Monday, August 20, 2012

ሰበር ዜና፤ በማኅበረ ቅዱሳን ትእዛዝ የተሰበሰበው ሲኖዶስ አቡነ ናትናኤልን በዐቃቤ መንበርነት ሾመ።



ሸምቆ ወጊው ማኅበር ብጹእ አቡነ ናትናኤልን ዐቃቤ መንበር ለማድረግ ዛሬ 14/12/ 2004 ዓ/ም  ሲኖዶሱን በጠራው ዘመቻ መሠረት ይህንኑ አስፈጽሞ ዓላማውን አሳክቷል።
ከዓውደ ምሕረት ብሎግ ያገኘነውን ዘገባ እንዳካፈልናችሁ ሁሉ ጉዳዩን በቅርብ ስንከታተል ቆይተን የዛሬው የሲኖዶስ ጉባዔ በማኅበረ ቅዱሳን እቅድ መሠረት ብጹእ አቡነ ናትናኤልን ዐቃቤ መንበር ማስደረግ እንደቻለ ምንጮቻችን አስረድተዋል። ብጹእ አቡነ ናትኤል ከእርጅና የተነሳ ራሳቸውን መቆጣጠር ከማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸው እየታወቀ በአስቸኳይ መምረጥ ያስፈለገው አቅም ኖሯቸው ስራ ይሸፍናሉ ተብሎ ሳይሆን ከሳቸው ጀርባ የሚፈለገውን ስራ ለማከናወን እንዲቻልና የፓትርያርክነቱን ስልጣን በእነ አቡነ ጢሞቴዎስ አቀናባሪነት ወደ አቡነ ማትያስ እንደማቅ እቅድ ደግሞ ወደ አቡነ ሉቃስ ላይ ለመወርወር እቅድ እንደተያዘ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን አስረድተዋል።

የሲኖዶሱ ዋርካ አቡነ ጳውሎስ ከወደቁለት ወዲህ ሸምቆ ወጊው ማኅበር «አልጋ ባልጋ ነው መንገዱ፤ ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰርጎ ለመግባት ሲሄዱ» የሚል መዝሙር መዘመር ከሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት ይቻላል። ተጨማሪ ዘገባ እንደደረሰን እናቀርባለን።