባ ዝንጣፊ ይይዛሉ፣ በጣታቸው፣ በግንባራቸው ያስራሉ። ወንበዴዎች ናቸው ተብለው እንዳይርቋቸው የአምልኰ መልክ አላቸው። ቤተመቅደሱን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁ ያለው በግብር ውንብድና በመልክ ግን አገልጋይ ይመስሉ የነበሩትን የመቅደሱን ሰዎች ነበር። ዛሬም እንደዚያው!!
በሌላኛው ቀንም በዚያው በመቅደሱ ሲያስተምር ዋለ። የወይኑ ጌታ ስለወይኑ ደኅንነት የላካቸውን አገልጋይ ሠራተኞች ታሪክ አወጋቸው። የሕይወት ለውጥ ለወይኑ ባይሆንለት ይፈሩት እንደሆነ አንድ ልጁን ቢልክም ገበሬዎቹ ወራሹ ይህ ነው እንግደለው ብለው መከሩበት፣ መክረውም አልቀረም፣ ከወይኑ አውጥተው ገደሉት። ስለዚህ የወይኑ ጌታ ገዳዮቹን ምን የሚያደርግ ይመስላችኋል? ሲል ይጠይቃቸዋል። እነሱም መልስ መለሱ። መልሱ ግን በራሳቸው ላይ የሚሆን የምስክርነት ፍርድ ነበር። «ፍታሕ በርእስከ» ማለት ይህ ነው። እነሱም እንዲህ ሲሉ በራሳቸው ፈርደው ተናገሩ።
«እርሱም፦ ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፥ የወይኑንም አትክልት ፍሬውን በየጊዜው ለሚያስረክቡ ለሌሎች ገበሬዎች ይሰጠዋል አሉት» ማቴ ፳፩፤፵፩
የአይሁድ ፋሲካ ከመሆኑ ሶስት ቀን ቀደም ብሎ ደብረ ዘይት ተራራ ላይ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ይነጋገር ነበር። ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይወድቅ የማይቀረው ለምድነው አሉት?
ስለረገማት በለስና ስለኢየሩሳሌም ጥፋት ተናገረ። ኋላም በሮማዊው ጥጦስ ትንቢቱ ተፈጸመ። ፍሬ አልባዋ በለስ እስራኤል ጠፋች።
ጴጥሮስ ደብረ ዘይት ላይ ሌላ ጥያቄ አነሳ።
«እርሱም፦ መምህር ሆይ፥ እንግዲህ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ይሆን ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ጠየቁት» የቅርቡን ጊዜና መጨረሻውን ዘመን ምልክቶች ነገራቸው። የቅርቡ ጊዜ የኢየሩሳሌም መከበብ የበለስ መድረቋ ጊዜ መሆኑን እንዲህ አለ። «ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ» ሉቃ ፳፩፤፳ በዚህ የኢየሩሳሌም የመጥፊያ የፍርድ ቀን መድረሱን አሳይቷል።
እንደገናም የኋለኛውንም ዘመን ትንቢት ደግሞ ይህች የተረገመች በለስ ስታቆጠቁጥ በጋ እንደ ደረሰ ታውቃላችሁ፤ ያኔ ደግሞ የመጨረሻው የፍርድ ቀን እንደደረሰ ምልክት ይሆናል አላቸው።
«ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል፦ በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፣ ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ።እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ» ሉቃ ፳፩፤፳፱-፴፩
አዎ ! የመጨረሻው ዘመን ዋናው ምልክት ፍሬ አልባዋና የደረቀችው በለስ ማቆጥቆጥ መጀመሯ ነበር። ያኔ የአጨዳው መከር ስለመድረሱ ጫፏ ሲለሰልስና ማቆጥቆጥ ሲጀምር በጋ እንደደረሰ እወቁ« ተብሏል። እናም የምንዘምረው ዝማሬ ትልቅ ትርጉም አለው። ማዳኑን አይተናል። «ሆሳዕና በአርያም » እያሉ መዘመር ብቻውን ግን ዋጋ የለውም። ኢየሩሳሌም ተዘምሮባት ነበር። ግን ፍሬ የሌለባት በለስ በመሆኗ ደረቀች። በሚያምር ውብ ድንጋይ ፵፮ ዘመን የታነጸውን መቅደስ ማዳን አልቻለም። ተራሮችን ውደቁብን እስኪሉ ድረስ የወረደውን መከራ መሸሸግ የቻለ ዝማሬ አልተገኘም። መቅደሱ በወንበዴዎች ተሞልቶ ነበር። ወንበዴዎቹ ልጁን አልተቀበሉትም። የተቀበሉትም ፍሬ አላፈሩም። ስለዚህ በጭፍራ ተከበው ለሺህ ዘመናት ጠፉ። ዛሬ በኛ የሚሆን ፍሬ አልባነት ጥፋቱ ለሺህ ዘመን አይደለም። ለአልቦ ማኅለቅት እንጂ!!
በእድሜአችን ስንት «ሆሳዕና በአርያም» አሳለፍን? ማዳኑ በተደረገለት ማንነታችን ውስጥ ስንት ፍሬ አፈራን? የተራበው ኢየሱስ ከእኛ የሚፈልገውን ፍሬ ይዘናል? ወይስ ፍሬ አልባ ሆነን ለቁጣ የተዘጋጀን እንሆን? «ሆሳዕና በአርያም» ማለቱ ብቻውን አያድንም፣ ማዳኑንም አያመጣም። የወንበዴ ዋሻ ማንነታችንን እናጽዳ። ከዚህ ዓለም ሽቃጭና ልዋጭ ማስመሰያ ማንነት እንውጣ! በጎ ፍሬ እንዲያፈራ ለተላከው የወይኑ ባለቤት ወራሽ እንገዛ! ያኔ «ሆሳዕና በአርያም» ስንል ማዳኑ ፈጥኖ ይሆንልናል። ከኢየሱስ በቀር ማዳን የሚቻለውና ተስፋ የሚሆነን ማነው? ከሥጋ ለባሽ ማንም የለም። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በሰው የሚታመን፣ በሥጋ ለባሽ የሚመካ፣ ልቡንም ከእግዚአብሔር የሚያርቅ የተረገመ ነው።
አዎ ሆሳዕና በአርያም! በዚህም አንተ ብቻ መታመኛ ነህ፣ በወዲያኛውም አንተ ብቻ! ሆሳዕና በአርያም።
ሃሌ ሉያ!!!!!!!!
Friday, April 8, 2022
ቻት ላይ ነን አትረብሹን!
ዮሐንስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
¹² እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።
¹³ ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል።
Sunday, August 22, 2021
በድንግል ማርያም የትንሣኤና የእርገት ታሪክ ላይ ችግር አለ!
ቅዱሳንን ስለማክበር ምንም ጥያቄ የለንም። ለቅዱሳንም መታሰቢያ ማድረግ የነገሮች ሁሉ ባለቤት የሆነው ኢየሱስን እስካልተካ ድረስ ችግር የለውም። ለክርስትና አስተምህሮና ለተጋድሎ ጽናት አርአያ ይሆኑናልና ታሪካቸውን እንናገራለን። ነገር ግን በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ወቅት በወንጌል ላይ ብዙ ጥያቄዎችን የሚያስነሱትና የስህተት ችካሎች አልነቀል ያሉት በመታሰቢያና በአክብሮት ምክንያት ስር ተወሽቀው ኢየሱስን እየጋረዱ ስላስቸገሩ ነው። ከነዚህ የስህተት አስተምህሮዎች መካከል አንዱ የሆነው በማርያም እረፍት፤ ቀብር፤ ትንሣኤና እርገት ላይ ያሉ አስተምህሮዎች ሰዎች ዓይናቸውን ከኢየሱስ ላይ አንስተው ወደሌላ የመዳን መንገድ እንዲመለከቱ ያደረገው ተጠቃሽ ነው።
ስለማርያም እረፍት፤ትንሣዔና እርገት አብያተ ክርስቲያናት አንድ ዓይነት የእምነት አቋም የላቸውም። እንዲያውም ስለማርያም ሞትና የእርገት ዕለት በግልጽ የሚታወቅ ማስረጃ እንደሌለ በ5ኛው ክ/ዘመን የኖረው የሳላሚሱ ኤጴፋንዮስ ተናግሯል። ዕረፍቷና እርገቷ በኢየሩሳሌም እንደሆነ የሚናገሩ ቢኖሩም ይህንን አባባል የማይቀበሉ አብያተ ክርስቲያናትና የቴኦሎጂ ምሁራን ሞልተዋል። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚለውን አባባል የማይቀበሉበትን ማስረጃ ሲያቀርቡም ዮሐንስ በወንጌሉ ላይ እንደተናገረው «እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት» ዮሐ19፤27 ባለው መሠረት ማርያም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ድረስ ከዮሐንስ ጋር ስለኖረችና ወንጌላዊው ዮሐንስም ከጌታ ሞት በኋላ በኢየሩሳሌም ጥቂት ዓመታትን ከቆየ በኋላ በ37 ዓ/ም ገደማ ወደ ቤዛንታይን ከተማ ኤፌሶን ሄዶ ወገኖቹን ወንጌል እያስተማረ መቆየቱንና ማርያም በሞት እስከተለየችው ድረስ ከ48-52 ዓ/ም እዚያው እንደነበር ብዙ ተጽፏል።
በኋላም በቅርብ ርቀት ባለችው ደሴተ ፍጥሞም በግዞት መኖሩንና በመጽሐፍ ቅዱሳችን የተጻፈውን ራእይ የተመለከተውም እዚያ እንደሆነ ይታወቃል ። አንዳንዶች ከዶሚኒሽን አገዛዝ ቀደም ብሎ የራእይ መጽሐፉን ከ55-65 ዓም ገደማ እንደጻፈም በታሪክ አስቀምጠዋል።
ዋናው ነገር ማርያም በኤፌሶን ከዮሐንስ ጋር ኖራለች ወይስ አልኖረችም? ነው ጥያቄው። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚሉ ሰዎች አንድም ጊዜ ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን ኖራለች ሲሉ አይደመጥም። ለምን? ዮሐንስ ማርያምን እንደእናት ሊይዛት አደራ ተሰጥቶታል የሚባል ከሆነ ከዮሐንስ ጋር ኤፌሶን ስለመቀመጧ የማይነገረው ለምንድነው? ዮሐንስ እስከ 96 ዓመቱ ድረስ ከኤፌሶንና ከደሴተ ፍጥሞ ውጪ ስለመኖሩ የተነገረ ታሪክ የለም። ማርያም ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን አልኖረችም ብሎ በመከራከርና በኢየሩሳሌም ኖራ፤ እዚያው ማረፏን በግልጽ በመናገር መካከል ትልቅ ልዩነት አለ። «እነኋት እናትህ» ባለው መሰረት አብረው ኤፌሶን ኖረው እዚያው ማረፏን በሚያምኑና ኢየሩሳሌም ኖራ እዚያው አርፋለች በሚሉት ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት የማይታረቅ ነው።
ሮበርት ክሬው የተባለ የነገረ መለኮትና የታሪክ ጸሐፊ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዘመኑን ሁሉ በኖረበት ከኤፌሶን ከተማ 8 ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ ባለች ኰረብታ ላይ በተሰራ ቤት ውስጥ እንደኖረና ማርያምም እዚያ ማረፏን ጽፏል። ይህንን በኤፌሶን ያለውን የማርያምን መቃብር የዓለም ክርስቲያኖች እንዲሆም ሙስሊሞች ሳይቀሩ ይጎበኙታል፤ ይሳለሙታል። በቱርክ ግዛት ያለው ይህ ስፍራ በቱርካውያን ሙስሊሞች ዘንድ «ሜሪዬማና» ተብሎ ይጠራል።
ቅድስት ማርያም ከዚህ ዓለም የተለየችው መቼ ነው? ለሚለው ጥያቄ ጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት የምሥራቁና የምዕራቡ ጎራዎች የተለያየ አመለካከት አላቸው።
በተወለደች በ58 ዓመቷ ዐርፋለች የሚሉ አሉ። በ72 እና 63 እድሜዋም አርፋለች የሚሉ መረጃዎች አሉ። እንደ ግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ግን የሚታመነው በ64 ዓመት እድሜዋ ማረፏ ነው። ኖረችበት ተብሎ ከሚገመተውና አርፋለች ከሚባለው ቦታ ያለው ልዩነት እንዳለሆኖ በጥር ወር ከዚህ ዓለም ተለይታ በ40ኛው ቀን ማረጓን የሚናገሩ አሉ። ይህም ሞትና ትንሣኤዋን ከልጇ ጋር ለማመሳሰል የተደረገ ጥረት ነው። በነሐሴ ወር አርፋ ከተቀበረች በኋላ ትንሣዔዋን ሳያዩ መቃብሯ ባዶ ሆኖ ስላገኙት ሐዋርያት ሱባዔ ይዘው በሦስተኛው ቀን ተገለጸችላቸው የሚሉም አሉ። እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ደግሞ በጥር ሞታ፤ በነሐሴ ተቀበረች የሚል ትምህርት አለ። በጥር ወር አርፋ፤ በነሐሴ ተቀብራለች የሚሉ ሰዎች ሥጋዋ በገነት ዛፍ ስር ለስምንት ወራት መቀመጡንና በሱባዔ ጸሎት በተደረገው ልመና የተነሳ ሥጋዋ ከሰማይ ወርዶ ለመቀበር መቻሏን አስፋፍተው ጽፈዋል።
በጥር ወር እንዳረፈች ያኔውኑ ለምን አልተቀበረችም?፤ ተብለው ሲጠየቁ ወደ ቀብር ሥጋዋን ተሸክመው ይሄዱ የነበሩት ሐዋርያት ላይ ታውፋንያ የሚባል ወንበዴ ጎራዴ ሲመዝባቸው ዮሐንስ ብቻ ሲቀር ሐዋርያቱ ጥለዋት በመሸሻቸውና ዮሐንስ ብቻውን ቀርቶ ወደ መቃብር ሳትገባ ወደ ገነት ዛፍ ስር በመወሰዷ እንደሆነ ይነገራል። ዮሐንስም ወደቤት በተመለሰ ጊዜ ሸሽተው የነበሩት ሐዋርያት ሥጋዋስ የታለ? ብለው ቢጠይቁት በገነት ዛፍ ስር መቀመጧን ስለነገራቸው ዮሐንስን ገነት ዛፍ ስር ሬሳዋ መቀመጡን አይቶ ለምን እኛስ ይቀርብናል በማለት ነሐሴ 1/ ቀን የጾም የጸሎት ሱባዔ ጀምረው በ15ኛው ቀን ትኩስ ሬሳ ከገነት ዛፍ ስር እንደመጣላቸውና እንደቀበሯት ይናገራሉ።
እዚህ ላይ ይሄንን ታሪክ የሚያፈርሰውና ተረት እንደሆነ የሚያሳየንን ነገር እናንሳ!
ገነት ውስጥ የሰው ሬሳ የሚቀመጥበት ዛፍ ስለመኖሩ ማስረጃችን ምንድነው? ሬሳውን ተሸክመው ገነት የገቡት ኃይሎች ታውፋንያ የተባለውን ሽፍታ ማስወገድ ለምን አልቻሉም? እጁን ቆረጡት የተባለው ተረት ለምን አንገቱን አልሆነም? ከሐዋርያቱ ተለይቶ ብቻውን የቀረው ዮሐንስ ከሽፍታው ሰይፍ እንዴት ተረፈ? ይሄ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲከናወን ሐዋርያቱ: መላእክቱ: ኢየሱስም አብረዋት ከነበሩ ከማርያም ሥጋ መንከራተት ጋር ምን ትርፍ አላቸው?
ታሪኩን በሚያማልልና ልብን በሚቦረቡር ተረት መቀባባት ያስፈለገው ሰዎች ከወንጌል እውነት እንዲወጡና ልብን በተረታ ተረት በመሙላት በከንቱ ሃሳብ ውስጥ አስጥሞ ለማስቀረት ነው።
ሌላው ጥያቄ የሚያስነሳው ነገር በጥር ወር አርፋ ከቀብር በፊት ወደገነት ዛፍ ስር ስለመወሰዷና ዮሐንስ ወደ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ከነገራቸው በኋላ እሱ ያየውን እኛም ማየት አለብን ያሉትና የጾም: የጸሎት ሱባኤ የገቡት ነሐሴ 1 ቀን ነው ይባላል። በጥር ወር ገነት ገባ ለተባለ ሬሳ ምላሽ ለማግኘት ሐዋርያቱ ለምን እስከነሐሴ መቆየት አስፈለጋቸው? ሥጋዋስ 8 ወር ሙሉ ለምን ሳይቀበር ቆየ? ሐዋርያቱ ሱባዔ ባያደርጉና እንዲቀብሯት ሬሳዋ ባይሰጣቸው ኖሮ የማርያም ሥጋ ከገነት ዛፍ ስር አይንቀሳቀስም ነበር ማለት ነው?
ለማርያም ሥጋ መቀበር ምክንያት የሆነው የሐዋርያቱ ሱባኤ መያዝ እንጂ ከቀብር ተለያይቶ የሚቀር ሆኖ ነበር ማለት ነው።
እንደሰዎቹ አባባል በጥር ወር አርፋ ሳይቀበር የቀረውን የማርያምን ሥጋ በስምንተኛው ወር ከገነት ወጥቶ ከተሰጣቸውና ከቀበሯትም በኋላ ቢሆን ወደሰማይ ስታርግ ሐዋርያቱ ለማየት አልቻሉም። የተረቱ ባለቤቶች እርገቷን ያየው ቶማስ ብቻ ነው ካሉን በኋላ ለተረቱ የታሪክ ፍሰት ውበት ሲሰጡት እንዲህ ነበር ይሉናል። ሐዋርያቱ ማርያምን ቀብረዋት ወደቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ቶማስ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ ከሕንድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ በሦስተኛው ቀን ወደ ሰማይ ስታርግ የዳመናው ጎዳና ላይ ማርያም ስታርግ አገኛት። ቀድሞ የልጅሽን እርገት ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ሳላይ ልቀር ነው? ብሎ ቢያዝን ትንሣኤዬን ያላንተ ማንም አላየም ካለችው በኋላ የተገነዘችበትን ጨርቅ እና ሰበን ለምልክት ሰጥታው እንዳረገች በሰፊው ይተረታል።
ሰዎቹ ነገሩን ሁሉ ለማጣፈጥ የሚጠቀሙበት ተረት አስገራሚ ነው። የሰው ልጅ ከትንሣኤው በኋላ የዚህን ዓለም ጨርቅና ልብስ እንደተሸከመ ወደ ሰማይ ይገባል የሚል ክርስቲያናዊ አስተምህሮ አለ ወይ?
ወንጌል ከትንሣኤ በኋላ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ እንለወጣለን ይላል እንጂ የመቃብሩን ልብስና ሰበን እየተሸከመ ሰው ወደሰማይ ያርጋል የሚል አስተምሮ የለውም።
« 2ኛ ቆሮ 3፤18
እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን»
ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በመቃብሩ የተገነዘበትን ጨርቅ ትቶ መነሳቱን እንጂ ያንኑ ለብሶ መነሳቱን አላነበብንም።
ዮሐ20፤6—8
ስለማርያም እረፍት፤ትንሣዔና እርገት አብያተ ክርስቲያናት አንድ ዓይነት የእምነት አቋም የላቸውም። እንዲያውም ስለማርያም ሞትና የእርገት ዕለት በግልጽ የሚታወቅ ማስረጃ እንደሌለ በ5ኛው ክ/ዘመን የኖረው የሳላሚሱ ኤጴፋንዮስ ተናግሯል። ዕረፍቷና እርገቷ በኢየሩሳሌም እንደሆነ የሚናገሩ ቢኖሩም ይህንን አባባል የማይቀበሉ አብያተ ክርስቲያናትና የቴኦሎጂ ምሁራን ሞልተዋል። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚለውን አባባል የማይቀበሉበትን ማስረጃ ሲያቀርቡም ዮሐንስ በወንጌሉ ላይ እንደተናገረው «እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት» ዮሐ19፤27 ባለው መሠረት ማርያም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ድረስ ከዮሐንስ ጋር ስለኖረችና ወንጌላዊው ዮሐንስም ከጌታ ሞት በኋላ በኢየሩሳሌም ጥቂት ዓመታትን ከቆየ በኋላ በ37 ዓ/ም ገደማ ወደ ቤዛንታይን ከተማ ኤፌሶን ሄዶ ወገኖቹን ወንጌል እያስተማረ መቆየቱንና ማርያም በሞት እስከተለየችው ድረስ ከ48-52 ዓ/ም እዚያው እንደነበር ብዙ ተጽፏል።
በኋላም በቅርብ ርቀት ባለችው ደሴተ ፍጥሞም በግዞት መኖሩንና በመጽሐፍ ቅዱሳችን የተጻፈውን ራእይ የተመለከተውም እዚያ እንደሆነ ይታወቃል ። አንዳንዶች ከዶሚኒሽን አገዛዝ ቀደም ብሎ የራእይ መጽሐፉን ከ55-65 ዓም ገደማ እንደጻፈም በታሪክ አስቀምጠዋል።
ዋናው ነገር ማርያም በኤፌሶን ከዮሐንስ ጋር ኖራለች ወይስ አልኖረችም? ነው ጥያቄው። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚሉ ሰዎች አንድም ጊዜ ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን ኖራለች ሲሉ አይደመጥም። ለምን? ዮሐንስ ማርያምን እንደእናት ሊይዛት አደራ ተሰጥቶታል የሚባል ከሆነ ከዮሐንስ ጋር ኤፌሶን ስለመቀመጧ የማይነገረው ለምንድነው? ዮሐንስ እስከ 96 ዓመቱ ድረስ ከኤፌሶንና ከደሴተ ፍጥሞ ውጪ ስለመኖሩ የተነገረ ታሪክ የለም። ማርያም ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን አልኖረችም ብሎ በመከራከርና በኢየሩሳሌም ኖራ፤ እዚያው ማረፏን በግልጽ በመናገር መካከል ትልቅ ልዩነት አለ። «እነኋት እናትህ» ባለው መሰረት አብረው ኤፌሶን ኖረው እዚያው ማረፏን በሚያምኑና ኢየሩሳሌም ኖራ እዚያው አርፋለች በሚሉት ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት የማይታረቅ ነው።
ሮበርት ክሬው የተባለ የነገረ መለኮትና የታሪክ ጸሐፊ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዘመኑን ሁሉ በኖረበት ከኤፌሶን ከተማ 8 ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ ባለች ኰረብታ ላይ በተሰራ ቤት ውስጥ እንደኖረና ማርያምም እዚያ ማረፏን ጽፏል። ይህንን በኤፌሶን ያለውን የማርያምን መቃብር የዓለም ክርስቲያኖች እንዲሆም ሙስሊሞች ሳይቀሩ ይጎበኙታል፤ ይሳለሙታል። በቱርክ ግዛት ያለው ይህ ስፍራ በቱርካውያን ሙስሊሞች ዘንድ «ሜሪዬማና» ተብሎ ይጠራል።
ቅድስት ማርያም ከዚህ ዓለም የተለየችው መቼ ነው? ለሚለው ጥያቄ ጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት የምሥራቁና የምዕራቡ ጎራዎች የተለያየ አመለካከት አላቸው።
በተወለደች በ58 ዓመቷ ዐርፋለች የሚሉ አሉ። በ72 እና 63 እድሜዋም አርፋለች የሚሉ መረጃዎች አሉ። እንደ ግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ግን የሚታመነው በ64 ዓመት እድሜዋ ማረፏ ነው። ኖረችበት ተብሎ ከሚገመተውና አርፋለች ከሚባለው ቦታ ያለው ልዩነት እንዳለሆኖ በጥር ወር ከዚህ ዓለም ተለይታ በ40ኛው ቀን ማረጓን የሚናገሩ አሉ። ይህም ሞትና ትንሣኤዋን ከልጇ ጋር ለማመሳሰል የተደረገ ጥረት ነው። በነሐሴ ወር አርፋ ከተቀበረች በኋላ ትንሣዔዋን ሳያዩ መቃብሯ ባዶ ሆኖ ስላገኙት ሐዋርያት ሱባዔ ይዘው በሦስተኛው ቀን ተገለጸችላቸው የሚሉም አሉ። እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ደግሞ በጥር ሞታ፤ በነሐሴ ተቀበረች የሚል ትምህርት አለ። በጥር ወር አርፋ፤ በነሐሴ ተቀብራለች የሚሉ ሰዎች ሥጋዋ በገነት ዛፍ ስር ለስምንት ወራት መቀመጡንና በሱባዔ ጸሎት በተደረገው ልመና የተነሳ ሥጋዋ ከሰማይ ወርዶ ለመቀበር መቻሏን አስፋፍተው ጽፈዋል።
በጥር ወር እንዳረፈች ያኔውኑ ለምን አልተቀበረችም?፤ ተብለው ሲጠየቁ ወደ ቀብር ሥጋዋን ተሸክመው ይሄዱ የነበሩት ሐዋርያት ላይ ታውፋንያ የሚባል ወንበዴ ጎራዴ ሲመዝባቸው ዮሐንስ ብቻ ሲቀር ሐዋርያቱ ጥለዋት በመሸሻቸውና ዮሐንስ ብቻውን ቀርቶ ወደ መቃብር ሳትገባ ወደ ገነት ዛፍ ስር በመወሰዷ እንደሆነ ይነገራል። ዮሐንስም ወደቤት በተመለሰ ጊዜ ሸሽተው የነበሩት ሐዋርያት ሥጋዋስ የታለ? ብለው ቢጠይቁት በገነት ዛፍ ስር መቀመጧን ስለነገራቸው ዮሐንስን ገነት ዛፍ ስር ሬሳዋ መቀመጡን አይቶ ለምን እኛስ ይቀርብናል በማለት ነሐሴ 1/ ቀን የጾም የጸሎት ሱባዔ ጀምረው በ15ኛው ቀን ትኩስ ሬሳ ከገነት ዛፍ ስር እንደመጣላቸውና እንደቀበሯት ይናገራሉ።
እዚህ ላይ ይሄንን ታሪክ የሚያፈርሰውና ተረት እንደሆነ የሚያሳየንን ነገር እናንሳ!
ገነት ውስጥ የሰው ሬሳ የሚቀመጥበት ዛፍ ስለመኖሩ ማስረጃችን ምንድነው? ሬሳውን ተሸክመው ገነት የገቡት ኃይሎች ታውፋንያ የተባለውን ሽፍታ ማስወገድ ለምን አልቻሉም? እጁን ቆረጡት የተባለው ተረት ለምን አንገቱን አልሆነም? ከሐዋርያቱ ተለይቶ ብቻውን የቀረው ዮሐንስ ከሽፍታው ሰይፍ እንዴት ተረፈ? ይሄ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲከናወን ሐዋርያቱ: መላእክቱ: ኢየሱስም አብረዋት ከነበሩ ከማርያም ሥጋ መንከራተት ጋር ምን ትርፍ አላቸው?
ታሪኩን በሚያማልልና ልብን በሚቦረቡር ተረት መቀባባት ያስፈለገው ሰዎች ከወንጌል እውነት እንዲወጡና ልብን በተረታ ተረት በመሙላት በከንቱ ሃሳብ ውስጥ አስጥሞ ለማስቀረት ነው።
ሌላው ጥያቄ የሚያስነሳው ነገር በጥር ወር አርፋ ከቀብር በፊት ወደገነት ዛፍ ስር ስለመወሰዷና ዮሐንስ ወደ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ከነገራቸው በኋላ እሱ ያየውን እኛም ማየት አለብን ያሉትና የጾም: የጸሎት ሱባኤ የገቡት ነሐሴ 1 ቀን ነው ይባላል። በጥር ወር ገነት ገባ ለተባለ ሬሳ ምላሽ ለማግኘት ሐዋርያቱ ለምን እስከነሐሴ መቆየት አስፈለጋቸው? ሥጋዋስ 8 ወር ሙሉ ለምን ሳይቀበር ቆየ? ሐዋርያቱ ሱባዔ ባያደርጉና እንዲቀብሯት ሬሳዋ ባይሰጣቸው ኖሮ የማርያም ሥጋ ከገነት ዛፍ ስር አይንቀሳቀስም ነበር ማለት ነው?
ለማርያም ሥጋ መቀበር ምክንያት የሆነው የሐዋርያቱ ሱባኤ መያዝ እንጂ ከቀብር ተለያይቶ የሚቀር ሆኖ ነበር ማለት ነው።
እንደሰዎቹ አባባል በጥር ወር አርፋ ሳይቀበር የቀረውን የማርያምን ሥጋ በስምንተኛው ወር ከገነት ወጥቶ ከተሰጣቸውና ከቀበሯትም በኋላ ቢሆን ወደሰማይ ስታርግ ሐዋርያቱ ለማየት አልቻሉም። የተረቱ ባለቤቶች እርገቷን ያየው ቶማስ ብቻ ነው ካሉን በኋላ ለተረቱ የታሪክ ፍሰት ውበት ሲሰጡት እንዲህ ነበር ይሉናል። ሐዋርያቱ ማርያምን ቀብረዋት ወደቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ቶማስ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ ከሕንድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ በሦስተኛው ቀን ወደ ሰማይ ስታርግ የዳመናው ጎዳና ላይ ማርያም ስታርግ አገኛት። ቀድሞ የልጅሽን እርገት ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ሳላይ ልቀር ነው? ብሎ ቢያዝን ትንሣኤዬን ያላንተ ማንም አላየም ካለችው በኋላ የተገነዘችበትን ጨርቅ እና ሰበን ለምልክት ሰጥታው እንዳረገች በሰፊው ይተረታል።
ሰዎቹ ነገሩን ሁሉ ለማጣፈጥ የሚጠቀሙበት ተረት አስገራሚ ነው። የሰው ልጅ ከትንሣኤው በኋላ የዚህን ዓለም ጨርቅና ልብስ እንደተሸከመ ወደ ሰማይ ይገባል የሚል ክርስቲያናዊ አስተምህሮ አለ ወይ?
ወንጌል ከትንሣኤ በኋላ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ እንለወጣለን ይላል እንጂ የመቃብሩን ልብስና ሰበን እየተሸከመ ሰው ወደሰማይ ያርጋል የሚል አስተምሮ የለውም።
« 2ኛ ቆሮ 3፤18
እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን»
ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በመቃብሩ የተገነዘበትን ጨርቅ ትቶ መነሳቱን እንጂ ያንኑ ለብሶ መነሳቱን አላነበብንም።
ዮሐ20፤6—8
«ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ»
የሁላችን አማኞች ትንሣዔ የክርስቶስን ትንሣዔ መምሰል ካለበት በቀብር ወቅት ከዚህ ዓለም ጉድጓድ የገባ ጨርቅ ወደ ሰማይ አብሮን የሚያርግበት ምንም መንገድ የለውም።
ተጠራጣሪ እንደሆነ ሁል ጊዜ የሚነገርበት ቶማስ በማርያም እርገት እሱ ብቻ የተለየ ተጠቃሚ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ ሲባል የማስረጃ ጋጋታ ሲፈለግ የማርያም የግንዘት ጨርቅ ተገኘና ወደሰማይ ከማረጉ በፊት ቶማስ ተቀበለ የሚል ተረት አቀረቡልን። ሌላው አስገራሚው ነገር በደመና ተጭኖ የመሄድ ተረት ነው። በመንፈስ ተነጠቀ የሚል መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት በደመና ተጫነ ከሚለው ጋር የትርጉም አንድነት የለውም። (የሐዋ 8:39)
ቶማስ በደመና ተጭኖ ሲጓዝ የሚለውን አባባል እንደፊልጶስ መነጠቅ አድርገን ብንቆጥረው እንኳን የቶማስ ሰብአዊ ማንነትና የማርያም ሰማያዊ የእርገት ማንነት የተለያየና ፈጽሞ የማይገናኝን ነገር ነው። የቶማስን የዳመና ላይ ውይይትን ከረቂቅ ክርስቶሳዊ አዲስ ፍጥረት ጋር ለማገናኘት መሞከር የጥንቶቹን የሮማውያን የቬነስ ወጎች/fable story/ እንድናስታውስ ያደርገናል።
በሞት: ትንሣዔና በእርገት መካከል እንደዚህ ዓይነት ተረቶችን በሰውኛ ትረካ መጫወት እግዚአብሔር ስለሞትና ትንሣዔ በተናገረው ላይ መቀለድ ነው። ከሁሉ የሚገርመው ደግሞ ማርያምን በጥር ሞታለች ያሉ ሰዎች፤ በመጀመሪያው ሞት ዮሐንስ ብቻ እድለኛ ሆኖ በገነት ዛፍ ስር ለማየት በመቻሉ ይሄንን እድል እነርሱም ለማግኘት ሐዋርያቱ ሱባኤ ነሐሴ 1 ቀን ገቡ ያሉን ሰዎች ማብቂያ በሌለው ተረታቸው እንዲህ በማለት ሆዳችንን በተረት ይነፉናል። ከቀበሯት በኋላ ቶማስ ብቻ ያየውን እርገቷን እኛም ማየት አለብን ብለው ሐዋርያቱ በድጋሚ በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ ይሉናል። ሐዋርያቱ ነሐሴ ወር ላይ ሙጭጭ ያሉበት የሱባኤ የፍቅር ጊዜ ለምን ይሆን? ደግሞስ እርገቷን ለሁለተኛ ጊዜ ለማረጋገጥ ለምን አንድ አመት መቆየት አስፈለጋቸው?
የሁላችን አማኞች ትንሣዔ የክርስቶስን ትንሣዔ መምሰል ካለበት በቀብር ወቅት ከዚህ ዓለም ጉድጓድ የገባ ጨርቅ ወደ ሰማይ አብሮን የሚያርግበት ምንም መንገድ የለውም።
ተጠራጣሪ እንደሆነ ሁል ጊዜ የሚነገርበት ቶማስ በማርያም እርገት እሱ ብቻ የተለየ ተጠቃሚ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ ሲባል የማስረጃ ጋጋታ ሲፈለግ የማርያም የግንዘት ጨርቅ ተገኘና ወደሰማይ ከማረጉ በፊት ቶማስ ተቀበለ የሚል ተረት አቀረቡልን። ሌላው አስገራሚው ነገር በደመና ተጭኖ የመሄድ ተረት ነው። በመንፈስ ተነጠቀ የሚል መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት በደመና ተጫነ ከሚለው ጋር የትርጉም አንድነት የለውም። (የሐዋ 8:39)
ቶማስ በደመና ተጭኖ ሲጓዝ የሚለውን አባባል እንደፊልጶስ መነጠቅ አድርገን ብንቆጥረው እንኳን የቶማስ ሰብአዊ ማንነትና የማርያም ሰማያዊ የእርገት ማንነት የተለያየና ፈጽሞ የማይገናኝን ነገር ነው። የቶማስን የዳመና ላይ ውይይትን ከረቂቅ ክርስቶሳዊ አዲስ ፍጥረት ጋር ለማገናኘት መሞከር የጥንቶቹን የሮማውያን የቬነስ ወጎች/fable story/ እንድናስታውስ ያደርገናል።
በሞት: ትንሣዔና በእርገት መካከል እንደዚህ ዓይነት ተረቶችን በሰውኛ ትረካ መጫወት እግዚአብሔር ስለሞትና ትንሣዔ በተናገረው ላይ መቀለድ ነው። ከሁሉ የሚገርመው ደግሞ ማርያምን በጥር ሞታለች ያሉ ሰዎች፤ በመጀመሪያው ሞት ዮሐንስ ብቻ እድለኛ ሆኖ በገነት ዛፍ ስር ለማየት በመቻሉ ይሄንን እድል እነርሱም ለማግኘት ሐዋርያቱ ሱባኤ ነሐሴ 1 ቀን ገቡ ያሉን ሰዎች ማብቂያ በሌለው ተረታቸው እንዲህ በማለት ሆዳችንን በተረት ይነፉናል። ከቀበሯት በኋላ ቶማስ ብቻ ያየውን እርገቷን እኛም ማየት አለብን ብለው ሐዋርያቱ በድጋሚ በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ ይሉናል። ሐዋርያቱ ነሐሴ ወር ላይ ሙጭጭ ያሉበት የሱባኤ የፍቅር ጊዜ ለምን ይሆን? ደግሞስ እርገቷን ለሁለተኛ ጊዜ ለማረጋገጥ ለምን አንድ አመት መቆየት አስፈለጋቸው?
ማርያም አንዴ ካረገች በኋላ በሱባኤ የሚደገም ሁለተኛ እርገት አለ ወይ? እንደዚህ ዓይነት ተደጋጋሚ ሞትና እርገት እንዲደረግላቸው ሐዋርያቱ ይጠይቁ ነበር ብሎ ለመቀበል ይቸግራል። ከጌታ የተማሩት ትምሕርት በእንደዚህ ዓይነት ጥያቄ እንዲዋከቡ የሚያደርግ አልነበረም። ማርያምን በመቅበር: በማንሳትና በማሳረግ ጣጣ ውስጥ ሐዋርያቱ ለምን እንዲህ ተጨነቁ? የተረት አባቶቹ ለዚህ ጥያቄ መልስ ባይኖራቸው ሐዋርያቱ ወንጌልን ለዓለም ያዳርሱ ዘንድ የተሰጣቸውን ሰማያዊ ተልእኮ ትተው ዋሻ ተወሽቀው የሆነ ሥጋ ከሰማይ እስኪወርድላቸው ጊዜያቸው ፈጁ የሚለውን ተረት ሰይጣን ለሚያዳምጡት ከሚረጨው በስተቀር የክርስቶ አማኝ የሆነ ሰው እውነት ነው ብሎ በጭራሽ ሊቀበል አይችልም።
የሚያሳዝነው ነገር ሐዋርያቱ ሱባኤ ከገቡ በኋላ የማርያም ሥጋ ከሰማይ እንደገና ወረደ የሚሉን አሳፋሪ ታሪክ ነው። እንዲያውም ኢየሱስ ራሱ ማርያምን ሥጋ መንበር (የቁርባን መቀመጫ) አድርጎ ጴጥሮስን ንፍቅ ቄስ፤ እስጢፋኖስን ገባሬ ዲያቆን ሆነው ቀደሱና ቆረቡ ይሉናል። የማርያም ሥጋ እንዴት መንበር መሆን ቻለ? ምን የሚባለውን ቅዳሴ ቀደሱ? ኢየሱስ ሰራዔ ካህን ሆኖ ከቀደሰ የማንን ሥጋ ቆረበ? የራሱን? ለየትኛው ድነት ይሆነው ዘንድ ሊቆርብ ይችላል?
አልቆረበም የሚባል ከሆነም ሰራዔ ካህናት በዚህ ምድር መቅደስ ውስጥ ከመቀደስ ባሻገር መቁረብ አይጠበቅባቸውም በማለት አብነታዊ የክህነት አስተምህሮን አያይዞ ማቅረብ የተገባ ይሆናል።
ኢየሱስ የቀደሰው ቅዳሴ ከ14ቱ ቅዳሴያት መካከል የትኛውን ይሆን? ያኔ ቅዳሴያት ተደርሰው ነበር? ወይስ የመጀመሪያው ደራሲ ኢየሱስ ነው?
እንደተለመደው አባባል ቅዳሴ እግዚእ ነው የተቀደሰው የሚሉ ቢኖሩም ክርስቶስ ራሱን በሁለተኛ መደብ አስቀምጦ « ነአኩተከ አምላክ ቅዱስ፤ ፈጻሜ ነፍስነ፤ ወሀቤ ሕይወትነ ዘኢይማስን» (ትርጉም) "የማይጠፋ ሕይወት የሰጠኸን: የነፍሳችን ፈጻሚ: ቅዱስ አምላክ እናመሰግንሃለን" ብሎ እንደእሩቅ ብእሲ ( እንደምድራዊ ሰው ሲማፀን አይገኝም። የማይጠፋ ሕይወት ራሱ ሰጪ ሆኖ ሳለ የዘላለም ሕይወት ይሰጠው ዘንድ ኢየሱስ ወደሰማይ አይማፀንም።
“እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።”ዮሐ 6፥47 ያለን ጌታ ሕይወት ከሱ ቁጥጥር ውጪ ያለ የሚያስመስለው ቅዳሴ እግዚእ የሰዎች ድርሰት እንጂ የኢየሱስ አይደለም።
እንደዚህ ዓይነቱ አደገኛ ክህደት፤ ሰዎች ለማርያም ባላቸው ፍቅር ውስጥ ተደብቆ ለዘመናት ሕይወትን ከመዳን መንገድ ሲያጠፋ ቆይቷል።
ደግሞም በምሴተ ሐሙስ በጉ የመስዋእቱን ሥርዓት ለሕይወታችን ድኅነት ከሰጠ በኋላ ወደምድር መጥቶ ሁለተኛ ማእድ የሚያዘጋጅበት ምንም መጽሐፍ ቅዳሳዊ አስረጂ የለም። እውነታውን ስናነብ እንዲህ የሚል ቃል ተቀምጦልናል።«ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ። እርሱም፦ ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው። ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት» ሉቃ 22፤14-17
"የእግዚብሔር መንግስት እስኪፈጸም ድረስ ከዚህ ማእድ ድጋሜ አልበላም" ያለውን ቃል ያጥፍ ዘንድ ኢየሱስን ዋሾ ማድረግ አደገኛ ክህደት ነው።
በጉ መስዋዕቱን ሕይወት ይሆናቸው ዘንድ ለሰዎች ከሰጠ በኋላ፤ በፍርድ ቀን የደሙን ምልክት ለተቀበሉት ሁሉ ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል እንጂ እሱ የመስዋእቱ ተካፋይ ስላልሆነ፤ ክርስቶስ በቀዳሽነት ቆርቦ፤ ማቁረብ የሚባል ታሪክ ከወንጌል ቃል የተገኘ ሳይሆን ክፉ ጠላት በጭለማ የዘራው ዘር ነው።
ወደዋናው ሃሳባችን ስንመለስ ለመሆኑ በማርያም ላይ ስንት ቀብር፤ ስንት ትንሣዔና ስንት እርገት ተደረገ? ብለን ብንጠይቅ እንደሚነገረው ከሆነ ፤
1/ዮሐንስ ያየውና አፈር ያልነካው እርገት በገነት ዛፍ ስር
2/ አፈር የነካው የሐዋርያቱ ቀብር በነሐሴ 14 ቀን /ከስምንት ወር በኋላ/
3/ ቶማስ ያየው የትንሳዔ እርገት፤ ከቀብር በኋላ በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16
4/ ከአንድ ዓመት በኋላ ሐዋርያት ያዩት የነሐሴ 16 ትንሣዔና እርገት ናቸው።
እንግዲህ በማርያም ሞትና እርገት መካከል አራት ትእይንት መከሰቱን ዛሬም ድረስ ከሚሰጡት የቃል አስተምህሮዎችና የተዘጋጁ ጽሁፎች ውስጥ በግልጽ እናገኛለን። ማርያምን መውደድ አንድ ነገር ነው። ማርያምን ግን እየቀበሩና እያነሱ በቀብርና ትንሣኤ ማሰቃየት ደግሞ ሌላ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል። እንዲያውም ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻልኩ ሰባት ጊዜም ቢሆን እሞታለሁ ብላ ለልጇ ተናግራለች የሚሉት ተረትም በተዛማጅ ትምሕርትነት ይሰጣል። የእሷ መሞት የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻለ የክርስቶስ ከእሷ መወለድ አስፈላጊ አይደለም የሚል ሃሳብን የሚያንጸባርቀው ይህ አባባል ከአሳሳች ትረካዎች ውስጥ የሚደመር ከመሆን አያልፍም።
እኛ ማርያምን ብንወዳትና ብጽእት ብንላት «እናትህንና አባትህን አክብር» ያለውን የአምላክ ቃል መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለእርሷ የተነገረ ቃል ስላለም ጭምር ነው። ከዓለመ አንስት መካከል በድንግልና መውለድ የሷ የተለየ ስጦታ ነው። በዚህም መመረጥ መቻሏን እናከብረዋለን። ነገር ግን የዘላለማዊ አምላክ የክርስቶስ ፤ እናቱ ስለሆነች በማዳላት ወይም አምላካዊ ባህርይውን በሰውኛ ጠባይ በመለወጥ ከፍርድ ሚዛኑ በማጉደል የእሷን ሞትና ትንሣዔ የተለየ ያደርጋል ብሎ ማሰብ ስህተት ነው። የእሷ ሞትም የመድኃኒትነትን ውክልና ለሰው ልጆች የያዘ እንደሆነ ማሰብ ክህደት ነው። ብቸኛው መድኃኒት አንዱ ኢየሱስ ብቻ ነው። ማርያምም ይህንን አሳምራ ስለምታውቅ
«ነፍሴ በአምላኬና በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች» ብላ ተነግራለች። ምክንያቱም ኢየሱስ ከእርሷ የተወለደ ቢሆንም ዓለሙን በማዳን ማንነቱ ውስጥ ለእርሷም አምላኳና መድኃኒቷም ስለሆነ ደስ እንደሚላት መስክራለች። የትንሣዔ በኩር የሆነው ሁላችንም በሞቱ እንድንመስለው እንጂ የተለየ አድሎአዊ ጥቅምን/ favour/ ለተለዩ ሰዎች በመስጠት አይደለም።ወንጌል የሚናገረው ይህንን ነውና። የክርስቶስ ሕይወት ተካፋዮች የምንሆነው በሞቱና በትንሣኤው እርሱን ስንመስል ብቻ ነው።
ሮሜ 6፥5 «ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን»
ስለዚህ ደጋግሞ መሞት፤ መነሳትና ደጋግሞ ማረግ አለ ከተባለ ያ ነገር ከክርስቶስ ትንሣዔ ጋር ያልተባበረ ስለሆነ አንቀበለውም። እንዲያውን ይህ ኑፋቄና ወንጌልን መካድ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስም የተናገረው ስለክርስቶስ ወንጌል በሞቱም ክርስቶስን እንዲመስል ነበር።
ፊልጵ 3፥10-11 «እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ»
የማርያም ሞትና ትንሣዔ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ካዘጋጀው የትንሣዔው በኩር አንድያ ልጁ የተለየ አያደርገውም። ከመግቢያችን ላይ ጀምሮ ለመግለጽ እንደሞከርነው የኤፌሶኑና የኢየሩሳሌሙ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አብያተክርስቲያናት ሁሉ የተለያየ የሞትና የትንሣዔ አስተምህሮ ከመያዛቸው አንጻር ኤጲፋንዮስ እንዳለው ትክክለኛው የታሪክ ቀን አይታወቅም። ቢታወቅም ስለድነታችን የሚጨምረውም: የሚቀንሰውም ነገር የለውም። አሁን የሚደረገውም ፍልሰታ ለማርያም በዓል ከልምድና ትውፊት ከተረትና ክህደት ጋር በማር የተለወሰ መርዝ ስለሆነ መጠንቀቅ አለብን።
ማርያምን እንወዳለን እያሉ በጥር ሞተች፤ ገነት ዛፍ ስር ስምንት ወር በሬሳ ቆየች፤ በስንት ሱባዔ ስጋዋ መጥቶ ነሐሴ ተቀበረች፤ እስከነ ምድራዊ ልብሷ አረገች፤ በዳመናው ጎዳና ላይ ከቶማስ ጋር ጨርቅ ተለዋወጠች፤ እድል ላመለጣቸው ሐዋርያት ዳግመኛ በስንት ሱባዔ በሌላ ትንሣኤና እርገት ተረጋገጠች፤ መንበር ሆና ተነጠፈች ወዘተ በማለት እየገደሉና እያነሱ በማርያም ላይ መጫወት ተገቢ ነው ብለን አናምንም። የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤንም ማፋለስና መካድ ይሆናል። የማርያም ትንሣኤና እርገት ለክርስትና ከታሪክ ባለፈ ለሕይወት የሚሰጠው የሕይወት ዋስትና የለውም። ሕይወት ኢየሱስ ብቻ ነው። ሕይወት እንዲሆንላችሁ ከፈለጋችሁ ከተረት ዓለም ውጡ።
“ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።” ዮሐ 5፥40 የተባለው እንዳይፈፀምባችሁ በሕይወት መኖር አይሻላችሁምን?
ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር የሌላ የማንም ሞትና ትንሣኤ ለሰው ልጆች መዳን የቀረበ መስዋእት የለም።
የማርያምም ሞትና ትንሣኤ ማንንም ሊያድን አይችልም።
የተነገረን በማርያም ትንሣኤ እንድናምን ሳይሆን “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።”
ዮሐ 3፥36 ተብሎ እንደተነገረው የቤዛነት ምትክ በሌለው በኢየሱስ ብቸኛ አዳኝነት ልናምን ይገባል!
መጽሐፍ እንዳለው "“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”ሐዋ 4፥12
የሚያሳዝነው ነገር ሐዋርያቱ ሱባኤ ከገቡ በኋላ የማርያም ሥጋ ከሰማይ እንደገና ወረደ የሚሉን አሳፋሪ ታሪክ ነው። እንዲያውም ኢየሱስ ራሱ ማርያምን ሥጋ መንበር (የቁርባን መቀመጫ) አድርጎ ጴጥሮስን ንፍቅ ቄስ፤ እስጢፋኖስን ገባሬ ዲያቆን ሆነው ቀደሱና ቆረቡ ይሉናል። የማርያም ሥጋ እንዴት መንበር መሆን ቻለ? ምን የሚባለውን ቅዳሴ ቀደሱ? ኢየሱስ ሰራዔ ካህን ሆኖ ከቀደሰ የማንን ሥጋ ቆረበ? የራሱን? ለየትኛው ድነት ይሆነው ዘንድ ሊቆርብ ይችላል?
አልቆረበም የሚባል ከሆነም ሰራዔ ካህናት በዚህ ምድር መቅደስ ውስጥ ከመቀደስ ባሻገር መቁረብ አይጠበቅባቸውም በማለት አብነታዊ የክህነት አስተምህሮን አያይዞ ማቅረብ የተገባ ይሆናል።
ኢየሱስ የቀደሰው ቅዳሴ ከ14ቱ ቅዳሴያት መካከል የትኛውን ይሆን? ያኔ ቅዳሴያት ተደርሰው ነበር? ወይስ የመጀመሪያው ደራሲ ኢየሱስ ነው?
እንደተለመደው አባባል ቅዳሴ እግዚእ ነው የተቀደሰው የሚሉ ቢኖሩም ክርስቶስ ራሱን በሁለተኛ መደብ አስቀምጦ « ነአኩተከ አምላክ ቅዱስ፤ ፈጻሜ ነፍስነ፤ ወሀቤ ሕይወትነ ዘኢይማስን» (ትርጉም) "የማይጠፋ ሕይወት የሰጠኸን: የነፍሳችን ፈጻሚ: ቅዱስ አምላክ እናመሰግንሃለን" ብሎ እንደእሩቅ ብእሲ ( እንደምድራዊ ሰው ሲማፀን አይገኝም። የማይጠፋ ሕይወት ራሱ ሰጪ ሆኖ ሳለ የዘላለም ሕይወት ይሰጠው ዘንድ ኢየሱስ ወደሰማይ አይማፀንም።
“እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።”ዮሐ 6፥47 ያለን ጌታ ሕይወት ከሱ ቁጥጥር ውጪ ያለ የሚያስመስለው ቅዳሴ እግዚእ የሰዎች ድርሰት እንጂ የኢየሱስ አይደለም።
እንደዚህ ዓይነቱ አደገኛ ክህደት፤ ሰዎች ለማርያም ባላቸው ፍቅር ውስጥ ተደብቆ ለዘመናት ሕይወትን ከመዳን መንገድ ሲያጠፋ ቆይቷል።
ደግሞም በምሴተ ሐሙስ በጉ የመስዋእቱን ሥርዓት ለሕይወታችን ድኅነት ከሰጠ በኋላ ወደምድር መጥቶ ሁለተኛ ማእድ የሚያዘጋጅበት ምንም መጽሐፍ ቅዳሳዊ አስረጂ የለም። እውነታውን ስናነብ እንዲህ የሚል ቃል ተቀምጦልናል።«ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ። እርሱም፦ ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው። ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት» ሉቃ 22፤14-17
"የእግዚብሔር መንግስት እስኪፈጸም ድረስ ከዚህ ማእድ ድጋሜ አልበላም" ያለውን ቃል ያጥፍ ዘንድ ኢየሱስን ዋሾ ማድረግ አደገኛ ክህደት ነው።
በጉ መስዋዕቱን ሕይወት ይሆናቸው ዘንድ ለሰዎች ከሰጠ በኋላ፤ በፍርድ ቀን የደሙን ምልክት ለተቀበሉት ሁሉ ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል እንጂ እሱ የመስዋእቱ ተካፋይ ስላልሆነ፤ ክርስቶስ በቀዳሽነት ቆርቦ፤ ማቁረብ የሚባል ታሪክ ከወንጌል ቃል የተገኘ ሳይሆን ክፉ ጠላት በጭለማ የዘራው ዘር ነው።
ወደዋናው ሃሳባችን ስንመለስ ለመሆኑ በማርያም ላይ ስንት ቀብር፤ ስንት ትንሣዔና ስንት እርገት ተደረገ? ብለን ብንጠይቅ እንደሚነገረው ከሆነ ፤
1/ዮሐንስ ያየውና አፈር ያልነካው እርገት በገነት ዛፍ ስር
2/ አፈር የነካው የሐዋርያቱ ቀብር በነሐሴ 14 ቀን /ከስምንት ወር በኋላ/
3/ ቶማስ ያየው የትንሳዔ እርገት፤ ከቀብር በኋላ በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16
4/ ከአንድ ዓመት በኋላ ሐዋርያት ያዩት የነሐሴ 16 ትንሣዔና እርገት ናቸው።
እንግዲህ በማርያም ሞትና እርገት መካከል አራት ትእይንት መከሰቱን ዛሬም ድረስ ከሚሰጡት የቃል አስተምህሮዎችና የተዘጋጁ ጽሁፎች ውስጥ በግልጽ እናገኛለን። ማርያምን መውደድ አንድ ነገር ነው። ማርያምን ግን እየቀበሩና እያነሱ በቀብርና ትንሣኤ ማሰቃየት ደግሞ ሌላ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል። እንዲያውም ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻልኩ ሰባት ጊዜም ቢሆን እሞታለሁ ብላ ለልጇ ተናግራለች የሚሉት ተረትም በተዛማጅ ትምሕርትነት ይሰጣል። የእሷ መሞት የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻለ የክርስቶስ ከእሷ መወለድ አስፈላጊ አይደለም የሚል ሃሳብን የሚያንጸባርቀው ይህ አባባል ከአሳሳች ትረካዎች ውስጥ የሚደመር ከመሆን አያልፍም።
እኛ ማርያምን ብንወዳትና ብጽእት ብንላት «እናትህንና አባትህን አክብር» ያለውን የአምላክ ቃል መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለእርሷ የተነገረ ቃል ስላለም ጭምር ነው። ከዓለመ አንስት መካከል በድንግልና መውለድ የሷ የተለየ ስጦታ ነው። በዚህም መመረጥ መቻሏን እናከብረዋለን። ነገር ግን የዘላለማዊ አምላክ የክርስቶስ ፤ እናቱ ስለሆነች በማዳላት ወይም አምላካዊ ባህርይውን በሰውኛ ጠባይ በመለወጥ ከፍርድ ሚዛኑ በማጉደል የእሷን ሞትና ትንሣዔ የተለየ ያደርጋል ብሎ ማሰብ ስህተት ነው። የእሷ ሞትም የመድኃኒትነትን ውክልና ለሰው ልጆች የያዘ እንደሆነ ማሰብ ክህደት ነው። ብቸኛው መድኃኒት አንዱ ኢየሱስ ብቻ ነው። ማርያምም ይህንን አሳምራ ስለምታውቅ
«ነፍሴ በአምላኬና በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች» ብላ ተነግራለች። ምክንያቱም ኢየሱስ ከእርሷ የተወለደ ቢሆንም ዓለሙን በማዳን ማንነቱ ውስጥ ለእርሷም አምላኳና መድኃኒቷም ስለሆነ ደስ እንደሚላት መስክራለች። የትንሣዔ በኩር የሆነው ሁላችንም በሞቱ እንድንመስለው እንጂ የተለየ አድሎአዊ ጥቅምን/ favour/ ለተለዩ ሰዎች በመስጠት አይደለም።ወንጌል የሚናገረው ይህንን ነውና። የክርስቶስ ሕይወት ተካፋዮች የምንሆነው በሞቱና በትንሣኤው እርሱን ስንመስል ብቻ ነው።
ሮሜ 6፥5 «ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን»
ስለዚህ ደጋግሞ መሞት፤ መነሳትና ደጋግሞ ማረግ አለ ከተባለ ያ ነገር ከክርስቶስ ትንሣዔ ጋር ያልተባበረ ስለሆነ አንቀበለውም። እንዲያውን ይህ ኑፋቄና ወንጌልን መካድ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስም የተናገረው ስለክርስቶስ ወንጌል በሞቱም ክርስቶስን እንዲመስል ነበር።
ፊልጵ 3፥10-11 «እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ»
የማርያም ሞትና ትንሣዔ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ካዘጋጀው የትንሣዔው በኩር አንድያ ልጁ የተለየ አያደርገውም። ከመግቢያችን ላይ ጀምሮ ለመግለጽ እንደሞከርነው የኤፌሶኑና የኢየሩሳሌሙ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አብያተክርስቲያናት ሁሉ የተለያየ የሞትና የትንሣዔ አስተምህሮ ከመያዛቸው አንጻር ኤጲፋንዮስ እንዳለው ትክክለኛው የታሪክ ቀን አይታወቅም። ቢታወቅም ስለድነታችን የሚጨምረውም: የሚቀንሰውም ነገር የለውም። አሁን የሚደረገውም ፍልሰታ ለማርያም በዓል ከልምድና ትውፊት ከተረትና ክህደት ጋር በማር የተለወሰ መርዝ ስለሆነ መጠንቀቅ አለብን።
ማርያምን እንወዳለን እያሉ በጥር ሞተች፤ ገነት ዛፍ ስር ስምንት ወር በሬሳ ቆየች፤ በስንት ሱባዔ ስጋዋ መጥቶ ነሐሴ ተቀበረች፤ እስከነ ምድራዊ ልብሷ አረገች፤ በዳመናው ጎዳና ላይ ከቶማስ ጋር ጨርቅ ተለዋወጠች፤ እድል ላመለጣቸው ሐዋርያት ዳግመኛ በስንት ሱባዔ በሌላ ትንሣኤና እርገት ተረጋገጠች፤ መንበር ሆና ተነጠፈች ወዘተ በማለት እየገደሉና እያነሱ በማርያም ላይ መጫወት ተገቢ ነው ብለን አናምንም። የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤንም ማፋለስና መካድ ይሆናል። የማርያም ትንሣኤና እርገት ለክርስትና ከታሪክ ባለፈ ለሕይወት የሚሰጠው የሕይወት ዋስትና የለውም። ሕይወት ኢየሱስ ብቻ ነው። ሕይወት እንዲሆንላችሁ ከፈለጋችሁ ከተረት ዓለም ውጡ።
“ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።” ዮሐ 5፥40 የተባለው እንዳይፈፀምባችሁ በሕይወት መኖር አይሻላችሁምን?
ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር የሌላ የማንም ሞትና ትንሣኤ ለሰው ልጆች መዳን የቀረበ መስዋእት የለም።
የማርያምም ሞትና ትንሣኤ ማንንም ሊያድን አይችልም።
የተነገረን በማርያም ትንሣኤ እንድናምን ሳይሆን “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።”
ዮሐ 3፥36 ተብሎ እንደተነገረው የቤዛነት ምትክ በሌለው በኢየሱስ ብቸኛ አዳኝነት ልናምን ይገባል!
መጽሐፍ እንዳለው "“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”ሐዋ 4፥12
ከላይ የተጻፈው ጽሑፍ ዋና መልእክት ማርያንም ለመቃወም ወይም ንጽሕት: ቅድስት ማርያምን ከመጥላት የተነሳ አይደለም። ማርያም ራሷ የማትቀበለው ከእውነትና ከወንጌል ቃል ተቃራኒ አስተምህሮን በእግዚአብሔር ቃል ለማፈረስና ሰዎች ሁሉ ባልተሸቃቀጠው ወንጌል ብቻ እንዲኖሩ ለማስቻል ነው። በዚህም እውነት ለመገዛት እግዚአብሔር ይርዳን! አሜን!
Tuesday, January 2, 2018
ኢየሱስ አዳነን እንጂ ከአብ ጋር እንታረቅ ዘንድ አላማለደንም ማለት ኑፋቄ ነው!!
****************
አንድ ሰው በፌስቡክ ገጹ ላይ "ኢየሱስ አዳነን እንጂ አላማለደንም" የሚል የስሕተት ትምህርት ፅፎ ስላየኹ ይቺን አጭር ፅሑፍ ለመጻፍ ተነሳሳሁ። ማስረጃችንም ቅዱስ መጽሐፍ ነው።
መልሴን በጥያቄ ልጀምር። " አዳነን እንጂ አላማለደንም" ማለት ምን ማለት ነው? ይህ አባባል "ኢየሱስ ይፈርዳል እንጂ አያማልድም" የሚሉ ሰዎች ለሞገት የሚያቀርቡት ክርክር እንደሆነ እረዳለሁ። ይህ የስነ ሞገት ክርክር ጥያቄ ማስከተሉ የግድ ነው። እርግጥ ነው: ኢየሱስ ፈራጅ አምላክ ነው። ታዲያ ፈራጅ አምላክ ሆኖ ሳለ እኛን የአዳም ልጆች ከዘላለማዊ ቁጣ ለማዳን ለምን ሰው መሆን ይጠበቅበታል? በሰማያዊ አምላካዊ ሥልጣኑ " ድናችኋል" የሚል ቃል ቢሰጥ የሚቃወመው ማነው? መከራና ሞት ወደሚያስከትል ደካማ ሥጋ በመምጣት ሰው መሆን ምን ያደርግለታል?
ያዳነን በፈራጅነቱ እንጂ በምልጃ አይደለም የሚሉ ሰዎች አምላክ ሰው መሆን ሳያስፈልገው በለይኩን ቃሉ ለምን እንዳላደን ወይም ከፈራጅነቱ ምን ጎድሎበት ሰው ወደመሆን እንደወረደ ሊገልፁልን ይገባል።
ከአብ ጋር ለማማለድ ካልሆነ በስተቀር የማዳን ሥልጣን አንሶት ነው ሰው የሆነው? ብለን እንጠይቃለን። ያለምልጃውም አልዳንም: መዳንም የለም እንላለን።
Sunday, November 5, 2017
እውነቱን ፈልፍለን ለማግኘት መጸሐፎቹን እንመርምር!
መነሻ ሃሳብ «ገመና ዘ81ዱ» መጽሐፍ (ጽሑፉ በድጋሚ ተስተካክሎና ረዘም ተደርጎ የቀረበ ስለሆነ በትዕግስት እንዲያነቡ ይጠየቃሉ።)
ሀተታ፤
በኦርቶዶክሳውያን ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ከታች ጀምሮ እስከላይኛው እርከን ድረስ ያለው ሰው ስህተት ይኖርብናል ወይም ልንሳሳት እንችላለን ብሎ የሚያስብ ሰው ማግኘት ከባድ ነው። በክርስቶስ ደም የተመሰረተችው ቤተክርስቲያን ፍጽምትና ንጽሕት መሆኗን በመቀበል መሪውና ተመሪውም በዚያው ዓይን ራሱን እያየ እኛ ፍጹማንና ንጹሐን ነን፣ የስህተት አስተምህሮ አይነካካንም በሚል ሰውኛ ተመካሂነት ራሱን በማስጠለል፤ ስህተትን አምኖ ለመቀበል አይፈልግም። ነገር ግን ትውልዱ አንባቢ፣ ጠያቂ፣ ስንዴውን ከእንክርዳዱ በመለየት ንጹሑን ቃለ እግዚአብሔር መመገብ የሚፈልግ በመሆኑ የስህተት አስተምህሮ አለ፤ በእግዚአብሔር ቃል ሲመረመር አደጋው የከፋ ነው፤ የክፉ መንፈስ አሰራር ወደማወቅ እንዳንደርስ ቃሉን በክሏል በማለት ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተሳስቶ ከሆነም በየዋህነት መንፈስ በማቅናት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ "2000 ሺህ ዘመን የኖረችን ቤተክርስቲያን ዛሬ የተነሱ አፍቃሬ ተሐድሶ መናፍቃን ሊያርሟትና ሊበርዟት ይፈልጋሉ" በማለት መጥፎ ስም በመለጠፍና ምላሽ መስጠት ሲከብዳቸው ሽልማት የሚያሰጥ ቢሆን ኖሮ የስም አጥፊዎችን ዋንጫ ያለተቀናቃኝ የሚቀበሉበትን የተመረጡና ለመስማት የሚዘገንኑ ስድቦች፣ ዛቻዎችና ውግዘቶችን በማዥጎድጎድ የሚጠይቅ እንዲሸማቀቅ፣ አዋቂ ጠያቂ እንዳይኖር አንገት ማስደፋትንና ማስወገዝን እንደበቂ መልስ ሲቆጥሩ ኖረዋል። ዛሬም በዚሁ ግብራቸው አሉ።
በእርግጥ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፍጽምትና ንጽሕት የመሆኗ ምስጢር የመሠረታት በዓለቱ ላይ በፈሰሰው ደሙ ነውና የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ህፀፅ አልባ ናት። ነገር ግን የአክሌሲያ ጉባዔ አባላት የአዳም ልጆች መሆናቸውን በመዘንጋት የቤተክርስቲያኗን መንፈስና ባህርይ እንዳለ ወደሰዋዊ ማንነት በመውሰድ እኛ ፍጹማንና ንጹሐን ነን በማለት ከስህተት አልባ ማንነት ጋር ራስን መቁጠር ትልቁ የስህተት መጀመሪያ ነው። ምክንያቱም ዓለም ላይ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት የተከፋፈሉት የአስተምህሮ ስህተቶች ወደክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሰተት ብሎ በመግባቱ የተነሳ ነው። የሚገርመው ደግሞ ሁሉም አብያተ ክርስቲያን ለራሱ ትክክል ሲሆን ሌላውን እንደስህተተኛ የመቁጠሩ ችግር ስህተቱን እንዳያውቅ አድርጎታል። ሌላውን ስህተተኛ ማለት እኔ ብቻ ትክክል ነኝ ከሚል ነጥብ ይጀምራልና ስህተቱን መቀበል አይችልም።
ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን በቀደመው ዘመን በገላትያ ቤተክርስቲያን የገባውን የስህተት መንፈስ በሐዋርያው ጳውሎስ ሲጠቀስ እናነባለን። የገላትያ ሰዎች በክርስቶስ አዳኝነት አምነው ወደ ሕይወት መንገድ የተመለሱ ሕዝቦች ነበሩ። ፍጽምትና ንጽሕት ወደሆነችው የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተጨምረው የቆዩ ሆነው ሳለ ሰብአዊ ማንነታቸው አሸንፎአቸው ወደስህተት መንገድ በመግባታቸው በሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ የተወቀሱ ሕዝቦች ሆነዋል።
«የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?» ገላ 3፤1
ክርስቶስ ኢየሱስ በፊታቸው የተሰቀለ ሆኖ በእምነት ይታያቸው የነበሩት ሕዝቦች የያዙትን የሕይወት ማንነትና እውነትን በመተው፤ የጠላት አዚም ሸፍኖአቸው ለእውነት እንዳይታዘዙ እስከመሆን መድረሳቸውን እናያለን። ሥራቸውን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የጀመሩ ሆነው ሳለ ቁልቁል ተመልሰው የሥጋን ሃሳብና የስህተትን አስተምህሮ ወደማመን መመለሳቸው በእርግጥም አሳዛኝ የሰው ልጆች ማንነት ማሳያዎች እንደሆኑ የሚያስገነዝበን ነገር ነው።
«እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን?» ገላ 3፤3
እንግዲህ ክርስቲያኖች ፍጽምትና ንጽሕት በሆነች ቤተክርስቲያን ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እምነታቸውን ሊጀምሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ይህንን ፍጽምና ወደአለማወቅ በመመለስም ስህተት ሊታይባቸው እንደሚችል አስረጂ ነው። ምን ጊዜም ቢሆን የስህተት መንፈስ አገልግሎት የሚገባው፤ የእውነቱን መንፈስ ከሰው ልቡና ላይ በመውሰድ ወደስህተት መንገድ በማምራት ስለሆነ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎች ውስጥ የስህተት አስተምህሮ ሊገባ እንደሚችል እናረጋግጣለን።
ብዙዎች የአብያተ ክርስቲያናት አባላት በክርስቶስ ፍቅር ላይ ጸንተው ከመቆም ይልቅ ወደ ምድራውያንና ሰማያውያን ፍጥረቶች ፍቅራቸውን ስለለወጡ የሕይወት መንገድን ስተው መገኘታቸው እውነት ነው።
በሌላ ቦታም እንዲህ የሚል አስረጂ እናገኛለን። ሐዋርያው ጳውሎስ መንፈሳዊ ልጁ የሆነው ጢሞቴዎስን በተሰሎንቄ ለነበረችው ቤተክርስቲያን የላከበት ዋናው ምክንያት ተሰሎንቄዎች ከእምነት ጽናታቸው ወደኋላ እንዳይመለሱ በመንፈስ ያበረታታቸው ዘንድ ነበር። ምክንያቱም ፈታኝ የምንጊዜም አዚሙን የሚያፈሰው የአማኞችን ልቡና በማደንዘዝ ወደ አልሆነ አቅጣጫ በመመለስ ስለሆነ ከዚህ ፈታኝ ይጠበቁ ዘንድ ነበር።
«ስለዚህ እኔ ደግሞ ወደ ፊት እታገሥ ዘንድ ባልተቻለኝ ጊዜ። ፈታኝ ምናልባት ፈትኖአቸዋል ድካማችንም ከንቱ ሆኖአል ብዬ እምነታችሁን ለማወቅ ላክሁ» 1ኛ ተሰ 3፤5
የስህተት መንፈስና አስተምህሮ በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን አጋጥሞ እንደነበር ስንረዳ 2000 ዓመታትን በመጥፋትና በመነሳት፣ በመለያየትና በመታወክ በጦርነትና በመከራ ባሳለፈች ቤተ ክርስቲያን ውስጥማ እንዴት ብዙ አይገኝ? የስህተት አስተምህሮ ማስተካከያ ሚዛኑ የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው።
ከከሳቴ ብርሃን አባ ሰላማ ወዲህ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ተብለው የሚጠሩ መነኮሳት በዋሻና በፍርክታ ገዳም መስርተው ሰው ሁሉ ወደዚያው እንዲከትም ከማድረግ ውጪ ሀገር ላገር ዞረው፤ እንደሐዋርያቱ ወንጌል ላልበራለት ሕዝብ ወንጌልን ስለማስተማራቸው ከአፋዊ ትውፊት በዘለለ መሬት ላይ ያለው እውነታ ያንን አያሳይም። ወንጌል ለሕዝቡ የበራ ቢሆንማ ኖሮ እስከዛሬ በዛፍ ስር ቡና የሚደፉ፤ ደም የሚያፈሱ፤ቅቤ የሚቀቡ፤በጨሌ፤ ቆሌና የቤት ጣጣ አምልኮ ሰርጾባቸው የሚኖሩ ባልኖሩ ነበር። እምነት አለን፤ አውቀናል የሚሉት እንኳን እስከፕሮቴስታንት መምጣት ድረስ መጽሐፍ ቅዱስን አያውቁትም። በመላዋ ኢትዮጵያ ይቅርና ክርስትና አስቀድሞ ገብቷል በተባለባት በትግራይ እንኳን ከአደይ ማርያምና ከአቡነ አረጋዊ በዘለለ የኢየሱስን ወንጌል በደንብ የሚያውቁ ምእመናን ቀርቶ ካህናቱ ቁጥር ስንት ይሆን?
ደረትን ነፍቶ ኦርቶዶክሳዊ ስለመሆን አረጋጋጭ ከሆኑት ከድርሳናት ውጪ መጽሐፍ ቅዱስን ይዞ መገኘት በራሱ ኮትልኳል ወይም ጰንጥጧል የሚያሰኝ በመሆኑ ይዞ መገኘት ቀደም ሲል ያሳፍር ነበር። ይህ በእድሜአችን ያየነው እውነት ነው። አንዳንዶች «ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን ናቸው» የሚለውን ቃል ጠምዝዘው ለራሳቸው መሸንገያነት በመጠቀም አንድም ሐዋርያ ሳይመጣ ያመንን ስለሆንን ቃሉ እኛን ኢትዮጵያውያንን ያመለከታል ለማለት ቢፈልግም የሐዋርያ ወይም የሰባኬ ወንጌል አለመምጣት እንደ ጉዳት እንጂ እንደጠቃሚ ነገር መቁጠር ስንፍናን መደገፍ ነው። መጽሐፍ የሚለን እውነት ይህንን ነው።
«እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?» ሮሜ 10፤14
እንደዚሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እውነተኛ ወንጌል በማስተማርና ሕዝቡን ከክርስቶስ ወንጌል ጋር በማስማማት እንዲኖር ለማድረግ እስከሞት ድረስ ከታገለው ከአባ እስጢፋኖስ ዘጉንዳጉንዶ በስተቀር ግብጻውያን ጳጳሳት ይሁኑ ተከታዮቻቸው ከልምድ አምልኮ በዘለለ የሰሩት የወንጌል አገልግሎት አልነበረም ማለት ይቻላል። ወንጌል በመጽሐፈ ግጻዌ በጥቅስ ደረጃ በየሥርዓተ ቅዳሴው ላይ ተመርጦ ከሚነበብ ውጪ ከተአምረ ማርያምና ከድርሳናት እኩል በመድረክ ተሰብኮ አያውቅም። አቡነ ቴዎፍሎስ የወንጌልን አስፈላጊነት በማመን አዳሪ ት/ቤቶችን በማጠናከር፤ ሰንበት ት/ቤቶች በማቋቋምና በቃለ ዓዋዲ እንዲደነገግ እስኪያደርጉ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት በግእዝ ቀድሰው፤ በግእዝ አንብበው፤ ለዓለመ ዓለም ካሉ በኋላ እግዚኦ መኀረነ ክርስቶስ እንበል 12 ጊዜ ብለው ጣት ከማስቆጠር ባለፈ ህዝቡ ወንጌልን እንዲያውቅ መርሐ ግብር ተቀርጾለት የስብከት መድረክ እንዳልነበረው ጠንቅቀን እናውቃለን።
እንዲያውም ወንጌል እቃ ግምጃ ቤት ገብቶ የሸረሪት፤ የአቧራና የአይጥ ቀለብ ሲሆን በአንጻሩ ልፋፈ ጽድቅ በየአንገት ላይ የሚንጠለጠል ክቡር መጽሐፍ ሆኖ ለዘመናት ኖሯል። ዛሬም እስከመቃብር ድረስ አብሮ የሚወርድ፤ ክቡር አዳኝ መጽሐፍ ሆኖ መቆጠሩን አላቋረጠም። የዲቁናም ይሁን የቅስና ማእርግ የሚሰጠው ሥርዓተ ቅዳሴውንና ኩሳኩሱን ከመልክዓ መልክዑ ጋር መሸምደዱ እንጂ ወንጌልን ተንትኖ ሕይወት የሚገኝበትን ቃል ማስተማር ስለሚችል የሚሰጥ ማእርግ አይደለም።
በዚህም የተነሳ ቀደምት የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዘርዓ ያዕቆብና ተከታዮቹ ፀረ ወንጌል አድናቂዎቹ ባስገቡት የሕጸጽ አስተምህሮ ከዘመን ዘመን ድምፅና ተሰሚነቷ እየቀነሰ ቁጥሯ እየተመናመነ ከመገኘቷ ባሻገር ዛሬም ህፁፀ አእምሮ በተሸከሙ ዘርዓ ያዕቆባውያን የተነሳ ወንጌል ተገቢውን ስፍራ መያዝ አልቻለም። ከዚህ በታች የምናቀርባቸው መጽሐፍ ቅዱሳችን በምንለው መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙ ስህተቶች፤ ነገር ግን እውነት እንደሆኑ ቆጥረን የምንከራከርላቸው ሲሆኑ ችግሩን እንደችግር ያለመቁጠራችን ዋና ምክንያት ከላይ በሐተታ እንደዘረዘርነው አንድም እኛ ፍጽምትና ንጽሕት በሆነች ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ስህተት አልባዎች ነን ከማለት የመነጨ ሰውኛ ማንነትን ካለመቀበል ችግር፤ አለያም- ክርስቶስ ከፊታቸው ተስሎ የነበሩት ገላትያውያን እንደሆኑት የሆነ አዚም አደንዝዞን እውነትን ለመቀበል ባለመፈለግ፤ አለያም ሳያዩ የሚያምኑ……በሚለው የሽንገላ ቃላት ተታለን እውነተኛውን የክርስቶስ ወንጌል የሚሰብክ እንዲኖረን ባለመፈለግ ራሳችንን ስናሞኝ በመኖራችን የተነሳ ነው።
የስህተት ትምህርት አስረጂዎች፤
ብዙውን ጊዜ «ከእውነተኛ የወንጌል አስተማሪዎች እጦት የተነሳ» /ከአስተማሪዎች እጦት የተነሳ አላልኩም/ ሕዝቡ እስካሁን ለወንጌል ቃል አዲስ በመሆኑ አሳማኝ መልስ መስጠት ስለማይችል እንደችግር መፍቻ መፍትሄ የሚጠቀምበት መንገድ በመሳደብ፤በማሳደድ፤በማሽሟጧጥ፤ በመደባደብ ብሎም በመግደል ልዩ ለሆነ ሃሳብ ሁሉ ምላሽ ሲሰጥ ቆይቷል። አሁንም ይህ አድራጎት አላቋረጠም። ከዚህ በታች ለሚቀርቡ አስረጂዎች ምላሽ መስጠት የሚችል አንድም ሰው እንደሌለ እርግጠኞች ስንሆን የሚሳደብ ወይም የሚያንቋሽሽ ክርስቲያን ነን ባይ ፍልፍሎችን ግን በሺህዎች እንጠብቃለን።
ጥያቄ 1፣
ስለታቦተ ጽዮን ትረካ፤
****************
1.1 ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ ታሪክ "በታቦተ ጽዮን ፍለጋ" መጽሐፍ፣
የታቦተ ጽዮን ፍለጋ መጽሐፍ አስተርጓሚ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን የሚናገረው ትረካ «ክብረ ነገሥት» የተባለውን መጽሐፍ ውሸታም ነው ብሎ ከቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ ሲወረውረው እናያለን። ከክብረ ነገሥት በተለየ መልኩ አዲስ ግኝት አለ ብሎ መናገር ወይም ማስተዋወቅ ማለት ክብረ ነገሥት ተአማኒ አይደለም ወይም ላይሆን ይችላል ብሎ መመስከር ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን ትውፊትንና ባህልን፤ ልምድንና አምልኰትን ለይቶ የማያውቅ የጅምላ እምነት አራማጅ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ራሱ እገዛበታለሁ የሚለውን የቤተክርስቲያኒቱን የትውፊት መጽሐፍ ሲሽር ሃይ ባይ ከልካይ የለውም። እንደሚታወቀው ግራሃም ሐንኰክ የተባለ እንግሊዛዊ ምሁር /The sign of the seal/ በሚል ርእስ እ/ኤ/አ በ1992 ዓ/ም ያሳተመውን
መጽሐፍ ይህ የትውፊት ጠበቃ ነኝ የሚለው የጅምላ እምነት አራማጅ ማኅበር፤ /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ/ በሚል ርእስ በጌታቸው ተስፋዬ አስተርጉሞ ያሳተመው መጽሐፍ እንደሚተርከው ታቦተ ጽዮን ወደኢትዮጵያ የመጣችው በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን በልጁ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ ቀዳማዊ ምኒልክ እጅ ሳይሆን በግብጽ በኩል ኤሌፋንታይን አቋርጣ ከዓመታት ቆይታ በኋላ የዓባይን ሸለቆ ተከትላ ቀስ በቀስ በጣና አድርጋ ነው በማለት የመጽሐፉን ትርክት በትርጉም ሥራው አጽድቆ ገበያ ላይ ካዋለው አመታት ተቆጥረዋል። በዚህ መጽሐፍ ጥናት መሠረት ክብረ ነገሥት ውሃ በልቶታል። «ክብረ ነገሥት» ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ የሚተርከው የእነ ቀዳማዊ ምኒልክ ታሪክ በውሸታምነቱ ተመዝግቧል ማለት ነው። ማኅበረ ቅዱሳን የታቦተ ጽዮንን አመጣጥ በግራሃም ሃንኰክ አተራረክ መሠረት የሚያምን ከሆነ የክብረ ነገሥትን ትረካ ዋጋ ቢስ በማድረጉ ለምን? ተብሎ ሊጠይቀው በተገባ ነበር። የሚገርመው አንድም የሊቃውንት ጉባዔ ይሁን የጳጳሳቱ ዓለም የክብረ ነገሥትን ትረካ የሚቃወመውን የማኅበረ ቅዱሳን እትም መጽሐፍ ሲያወግዝ ወይም ታሪካችንን አፋልሷል ሲል አልተሰማም። ሁሉም ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ አንድ የሆነ እምነት የላቸውም ማለት ነው። ከዚህ አንጻር ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ የሚናገር የተለያየ ሃሳብ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ ስላለ እውነተኛው የትኛው እንደሆነ ስለማይታወቅ ሁለቱንም ሃሳብ ላትስማሙ ተስማሙ ብለን ቤተ ክርስቲያኒቱ ለምትቀበለው ወደሌላ ሦስተኛ ተቃራኒ ትረካ አልፈናል።
1.2/ የኢት/ ኦር/ ቤተ ክርስቲያን ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ አልመጣችም የሚልና የምታምነው መጽሐፍም አላት!
ከላይ እንዳስቀመጥነው ማኅበረ ቅዱሳን ክብረ ነገሥትን ውሸታም በማለት በግብጽ በረሃ አድርጋ ነው ታቦተ ጽዮን የመጣችው የሚለውን የግራሃም ሃንኰክን መጽሐፍ ለተከታዮቹ ሲያከፋፍል የምንረዳው ሁለት የተለያየ የአመጣጥ ትረካ መኖሩን ነበር። ይሁን እንጂ ሰማንያ አሀዱ በተባለው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በመጽሐፈ እዝራ ካልዕ ምዕራፍ 1 ቁጥር 54 ላይ እንዲህ በማለት ከላይ የቀረቡትን ሃሳቦች ሁሉ ውድቅ በማድረግ ታቦተ ጽዮን ወደኢትዮጵያ እንደመጣች ሳይሆን ወደባቢሎን መሄዷን በግልጽ ይናገራል።
«እግዚአብሔርን የሚያገለግሉበትን ንዋየ ቅድሳቱንና ጥቃቅኑንና ታላላቁን ዕቃ ሁሉ የእግዚአብሔር ማደሪያ ታቦትንም፤ ከቤተመንግሥት ዕቃ ቤት ያለውን ሣጥኑንም ሁሉ ማርከው ወደ ባቢሎን ወሰዱ» እዝራ ካልዕ 1፤54
ናቡከደነጾር ከ634-562 ዓ/ዓ የነበረ የባቢሎን ንጉሥ ኢየሩሳሌምን ጥሶ፣ ቤተ መቅደሱን አፍርሶ፣ እስራኤላውያንን በባርነት አግዞ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። እንደመጽሐፈ እዝራ አተራረክ ከቤተ መቅደሱ ንዋያተ ቅድሳት መካከል ታቦቱን ጨምሮ ወደባቢሎን ያልተወሰደ እንደሌለ እናነባለን። ይህ መጽሐፍ ታቦተ ጽዮን በግብጽም ሆነ በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል ወደኢትዮጵያ መጥታለች የሚለውን ታሪክ ውድቅ ያደረገ ትርክት ነው። እርስ በእርሳቸው ያልተስማሙት የክብረ ነገሥትና የታቦተ ጽዮንን ፍለጋ መጻሕፍት ትረካ ውድቅ በማድረግ ወደ ባቢሎን ማርኰ ስለመውሰዱ ሰማንያ ወአሀዱ የተባለው መጽሐፍ ቅዱስ አፖክሪፋ መናገሩ ነገሩን ሁሉ መያዣ መጨበጪያ የሌለው አድርጎታል። አሁን እንግዲህ ሊነሳ የተገባው ጥያቄ፤
ሀ/ ክብረ ነገሥት የተባለው መጽሐፍ ታሪክ ትክክል ነው?
ለ/ ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ የተባለው መጽሐፍ ትረካስ ትክክል ነው? ወይስ
ሐ/ ታቦቱ ወደባቢሎን በምርኰ ተወስዷል የሚለው የመጽሐፈ እዝራ ካልዕ ቃል ትክክል ነው ወይ? ብለን እንጠይቃለን። መላሽ የለም እንጂ ጥያቄስ ሞልቷል።
1.3 ታቦቱ ከሰሎሞን ሞት በኋላ እስከ 300 ዓመት ድረስ በኢየሩሳሌም እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
አፖክሪፋ ወይም ቀኖና መሰል መጻሕፍት ወይም ታሪክ ቀመስ መጽሐፍ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተጻፉ ስላልሆኑ ሊሳሳቱ ይችላሉ። የኢት/ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዘመኗ ሁሉ ከሰራችው ስህተት ከሁሉ የከፋው እንደቀኖና መጻሕፍት እንጂ እንደምሉዕ የቤተ ክርስቲያን ዶግማዊ መጻሕፍት ቆጥራቸው የማታውቃቸውን መጻሕፍት በ2000 ዓ/ም ባሳተመችው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በስርዋጽ በማስገባት ዶግማዊ መጻሕፍት አድርጋ መቁጠሯ የቁልቀሊት መሄዷን ማፋጠንዋ እንጂ የቅዱሳት መጻሕፍትን እውነት አይለውጠውም። ቅዱስ አትናቴዎስን አደንቃለሁ፣ እወዳለሁ እያለች በአደባባይ የምትለፍፍ ቤተ ክርስቲያን እነቅዱስ አትናቴዎስ በቅርጣግና ጉባዔ ላይ ካጸደቋቸውና በእስትንፋሰ እግዚአብሔር ተጽፈዋል ከተባሉት 39 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውጪ ለመያዝ ድፍረቱን ከየት አገኘች? ለመሆኑ አትናቴዎስን ከስም ውጪ ተግባሩን ተረክባለች ወይ ብለን እንድንጠይቅ የምንገደደው በእነቅዱስ አትናቴዎስ ቅቡል የተደረጉት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ቁጥር ለመቀበል ለምን አመጸኛ ሆንሽ? እያልን ነው።
ወደጀመርነው ሃሳብ ስንመለስ መጽሐፈ ነገሥት እስከ ባቢሎን ምርኰ ድረስ ታቦቲቱ ኢየሩሳሌም እንደነበረች ይናገራል።
ታቦተ ጽዮን በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ወደኢትዮጵያ መጣች የሚለውን አባባል ውድቅ የሚያደርገው ሌላው አስረጂ ከ300 ዓመት ቆይታ በኋላም በኢዮስያስ ዘመን/ ከ649-609 ዓ/ም/ ኢየሩሳሌም እንደነበረች መጽሐፍ ቅዱስ መናገሩ ነው። ኢዮስያስ ንጉሥ ሰሎሞን ከሞተ ከ300 ዓመት በኋላ በኢየሩሳሌም የነገሠ ንጉሥ ነበር። የሚከተሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የሚነግሩን የሕጉ መጽሐፍ መነበቡን/ 2ኛ ነገ 22፤8/ ንጉሡ የሕጉን መጽሐፍ ሲሰማ ልብሱን መቅደዱን /2ኛ ነገ 22፤11/ የእግዚአብሔር ቤት ይጠገን ዘንድ ማዘዙን /2ኛ ዜና 34፤10/ ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት በመቅደሱ እንዲያኖሩት ማድረጉን መጽሐፍ ቅዱስ እናነባለን።
«እስራኤልንም ሁሉ ያስተምሩ ለነበሩት፥ ለእግዚአብሔርም ለተቀደሱት ሌዋውያን እንዲህ አለ፦ ቅዱሱን ታቦት የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ አኑሩት ከዚህም በኋላ በትከሻችሁ ላይ ሸክም አይሆንባችሁም አሁንም አምላካችሁን እግዚአብሔርንና ሕዝቡን እስራኤልን አገልግሉ» 2ኛ ዜና 35፤3
እንደእኛ እምነት የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ስለማይሳሳት መጽሐፍ ቅዱስን የሚቃወሙ መጻሕፍት ሁሉ ስሁታን ናቸው እንላለን። በዚሁ መሠረት ታቦቲቱ ወደኢትዮጵያ መጥታለች የሚለውን ትረካ ከ300 ዓመት በኋላ እዚያው ኢየሩሳሌም መኖሯን መጽሐፍ ቅዱስ ስለሚነግረን የሰውን ትርክት ትተን የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት እንቀበላለን። ለሰው ሊነገር የሚገባው የማኅበረ ቅዱሳንን? ወይስ የክብረ ነገሥት? ወይስ የእዝራ ካልዕን? ወይስ የመጽሐፈ ነገሥትን እውነት? ሁሉም ታሪኮች ስለአንዱ ታቦት የተለያየ ነገር ያወራሉና ቤተ ክርስቲያን ሆይ የትኛውን ቃል ለሚጠይቁሽ ትናገሪያለሽ? ሌላው ማፈሪያ ትምህርትሽ ደግሞ የሙሴ ሁለት ጽላት ( የማርያምና የሚካኤል) ነው የሚለው ተረትሽ ነው። ዐሥርቱ ትእዛዛት በሁለቱ ሰሌዳ ላይ በቀኝና በግራ ከመጻፉ በስተቀር የሚካኤልና የማርያም የሚባል ጽላት አልነበረም።
"ታደርጉትም ዘንድ ያዘዛችሁን ቃል ኪዳን አሥሩን ቃላት ነገራችሁ፤ በሁለቱም በድንጋይ ጽላቶች ላይ ጻፋቸው። " (ዘዳ 4: 13)
ድንግል ማርያም ከመፈጠሯ ከ2000 ዓመት በፊት ለድንግል ማርያም ጽላት ተቀረላት የሚለው ተረት ገደብ ይበጅለት። ሲጀመር ጽላት የትእዛዛቱ ቃል ማክበሪያ እንጂ የሰው ምስልና የሆነ ያልታወቀ ኅቡዕ ጠልሰም መቅረጫ አልነበረም። ቤተ ክርስቲያኒቷ መጻሕፍትን መርምረው ከሚጠይቋት የምትሰጠው መልስ እውነቱን በመግለፅ ነው ወይስ ተሐድሶ መናፍቅ በሚል የውግዘት ማስፈራሪያ?
2/ ቤተ ክርስቲያን ዲያብሎስን ክብሩ የወደቀው በምንድነው ብላ ታስተምራለች? ዲያብሎስ የወደቀ በትዕቢቱ አምላክ ለመሆን ስለፈለገ ነው ወይስ ለአዳም ስገድ ተብሎ እምቢ በማለቱ ነው?
እንደቤተክርስቲያን አስተምህሮ ሰይጣን እስከነሠራዊቱ የወደቀው በመታበዩ ምክንያት እንደሆነ ነው የሚታመነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ 14፥12
«አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ!»
ይለዋል።
ራሱን የሁሉ ገዢ ለማድረግ ክሳደ ልቡናው ስለተነሳሳ በስሁት መንፈሱ ለውድቀት ተዳርጓል የምትል ቤተክርስቲያን፤ «የለም! ሰይጣን የወደቀው በትእቢቱ መላእክትን እኔ ፈጠርኳችሁ ስላለ ሳይሆን ለአዳም አልሰግድም ስላለ ነው» የሚል አስተምህሮ ይዛ መገኘቷ ነገሩን ሁሉ አስገራሚ ያደርገዋል።
መጽሐፈ መቃብያን ለአዳም ስላልሰገደ ዲያብሎስ ወደቀ ይለናል።
እንደዚህ የሚል ትምህርት በቤተክርስቲያናችን የለም የሚል ሰው ቢኖር ቁጥሩ ከአፖክሪፋ የሆነውንና እንደመጽሐፍ ቅዱስ አንድ ክፍል እንዲቆጠር በግድ የተበየነበትን መጽሐፈ መቃብያንን አያነብም ወይም ስለተሸከመው ብቻ የገባው ይመስለዋል ከማለት ውጪ ምን ልንል እንችላለን?
«የሚጠፉ በኔም የሚስቱ ሰዎች ፈጽመው ይበዙ ዘንድ፤ የአዳምም ልጆች ይጠፉ ዘንድ፤ ይህንን በተናገሩ ጊዜ እኔ ደስ ይለኛል፤ ለሚዋረድልኝ ለአዳም አልሰግድም በማለቴ እግዚአብሔር ስለአባታቸው ስለአዳም ከማዕረጌ አዋርዶኛልና፣ 3ኛ መቃ 1፤15
እንዲሁም በ2ኛ መቃብያን ላይ በተጨማሪ እንዲህ የሚል እናገኛለን።
«ክሳደ ልቡናውን በማጽናትና ራሱን በማኩራት ፈጣሪው ለፈጠረው ለአዳም መስገድን እንቢ እንዳለ»2ኛመቃ 9፤1-3
የጥንቱ ተጨማሪ ቀኖና የአሁኑ የቤተ ክርስቲያኒቱን የዶግማ መጽሐፍ ክብርን የተጎናጸፈው መቃብያን፣ ዲያብሎስ የወደቀው ለአዳም አልሰግድም ብሎ እምቢ በማለቱ ነው ይለናል። ይህ የመቃብያን መጽሐፍ ዲያብሎስ የወደቀው ለአዳም አልሰግድም ብሎ እንጂ ራሱን ከፈጣሪ ጋር አስተያይቶ በትእቢት አይደለም ከሚለው ከቁርአን ጋር ተመሳሳይ ሃሳብ አለው። ሱረቱል አልበቀራህ ወይም የላም ምዕራፍ 2፤ 34
وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ أَبَى وَاسْتَكْبَرَ وَكَانَ مِنَ الْكَافِرِينَ ንባቡም ።
Waith qulna lilmalaikati osjudoo liadama fasajadoo illa ibleesa aba waistakbara wakana mina alkafireena
ወደአማርኛ ሲመለስ፤
«ለመላእክትም ለአዳም ስገዱ ባልን ጊዜ (አስታውስ) ሁሉም ወዲያው ሰገዱ። ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር እምቢ አለ፤ኮራም ከከሀዲዎቹ ሆነ» የቁርአንና የመቃብያን መመገጣጠም የአጋጣሚ ነው ወይስ የክርስትና ቁርጥራጭ ሃሳቦችን ለመሀመድ ያስተማረ የመቃብያን አቀናባሪ ግብፃዊ መነኩሴ ይኖር ይሆን?
(የጥቅሱ መጨረሻ)
ይህንን የመቃብያን መጽሐፍ የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር በእኩል ደረጃ አትቀበለውም። እነሱ ያልተቀበሉትንና ያልፈለጉትን መጽሐፍ ጭነውብን ነው ወይስ ለእኛ ለኢትዮጵያኖች ለብቻችን መቃብያን መጽሐፍ ከሰማይ የወረደልን ሆኖ ይሆን?
ዲያብሎስ ክብሩ የተዋረደው ለአዳም አልሰግድም ብሎ እንቢ ስላለ ነው? ለአዳም እንዲሰግድ የታዘዘውስ መቼ ነው? ይህስ ከየት የተገኘስ አስተምህሮ ነው? ብሎ ለሚጠይቃት አንድ ምስኪን ልጇ ቤተ ክርስቲያን ምን ብላ ትመልስለታለች? መቃብያንን የምትመድበው እስትንፋስ እግዚአብሔር ካለበት መጽሐፍ ወይስ ከህፁፅ አፖክሪፋ?
3/እንጠይቃለን መላሽ ከተገኘ፣ ለሰዎች በቀይና በጥቁር መጻፍን ያስተማረው ማነው?
ለሰዎች በጥቁርና በቀይ ቀለም መጻፍ ያስተማረው አጋንንት ነው ትይናለሽ። ይህንን እንዴት እንመን።
ለዚህ ጥያቄ አዎን አጋንንት ነው ያስተማሩት የሚል ምላሽ ቢሰጥበት ሰዎች መቃወማቸው እርግጥ ነው። ምክንያቱም ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ በጥቁር ወይም በጥቁርና ቀይ መጻሕፍት እያዛነቁ መጻፍ የተለመደ ስለሆነ የጥቁርና ቀይ ቀለማትን ምንጭ ከአጋንንት ጋር ማያያዝን ማንም አሜን ብሎ አይቀበልም። ምክንያቱም የአጋንንት ተማሪና መንገዱንም ተቀባይ ፈቃደኛ ሰው መቼም የእግዚአብሔር መሆን አይችልም። ይሁን እንጂ የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር ውስጥ የማትቆጥረው መጽሐፈ ሄኖክ የተባለው አፖክሪፋ / */በቀይና በጥቁር ቀለም መጻፍ ለሰው ልጆች ያስተማረው አጋንንት ነው ይለናል። መጽሐፈ ሄኖክ 19፤22-24 ይመልከቱ። እንግዲህ ለመልካም ይሁን ለጥፋት በዚህ ዘመን የሰው ልጅ የሚጠቀምበት የመጻፊያ ጥቁርና ቀይ ቀለም ተጠቃሚዎች ሁሉ የአጋንንት ተማሪዎች ናቸው ማለት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ተስፋ ገ/ሥላሴ ዘብሔረ ቡልጋና ትንሣዔ ዘጉባዔ ማተሚያ ቤቶች ይበልጥ የአጋንንትን ትምህርት ፈፃሚዎች ናቸው ማለት ነው።
ይሁን እንጂ የጽሕፈት፤ የፊደላትና የእውቀት ባለቤት የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንጂ አጋንንቶች ሊሆኑ በፍጹም አይችሉም። አጋንንት የበጎ ነገር ጠላቶች እንጂ ለሰው ልጅ የእውቀት ምንጮች የመሆን ተፈጥሮ የላቸውምና። ሰዎች የተሰጣቸውን እውቀት ላልተፈለገ ዓላማ ሊገለገሉበት ይችላሉ እንጂ አጋንንት የአዳምን ልጆች የጽሕፈት እውቀት አስተማሩ ማለት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለውና ሰውን የአጋንንቶች ወዳጅ አድርጎ የሚያቀርብ የክህደት አስተምህሮ ነው። ጥቅመ ሰናኦር ቋንቋን የሰጠ እግዚአብሔር፤ የቋንቋ መጻፊያ ቀለማትን ደግሞ ሰይጣን በመፍጠር በምንም መልኩ የፈጣሪ አጋዥ ሊሆን አይችልም። ቤልሆር ከክርስቶስ ጋር ምንም ኅብረት የለውምና።
መጽሐፍ ቅዱስ ግን እግዚአብሔር ለነቢያቱ ይህን ጻፉ፤ እንዲህም ጻፉበት እያለ የጽሕፈት ባለቤትነቱን ይመሰክርለታል። «ሙሴም የእግዚአብሔርን ቃሎች ጻፈ ማለዳም ተነሣ» ዘጸ 24፤4
«ሙሴም በዚያ ቀን ይህችን መዝሙር ጻፈ፥ ለእስራኤልም ልጆች አስተማራት» ዘዳ 31፤22
«አንድ የመጽሐፍ ክርታስ ውሰድ፥ ለአንተም ከተናገርሁበት ቀን ከኢዮስያስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በእስራኤልና በይሁዳ ላይ በአሕዛብም ሁሉ ላይ የተናገርሁህን ቃል ሁሉ ጻፍበት» ኤር 36፤2
«ዳግመኛም ሌላ ክርታስ ውሰድ፥ የይሁዳም ንጉሥ ኢዮአቄም ባቃጠለው ክርታስ ላይ የነበረውን የቀድሞውን ቃል ሁሉ ጻፍበት» ኤር 36፤28
እጅግ ብዙ አስረጂዎችን ማቅረብ ይቻላል። እውነትን ለመግለጥ በቂ ነውና በሄኖክ ስም ራሱን በእግዚአብሔር ቦታ አስቀምጦ እኔ ለሰው ልጆች እውቀትን የሰጠሁ ነኝ የሚለው ክፉ መንፈስ ግን በእግዚአብሔር ቃል የተሳሳተ አስተምህሮ ነው። አጋንንት ጽሕፈትን እንዴትና መቼ እንዳስተማረ ማስረጃ ከሚያቀርቡ የቅርብ ወዳጆቹ ለመስማት ዝግጁ ነን። ይሁን እንጂ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እጅግ የምታደንቀው የሃይማኖት አባት አትናቴዎስ የማያውቀውንና የኮፕት ቤተክርስቲያንም እንደቅዱሳት መጻሕፍት የማትቀበለውን መጽሐፈ ሄኖክ የመምህርነቱን ስፍራ ለአጋንንት ሰጥቶት ይገኛል። የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንስ ያልተቀበለችው ለምን ይሆን? አጋንንት እስከተጠበቀላቸው የፍርድ ቀን ድረስ የሰው ልጆች ተቃዋሚዎች እንጂ በጎ አድራጊዎች ሊሆኑ አይችሉም። በእርግጥ በቀይና በጥቁር ቀለም ለሚፅፉ፣ ቃል ኪዳን ለገቡ ደብተራና ኅቡእ ስም ደጋሚ ባለተዋርሶ የቤተክርስቲያን ሰዎች በትርፍ ጊዜአቸው ለመስተሐምም፣ ለመቅትል፣ ለመስተአብድ፣ ለመስተባርር፣ ለአምጽኦ ብእሲት፣ ለመስተፋቅር፣ ለመስተጻልእ፣ ለመንድግ ወዘተ ሰይጣናዊ ሥራ ያገለግሉ ይሆናል።
4/ የቤተክርስቲያኒቱ ዲያቆናት ሲኦል ውስጥ ለሚቃጠሉ ሰዎች ምሳሌ ናቸው!
ቤተ ክርስቲያኒቱ ካልጠፋ ምሳሌ ዲያቆናቱን ወደእሳት ከሚወረወሩት መካከል አድርጋቸዋለች። አስፀያፊ ምግባር ያለው በፍርድ ቀን እግዚአብሔር ፊት ሲቆም ጳጳስም ቢሆን ከቅጣት ሊድን አይችልም። ፍርድ በክርስቲያናዊ ማንነት የሚሰጥ ዋጋ እንጂ በማእረግ ሚዛን የሚደረግ ማበላለጥ አይደለም። ለእያንዳንዱ እንደስራው የሚከፍል እግዚአብሔር ዲያቆናትን ብቻ ለይቶ ወደእሳት አይጥልም።
ዲያቆናት ጥርስ ማፋጨትና እሳቱ ወደማይጠፋ ቅጣት ይወርዳሉ የሚል የዉሸት ምሳሌ የመጣው ከየት ነው?
በማቴዎስ ወንጌል ላይ የተሰጣቸውን መክሊት ከሦስተኛው በስተቀር ሌሎቹ አራብተው ለባለቤቱ ዋናውን የመለሱ ሠራተኞችን ማንነት የሚገልጽ ቃል አለ።
(የማቴዎስ ወንጌል 25፤14-30 ያለውን ይመለከቷል)
በቁጥር 15 ላይ «ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ» ይላል። እነዚህ ሰዎች በተሰጣቸው መክሊት አትርፈው ዋናውን ለባለዋናው መመለስ በሚገባቸው ወቅት የተገኘባቸው ትጋት እንዲህ ተቀምጧል።
« አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ። ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ። ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ። ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ»
በዚህ ውስጥ ያተረፉት ሲሾሙና ሲሸለሙ፤ ያላተረፈውን ባለአንድ መክሊት ባሪያ ግን ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት እሳት መጣሉን ቃሉ ይናገራል። ይህንን ቃል አንድምታ በተባለው ትርጉም ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል ተቀምጧል።
ባለአምስት መክሊቱ ሊቀጳጳስ ነው፤ ባለሁለቱ መክሊት በቄስ ይመሰላል። ባለአንድ መክሊቱ ደግሞ በዲያቆን ይመሰላል በማለት እጣ ፋንታውን በቤተክህነቱ የስልጣን እርከን መሠረት ይደለድልና ዲያቆናትን « ወለገብርሰ ዘእኩይ» ተብለው እድል ፈንታቸውም የዘላለም እሳት እንደሆነ በምሳሌ የተቀመጡበት የሥልጣን እርከን ትርጉም በፍጹም ትክክል አይደለም እንላለን። (ወንጌል ቅዱስ ንባቡና ትርጓሜው 1916 ዓ/ም)
በዚህ ዘመን ያለውን ግብር ተመልከተን ብንመዝን በያዙት ሥልጣንና ኃላፊነት ደረጃ ተጠያቂ በመሆን የሚወዳደራቸው የማይኖረው ለራሳቸው የባለአንድ መክሊቱን ሥፍራ ቆርሰው የያዙት ጳጳሳቱ በሆኑ ነበር። ለተልእኰ በመፋጠንና ከሙጋድ ጢስ ጋር ሲታገል የሚኖረውን ዲያቆን የገብር ዘሀካይን ደረጃ በማጎናጸፍ መክሊቱን የቀበረ፣ በተሾመበት ያልታመነ፣ ክፉና ተንኮለኛ አድርጎ መተርጎም የጤነኛ ቤተ ክርስቲያን አስተምሀሮ አይደለም። ስልጣኑም፣ ሚስቱም፣ ቤቱም፣ መኪናውም ብሩም ሁሉን ሰብስቦ ነፍሴ ሆይ እረፊ፣ ደስ ይበልሽ የሚል ጳጳስና አለቃ ባለባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሌሊት ለሰዓታት፣ ቀን ለቅዳሴ የሚባትለውን ዲያቆን ገብርሰ ዘለእኩይ ማለት ተሳልቆ ነው። እንደዚህ ጽሁፍ አቅራቢ "ገብርሰ ዘለእኩይ" የሚባለው በብዙ የተሾመ፣ በብዙ የሚጠበቅበትና በብዙ ሊሰራ ሲገባው ስጋውን በምቾት ያሰረ ሹም ነው።
ስናጠቃልል እስካሁን ለዘረዘርናቸው መጠይቅ መላሾች እውነቱ የቱ ነው? በማለት እንጠይቃለን። ስህተት ካለብን ስለሃይማኖት ከማሽሟጠጥ ይልቅ እውነቱ ሊነገረን ይገባል። ያ መሆን ካልቻለ እውነቱን ለመቀበል ባንፈልገውም እውነት ምን ጊዜም እውነት እንደሆነ ሲኖር ውሸትም ለእውነት ጊዜውን ጠብቆ ሥፍራውን መልቀቁ አይቀርም።
«ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና» 2ኛ ቆሮ 13፤8
Subscribe to:
Posts (Atom)