Sunday, September 2, 2012

««ኦ አዳም መሬት አንተ ወትገብእ ውስተ መሬት»


አዳም ሆይ አንተ መሬት ነህና ወደ መሬት ትመለሳለህ»
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በተወለዱ በ57 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተው እነሆ ለሳምንት ከዘለቀው የሀዘን ቀናት በኋላ ዛሬ ነሐሴ 27/ 2004 ዓ/ም ስርዓተ ቀብራቸው በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።  በጸሎተ ፍትሃቱና ስርዓተ ቀብሩ ላይ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፤ ሚኒስትሮች፤ ዲፕሎማቶች፤ የመንግሥታት ተወካዮች፤ አምባሳደሮች እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማና ከየክልላቱ የመጡ የሀዘኑ ተካፋዮች በተገኙበት ሌሊት ከጀመረው ጸሎተ ፍትሃት አንስቶ እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ግብዓተ መሬት እስከተፈጸመበት ጊዜ ድረስ ሳያቋርጥ ይጥል የነበረው ከፍተኛ ዝናብ በላያቸው እየወረደ ሙሉ ቀን ውለው እነሆ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አቶ መለስ ዜናዊን ዛሬ ሸኝተዋል።
ደጀ ብርሃን ብሎግ ላዘኑት መጽናናትን፤ ለቤተሰቦቻቸው መረጋጋትን፤ ለሀገሪቱ ደግሞ እግዚአብሔርን ሕዝቡንና ሀገሪቱን የሚወድ መሪ እንዲሰጥልን እንመኛለን።
የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የመጨረሻው የሽኝት ድባብ ምን እንደሚመስል የፎቶ ምስሎችን እንድትመለከቱ እነሆ ግብዣችን ነው።

የቀብር ሽኝት ፎቶዎችን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ