Friday, August 31, 2012

በአሜሪካ ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ለአቡነ ጳውሎስ የሀዘን መግለጫ አወጣ!


ቤተክርስቲያን ለሁለት የመከፈሏ ምክንያት የሥርዓት ለውጥ መከሰቱ እንደሆነ ይታወቃል። ከጊዜው ንፋስ ወዲህና ወዲያ የሚነፍሱ ወገኖች አንደኛውን ወገን የዚያ ሥርዓት ጥገኛ ሲል አንደኛውን ደግሞ የዚህ ቡድን ደጋፊ እያለ የገመድ ጉተታ ዓይነት ሃሳብ በመዘፈቁ የቤተክርስቲያን እርቅና ሰላም በሰመመን ውስጥ ሰጥሟል። አንዳንዶች ደግሞ ፓትርያርክ መርቆሬዎስ ማናቸው? የት ናቸው? በማለት ከ21 ዓመት በኋላ ጥያቄ የሚያቀርብ ጽሁፎቻቸውን በየድረ ገጾቻቸው ላይ ለጥፈዋል። ድምጽዎትን እንስማ፤ እዚህ ቦታ አለሁ በሉን! የሚለው ጥያቄ የፍቅር ከሆነ ይህንን ጥያቄ ለማቅረብ ዛሬ ምን ተገኘ? እንድልንል ያደርገናል። እንዲያውም ወደመንበራቸው ይመለሱ! የሚባሉት እርስዎ ማነዎት? የሚለው ፌዝ መሰል ጥያቄ ግልጽነትና ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ የቤተክርስቲያንን እርቅ ገና ብዙ ፈተና እንደሚጠብቀው ያመላክታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካው ሲኖዶስ በሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ፓትርያርክ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። ለቤተክርስቲያን አንድነትና ሰላም በጋራ እንስራ! የሚል መልእክቱንም አስተላልፏል።
ከቤተ ጳውሎስ ድረ ገጽ ላይ ያገኘነውን መረጃ አካፍለናችኋልና ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን እንዲያነቡ ተጋብዘዋል።


( መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)