Tuesday, October 15, 2013

«እስኪ በቁጣ ሳይኾን በጥሞና ነገሩን አስተውሉት!»

(ይህ ጽሁፍ በአባ ሰላማ መካነ ድር ላይ አንድ አስተያየት ሰጪ ያቀረበው ሲሆን ስለማኅበረ ቅዱሳን ወቅታዊ ሁኔታ በአጭሩ ስለገለጸ ማቅረቡን ወደነዋል።)

የማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ ትልቁ ችግር ይኽ ይመስለኛል፡፡ አንደኛ፣ የነገረ መለኮት ዕውቀት የላቸውም፡፡ ኹለተኛ፣ ራሳቸውን የቤተክርስቲያን ወታደሮች አድርገው ይስላሉ፡፡ እነርሱ የቤተ ክርስቲያቱ ወታደሮች ናቸው የሚለውን ሐሳብ የተቀበለ ኹሉ ከእነርሱ ጋር የማይተባበር ኹሉ የቤተ ክርስቲያን ጠላት ነው የሚለውን አቀንቅኖት መቀበሉ አይቀርለትም፡፡ “ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ጠበቃ ነው! የቤተ ክርስቲያኒቱ የመከላከያ ሠራዊት ነው!” የሚለው ዐረፍተ ነገር በራሱ የጽንፈኝነት ወጥመድ አለበት፡፡ ምክንያቱም ጠበቃ የምንፈልገው የተጠቂነት ፍርኀት ሲኖርብን ነውና፡፡ ምናልባት ይኽ ነገሮችን ጥቁር ወይም ነጭ ብቻ ናቸው ከሚለው ጽንፈኝነት ከሰፈነበት ባህላችን የተወለደ ይመስለኛል፡፡ አለማወቅ ላይ ፍርኀት ሲጨመርበት ጽንፈኝነት መወለዱ አይቀርም፡፡ (ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን “ምስክሮቼ ናችኹ፡፡” እንጂ “ጠበቆቼ ናችኹ፡፡” አላለም፡፡)
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት አላስተዋለው እንደኾነ እንጃ እንጂ የተናገረው ነገር የማኅበረ ቅዱሳንን ጽንፈኝነት በደንብ ያሳያል፡፡ ማኅበሩንም በመንግሥት በደንብ ሊያስመታው ይችላል፡፡ እኛ የምንለውን የማይሉ፣ በእኛ ቅኝት ያላቀነቀኑ ኹሉ የቤተ ክርስቲያኒቷን ህልውና ለማጥፋት የሚታገሉ ናቸው ከማለት በላይ ጽንፈኝነት አለን? ዳንኤል ይኽን በማለቱ የማኅበሩን እውነተኛ ማንነት ዐደባባይ አውጥቶታል፡፡ ጽንፈኛ ደግሞ ከራሱ ውጪ ማንንም ለመስማት ፈቃደኛ አይደለም፡፡

Friday, October 11, 2013

«የማኅበረ ቅዱሳን ሰዎች የሰሞኑ የአዞ እንባ የማኅበረ ቅዱሳንን ማንነት አይለውጠውም»


አንዳንዶች ማኅበረ ቅዱሳንን ስናነሳ ለምን ተነክቶ በሚል ቁጣ ወባ እንደያዘው ሰው ይንዘፈዘፋሉ። በእርግጥ በማኅበሩ የድንዛዜ መንፈስ የተወጉ ሰዎች እንደዚያ በመሆናቸው ከያዛቸው የወባ ዛር የሚያድን ምሕረት እንዲመጣላቸው እንመኝላቸዋለን እንጂ አንፈርድባቸውም። ሌላው ቀርቶ ማኅበሩ ራሱ ከእውነት ጋር ታርቆና ራሱን በንስሐ ለውጦ ከስለላና ከከሳሽነት ማፊያዊ ሥራ ተላቆ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለራሱ አቋም ከመጠምዘዝ ቢታቀብ ሁላችንም አብረነው በቆምን ነበር።  ከወንጌል እውነት ጋር እየተላተመ በተረት ዋሻ ሥር አናቱን ቀብሮ ከኔ ወዲያ ለቤተ ክርስቲያን ጠበቃ የለም ከሚለው ትምክህት ቢወጣ እንዴት ባማረበት ነበር። ዳሩ ግን ማኅበረ ቅዱሳን ገና ከመሠረቱ የቆመበት የህልውናው መንፈስ በደምና በማስመሰል በመሆኑ ከዚያ አቋሙ ፈቀቅ ይላል ተብሎ አይታሰብም። ጉዳዩ የታጠቀው የእልህና የበቀል መንፈስ እስኪያጠፋው ድረስ አይለቀውምና ሄዶ ሄዶ መጨረሻው እስከዚያው ድረስ መሆኑን ደጋግመን ስንለው ቆይተናል። ያ ሰዓት የደረሰበት መሆኑን ያሸተተው ይህ ማኅበር በቀንደኛ ሰዎቹ በኩል የአዞ እንባውን ማፍሰስ ጀምሯል።

 ከማኅበሩ ቀንደኛና ተላላኪ ሰዎቹ መካከል ታደሰ ወርቁ፤ ዳንኤል ክብረት፤አባ ኃይለማርያም( የጵጵስና ተስፈኛው)፤ ሐራ ዘተዋሕዶና አንድ አድርገን ብሎጎች የመሳሰሉት ሁሉ እየተቀባበሉ የቃጠሎው እሳት የደረሰባቸው ያህል የአድኑን ጩኸታቸውን ሲያሰሙ እያየን ነው። የሁሉም ጩኸት በአጭር ቃል ሲገለጽ በክርስትና አክራሪነት ቦታ የለውም ወይም ለማኅበረ ቅዱሳን ይህንን የመሳሰለ ስም ሊጣበቅበት ተገቢ አይደለም የሚል ድምጸትን የያዘ ሆኖ አግኝተናል። ይሁን እንጂ ሰዎቹ በገደል ማሚቱ ድምጻቸው እየተቀባበሉ እውነታውን ለማዳፈን ቢፈልጉም እውነቱ በማስረጃ ሊገለጥ ይገባዋልና በዚህ ዙሪያ ጥቂት የምንለው አለን። ይከተሉን።

1/ ክርስትና፤

ክርስትና ክርስቶስ የሞተለት እምነት ስለሆነ ከሚሞቱለት በስተቀር ሌሎችን ሊገድሉለት፤ ሊደበድቡበትና ሊያሳድዱበት የተገባው ስላይደለ በእርግጥም ክርስትና ወግ አጥባቂነት፤ አክራሪነትና፤ ጽንፈኝነትና አይመለከተውም።

Sunday, October 6, 2013

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አረፉ!



በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ባሉ የኢትዮጵያ ገዳማት ውስጥ ላለፉት 43 ዓመታት ያህል የኖሩትና በምንኩስና ስማቸው አባ ላዕከ ማርያም በመባል ሲጠሩ ቆይተው በ1985 ዓ/ም  በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አንብሮተ እድ  ኤጲስቆጶስ ሆነው የተሾሙት ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲታገዙ ቆይተው መስከረም 25/ 2005 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የደረሰን ዜና ያስረዳል።
እግዚአብሔር አምላክ የብፁዕነታቸውን ነፍስ በአፀደ ቅዱሳን ያሳርፍልን!!

Saturday, October 5, 2013

የተሻለ የሥራ ጊዜ እንዲሆንልን ጸልዩልን!

 
በሃሳባችሁ፤ በምክራችሁ፤ በእውቀታችሁ፤ በገንቢ አስተያየታችሁ አብራችሁን ለዘለቃችሁ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!
በዘለፋ፤ በፉከራ፤በስድብና በኢ-ክርስቲያናዊ ጽሁፎቻችሁ ለቆያችሁም አስተዋይ ልቡና ይስጣችሁ! ከጥላቻ የራቀ ማንነት እንዲሰጣችሁ እንመኛለን።
አግዚአብሔር ኢትዮጵያችንን ይባርክ
                                    ደጀብርሃን

Tuesday, October 1, 2013

“መስቀል የሚያቃጥል አይደለም”

ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ሲኖዶሱ ውሣኔ ይሰጣል - አቡነ እስጢፋኖስ

(ከደጀ ብርሃን ) ከሰማይ ወረደ ስለተባለው ሰሞነኛ ወሬ ብዙ ብዙ ተብሏል። እንደዚህ ዓይነት ደብተራዊ ቁመራ የተለመደ ሆኖ መታየቱ ለክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ፈላጊነት ጥሩ አጋጣሚ ሆኖ ቀጥሏል። ከሰማይ ለወረደውና ወደሰማይ ለወጣው ለአብ አንድያ ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ በእምነት ልብን አሳልፎ ከመስጠት ይልቅ ከሰማይ ወረደ ለተባለው ቁራጭ ብረት መንጋጋት አሳፋሪም አሳዛኝም ነው።  በእርግጥ ይህ ትውልድ በክርስቶስ አምኖ ልቡን ከማሳረፍ ይልቅ ምልክት እንደሚሻ ዕለት ዕለት እናያለን። ለኃጢአት ሥርየት የተሰነጠቀ ድንጋይ ሲሾልክ፤ የማያየውን የተቀበረ መስቀል ፍለጋ ከወሎ ተራራ ሲንከራተት፤ ይቅርታን ለማግኘት ፍርፋሪና ዳቦ ለመብላት ሲሻማ ማየቱ በክርስቶስ ደም ሥርየትን፤ ንስሐ በመግባት ብቻ ይቅርታን በማግኘት ማረፍ እንዳልቻለ ያሳያል። እረፍት ፍለጋ ምልክት መከተል መፍትሄ አይደለም። በእውነታው  ሰዎቹ እንደሚሉት እግዚአብሔር የተመሳቀለ እንጨትም፤ ብረትም ከሰማይ እርሻ ማሳ ውስጥ በመወርወር ከሰው ልጆች ጋር ይጫወታል ማለት ባህርይውን አለማወቅ ነው። ድንጋይ በመሹለክም፤ ፍርፋሪ በመብላትም፣ ተራራ በመውጣትም፤ ደረትን በመድቃትም ሆነ ጸጉርን በመንጨትም ኃጢአት አይደመሰስም። ሥርየትም አይገኝም። «በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት» እንደሆነ ወንጌል ቢናገርም (ኤፌ 1፤7) ይህንን ወደጎን ገፍቶ በሰንጥቅ ድንጋይ ለመሹለክ መሽቀዳደም ምልክት ፈላጊዎችን ከማብዛቱም በላይ ወንጌል ከስሙና ከንባቡ በስተቀር ለመታወቅ ብዙ እንደሚቀረው ነው።  ከዚህ ዓይነቱ እርባና የለሽ ሰሞነኛ ወሬዎች ውስጥ አንዱ በአዲስ አበባ ከተማ እርሻ ማሳ ውስጥ ወድቆ ተገኘ ስለተባለው መስቀል ብዙ መወራቱ እንዳለ ሆኖ አንስተው፤ ወደመቅደስ አስገብተውታል የሚባሉት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ስለእውነታው በሲኖዶስ ውሳኔ ይሰጥበታል የሚል ዜና ስናነብ እጅጉን ገረመን። ምክንያቱም የነደብተራ ገለፈት ፈጠራ እንደቁም ነገር ሊቆጠር አይገባውም። እንዲያውም እንደዚህ ዓይነቶቹን ጸረ ወንጌል አጭበርባሪዎች ማስወገድ ይገባ ነበር።  ለማንኛውም የአቡኑን የአዲስ አድማስ ዘገባ እንዲያነቡት እነሆ ብለናል።
 
በአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ እስኪያስተላልፍ ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ የአዲስ አበባና የጅማ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አሣሠቡ፡፡ “መስቀል ከሠማይ ወርዷል አልወረደም? ትክክለኛ ነው አይደለም?” የሚለውን ለመመለስ የግድ ቅዱስ ሲኖዶሡ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው፤ ይህን ለማድረግም ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ቋሚ አባላት እንዳሣወቁ ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ እንደተባለው ከሠማይ የወረደ አለመሆኑ ከተረጋገጠም የቤተክርስቲያኒቱ ሃላፊዎች ይጠየቁበታል ብለዋል ብፁዕነታቸው፡፡
መስቀሉ ከሠማይ ወረደ በተባለ በ4ኛው ቀን ነሐሴ 27 ቀን 2005 ከሠአት በኋላ ወደ ስፍራው በማቅናት ተገቢውን የፀሎት ስርአት ከካህናቱና ከቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ጋር ካደረሡ በኋላ መስቀሉን ከወደቀበት መሬት አንስተው ወደ ቤተመቅደሡ እንዲገባ ማድረጋቸውን የገለፁት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፤ መስቀሉ ከሠማይ ስለመውረዱ በአይናችን አይተናል ካሉት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እንደማንኛውም ሠው መስማታቸውን ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
መስቀሉን ከወደቀበት መሬት ያነሱት ብፁዕነታቸው፤ “መስቀሉ ያቃጥላል፤ ብርሃናማ ነፀብራቅ አለው” የሚባለውን አለማስተዋላቸውን ጠቁመው፤ “መስቀል የሚያቃጥል ሣይሆን የድህነት ሃይል ነው ያለው፣ የሚያቃጥል ቢሆን ኖሮ ከመሬት ላይ ማንሣት ባልተቻለ ነበር” ብለዋል፡፡ ወረደ የተባለውን መስቀል ለመመልከት ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ምዕመናን ለምን እንዳይመለከቱት ተከለከለ የሚል ጥያቄ ያነሣንላቸው ብፁዕነታቸው፤ ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶሡ ተጣርቶ ውሣኔ እስኪያገኝ ድረስ ህዝበ ክርስቲያኑ ጉዳዩን በጥሞና እንዲያጤነው በማሠብ ነው” ብለዋል፡፡ (ምንጭ: አዲስ አድማስ)

 

Saturday, September 21, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!


ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ ሳቢያ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው።

(ክፍል አራት)

በክፍል ሦስት ጽሁፋችን በአውሮፓ ሀገራት የእምነት መላሸቅ ስላስከተለውና በለውጡ ገፊ ምክንያትነት በቁጥር አንድ ስለተመዘገበው ነጥብ  ጥቂት ለማለት ሞክረናል። በሥራ ውጥረትና በጊዜ ማጣት የተነሳ የሰው አእምሮ በመባከኑ ሳቢያ በማኅበራዊ ኑሮው ያለውን ግንኙነት አላልቷል። ቤተሰባዊ ፍቅሩን የሚያሳልፍበትን ሰዓት አጣቧል። ከፍላጎት ማደግና ከወጪ ዓይነት ንረት ጋር ለመታገል በሚያደርገው ሩጫ የተነሳ ማንነቱን ለዚህ ዓለም ኑሮ አሳልፎ በመስጠቱ ለሰማያዊ እሱነቱ የሚገባውን እሳቤ ሸርሽሮታል። በዚህም የተዳከመ የእምነት ሰው አለያም እምነት ማለት ሰርቶ ኑሮን ማሸነፍ ብቻ ነው ወደሚል እሳቤ ወስዶታል። ከመላው አውሮፓ የክርስቲያን ቁጥር ውስጥ 45% ክርስትናውን ትቶታል ወይም ክዶታል። በፈረንሳይ ብቻ 40% እምነት የለሽ ወደመሆን የወረደው በክፍል ሦስት ያየነው ለለውጡ ገፊ ምክንያት በሆነው አንዱ ነጥብ የተነሳ ነው። ያንንም ምክንያት ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ተነስተን የት ነበርን? የት ደረስን? አሁንስ በምን ሁኔታ ላይ እንገኛለን? አሉታዊ ጎኑን ለማስወገድ የወስድናቸው ርምጃዎች ካሉም ያንን በማንሳት ጥቂት ለመዳሰስ ሞክረን ነበር። በዚህ ጽሁፋችን ደግሞ ሁለተኛውን ምክንያት በማንሳት ጥቂት እንላለን።

2/ ኢንዱስትሪው በየጊዜው በሚፈጥረው ትንግርታዊ እድገትና ጥበብ የሰው ልብ መማረኩ፤ ያልነበሩና የማይታወቁ ልምዶችን፤ ባህሎችንና ሥነ ምግባርን የሚያላሽቁ ክስተቶች መምጣታቸው፤

ኢንዱስትሪው ረጅም የሥራ ጊዜና ኃይል እንደመውሰዱ አእምሮን ሁሉ ለእውቀትና  ለእድገት ሽግግር ጋብዞታል። በዚህም የተነሳ ቴክኖሎጂው መጥቆ ትንግርት እስኪሆን ድረስ ፈጠራና ክሂሎት ተመንድጓል። የመረጃ መረብ መዘርጋት፤ በመረጃ መረብ ላይ የሚተላለፉ የድምጽ፤ የምስል፤ የጽሁፍና የፈጠራ ውጤቶች ሉላዊውን ዓለም እንደማቀራረቡ መጠን የሰውን ሁሉ ልብ ሰርቆታል። ይህ ሰፊና ቁጥጥር የለሽ መረጃ መረብ የሚያስተናግደው ቁም ነገር ብቻ ሳይሆን ጸያፍና ጋጠ ወጥ የሆነው ሁሉ የሚለቀቅበት በመሆኑ የሰው ልብ በሚታይ ነገር እንዲማረክ፤ የማያውቀውን ልምምድ እንዲለማመድ፤ የነበረውን ባህል እንዲያራግፍ፤ ሥነ ምግባሩ እንዲላሽቅና የሥራ ውጥረቱን በሚያባብስ የክዋኔ ሂደት ውስጥ በማስገባቱ የተነሳ መንፈሳዊውን ዓለም በገሃዳዊው ዓለም የደስታም ይሆን የኅሊና ስካር እንዲለውጥ አስገድዶታል። ለልቅ ወሲብ/Pornography/፤ ለግብረ ሰዶም፤ ለአደንቋሪ ዘፈንና ጫጫታ፤ በስፖርት ሽፋን መንፈሳዊ ልብን ለሚሰርቅ የዓይን ጫወታ ስሱዕ መሆን፤ ለዕጽ ተጠቃሚነት፤ ለአስገድዶ መድፈር፤ ለሰው ጉልበት ሽያጭ ወዘተ ድርጊቶች በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ተገዢ እንዲሆን አድርጎታል።

Saturday, September 7, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!!




ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው።
(ክፍል ሦስት) ጳጉሜን 2/2005 ዓ/ም በክፍል ሁለት ጽሁፋችን ለአውሮፓው የኢኮኖሚ ለውጥ እድገትና ለአዲሱ የእምነት ይትበሃል ተግዳሮቶች ገፊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ በጥቂቱ ለመጥቀስ ሞክረናል። ይህ የአዲስ ለውጥ ገፊ ምክንያት አውሮፓን ወደእምነት የለሽነትና የሥነ ምግባር ልሽቀት ቁልቁል እያወረደ መገኘቱን እንደመነሻ በመውሰድ የሀገራችንን አንዳንድ ክስተቶች እንድንመለከትበት መፈለጋችንን በመጠቆም ስድስት ነጥቦችንን አቅርበናል። ዛሬም በዚህ ክፍል ነጥቦቹን በመዘርዘር ለውጥ ሊያስከትል የሚችለውን ተግዳሮት ለመቃኘት ቅድሚያ ለውጥ አምጪ ቁጥር አንድ ገፊ ምክንያቱን አቅርበን እንመለከታለን።
1/ የኢንዱስትሪው አብዮት በሚፈልገው የሰው አቅምና በሚወስደው ረጅም የሥራ ጊዜ ሳቢያ የክርስቲያኖች አእምሮ ያለእረፍት መባከኑ፤ ኢትዮጵያ የሉላዊው ዓለም ባመጣው ቅርርቦሽ፤ ጥንት ትኖርበት ከነበረው በራሷ ዛቢያ ላይ ብቻ ከመሽከርከር ጡዘት ወጥታ ለመቀላቀል በመቻልዋ የእድገትና የልማት ጎዳና ላይ መገኘቷ እውነት ነው። በምን ያህል ደረጃ አደገች? በምን ዓይነት ሁኔታ ለማች? የሚለውን ቀመር ለጊዜው ይቆየንና ሉላዊው ዓለም በሚያስገድዳት የመኖርና ያለመኖር የለውጥ ህግጋት ግዴታ የተነሳ ካንቀላፋችበት ተነስታ ለመራመድ በምታደርገው መታተር ለእድገትና ለልማት ለውጥ ያላት ጉዞ የሚታይና የሚዳሰስ እንደመሆኑ መጠን በዚህ አስገዳጅ ለውጥ የተነሳ ዜጋ ሁሉ ለመሥራት ሲባትል ይታያል። የገጠር ልማት ጥረትና የኢንዱስትሪ እድገት ለውጥ የሰውን ጊዜ፤ አቅምና ሃሳብ በመውሰዱ ምክንያት ጊዜ ለመግደል በሚል ፈሊጥ እንደበርጩማ እግርን አንፈራጦ ወግ የሚጠርቅበት ዘመን አብቅቶ በመሥራት ጥሪት የሚቋጥርበት፤ ራሱን ለማሸነፍ የሚወጣ የሚወርድበት ሁኔታ ውስጥ ይገኛል። በባህርና በየብስ እስከመሰደድ የሚደርሰው የኑሮ ተግዳሮትን ለመጋፈጥ እንጂ ሽርሽር ስላማረው አይደለም። የኑሮው ውድነት የሚፈጥረውን ጫና ለመቋቋም የሚደረገው ትግል፤  እያደገ የሚመጣውን ፍላጎት ለማሟላት ብዙ መሥራት የግድ በመሆኑ፤ እቅድንና ዕለታዊ ኑሮን ለማሳካት ማለትም የዕለት ጉርስ፤ ልብስና መጠለያን፤ የትምህርት፤ የጤና፤ የመጓጓዣ ወዘተ ለኑሮ አስፈላጊ እሴቶችን ለማግኘት ማንኛውም ሰው ባይፈልግም በግድ ወደሥራ እንዲገባ መገደዱ እርግጥ ነው።  የትም ውለውና ዞረው የመሶብ እንጀራ አጥፎ መብላት አይቻልም።የሰው ቁጥር መጨመርና የዕለታዊ ፍላጎቶች ግኝት ከባድ መሆን በሚፈጥሩት የአካልና የሥነ ልቡና ትግል የተነሳ ይህንን ለማሟላት ብዙ መሥራት፤ ብዙ መጣር ግድ ብሏል። በዚህ ላይ የኢንዱስትሪው እድገት የሚጠይቀው የስራ ጊዜና የሚፈልገው የሰው አቅም ማንኛውንም ሰው ያለዕረፍት ወይም በዕረፍት ውስጥም ሆኖ ሳለ አእምሮው እንዲባክን አድርገውታል።

Tuesday, August 27, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!




ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው!
ክፍል ሁለት / ነሐሴ 21/ 2005/

በክፍል አንድ ጽሁፋችን ስለለውጥና የለውጥ አስተሳሰብ ጥቂት ለማለት ሞክረን ነበር። ጊዜውን ጠብቆ በመጣው ለውጥ ሳቢያ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስላቋቋመችው የለውጥ ማስታገሻ መንገድና ስለኢየሱሳውያን/ JESUIT/ አመሰራረት መንስዔም በመጠኑ አስቃኝተናል። ስለጀስዊትስ ዓላማና ግብ በዝርዝር እዚህ ላይ እንዳንሄድ የተነሳንበት ርእስ መሠረተ ሃሳብ ይገድበናልና ትተነዋል። አንባቢዎቻችን ተጨማሪ መረጃ ያገኙ ዘንድ በዚህ ሊንክ እንዲገቡ እንጠቁማለን።/http://www.biblebelievers.org.au/jesuits.htm የጀስዊትስ መመሥረት የአዲስ አስተሳሰብና የለውጥ እንቅስቃሴን ባያቆምም የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን ከመፈራረስ በተወሰነ መልኩ አግዟታል። ወደማትፈልገውና ወዳላሳበችው የለውጥ መንገድ እንድትንሸራተት ያስገደዳት ሲሆን የነበራትን የሮማን ህግና ደንብ በየሀገራቱ ውስጥ ከመትከል ይልቅ የየሀገራቱን ባህልና ወግ ከካቶሊክ አመለካከት ጋር እያስማማች ለመጓዝ ረድቷታል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ውስጥ አብዛኛው ሕዝብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ እንደመሆኑ መጠን የኢትዮጵያ ካቶሊክም ኢትዮጵያዊ ካቶሊክ እንዲመስል እንጂ ቫቲካናዊ ካቶሊክ እንዲመስል ስለማይጠበቅበት ማንኛውም የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግልባጭ ነው። ታንዛንያ ስንሄድ ደግሞ ታንዛንያዊ ቋንቋ፤ ባህልና ወግን ይከተላል። ሌላ ቋንቋ፤ ባህልና ሥርዓት አምጥቶ ከመጫን ይልቅ ሕዝቡ በሚኖርበት ቋንቋ፤ ባህልና ሥርዓት ሲያስተምሩት ውጤታማ መሆኑ አይጠረጠርም። ሐዋርያው ጳውሎስም ያደረገው እንዲሁ ነበር። ያልተገረዘ ወደ መገረዝ አይሂድ ማለቱ ወንጌል ማለት አይሁዳዊውን ሥርዓት በሌላ ሕዝብ ላይ በመጫን የሚፈጸም እንዳልሆነ መግለጡ ነበር። እንኳን ግእዝን አማርኛን በውል ለማይሰማ ለሸኮ መዠንገር ሕዝብ ሄደህ የያሬድ የቅዳሴ ዜማ ነው ብለህ ብትጮህለት ለምሥጋናህ እንዴት አሜን ሊል ይችላል? ክርስትና የሰዎችን ቁጥር የማብዛት ጉዳይ ባይሆንም ወንጌል ያልደረሳቸውን ለማዳረስ ትክክለኛው መንገድ እኛ የምንኖርበትን ሥርዓትና ሕግ በማያውቀው ሌላ ሕዝብ ላይ የመጫን ጉዳይ ሳይሆን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወታችን መድኃኒት መሆኑን ከማስተማር ባለፈ አሳማ በመብላትና ባለመብላት የማትገኘውን የጽድቅ መንገድ በላተኛውን በመከልከል ሊሆን አይችልም።
በዚህ አንጻር የካቶሊክ ተገዳዳሪ ሆኖ ለመጣው አዲስ የፕሮቴስታንት ዓለም ያልተፈለገውን የለውጥ መንገድ ለመጀመር ምክንያት ሆኗል። በ 12ኛው ክ/ዘመን መገባደጃ ላይ ካቶሊክ የፈጠረችውን የመካነ ንሥሐ/ purgatory/ ጽንሰ ሃሳብ የግድ ህግ እንደሆነ ማስተማርን ለመተው ተገዳለች። ኃጥእ ሰው ንስሐ ሳይገባ ከሞተ፤ የንስሐ ቦታ በሰማይ አለው የሚለው ጸረ ወንጌል አስተሳሰብ በአዲስ ለውጥ እንቅስቃሴ ተቀባይነቱን አጥቷል። በእርግጥ ይህ አስተምህሮ ዛሬም ሳይጠፋ ተጠብቆ በሀገራችን ይገኛል።  መጽሐፈ ግንዘት «እምድኅረ ሞቱ ለሰብእ አልቦቱ ንስሐ» ሰው ከሞተ በኋላ የንስሐ ጊዜ የለውም» ቢልም ፍታትና ተስካር ንስሐ ሳይገባ የሞተውን ሰው ሥርየት ለማሰጠት የሚደረገው ሥርዓት አሁን ድረስ አለ። በካቶሊክ አስተምህሮ ላይ ከተነሳው የለውጥ ጥያቄ አንዱ ይህ ነበር።

Thursday, August 22, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!

ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው!

ክፍል አንድ፤

ለውጥና የለውጥ አስተሳሰብ
ለውጥ የሂደት ውጤት ነው። ስለወደድነው አይመጣም፤ ስለጠላነው አይቀርም። አንዳንዶች ለውጥን ለማስቀረት ይታገላሉ፤ ወይም በእነሱ ትግል የሚቀር ይመስላቸዋል። የለውጥ ህግጋት ግን አይቀሬ መሆኑን ስለሚያሳይ ይዘገይ እንደሆን እንጂ ያ የተፈራው ለውጥ እንደሚሆን አድርገው ለመቀበል ካልፈለጉት እንደማይሆን ሆኖ ይመጣል። በዚህ ምድር ላይ ባለበት ችክ ብሎ የኖረ ነገር የለም። ድንጋይ እንኳን ተፈረካክሶ አፈር ይሆናል። ፀሐይም በጭለማ ትጋረዳለች። በጋም በክረምት ይቀየራል። ብሉይም በሐዲስ ተሽሯል። ከእስራኤል ዘሥጋ ይልቅ እስራኤል ዘነፍስ የጸጋ ፍሰት ደርሶታል።በመወለድና በመሞት፤በመምጣትና በመሄድ፤ በመፈጠርና በማለፍ መካከልም የለውጥ ሕግጋት አለ። እግዚአብሔር ነገሮችን በጊዜ ዑደት ውስጥ እንዲያልፉ አድርጎ ፈጠረ እንጂ ባለበት ቆሞ እንዲቀር ያደረገው አንዳች ነገር የለም። ሌላው ቀርቶ ያለንባት ሰማይና ምድር እንኳን በአዲስ ሰማይና ምድር ትለወጣለች። መቼም የማይለወጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ዘመን የማይቆጠርለትና የማይለወጥ እሱ ብቻ ስለሆነ ነብዩ ዳዊት እንዲህ አለ።
«አንተ ግን ያው አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም» መዝ 102፤27      
  የሀገራችን ገበሬ ክረምት ከመድረሱ አስቀድሞ የወራቶችን ለውጥ አስልቶ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ መጻዒውን ጊዜ ይጠባበቃል። ዘመኑን ጠብቆ በሚመላለሰው ለውጥ ውስጥ ራሱን አስማምቶና ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ ቅድመ ዝግጅቱን በየተራ ካልፈጸመ በስተቀር የበጋው በክረምት መለወጥ በራሱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖውን አሳርፎ ያልፋል።    በሰለጠነው  ዓለም ያሉ ምሁራን በማይቀረው የለውጥ ሂደት የተነሳ ስለለውጥ ያላቸው ግንዛቤ ትልቅ ስለሆነ ሥራቸውን ከለውጥ ጠቀሜታና ተግዳሮት አንጻር ቅድመ ምልከታ በማድረግ ለምላሹ አስቀድመው ይዘጋጃሉ።                                                                                                                                    
 

Thursday, August 15, 2013

ለአቡነ ገብርኤል ጥሪ የሀዋሳ ምእመናንና የሰ/ት/ቤት ወጣቶች ምላሽ ሰጡ!

«እስከ ጥቁር ዉሃ ሄዶ የተቀበለ  ሕዝብ እስከ ጥቁር ውሃ ተሰደደ» (ደጀ ብርሃን)

 /ምንጭ፦dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com/
 በሀዋሳ በግፍ የተሰደዱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ብፁዕ አቡነ ገብርኤል "ኑ ልጆቼ ወደ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተመለሱ" ሲሉ ላደረጉት ጥሪ ምላሽ መስጠታቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ምዕመናኑ ለአቡነ ገብርኤል በአድራሻ፣ ለ17 የቤተክርስቲያንና መንግሥታዊ ተቋማት ደግሞ በግልባጭ ያሠራጩትን ደብዳቤ በብሎጋችን ፖስት እንድናደርግላቸው ለዝግጅት ክፍላችን በኢሜይል ልከውልናል፡፡ የደብዳቤው ሙሉ ይዘት የሚከተለውን ይመስላል፡፡
ነሐሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም
ለብፁዕ አቡነ ገብርኤል
የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ
ሀዋሳ፣
ጉዳዩ: ̶  "ወደ ቤተክርስቲያን እንድትመለሱ" በማለት ለተጻፈልን ደብዳቤ ምላሽ ስለመስጠት
በቀን 25/1/171/2005 (ቀኑን ከደብዳቤው ላይ ማየት እንደሚቻለው) በቁጥር 1459/171/2005 የተጻፈ ደብዳቤ ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት በሁለት ፖሊሶች እጅ ተልኮልን ወንጌል ከምንማርበት ሥፍራ ተጠርተን መተማመኛ ፈርመን በመቀበል በአንክሮ ተመልክተነዋል፡፡ ቀጥሎም ለምዕመናን ተነቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የጋራ አቋም የተወሰደበት ሲሆን፣ ጥሪ ማድረግዎን በስምንቱም አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ዐውደ ምሕረቶች እንዲነበብ እንዳደረጉት ሁሉ ይህንን የምላሽ ደብዳቤያችንንም  ለሰፊው ምዕመን በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲያስነብቡልን አደራ እንላለን፡፡ የሰጠነውም ምላሽ የሚከተለው ነው፡፡ 
አንደኛ፣ ደብዳቤውን እንደ ወንጀል ክስ መጥሪያ በፖሊስ እጅ መላኩ እና ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪ ከምሽቱ 1፡30 ከሆነ በኋላ መምጣቱ፣ እንዲሁም መተማመኛ ፈርመን እንድንቀበል መደረጉ ከሕግ አንፃር ተገቢ ካለመሆኑም በላይ የጥሪው አካሄድ የፍቅር እንዳልሆነ ተገንዝበናል፡፡ በተጨማሪም ደብዳቤው ቅንነትና እውነት ያለበት ሳይሆን ማስመሰልና ውሸት የተሞላበት ከመሆኑም በላይ እርቅ፣ ሠላምና አንድነትን ከማምጣት ይልቅ ራስን ከሕዝብ (ከታሪክ) ፍርድ ለመከላከልና ለገጽታ ግንባታ (ፕሮፖጋንዳ ፍጆታ) ሲባል ብቻ የተዘጋጀ መሆኑን ተረድተናል፡፡
በደብዳቤው ውስጥ "የተወደዳችሁ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች" የሚል ሐረግ ተደጋግሞ ይታያል፡፡ ልጆቻችሁ እንደሆንን ሲነግሩን ከእርስዎ ሳይሆን ከሌላ አካል የሰማነው ያህል መስሎ ነው የተሰማን፡፡ ምክንያቱም እኛ ልጆችዎ እንደሆንን ባንክድም ከእርስዎ ዘንድ ግን የአባትነት ወግ ፈጽሞ አይተን ስለማናውቅ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የደብዳቤውን ይዘት ስንመረምረው የተረዳነው ነገር ቢኖር ̶ አንዳንዴ በግልጽ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በስውር በሀገረ ስብከታችን የሚካሄዱትን ሕገወጥ ሥራዎች ለመሸፋፈንና "ለምን አሳደዳችኋቸው? ለምን አትመልሷቸውም"? ብሎ ለሚጠይቃችሁ አካል "ይኸው፣ በደብዳቤ ጠርተናቸውም እምቢ ብለውናል" በማለት በብልጣብልጥ አካሄድ ሪከርድ ለማስያዝ እና ወደፊት ለምታደርጉት የተለመደ እንቅስቃሴ ምክንያት ለማመቻቸት መሆኑን ለማወቅ ልዩ ጥበብ አያስፈልገውም፡፡
ጥሪዎ ቅንነት ቢኖረው ኖሮና እኛን "ልጆቻችን" እንዳሉን ሁሉ እርስዎም አባትነትዎን አምነውበት ቢሆን በአባትና በልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ልጅ ቤቱን ለቆ ቢኮበልልና አባትም በበኩሉ የኮበለለው ልጅ ወደ ቤቱ እንዲመለስ ቢፈልግ ደብዳቤ ጽፎ በፖሊስ በኩል መላክ ትክክለኛው መንገድ አለመሆኑን ለእርስዎ መንገር ለእናት ምጥ እንደማስተማር ይቆጠራል፡፡
በተጨማሪም፣ ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተባርረን ከወጣን ሁለት ዓመታት እስኪቆጠሩ ድረስ ከሀገረ ስብከቱ ውጪ ያሉ ካህናትና አገልጋዮች መጥተው ሲባርኩንና ሲያፅናኑን እርስዎና ከእርስዎ ሥር ያሉ አባቶች ግን የጠፉትን በጎች ፍለጋ ሳትወጡ ኖራችሁ፣ ዛሬ ከረፈደና ከመሸ፣ ጉዳዩም ከእጃችሁ ወጥቶ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤትና በቅዱስ ሲኖዶስ ከተያዘ በኋላ ድንገት ይህንን ኦፊሴላዊ ጥሪ ለማድረግ የተገደዳችሁበትን ሚስጥር ስናሸተው ጠረኑ የሚነግረን ሌላ ጉዳይ መሆኑን ነው፡፡ ደብዳቤው ሆን ተብሎ እውነታውን ለማዛባት የተደረጉ ጥረቶች እንዳሉበት ከማሳየቱም በላይ "እንዳያማህ ጥራው፤ እንዳይበላ ግፋው" እንደሚባለው ለይተበሀል ያህል ብቻ የተጻፈ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ሁለተኛ፣ በደብዳቤው የመጀመሪያ መሥመር ላይ፣ "ከቤተክርስቲያን ተባረናል በሚል . . .  እየተሰባሰባችሁ የምትገኙ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች . . . " የሚል ሐረግ ሰፍሯል፡፡ ይህ የሚያሳየን እኛ ተባረናል እንላለን እንጂ እናንተ ማባረራችሁን አምናችሁ ለመቀበል እንደማትፈልጉና ዛሬም እንኳን ፀፀት እንዳልተሰማችሁ ያመለክታል፡፡  ታዲያ ከእናት ቤተክርስቲያናችን ውጪ ለመገኘታችን ምክንያቱ እርስዎ፣ የእርስዎ አስተዳደር እና እርስዎ ያደራጁት ማኅበር ካልሆነ፣ ቤተክርስቲያንና ቅጥሯ አስጠልቶን አካባቢ ለመለወጥና ለሽርሽር የሄድን መስሎዎት ይሆንን? ይሁን እንጂ እንዳባረራችሁን መላው የሀዋሳ ምዕመናን ምሥክር ናቸው፡፡

Tuesday, August 13, 2013

ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን እንድታድስ የተቋቋመ ትምህርት ቤት

                          ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ 
  ከተመሠረተበት እስከ አሁን
  (ክፍል አንድ) www.tehadeso.com
  ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀድሞ መጠሪያው “ከፍተኛ የትምህርት ማዕከል”፣ አሁን ወዳለበት ቦታ ከመዘዋወሩና ደረጃውም ወደ ኮሌጅነት ከፍ ከማለቱ በፊት ትምህርት ማስተማር የጀመረው በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ውስጥ ነበር፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጣልያን ወረራ ምክንያት ሕገ ወጥ የሆነውን ወረራ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማስረዳትና አቤቱታን ለማቅረብ ከሀገር ውጭ ተጉዘው ነበር፡፡  በውጪው ዓለም በስደት በቆዩበት ዓመታት እርሳቸውና አብረዋቸው የተሰደዱ ባለስልጣናት ከጎበኟቸው ልዩ ልዩ ተቋማት መካከል የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን አንዷ በመሆኗ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጥንካሬ ምክንያት ደግሞ መንፈሳዊ የትምህርት ተቋማቶቿ አገልጋዮችን በብቃትና በጥራት እያስተማሩና እያዘጋጁ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አገልግሎት በማሰማራቷ መሆኑን በመገንዘባቸው ይህንንም ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ጋር አገናዝበው ቤተ ክርስቲያን ልትታደስ ይገባታል ብለው በማመናቸው ከስደት እንደተመለሡ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናን የምትሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንዲሆንና ሰባክያንና መምህራን በትምህርተ ወንጌል ዘመኑንና ትውልዱን መዋጀት የሚችሉ እንዲሆኑ፣ እውቀት የበለጠ እንዲስፋፋ ትኩረት በመስጠታቸው፣ በተለይም ካህናት በሕዝቡ ዘንድ ተሰሚነት ስላላቸው እውቀታቸው ከተሻሻለ ለሕዝቡ የተሻለ አገልግሎት ይሰጣሉ ብለው በማሰብ፣ ትምህርት ቤት እስኪዘጋጅ ድረስ እንኳ ሳይጠብቁ ቤተ መንግሥታቸውን (አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ) ትምህርት ቤት አድርገው ተማሪዎችን በመቀበል፣ በቶሎ ደርሰው ሀገርንና ቤተ ክርስቲያንን በበለጠ ያገለግላሉ ተብለው የተገመቱትን ሊቃውንት ሰብስበው መምህር መድበው የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲማሩ አደረጉ፡፡ የዚህን ቋንቋ ትምህርት ቤት ጀምረው እስከ መጨረሻው ከተከታተሉት ሊቃውንት መካከል መምህር መልእክቱ (በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ.አቡነ.ቴዎፍሎስ) ይጠቀሳሉ፡፡

       ከዚህ በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በ1935 ዓ.ም. የቅድስት ሥላሴን መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ሕንጻ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ፤ በ1937 ዓ.ም. በይፋ ተመርቆ ተከፈተ፡፡ በዚያ ወቅት የአስተዳደር ኃላፊነት የተሰጣቸው የሚከተሉት ነበሩ፡-
1.     ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ (በኋላ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ)- ሊቀ መንበር
2.    ሚስተር ሃፍዝ ዳውድ ግብጻዊ- ዳይሬክተር
3.    ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ-  አባል
4.    አለቃ ሐረገ ወይን- አባል
5.    ባላንባራስ ወልደ ሰማዕት- አባል
6.    መ/ር ፌላታያስ ሰማዕት- አባል
7.    መጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል- አባል
የትምህርት ቤቱ መምህራንም፡- ሃፍዝ ዳውድ፣ መ/ር ፌላታዎስ፣ አለቃ መኩሪያ፣ አለቃ ወልደየስ፣ አባ ፍስሐ፣ አባ አሥራት ዘገየ፣ ሊቀ ጠበብት አክሊለ ብርሃን ወልደ ቂርቆስ ይባሉ ነበር፡፡ ለትህምርት ቤቱ በአመራር ደረጃ እና በመምህርነት የተመደቡ በወቅቱ ሀገሪቱ ላይ ዕውቅ ሊቃውንትና ባለ ሥልጣናት መሆናቸው ተቋሙ የታለመለትን ዓላማ ከግብ እንዲያደርስ ከልብ የታሰበበት እንደነበረ በግልጽ ያስረዳል፡፡

Sunday, August 4, 2013

የማኅበረ ቅዱሳን የተሸፈነ ማንነት በአሜሪካ ተገለጠ!



One of his loyal bishop
እንደስንዝሮ ታሪክ ሰኞ ቀን ዩኒቨርስቲ ተረከዝኩ፤ ማክሰኞ ብላቴ ላይ ተወለድኩ፤ ረቡዕ ዕለት በአቡነ ገብርኤል ማኅበረ ቅዱሳን በሚል የክርስትና ስም ተጠመኩ፤ ሐሙስ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ ልሰብር የነገር እንጨት ለቀማ ሄድኩ የሚለው ይህ ማኅበር ብዙዎቹን ለማሰለፍ ቢችልም የስንዝሮ ታሪኩ እየተገለጠና እየተገፈፈ በመታወቅ ላይ ይገኛል። በተለይም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት ይህንን ማኅበር በጭለማ መንፈስ የሚነዳ፤ የክፋት ኃይል አድርጎ በመመልከቱ ደረጃ ትልቅ ግንዛቤ እንዳለ ይታወቃል። ወጣቱ ትውልድም ቢሆን እየዋለ እያደረ የማኅበሩን እንቅስቃሴና እርምጃ ፤ የገንዘብ አቅሙን ማደርጀትና ወደንግዱ ዓለም ጎራ ማለቱን በማየት ከየት ተነስቶ ወደየት? ለመሄድ እንደፈለገ በተፈጠረበት ግርታ የተነሳ ባለበት ቆም ብሎ ለማስተዋል መገደዱን የምናገኛቸው ትዝብቶች ያስረዱናል። አንዳንዶቹም ርቀው ሲያዩት ወርቅ የመሰላቸው ይህ ማኅበር ቢቀርቡት የመዳሪያና የገንዘብ መሸቀጫ ስብስብ መሆኑን ተመልክተው አፍረውበት እርባና እንደሌለው ሲናገሩም ይደመጣል።  ይህ ማኅበር ከራሱ ከንግድ ተቋሙ ኃላፊዎችና የእንደጋሪ ፈረስ ከሚነዱለት ጥቂት ተከታዮቹ በስተቀር እንደመንፈሳዊና ጠቃሚ ማኅበር የመቆጠሩ ነገር እንደገለባ በመቅለል ላይ ይገኛል
በ1950 ዓ/ም የተቋቋመውና  ከሃይማኖት የለሹ የደርግ መንግሥት ጋር በመተባበር የጠቅላይ ቤተክህነት ሹማምንት በ1975 ዓ/ም እንዲፈርስ የኢሠፓአኮ ሠይፍ የመዘዙበት «ሃይማኖተ አበው» የተሰኘውን አንጋፋ ማኅበር ከደርግ ውድቀት በኋላ እንደገና ነፍስ ዘርቶ ሊቋቋም ሲንቀሳቀስ ከእኔ ሌላ ማንንም አልይ የሚለው የብላቴው የወታደሮች ማኅበር፤ ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ ሁለተኛ ጊዜ ሠይፍ አሳርፈውበት ከነአካቴው እንዳይኖር አድርገው አከርካሪውን እንደመቱት የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ከክፋቶቹ ሁሉ የላቀው ክፋት ከእርሱ በስተቀር አንድም ማኅበር ኅልውና አግኝቶ እንዳያንሰራራ በተለጣፊ ጳጳሳቶቹና በአገልጋዮቹ በኩል ማስመታት መቻሉ ነው። እንኳን ማኅበራት ጳጳሳሶቹ እንኳን ከፓትርያርኩና ከፌዴራል ፖሊስ በላይ የሚፈሩት ይህንን ማኅበር መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው። በሹክሹክታ የሚያወሩትን የሚሰማቸው እስኪመስላቸው ድረስ ይህንን ማኅበር እንደሚከተላቸው ጥላ ይከታተለናል ብለው ይንቀጠቀጡለታል። ገሚሶቹም ነውራሞች ሳይወዱ እየሳቁ በታማኝ ሎሌነት ያገለግሉታል።

Monday, July 22, 2013

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጉዞና ልምላሜ የተለየው ዛፍ አንድ ናቸው!

አዲስ አበባ የሀገሪቱ ርእሰ መዲና እንደመሆኗ መጠን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በገንዘብ፤ በባለሙያና በሠራተኛ አቅም ትልቁ ሀገረ ስብከት ነው። በዚህ ሦስት ተቋማዊ አቅም በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ለሌሎች ሀገረ ስብከቶች የሚተርፍ በቂ ኃይል ያለው ሀ/ስብከት ነው። የርእሰ መዲናይቱ ሀ/ስብከት እንደመሆኑ መጠን የተሻለ ሥራ፤ ክፍያና ኑሮ ለማግኘት ከገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን የሚፈልሰው አገልጋይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። የሚያሳዝነው ግን አዲስ አበባ ከተማ ከተኛችበት እየነቃች እዚህም እዚያም ጉች ጉች ብለው የሚታዩት ግንባታዎችና የተዘረጉ መንገዶች ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለውጥ ምን እንደሚመስል ለማየት የሚያስችል ዐይን እንዲኖረው የፈየደለት ነገር አለመኖሩ ነው። የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት አስተዳደር ወደኋላ መሄድ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል። ዛሬም የሚታይበት አንዳች እንቅስቃሴ የለም። ለውጥ የሂደት ክስተታዊ ግዴታ ቢሆንም ይህ አመክንዮ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ለምን እንዳልጎበኘው ግራ ያጋባናል። ምናልባት እንደ ቀንድ አውጣ የዐርባ ዓመት እንቅልፉን አልጨረሰ ይሆን? ጊዜ ደግሞ ታክሲ አይደለም። ጊዜ ሲሄድ ባለበት ከሚቆመው ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በስተቀር።
የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ተቋማዊ የኋሊዮሽ መንገድ ስንገመግም ቤተክርስቲያኒቱ የት እንዳለች ፍንጭ ሊሰጠን ይችላል። እነማን ቤተ ክርስቲያኒቱን እየመሯት እንዳሉ ያመላክተናልም። በሌላ ቋንቋ ቤተ ክርስቲያኒቱን የ40 ዓመት የቀንድ ዐውጣ እንቅልፍ ውስጥ እንደገባች የተቀመጡባት ሰዎች አመራር ይጠቁመናል። ዋልታ የሌለው ጣሪያ በአናቱ ዝናብ ማስገባቱ አይቀርምና ለጣሪያው መበስበስ የአናቱ ክፍተት ምክንያት ከመሆኑ ውጪ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት መበስበስ የላይኛው ጣሪያ የመበስበሱ ምልክት ተደርጎ ቢወሰድ አያስኬደንም ትላላችሁ?
የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን የበሰበሰ ጣሪያ ለመጠጋገን ብዙ ተሞክሯል። መጽሐፉ እንደተናገረው በአሮጌው አቁማዳ ላይ አዲስ ለመጣፍ እየተሞከረ መበጣጠሱን የከፋ አደረገው እንጂ የተቀየረ አንዳች ነገር የለም። በእነ እገሌ ዘመን የነበረው አስተዳደር ጥሩ ነበር እንዳንል የሁሉም ዘመን ችግር በመጠን ከሚበላለጥ በስተቀር በይዘቱ አንድ ነው። በእርግጥ ይዘቱ መጠኑንና ዓይነቱን ጨምሮ ዛሬ ሀ/ስብከት ሳይሆን «ኃላፊነቱ የተወሰነ የነጣቂዎች ማኅበር» ወደመሆን በመሸጋገሩ ከድሮዎቹ አስተዳደር ዛሬ የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱ እውነት ነው። አንዱን ሾሞ አምሮቱ ሲጠረቃ ሌላ ያልጠረቃ በመሾም ችግሩን በማባባስ በኩል ያ! ያልታደለው ሲኖዶስ ለሀ/ስብከቱ ውድቀት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ምክንያቱም ሲኖዶሱ ያልጠረቃውን በጠረቃው አመራር በማለዋወጥ ካልዘሩበት የሚያጭዱ ነጣቂዎችን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በማኅበር አደራጅቶ ባልለቀቃቸውም ነበር። 

ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነን ንቡረ እድ መምህር ገ/ማርያም ገ/ሥላሴ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እያሉ አውድማውን ሳያሄዱ የተመረተውን ዝም ብለው የሚቅሙ አጋሰሶችን አፍ በመዝጋታቸው ብቻ በእህል በሎች ክስ ባላባረሯቸውም ነበር። የሆነው እውነታ ግን ጠርጎ በሎችን መረን ለቆ፤ «ሊሰራ የማይወድ አይብላ» ብለው የታገሉትን ጠንካራ ሰው ባላባረረም ነበር። ድሮስ ጠርጎ በልን ሊታደግ የሚችለው ከጠርጎ በል በቀር ማን ሊሆን ይችላል?
የንቡረ እድ ገ/ማርያም ገ/ሥላሴ ወንጀል የቤተ ክርስቲያኒቱን ሙዳየ ምጽዋት ዘረፋ ማስቆም መቻላቸው ነበር። ከ200 ሺህ ብር በላይ ተቆጥሮ የማያውቀው የመንበረ መንግሥት ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ  ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የተቆጠረው በንቡረ እድ ገ/ማርያም ክትትል መሆኑ ታሪክ መዝግቦታል። የሌሎቹም አድባራት ሙዳየ ምጽዋት ሣጥኖች እየተዘቀዘቁ ከመገልበጥ የተረፉት በኚሁ ሰው አስተዳደር ዘመን ስለመሆኑ ገልባጮቹ ሳይሆን አገልጋይ ካህናቱ የሚናገሩት እውነታ ነው። ምን ያደርጋል ታዲያ? እውነተኛና ሀቀኛ እርሟ የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ንብረ እድ ገ/ማርያምን ከአዲስ አበባ ወደሽሬ  በመወርወር ሲኖዶሱ ቁጭቱን ተወጣባቸው። ገልባጮችንም አስደስቷል። አባ ገ/ማርያም ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት መነሳታቸውን የሰሙ ምሽት ሙዳየ ምጽዋት ገልባጮች ሻምፓኝ ሲራጩ ማደራቸው ተሰምቷል። እንግዲህ ይህ ክፍል ነው በመበደሉ ምክንያት ሲኖዶሱ በነፍሱ የደረሰለት። አሳዛኝ ዘመን?
ዛሬ ደግሞ በፓትርያርክ ማትያስ ምርጫ ላይ የአንበሳውን ድርሻ የወሰዱት አባ እስጢፋኖስ ለፈጸሙት የታማኝነት አገልግሎት ከፓትርያርኩ በገጸበረከትነት የቀረበላቸው ስጦታ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሲሆን በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስነት ሽፋን ተዝቆ የማያልቀውን ካዝና የድርሻቸውን እንዲናኙ  ተመድበው እነሆ ከመነሻው በስመ ሥልጠና ሽፋን ተረክበው እያመሱት ይገኛሉ። የሚያሳዝነው ደግሞ ገና ምኑንም ሳይጀምሩ አባ እስጢፋኖስ አድባራቱን ገንዘብ አዋጡና ወደ ሀገረ ስብከቱ ገቢ አድርጉ እያሉ ሥልጠና በተባለው አሰልቺ መድረክ ላይ ነጋ ጠባ መጮሃቸው ነው። አዋጡ ማለት ምን ማለት ነው? ፐርሰት ክፈሉ ነው? ወይስ የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት የሚጦራቸው ድኩማን አሉት? ጥያቄውን ለአቡኑ እንተውና ከአዋጡ ጭቅጨቃቸው የምንረዳው እውነታ ቢኖር ሀ/ስብከቱ ዛሬም ፈውስ የራቀው መሆኑን ነው። ሥልጠና በተባለው የጩኸት መድረክ ላይ ሥልጠናውን የሚካፈሉት እነዚያው የቤተ ክርስቲያንን ሙዳየ ምጽዋት የሚገለብጡ ሰዎች መሆናቸውን ስናይ አቡኑ አዲስ ነገር መጀመራቸውን በማሳየት በቀደመው ጎዳና ለመሄድ ያቀዱት ስላለመሆኑ የሚያሳምን አንዳች  ሥር ነቀል ተቋማዊ ለውጥ አለመኖሩ ቁልጭ ብሎ ይታየናል።  ስልጠና በተለወጠ ሰውና ለለውጥ በተዘጋጀ አእምሮ ላይ የሚዘራ ዘር እንጂ የለውጥ መንገድ እንቅፋት ሆኖ በቆየና በጨቀየ አእምሮ ላይ ሲሆን ስናይ ረዳት ሊቀጳጳሱ ወይ ስራውን አያውቁትም፤ ወይም ስራው አያውቃቸውም።
 አቡነ ቀውስጦስ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሳሉ በተጠናወታቸው ዘረኝነት የጎጣቸውን ሰዎች እያመጡ ሲሰገስጉና ሲያሳድጉ ንቡረ እድ ገ/ማርያም በሩን ዘግተ አላሳልፍ ስላሏቸው ብቻ በሲኖዶስ ጉባዔ ላይ ከሳሽ ሆነው መገኘታቸውን አንዘነጋውም። ዛሬም አቡነ እስጢፋኖስ የንቡረ እድ ገ/ማርያምን ወደ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነት ዳግም የመመለስ የካህናት ጥያቄ አልቀበልም ያሉት ንቡረ እዱ እጅ ከወርች አስረው ረጅም እጆችን ሁሉ ስለሚያስቆሙ ከወዲሁ የተወሰደ መላ መሆኑ ይገባናል። አቡኑ ሙስናን የሚዋጉ ከሆነ ምነዋ! የሙስናውን በር ድርግም አድርገው የዘጉትን ንቡረ እድ በሥራ አስኪያጅነት ማስቀመጥ ፈሩ? በእርግጥ አቡኑ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሳሉ ጥንቱኑ በሩን የከፈቱት እሳቸው አይደሉ እንዴ? ስለሆነም ሙስናን የመዋጋት ብቃትም፤ ሞራልም የላቸውም። ስልጠና መልካም ቢሆንም ሙስና በስልጠና አይጠፋም። ሙስናን በሚጠየፍና ለመዋጋት በተዘጋጀ አመራር እንጂ በገንዘብ አዋጡ ስልጠና ሊሆን አይችልም። የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤትም ይሁን አድባራቶቹ በእነማንና በተደራጀ አዲስ አመራር ተዋቅሯል?
 ሙስናው ከዐለማውያኑ በዐይነቱ የከፋ ሆኗል። አፍኒንና ፊንሐሶች ተፈልፍለዋል። ሁሉም በዐመጻው ተካክሏል። ጠቅላላው ታማሚ በመሆኑ መድኃኒት የሚሆን ነገር ርቋል። ለዓለም ትተርፍ ዘንድ አደራ የተጣለባት ቤተ ክርስቲያን በባላንጣ ተወራለች።  አሳዛኝ ዘመን!
የሚገርመው ደግሞ ሰሞኑን ከጳጳሱ እግር ከሥር ሥራቸው ቱስ ቱስ የሚሉ የማኅበረ ቅዱሳን አሸርጋጆችን ስንመለከት  በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ እንደፈለጉ ለመፋነን እድል ማግኘታቸው ጠቋሚ ሲሆን የሚፈሩትን ማኅበር ለማገልገል ግንባራቸውን እንደማያጥፉ  የሊቀ ጳጳሱ የቆየ ልምድ ደግሞ ያረጋግጥልናል። ከወዲያ ፓትርያርክ ማትያስ በቀጥታ መስመር በውዳሴና በተጠናው ደካማ ጎን በኩል በለስላሳ ጥበብ ተይዘዋል። ከወዲህ አቡነ እስጢፋኖስ በረዳት ሊቀ ጳጳስነት ተጠፍንገዋል። በመሀከል የሲኖዶስ ጸሐፊው የማቅ ታማኝ አባል አባ ሉቃስ ተቀምጠዋል። ጥሩ የመድረክ አዳማቂ የነበሩት አቡነ ጢሞቴዎስ ለማኅበሩ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ለምርቃት ሳይበቃ በጎዶሎ ቀን ከኮሌጅ ተማሪዎች ጋር ተጋጭተው ከሥፍራ ተወግደዋል።  ያገለገሉትን መለስ ብሎ የማያየው ይህ ማኅበር ከአባ ጢሞቴዎስ ጋር ራሱ ተጣልቶ ከመለያየት የገላገለው የተማሪዎቹ ግርግር ሳያስበው መከሰቱ ነበር። ከጀርባም ሆኖ የተማሪዎቹን ችግር በማራገብ ነዳጅ ያርከፈክፍ የነበረው ይህ እድል ሳያልፈው ለመጠቀም ካለው ፍላጎት የመነጨ ነበር። ያሰበው በተማሪዎቹ ችግር ጀርባ ፍጻሜ አገኘ።  ከዚህ የተነሳ ማኅበሩ በትኩስ በትኩስ ምድብተኞች ለመገልገል እድል ያረግድለታል ወይም  አካሄዱን ያውቅበታል። ይኸው እንደ ሳሙና እየተሙለጨለጨ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከዚህ በፊት ውጥረት ሲበዛበት የዐባይን ቦንድ እገዛለሁ እስከማለት መድረሱ እንደሳሙና በመሙለጭለጭ ላለመያዝ መሄድ የሚችልበት ስልት ረቂቅ መሆኑን ያሳያል።
ከላይ እያልነው እንደመጣነው በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ  ዛሬም አዲስ ለውጥ የለም። በላተኞች ስልጠና እየወሰዱ ከመሆኑ በስተቀር አዲስ የሥራ ኃይል፤ አዲስ የመዋቅር ለውጥ የለም። አሁንም የታመነባቸው፤ የሚታወቁና የተመሰከረላቸው ሰዎች በለውጥ ሂደቱ ውስጥ የሉም። በአምናውና በካቻምናው በሬ አርሶ ምርት መጠበቅ ከቶ እንዴት ይቻላል? ካልዘሩበት ማጨድ ማለት ይህ ነው።
ሁለት ወገኖች ግን ተጠቃሚዎች ይሆናሉ። ሀ/ስብከቱ በፓትርያርክ ማትያስ የተሰጣቸው ሽልማት ሲሆን ከዚህ በሚገኘው ሲሳይ የሚናኙት አዲሱ ሊቀ ጳጳስና ከአባ ጳውሎስ ሞት በኋላ ታማኞቹ ብቻ ቦታ ቦታቸውን የያዙለት ማኅበረ ቅዱሳን ተጠቃሚዎች ናቸው።
ከዚህ በተረፈ ሀ/ስብከቱ ከሕመሙ ይድናል ብለን እንድንጠብቅ የሚያደርገን የሚታይ አዲስ መንፈስ፤ አዲስ መዋቅር፤ አዲስ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት፤ አዲስ የውጤት ምዘና ስልት፤ አዲስ የልማት እቅድ የለም። ካህናቱ ከላይ የሚፈሰውን መመሪያ እንደቧንቧ ከሚጠጣ በስተቀር በሂደቱ ላይ ወሳኝ አካል ተደርጎ አልተወሰደም። ጉዞው ከየት ወደየት? ነው ብንል ከድጡ ወደማጡ ነው መልሳችን። ገንዘብ አዋጡ፤ ገንዘብ አዋጡ! ድሮም ዛሬም ከሀ/ስብከቱ ውስጥ ያልጠፋ የበላዮች ድምጽ አልቀረም። ዛሬ ላይ ይህንን እንደዘገብን አምላክ ቢፈቅድ የዛሬ ዐመትም እንዲሁ የለውጥ ያለህ ብለን እንዘግብበት ይሆናል። የዚያ ሰው ይበለን!

Friday, July 19, 2013

«መጽሐፈ አበው» ስለመነኮሳት ምን አለ?

ምንኩስና ምንድነው? ለመጽደቅስ ጠቃሚ ነው?  የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ስልት ነው? የክብር ወይስ የመከራ፤ የተጋድሎ ወይስ የፍልሰት ጎዳና ነው? ብዙ ሊባልለት የሚችልና ሊባልበት የሚገባ ይህ ሰዋዊ ሥርዓት ቆሜለታለሁ ከሚለው ዓላማ ጋር እየተጣረሰ ዘልቆ በዚህ ዘመን ያለበትን ደረጃ እንድንመለከት «መጽሐፈ አበው» የተባለው ትልቁ መጽሐፍ  በምንኩስና ላይ ካሰፈራቸው ሕግጋት ውስጥ በጥቂቱ ለማቅረብ ወደድን። የግእዙን ትርጉም አንብበው ይህ ሰዋዊ ሥርዓት ዛሬ በሕይወት አለ ወይ? ብለው ራስዎ ይጠይቃሉ።  የሕይወት መንገድ የመሆን፤ አለመሆኑ ጉዳይ ተከድኖ ይቆየንና ምንኩስና ራሱ ተነስቼበታለሁ ከሚለው አቋሙ ጋር ዛሬ ላይ የለም። መነኩሴስ ማነው? «መጽሐፈ አበው» እንዲህ ይናገራል።
መነኮስ ከሀገሩ ወደሌላ ሀገር ይሂድ። በዚያም በዋሻ፤ በኮረብታው፤ በተራራው ይንቀሳቀስ። በረሃብ፤ በብርድ፤ በጥም፤ በመራቆት፤ በድካም፤ በትጋት ይኑር። ልብሱ የከብት ቁርበት፤ የፍየል ቆዳና ለምድ ይሁን። ሥጋ በሕይወት ዘመኑ አይብላ። የዘወትር ምግቡ የበረሃ ጎመን፤ ቅጠልና የዛፎች ፍሬ ብቻ ይሁን። ካገር አገር አይዙር። ወደሠርግ፤ ወደ ድግስ አይግባ። በሕዝብ መካከል የሚኖር መነኮስ ቢኖር እርሱ ውሸታም ነው። የአጋንንት ረድእ፤ አገልጋይ ነው። ወንድ መነኩሴና ሴት መነኩሲት በአንድ ላይ አይኑር፤ ይራቁ። በአንድ ላይ እየኖሩ፤ በአንድ አጸድ እያደሩ ንጽህ እንጠብቃለን ቢሉ ውሸት ነው። ነብርና ፍየል አንድነት ይኖሩ ዘንድ እንዴት ይቻላል? መነኩሴ ማንንም አይማ። ሃሜተኛ ጸሎተኛ አይደለም። አብዝቶ የሚበላ መነኩሴ የትም እንደሚፈነጭ ፈረስ ነው። መነኩሴ በፀሀይ ግባት አንድ ጊዜ ብቻ ይብላ። ወፎች መብል አይተው በወጥመድ ይያዛሉ። ትልቁ አንበሳ በመብል ምክንያት ወጥመድ ውስጥ ይወድቃል። አዳም በመብል ወደቀ። ይሁዳ ከወጡ አጥልቆ በበላ ጊዜ ሰይጣን ገባበት። ሠይጣን መነኮሳትን በመብል ፤በመጠጥ፤ በሃሜት፤ በሳቅና በስካር ያድናቸዋል። ልቅ፤ ልቅ እየጎረሱ፤ የላመ የጣመ እያግበሰበሱ መነኮስ መባል አይገባቸውም። በእንቅልፍ ተውጠው፤ ከጸሎት ተለይተው እንደአዞ ተገልብጠው እንዲተኙ ያደርጋቸዋል። ዘማውያንም ይሆናሉ። ያኔም አጋንንቱ በመነኮሳቱ ላይ ይዘፍናሉ። በእጃቸውም ይጨበጭባሉ። እንደፈረሶች ሰኮና ሆነው ይረግጡአቸዋል። የዓለምን ጣዕም የቀመሱ፤ የወደዱ መነኮሳት የነፍሳቸውን ደዌ ያያሉ። የነፍሳቸውንም መድኃኒት ይተዋሉ። በሕዝባውያን መካከል የሚመላስ መነኮስ  ከቅዱሳን ክብር መድረሻ የለውም። መነኮስ ወደዓለማዊ ችሎት፤ ሸንጎና ፍር አይሂድ።  ምሥክር አይሁን። መነኩሴ ማለት ምዉት ማለት ነውና አይቻለሁ፤ ሰምቻለሁ፤ ዳኝነት አውጡልኝ አይበል። ለሕዝባውያን አበ ነፍስ አይሁን። መነኮስ የሞተ ነውና የሚሰማ ጆሮ፤ የሚናገር አፍ የለውም። ዓለም ውስጥ እየኖረ ዓለምን አሸንፋለሁ ቢል ውሸታም ነው። አትመነው። አፉን፤ ጆሮውንና ዓይኑን የማይጠብቅ መነኩሴ ነፍሱን አያድናትም። መነኮስ እነዚህን ሦስት ሰይፎች ካልታጠቀ መነኮስ አይባልም። የዋህነት፤ ትህትናና ድህነት ናቸው። የዋህነት ከቂም፤ ከበቀል ከጥላቻና ከስጋዊ ነገር ሁሉ መራቅ ነው። ትህትና ራስን ዝቅ ማድረግ ሲሆን ድህነት የኔ የሚለው ሀብትና ገንዘብን ሁሉ መናቅ ናቸው። መነኮስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል። በሕይወት ዘመኑ በእንደዚህ ያልተጠበቀ መነኮስ፤ መነኮስ አይደለም።

Thursday, July 18, 2013

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለምን ተሐድሶ ያስፈልጋታል? ክፍል ሁለት፡-

      
              (www.tehadeso.com)
ላደግንባት፣ ቃሉን ላወቅንባት እና አሁንም እያገለገልንባት ላለችው ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት ሁሉ ዐዲስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል በመደገፍ እንደ ቃሉ የሆነ እና የሰላም አለቃ የሚሰለጥንበት ተሐድሶ እንደሚያስፈልጋት፣ በሙሉ ልባችን እናምናለን፡፡ ቤተ ክርስቲያን ተዘፍቃበት ካለው ሁሉን አቀፍ ችግር ለመውጣት የሚያግዛት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የሚከናወን ተሐድሶ አስፈላጊ ነው፡፡
“…እንደ ምሕረቱ መጠን ለዐዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን..”  የሚለው ዐረፍተ ነገር፣ ተሐድሶ በእግዚአብሔር መንግሥት አስፈላጊው እና ፍሬያማው እውነት እንደሆነ ያሳያል፡፡ የእግዚአብሔር ምሕረት ከፍተኛነት በመንግሥቱ ውስጥ ለሚኖረን ቦታ የሚያበቃን፣ በመንፈስ ቅዱስ በኩል የሆነው መታደስ ነው፡፡ ይህ እውነት ለግለሰብም ለቤተ ክርስቲያንም በእኩልነት ይሠራል፡፡ አንድ ሰው ከጠፋው ማንነቱ ተመልሶ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዜጋ እንዲሆን ከመንፈስ ቅዱስ የሆነው ተሐድሶ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ቤተክርስቲያንም የቀበረችውን እውነት ቆፍራ እንድታወጣ እና ለእግዚአብሔር ሐሳብ እሺ በጄ ብላ እንድትታዘዝ ከመንፈስ ቅዱስ የሆነው ተሐድሶ ያስፈልጋታል፡፡

ባለፈው በክፍል አንድ ጽሑፋችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለምን ተሐድሶ አንደሚያስፈልጋት ሦስት መሠረታዊ ምክንያቶችን አንሥተን ማቅረባችን ይታወሳል፡፡  ዛሬ ደግሞ ቀጣይ ሐሳቦችን እናቀርባለን፡፡

•    የሥጋዊ  አሠራር ሥር መስደድ፡-


በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሰውና መንፈሳዊ አሠራር ከጠፋ ሰነባብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገሮች ሁሉ በጸሎት የእግዚአብሔርን ምሪት በመፈለግ ሳይሆን የሚሠራባት፣ የሰውን ፊት በማየት የሚከናወኑባት የዓለማውያን ሸንጎ ሆናለች፡፡ ከሞላ ጎደል በማንኛውም ጉዳይ ለማለት ይቻላል ቤተ ክርስቲያኗ የእግዚአብሔርን ምሪት ጠይቃ አገልጋዮችዋንና ምእመናኗን አስተባብራ በአንድነት በጸሎት በፊቱ ወድቃ የምትከውናቸው ነገሮች የሏትም፡፡ ይልቁንም በአሠራርዋ ከእሷ የተሻለ እንቅስቃሴ ካለው ከመንግሥት ፖሊሲዎች እና ወቅታዊ አጀንዳዎች በመነሣት እነዚያን አጀንዳዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለማስፈጸም ከመሯሯጥ ያለፈ ሥራ ተሠርቶ አይታወቅም፡፡ መንግሥት “አቅም ግንባታ” ሲል ቤተ ክህነትም አቅም ግንባታ፣ መንግሥት “ደን ልማት” ሲል ቤተ ክርስቲያንም ደን ልማት፣ መንግሥት የፀረ ሙስና ርምጃ ሲወስድ ቤተ ክርስቲያንም ያውም ላትተገብረው ስለ ሙስና ማውራትን እንደ ትልቅ ቁም ነገር ወስዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነ የአሠራርም ሆነ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት ምንም  ዝግጅትና ርምጃ ሳታደርግ የሰሞኑ ነጠላ ዜማዋ አድርገዋለች፡፡
እውነተኛው ባለ ራእይና የምሪት አለቃ እግዚአብሔር ተረስቶ፣ ትልቁ ሕገ መንግሥት መጽሐፍ ቅዱስ ተዘንግቶ “ምን ተባለ” እያሉ ሥራ ለመሥራት መሞከር በእስካሁን እንቀስቃሴዋ እንደታየው የተሻለ ለውጥ አላመጣላትም፡፡ መንግሥት የሚያወጣቸው ሕጎችና አፈጻጸሞች የተሳሳቱ ናቸው ባንልም፣ ቤተ ክርስቲያን ግን በእግዚአብሔር መንግሥት አሠራር ውስጥ የዓለማዊውን መንግሥት አሠራር ሙሉ በሙሉ ያውም ምን እንደሆነ እንኳ ሐሳቡ ሳይገባት ለመፈጸም ከሞከረች የሥጋዊነት መገለጫዋ ነው፡፡
በሌሎችም በቤተ ክርስቲያን በሚሠሩ ሥራዎች፣ የእግዚአብሔርን ቤት እንደ መንደር እድር በዘፈቀደ የመምራት እንቅስቃሴዎች ስለምታደርግ፣ ይበልጥ ከእግዘአብሔር ሐሳብ ሲያርቃት እንጂ ወደ ዘላለማዊ አምላኳ ሲያስጠጋት አላየንም፡፡ የሚደረጉት ማንኛቸውም ነገሮች ሥጋ ሥጋ ከመሽተት ያለፈ አንዳች መንፈሳዊነት አይታዩባቸውም፡፡ ከነጭራሹም መጽሐፍ ቅዱስ ተነብቦ የማይታወቅ እስኪመስል ድረስ ከመንፈስ ቅዱስ የሆነ አሠራር ጠፍቷል፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሲኖዶስ ጉባኤ እንደሚገኝ ለማሳየት  በጉባኤው አንድ ባዶ ወንበር ቢቀመጥም፣ መንፈስ ቅዱስ ከሲኖዶስና ከቤተ ክርስቲያን ሥፍራ ካጣ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ የማናውቃቸውን ብዙ “ቅዱሳትና ቅዱሳን” እንድንቀበል አድርጋ በስማቸው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ስታስገነባላቸው ለመንፈስ ቅዱስ ግን ሥፍራ አልተገኘለትም፤ በርግጥ በሚያምኑበት ልብ ውስጥ ያድራል እንጂ የሰው እጅ በሚሠራው ሕንፃ አይኖርም፡፡
ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ሥጋዊነትም፣ ሕዝቡን ከእግዚአብሔር ቤት ገፍቶ ሲያስወጣው እንጂ ወደ ንጉሥ ክርስቶስ ቤት ሲመልሰው አልታየም፡፡ ያደጉባትን ቤተክርስቲያንንም፣ በዚህ ሥጋዊነትዋ ምክንያት “አይንሽን ለአፈር” እያሉ ጥለዋት የሚሄዱ ምእመናን ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ሥጋዊነትዋን ጥላ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራች ለብዙዎች ፈውስ ትሆን ዘንድ ተሐድሶ ያስፈልጋታልና “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ” እንላለን ፡፡


•    አስተዳደራዊ ብልሽቷ አገልጋዮቿንና ሕዝቧን ስላስጨነቀ


ስለ ኦርቶዶክሳዊቷ ቤተ ክርስቲያናችን ሲነሣ፣ አብሮ ሳይነሣ የማይታለፍ ነገር አስተዳደራዊ ብልሽቷ ነው፡፡ ይህ ርእስ፣ ቤተ ክርስቲያናችን በመንፈስ ቅዱስና በእግዚአብሔር ቃል የተመሠረተ ሁለንተናዊ ተሐድሶ አግኝታ ወደ ጥንተ ቅድስናዋና ክብሯ መመለስ ይገባታል የምንለውን እኛን እና ቤተ ክርስቲያን ከቶውንም ለውጥ አያስፈልጋትም “ስንዱ እመቤት ናት” የሚሉትን ወገኖች ያስማማናል፡፡ አስተዳደራዊ ብልሽቱን ሰዎች የሚያነሡበት መንገድ ይለያይ እንጂ  “የቤተ ክርስቲያኗ ህልውና ያሳስበኛል” የሚል ወገን ሁሉ ያለ ልዩነት የሚያነሣው ርእስ ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያንዋ ከተቋማዊ እንቅስቃሴ ይልቅ የግለሰቦች ጠንካራ እና ደካማ ጎን ተገዢ መሆኗ በርግጥ ያሳስባል፡፡ ባለፈው ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አካባቢ የነበረው የአሠራር ዝርክርክነት ከእሳቸው ጋር ጠቅላይ ቤተክህነቱም የሞተ አስመስሎት እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ በሰው ላይ የተደገፈ አስተዳደራዊ ሥርዓት ፍጻሜው ይሄ ነው ለማለት፣ የብፁዕነታቸውን እንደ ምሣሌ አነሣን እንጂ፣ ከእሳቸው በፊት የነበሩትም አሁንም ያሉት ፓትርያርኮች አሠራር ተመሳሳይ ነው፡፡ በዙርያቸው የሚሰበሰቡ ሰዎችም እነርሱ የሚፈልጉት እስከተሳካ ድረስ ለሌላ ነገር ግድ የሚላቸው አይደሉም፡፡
የደብር አስተደደር ሹመት እንኳ በጥንት ዘመን ከነበረው አውቀት ተኮር ሹመት፣ አሁን ወደ ዝምድና እና ጉቦ ተኮር ወደ መሆን ተሸጋግሯል፡፡ እንዲህ ያለው ሹመት፣ አንድን የደብር አስተዳዳሪ፣ በደብሩ ውስጥ ከሚገኙት በእውቀት ሻል ካሉ አገልጋዮች ይቅርና ከአንድ ዲያቆን ጋር እንኳ የሚስተካከል  ክብር ስለማያሰጠው መናናቁና ጥላቸው፣ ቡድናዊነቱና ወገንተኝነቱ ሥር የሰደደ ነው፡፡ በእውነትና በእውቀት ማስተዳደር ስላልተቻለ፣ ሊቃውንቱ ተገፍተው ጨዋና ወሬ አመላላሹ ተከብሮ እና ተፈርቶ ይገኛል፡፡  የሥራ ድርሻውን የሚያውቅና ሥራውን በአግባቡ የሚሠራ ሰውም ስለጠፋ ምእመኑ የክርስትና ካርድ እንኳ ለማውጣት ጉቦ እየተጠየቀ ይገኛል፡፡ የአገልጋዮች ቅጥር፣ ዝውውር እና የደመወዝ ጭማሪን በተመለከተ ወጥ የሆነ ሕግ ስለሌለ በአስተዳዳሪው እና በሀገረ ስብከት ሹመኞች ይሁንታና ተጠቃሚነት፣ ነገሮች እንደፈለጉ የሚደረጉበት ደብር እጅግ ብዙ ነው፡፡ በብዙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ መሪጌቶች ከዲያቆን ያነሰ ደመወዝ ስለሚከፈላቸው፣ ተስፋ የሚቆርጡበት ሁኔታ የተለመደ ነው፡፡ ከተማ አቀፍ የደመወዝ አከፋፈል እስኬል ስለሌለ የተሻለ ደመወዝ የሚከፍል ደብር ለመቀጠር እና ለመዘዋወር ያለው ሹክቻና የሚጠየቀው መደለያ ገንዘብ ቀላል አይደለም፡፡ ይህ የአስተዳደር ችግር ውጤት ነው፡፡
በአስተዳደር ችግር ውስጥ እንደገና ሊታይ የሚገባው ቤተ ክርስቲያንዋ የፋይናንስ አያያዝ ነው፡፡ ከገንዘብ አሰባሰቡ ጀምሮ በዐፄ ምኒልክ ጊዜ ከነበረው የገንዘብ አስተዳደር የተሻለ ነገር ምንም  የላትም፡፡ በገንዘብ አቆጣጠር ላይ ያለውን አካሄድ ስንመለከተው፣ ለአታላይ በጣም የተመቸ ነው፡፡ ምንም ዐይነት ዘመናዊ የሂሳብ አያያዝ መንገድ የማይታይበት፣ ዘመናዊውን የሂሳብ አያያዝ ዘዴ የተማረ ሰው የማይቀጠርበት፣ የደመ ነፍስ መድረክ ሆናለች፡፡ ሌላው የሂሳብ አያያዙ ከፍተኛው ድክመቷ፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት ተረስቶ  “ወነአምን በአሀቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” የሚለው የአባቶች ትምህርት ተዘንገቶ፣ ደብሮች  እንደ ፌደራል መንግሥት፣ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት የሚፈለግባቸውን ብር ከሰጡ በኋላ፣  ገንዘቡን በገዛ ፈቃዳቸው የፈለጉትን ማድረግ የሚችሉበት መሆኑ ነው፡፡ ገጠር ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በደመወዝና በንዋየ ቅዱሳት እጦት እየተዘጉ በአዲስ አበባ ግን ሰባ እና ሰማንያ ሚሊየን ብር በዝግ አካውንት የሚያስቀምጡ ደብሮች መኖራቸው የተለመደ ነገር ሆኗል፡፡
ቤተ ክርስቲያን አንድ እንደሆነች ከንግግር ባለፈ በቃሉ የሚታመን ከሆነ፣ የኑሮ ድካም ትከሻቸውን አጉቡጧቸው ወደ ከተማ የሚሰደዱትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችን ለመታደግና ባሉበት ቦታ በቂ ገንዘብ ከፍሎ ለማኖር ይቻል ነበር፡፡ ምእመኑ ከቤተ ክርስቲያን የሚፈልገውን አገልግሎት ለማግኘት ሲመጣ ቀድሞ የሚታየው ኪሱ እንጂ ልቡ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የድሆች መጠጊያ መሆንዋ ከቀረ ሰንብቷል፡፡ እንደ መንግሥት ቢሮ  ገንዘብ ያለው ከፍሎ የሚስተናገድባት የሌለው ተገፍቶ የሚወጣባት ቤት መሆንዋ ለብዙዎች የልብ ስብራት ምንጭ አድርጓታል፡፡
እንደዚህም በእጅጉ የሚያሳዝነው የአስተዳደር ብልሹነት መገለጫ በገጠር ያሉ እና ሊዘጉ የተቃረቡ አብያተ ክርስቲያናትን ለሀገረ ስብከት የተመደበባችሁን ብር አልላካችሁም በመባል የሚደርስባቸው ማስፈራራት እና “ቤተክርስቲያኑን እንዘጋዋለን” ቁጣ ነው፡፡ ለእነዚህ የገጠር ካህናት፣ በነጻ የሚያገለግሏት ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊዎች የአባትነት ፍቅርና ምስጋና ማቅረብ ቢያቅታቸው እንኳ የኑሯቸውን ሁኔታ እያወቁ ማስጨነቅ ባልተገባቸው ነበር፡፡ ዲታዎቹን የአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናትን፣ የእስፖንሰር ገንዘብ እየጠየቁ ለቅንጦት ነገሮች ከማዋል፣ በጭንቅ በሬ ሸጠው ዓመታዊ መዋጯቸውን እንዲከፍሉ የሚገደዱትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናት አባቶች መታደግ ይገባ ነበር፡፡
ይህንን የአስተዳደር ብልሹነት በቤተክህነት ሥር የሰደደውን ሙስና ባለፈው ሰኔ 29/2005 ዓ. ም.  ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ምረቃ ላይ መምህር ልዑል የተባሉ ሰው በዘይእሴ ቅኔ እንዲህ ሲሉ ገልጠውታል፡፡
ቤታችን ሆኗል ቤተ ወንበዴ፣ እጅግ ያሣዝናል በእውነት የሚፈጸመው ግፍ ተግባሩ፡፡
ሊቃነ ጳጳሳት ፍቀዱና፣  ቢ. ፒ. አር. ወፀረ- ሙስና ገብተው ይመርምሩ፡፡
ብዙዎች ስላሉ በግል መዝብረው የከበሩ፡፡
ዘረፉኝ እያለች በቀን ምንም ሳይፈሩ፡፡
ሙዳየ ምፅዋት ምስኪን ትጮኻለችና በበሩ
ዘረፉኝ እያለች በቀን ምንም ሳይፈሩ፡፡

እንዲህ ያለውን የውስጥ ብሶት በአደባባይ ሲቀርብ ሰምቶ ከማጨብጨብ እና ይበል ብለናል ከማለት ያለፈ የተደረገ ነገር የለም፡፡
ባለፉት ብዙ ወራት ሊፈታ ያልቻለውና ይልቁንም እየተባባሰ ያለው፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ጉዳይ ሌላው በቤተክርስቲያን የተንሰራፋውን አስተዳደራዊ ችግር አጉልቶ የሚያሳይ ነው፡፡ ተማሪዎች ችግር አለብን ሲሉ ሰምቶ የሚያስተናግድ እና ችግሩን የሚፈታ አባት አልተገኘም፡፡ በየአቅጣጫው ከእውነታ ይልቅ ለሁኔታ እና ለቀረቤታ የሚያደሉ አሠራሮች ቤተክርስቲያኗን ይጎዳል እንጂ አይጠቅምም፡፡ ደቀመዛሙርቱን በግፍ ለማባረርና አስተዳደራዊ ጥያቄያቸውን ላለመመለስ፣ ፖለቲካዊ መልክ እንዳለው በማስመሰል ከመንግሥት ጋር ለማጋጨት በመሪዎች እየተወሰደ ያለው ርምጃ አስተዳደራዊ ብልሽቱን ከማጋለጡም በላይ ጉዳዩን በንቀት እየተመለከቱት መሆኑን ማሳያ ነው፡፡  
ሌላው የአስተዳደር ብልሹነቱ ገጽታ የሆነው በሐዋሳ፣ በክብረ መንግሥት፣ በዲላ፣ በሐረርና በሌሎችም የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት ችግሮች እና የምእመናን መንገላታት ነው፡፡  ለችግሮቹ “ይህ ነው” የሚባል መፍትሔ ሳይሰጠው አሁንም እንደ ቀጠለ መሆኑን ስናስብ በተለይ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ፣ ሲኖዶሱን እየተማጠነ ላለው ሕዝብ በእጅጉ እናዝናለን፡፡ የዚህ ችግር ፈጣሪዎች ከሆኑት መካከል አንዳንዶቹም መንፈስ ቅዱስ ይመራዋል የሚባለው ሲኖዶስ አባላት የሆኑ ጳጳሳት መሆናቸውን ማሰብ ልብን ያደማል፡፡ የመፍትሔ አመንጪ መሆን የሚገባቸው አባቶች የችግሩ ፈጣሪዎችና አባባሾች መሆናቸው የሚያስገርም እውነት ነው፡፡
በቤተ ክርስቲያን ያለው የአስተዳደር በደል እና የሥራ ዝርክርክርነት ከመነገር በላይ ነው፡፡ አገልጋዩም ሆነ ሕዝቡ በቤተ ክርስቲያን ባለው አስተዳደራዊ በደል ተስፋ ቆርጦ እና አዝኖ ይገኛል፡፡ እንዲህ ያለው ችግር በቶሎ መስተካከል ካልቻለ እንደደነበረ በግ እየበረረ የሌሎችን በረት በመሙላት ላይ ያለውን የምእመናን ፍልሰት በእጅጉ ያባብሰዋል፡፡ ከዚህ እና ከሌች አስተዳደራዊ ችግሮች ለወውጣት ተሐድሶ አማራጭ የሌለው መንገድ ነውና ደግመን መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ ልንል እንወዳለን፡፡
ይቀጥላል! …

Friday, July 12, 2013

በቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ ያለው ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል!

ቀደም ሲል ስንል እንደቆየነው ሁሉ አሁንም ደግመን እንለዋለን። የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደራዊና አካዳሚያዊ ችግሮች ይህንን ያህል እንኪያ ሰላንትያ ውስጥ የሚያስገባ አልነበረም። ቤተክርስቲያኒቱ ባላት አቅም፤ የሰጠችውን መክፈልተ ሲሳይ ለተማሪዎቹ በተገቢው መንገድ ማድረስ ለመቻል ባለሙያና ትጉህ አስተዳደር ለማስቀመጥ መሞከር ቀዳሚው ነጥብ ሲሆን፤ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ እንደመሆኑ መጠን ቀሚስ ለባሽ ሳይሆን ራሱን ለውጦ ሌላውን መለወጥ የሚችል የተማረ ኃይል ለማፍራት ደረጃውን የጠበቀ የምሁራን ስታፍ በመመደብ የነገይቱን ቤተ ክርስቲያን ይረከቡ ዘንድ ማስቻል ሁለት የተሰናሰሉ አስፈላጊ ኩነቶች ሆነው ሳሉ የአስተዳደርና ብቃትና አርቆ የማሰብ ርእይ በዞረበት ያልዞረው ቤተ ክህነት ጉዳዩን አጡዞ መውጫ ወደሌለው አዘቅት ውስጥ ኮሌጁን እየወረወረው ይገኛል።
መነሻ ምክንያቶቹም ሁለት ናቸው።
1/ የአባ ጢሞቴዎስ ደካማ አስተዳደርን ለማስወገድና ከእርሳቸው ጋር የተማማሉ መሰሪ የኮሌጁ ሹማምንት የሚፈትሉት ውል የለሽ የነገር ልቃቂት ጋር የፓትርያርክ ማትያስ « ከእርስዎ ጋር ሞቴን ያድርገው » ቃል ኪዳን ላይበጠስ መተሳሰሩ ቀዳሚው ነው።
2/ ከነዚሁ ወሳኝ ከሆኑና ነገር ግን ጉዳዩን እንደናዳ ድንጋይ እያንከባለሉ ተማሪዎቹ ላይ የሚመርጉት ትላልቅ ኃይሎች እንዳሉ ሆነው በተገኘው አጋጣሚና ክፍተት ተጠቅሞ ከኮሌጁ ድኩምና መዝባሪ አስተዳደሮች ጋር በፕሮቴስታንታዊ ተሓድሶ ዜማ እየታገዘ የሚጠላቸውን ሰዎች በመጥረግ ራሱ ባዘጋጃቸው ተላላኪዎች በመተካት የኮሌጁን የመተንፈሻ ሳንባ ለመቆጣጠር የሚፈልገው ያ መሰሪ ማኅበር ባሰማራቸው ጉዳዩ ፈጻሚዎቹ በኩል ከወዲህ ጠርዝ ከተማሪዎቹ ችግር ጋር እንደአዞ እያነባ ከጀርባ ሲጮህ መገኘቱ ነው።
ከእነዚህ ሁለት ስውርና ግልጽ ኃይሎች ማለትም አንዱ የተማሪዎቹን ጩኸት እየጮኸ ከጀርባ ሆኖ ግፋ በለው ቢልም  ሌላኛውን ኃይል የተማሪዎቹን ጩኸት ላለመስማት ምክንያቶችን እየደረደረ እነሆ ወራቶችን አስቆጥሯል። ከዚህ ቀደም እንዳልነው አዲሱ ፓትርያርክም የመጣ ደብዳቤ ከመፈረም ውጪ እርባና የሌለው ሥራ ሳይሰሩ፤ ይባስ ብለው በሰላም ሀገር ኮሌጁ ይዘጋ ወደሚል ምክንያት የለሽ ውሳኔ ደርሰዋል። በጣም አሳዛኝ ነገር ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን በአባ ጢሞቴዎስ እጅ እንዳልበላና እንዳልጠጣ ( ስንት ደብዳቤ እንዳላስፈረማቸው) ዛሬ በማኅበሩ የተሐድሶ ጥቁር ፋይል ላይ የተመዘገቡና አልታዘዝ ያሉትን ሰዎች አባ ጢሞቴዎስ ከጎናቸው ስላቆሙና አባረው ወደማኅበሩ ጊሎቲናዊ ጥርስ ውስጥ ስላላስገቡ ብቻ «ሐራ ተዋሕዶ» በተባለ የመጮኺያ ማሽን በኩል በአባ ጢሞቴዎስ ላይ አንዲት ቅጠል የማይበጥስ እርግማኑን ይወረውራል።
እውነት የአባ ጢሞቴዎስ አስተዳደራዊ ድኩምነትና ግትርነት ለማኅበሩ የታየው ዛሬ ነው? ነፍሳቸውን ይማርና ከአቡነ ጳውሎስ ጋር አባ ጢሞቴዎስ በነገር ሲፋጠጡ፤ ማኅበሩ ለአባ ጢሞቴዎስ እሳቱ፤ ቅባቱ፤ መርዙ፤ ብረቱ እያለ ሲያሞካሽ አልነበረምን? ያንን ሁሉ ዛሬ ምን ውሃ በላው? ነገሩ ወዲህ ነው። ፈረንጆቹ /Use and throw/ ይሉታል። አንዴ ተጠቅመህ ሲያበቃ ወርውረህ መጣል ማለት ነው። አባ ጢሞቴዎስ እኔ ያልኩት እንደሚሉ፤ ግትርነት እንደሚያጠቃቸው፤ ተላላና ተደላይ መሆናቸው የዋለ ያደረ ባህርያቸው ነው። ይሁን እንጂ ማኅበሩ ያስፈልጉት በነበረበት ወቅት አገልግለውታል። ዛሬ ደግሞ አስፈላጊው አይደሉምና ከግዙፉ የተማሪዎቹ ችግር ጀርባ የቀድሞውኑ የምናውቃቸውን አባ ጢሞቴዎስን ይራገማል።
በሌላ መልኩ አዲሱ ፓትርያርክ የቀድሞውን ፓትርያርክ በየሚዲያው ሲያብጠለጥሉ እንዳልነበር ያቺ ታስነቅፍ የነበረችው ሥልጣን ተሽከርክራ እጃቸው ላይ ስትወድቅ ታሪክ ራሱን ይደግማል እንዲሉ ትንሹን የተማሪዎች ችግር መፍታት አቅቷቸው ታንክ የታጠቁ ያህል ቆጥረው ግቢያችን የሆነው ባድመን ልቀቁ የሚል አዋጅ ለማስነገር ሲበቁ ስናይ «ከበሮ በሰው እጅ ሲያዩት ያምር፤ ሲይዙት ይደናገር» የሚለውን ብሂለ አበው አስታወሰን። ለአባ ጢሞቴዎስ የሚከፈል ትንሹ ዋጋ መሆኑ ነው።
ተማሪዎቹም ራሳቸውን ማጥራት የሚገባቸው ማንም አፍና ምላስ ሆኖ የሚጮህላቸው ማኅበርና የማኅበሩ አቀንቃኝ ቀሚስ ለባሽ በመሃከል ተሰግስጎ መኖር እንደሌለበት ነው። ጥያቄያቸው አጭርና ግልጽ ነው። «አስተዳደራዊና የተማሪ ዕለታዊ ኑሮ ይስተካከል» የሚል ብቻ መሆኑን አበክሮ ማስረገጥ ይገባል። ከዚህ ውጪ ቤተ ክርስቲያኒቱ ራሷ መተኪያ የሌላትና ሁሉን የሰበሰበች ማኅበር ሆና ሳለ ሌላ የቀኝ ክንፍ ማኅበር አባል በመሆን ችግሩን የታከከና ለራስ መደላድል ሁኔታዎችን ማጽዳት የሚሉትን አንጥሮ አለመግፋት በራሱ ወንጀልም ኃጢአትም ነው።
ከዚህ የተነሳ ማለት የሚቻለው ነገር ቤተ ክህነቱም ራሱ ገርፎ ራሱ እየጮኸ ነው። ግቢውን ለቃችሁ ውጡልኝ ማለት ምን ማለት ነው? በሌላቸው ውክልናና እውቀት በአንድ በኩል የተሐድሶ አቀንቃኞች በኮሌጁ ተሰግስገዋል እያሉ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ የአስተዳደር በደል ተፈጽሟል በሚል ዲስኩር ከተማሪዎች ጋር የሚጮሁ የሰው አራዊቶች ድምጻቸውን ያቁሙ። እነዚህኞቹም ራሳቸው ገርፈው ራሳቸው የሚጮሁ ቀላማጆች ናቸው።
እኛ የምንለው ተማሪዎቹም መባረር የለባቸውም፤ ማኅበር የሚባል የወፍ ጉንፋን በሽታ ከግቢው ይውጣ! አባ ጢሞቴዎስም ሌላው ቢቀር ዓይናቸው ደክሟልና ከሥራው አሳርፏቸው። በሽታው እንዳይዛመት የማኅበሩ የወፍ ጉንፋን ቫይረስ ያልለከፈው አባት ይሾም። ለዚያውም ካለ!!!  ጅራፎች ሆይ፤ በመከራ በገረፋችሁት ተማሪ ላይ ራሳችሁ ገርፋችሁ፤ራሳችሁ እንደተበደለ ሰው አትጩሁ!!!!!!!!!!

Sunday, July 7, 2013

እነ አርቲስት ጀማነሽ “የቅዱስ ኤልያስ”ን መልዕክት ለፓትሪያሪኩ እንዳናደርስ ተከለከልን አሉ


(አዲስ አድማስ )“የማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” አባላት፤ ከቅዱሳን አባቶች የተላክነውን የቅዱስ ኤልያስን መልዕክት ለአዲሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ እንዳናደርስ ተከለከልን አሉ፡፡ አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን የተካተተችበት መልዕክት አድራሽ ቡድን፤ ባለፈው ማክሰኞ ረፋዱ ላይ መልዕክታቸውን ጋዜጠኞች ባሉበት ለፓትርያርኩ ለማቅረብ ፓትሪያሪኩ ጽ/ቤት በር ላይ ተገኝተው የነበረ ቢሆንም የጥበቃ አባላት “ለማነጋገር ፍቃድ የላችሁም” ብለው መልሰዋቸዋል፡፡ ከማህበሩ አባላት መካከል አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን እና መ/ር ወልደመስቀል ፍቅረማርያም ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ለሁለት ጊዜያት ያህል 4 ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትሪያሪክ ጽ/ቤት በመሄድ ከአባቶች የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ ቢሞክሩም ከጽ/ቤቱ የጥበቃ ሃላፊዎች ማለፍ አልቻሉም።
“በመጀመሪያው ቀን ከማህበረ ስላሴ መልዕክት ይዘን መምጣታችንን ለጥበቃዎች በመንገር ወደ ውስጥ እንድንገባ ከተፈቀደልን በኋላ ሌሎች በግቢ ውስጥ የነበሩ ጥበቃዎች በድጋሚ አስቁመውን ከስላሴ ካቴድራል ማኅበር የመጣችሁ መስሎን ነው እንጂ እናንተ መግባት አትችሉም በማለት ፓትሪያሪኩን እንዳናገኝ ተደርገናል” የሚሉት መ/ር ወልደመስቀል፤ በተለይ አንዲት ሴት የጥበቃ አባል ከአግባብ ውጭ ጀማነሽን እየገፈታተረች እንድትወጣ ማድረጓን ገልፀዋል፡፡ በሚዲያ ሳይቀር ቅዱስ ፓትሪያሪኩ ማንም ሰው ያለከልካይ በአካል መጥቶ ሊያነጋግረኝ ይችላል ያሉትን መነሻ አድርገን በመጀመሪያ ቀን ያለቀጠሮ የሄድን ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ቀጠሮ ለማስያዝ ብንፈልግም የሚያስተናግደን አካል በማጣታችን ለመመለስ ተገደናል የሚሉት መ/ር ወልደመስቀል፤ ጥበቃዎቹ የሄድንበትን ጉዳይ ጠይቀውን ከተረዱ በኋላ ፈጽሞ መግባት አትችሉም፤ ቀጠሮ ማስያዝ ከፈለጋችሁ አንድ እማሆይ አሉ፤ እሣቸውን አነጋግሩ ተባልን፤ የተባሉት ግለሰብ ግን ፍቃድ ወጥተዋል የሚል ምላሽ አገኘን ብለዋል፡፡ “አሁንም ለሶስተኛ ጊዜ ስንሄድ ጥበቃዎቹ ፈጽሞ መግባት አትችሉም፡፡ አካባቢውን ለቃችሁ ሂዱ አሉን” ብለዋል - የማህበሩ አባላት፡፡
ባለፈው ማክሰኞ 10 የሚደርሱ ሴቶችና ወንዶች የማህበሩ መገለጫ የሆነውን ነጭ ባለቀስተ ደመና ጥለት ልብስ ለብሰው ፓትሪያርኩ ጽ/ቤት በሩ ላይ ቆመው ነበር፡፡ የነብዩ ኤልያስ መልዕክት ምንድነው ብለን የጠየቅናት አርቲስት ጀማነሽ ሠለሞን “መልዕክቱ ለፓትሪያሪኩ ስለሆነ እሳቸው ከሰሙ በኋላ ለህዝብ እንድታደርሱ ይነገራችኋል” ብላለች፡፡ የመንበረ ፓትሪያሪክ ልዩ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ አበራ ከአዲስ አድማስ ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ ተጠይቀው “እስካሁን ጥያቄ ያቀረበልን የለም፤ ቤተክርስቲያኒቷ የራሷ የቅሬታ አቀራረብ ሥርዓት አላት፡፡ ለቅሬታም ሆነ ለቡራኬ የሚመጡትን በቀጠሮ እናስተናግዳለን፡፡ እስከ ሀምሌ 21 ቅዱስ ፓትሪያሪኩን በስልክ ለማነጋገር የተያዙ ቀጠሮዎች አሉ” ብለዋል፡፡ ከነብዩ ኤልያስ መልዕክት አለን ያሉት ግለሰቦች “ኦርቶዶክስ” የሚለው ስያሜ “ለተንኮል” የገባ ስለሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ስያሜ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መባሉ ቀርቶ “የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን” መባል አለበት በሚል አላማ እንደሚንቀሳቀሱ ይታወቃል፡፡

Saturday, July 6, 2013

የካህናቱ የ«እናውቃለን» እና «አናውቅም» እውቀት!



ካህናቱ ከተራው ሕዝብ በቃለ እግዚአብሔር የተሻለ እውቀት እንዳላቸው ይታመናል። ይጠበቃልም። ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ መጻሕፍቱ ላይ «እያዩ የማያስተውሉ» ተብሎ የተነገረባቸው ደግሞ እነዚህ የእውቀት ማዕድ ያካፍሉ ዘንድ በክህነት አገልግሎት የተሰለፉትን ሆኖ ስናይ እጅግ ያስገርመናል። ካህናቱ እያዩ የማያስተውሉ ከሆነ የሚመሩት ሕዝብ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም።
አይሁዳውያኑ ካህናትና የመጻሕፍቱ መምህራን ስለብሉያት መጻሕፍት በቂ እውቀት እንዳላቸው ከመገመቱም በላይ ራሳቸውም በቂ እውቀት እንዳላቸው ስለራሳቸው ሲመሰክሩ እናነባለን። ይሁን እንጂ እውቀታቸው ሲመዘን ብዙውን ጊዜ አውቀን ተናገረናል የሚሉት አንደበት እርስ በእርሱ ከመጋጨቱ አልፎ ተርፎም ሰዎቹ ራሳቸውም ጭምር እርስ በእርሳቸው የሚጋጩበትም አጋጣሚ ታይቷል።
ለዚህም ጥሩ ማሳያ የሚሆነን ከላይ በርዕሱ ላይ ያስቀመጥነው ነጥብ ጥሩ መነሻ ይሆነናል። እነዚህ የእውቀት ማዕድ አደላዳዮች እንደሆኑ የሚታሰብላቸው ካህናት በአንድ ወቅት በአንድ ምላስ ሁለት ቃል በመናገር አንዴ «እናውቃለን» ያሉትን አንደበት ሽረው ወዲያው ደግሞ «አናውቅም» በማለት ሲናገሩ እናገኛቸዋለን።
ካህናቱ ይኸንን ቃል የተናገሩት ጌታ ኢየሱስ ከደብረ ዘይት ተራራ መልስ በቤተ መቅደስ ብዙ ካስተማረ በኋላ በድንጋይ ሊወግሩት በፈለጉና በመካከላቸው ተሰውሮ በወጣ ጊዜ ነበር።  ከዚያ አልፎ እንደወጣ ዘመኑን ሁሉ ዓይነ ስውር የነበረና በልመና የሚተዳደር አንድ ሰው ባገኘ ጊዜ «ደቀ መዛሙርቱም መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ወይስ ወላጆቹ? ብለው ጠየቁት» ዮሐ 9፤2
ጌታም ሲመልስ፤ «በራሱም ይሁን በቤተሰዎቹ ኃጢአት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ ይገለጽ ዘንድ» እንደዚያ መሆኑ ከገለጸላቸው በኋላ የመጣበትን የማዳን ስራ በማሳየት በምራቁ ጭቃ ለውሶ ዓይኑን በመቀባትና በሰሊሆም መታጠቢያ በመታጠብ ዓይነ ብርሃኑ እንዲመለስ እንዳደረገለት እናነባለን።
የሚገርመው አስደናቂ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው። ዓይነ ብርሃኑ የጠፋው ይህ ሰው ዓይኑ ከበራለት በኋላ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ከመወለዱ አንስቶ እውር የሆነን ሰው ዓይን ያበራ ሰው ስለመኖሩ እንዳልተሰማ በመሰከረ ጊዜ ካህናቱ በተቃራኒው ሃሳቡን በመቃወም «ይህ ሰው ኃጢአተኛ እንደሆነ እናውቃለን» በማለት የመጀመሪያ ቃለ ጽርፈት ሲሰነዝሩ ታይተዋል። ዮሐ 9፤24
ዓይነ ስውር የነበረው ሰው የተደረገለትን ነገር አድንቆ ለካህናቱ ሲመልስ «ኃጢአተኛ መሆኑን አላውቅም፤ ዕውር እንደ ነበርሁ አሁንም እንዳይ ይህን አንድ ነገር አውቃለሁ አለ» ዮሐ 9፤25
ካህናቱ የማያውቁትን የብርሃን ጌታ እንደሚያውቁት አድርገው በላዩ ላይ የሀሰት አንደበት ሲከፍቱ፤ እውር ሆኖ መወለዱንና አሁን ግን ብርሃን እንደተሰጠው የተግባር ምስክር ሆኖ የራሱን ሕይወት ስለቀየረው ስለኢየሱስ ማንነት ከካህናቱ በተሻለ ማወቅ መቻሉ በእርግጥም አስገራሚ ነገር ነው። ምናልባትም ራሱ ባለቤቱ እንደተናገረው « የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩም እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጣሁ አለ» ያለው ቃል እንደተፈጸመባቸው የሚያስረዳን ነገር ይሆናል። ዓይነ ስውሩ የሥጋ ብርሃንም፤ የልቡና ዓይንም ሲገለጥለት የልቡናቸውን ብርሃን በእውቀት እንደሞሉ የሚያስቡና ዓይነ ሥጋቸውም ከልደታቸው ጀምሮ ምሉዕ እንደሆነ የሚተማመኑት ካህናት ግን በሁለቱም ወገን መጋረዳቸውን አንደበታቸው ያረጋግጣል። ይኸውም ከእናቱ ማኅጸን አንስቶ እውር ሆኖ የተወለደን ሰው ብርሃን መስጠት የቻለ ስለመኖሩ ከዚህ ቀደም እንዳልተሰማና ይህንን ለማድረግም ከእግዚአብሔር ካልሆነ በስተቀር ኃጢአተኛ ሰው ብርሃን መስጠት እንደማይችል ልቡናቸው እያወቀ የለም! ይህ ሰው «ኃጢአተኛ እንደሆነ እናውቃለን» ሲሉ በቃለ ሀሰት ምስክርነት እስከመስጠት ያደረሳቸው ነገር እያዩ የማያዩ ሰዎች ስለሆኑ ነበር።
 እነዚህ ልበ ዕውራን ካህናት የዕውርነታቸው መጠን የለሽነት የሚገለጸው ደግሞ የተነገራቸውን እውነት ለመቀበል አለመፈለጋቸው ብቻ ሳይሆን እየተነገራቸው የሰሙትን ለመሸከም የሚችል ልቡና የሌላቸው መሆናቸው ደግሞ ሌላው አስገራሚ ነገር ነው።
ካህናቱ ዓይኑ ስለበራለት ሰው በቅድሚያ ጥያቄ ያቀረቡት ለወላጆቹ ነበር። «እናንተ ዕውር ሆኖ ተወለደ የምትሉት ልጃችሁ ይህ ነውን? ታድያ አሁን እንዴት ያያል? ብለው ጠየቁአቸው» ዮሐ 9፤19
ወላጆቹም፤ ዓይነ ስውሩ ልጃቸው አሁን ዓይኑ እንደበራለት ከመሰከሩ በኋላ ማን እንዳበራለትና እንዴት እንደበራለት እንደማያውቁ በተናገሩ ጊዜ ካህናቱ ሁለተኛ ማረጋገጫ በመሻት ወደ ጉዳዩ ባለቤት በመሄድ ጥያቄያቸውን ዓይነ ስውር ለነበረው ሰው አቅርበዋል። እሱም ሲመልስ «ያበራለት ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን እንደማያውቅ፤ ነገር ግን ዓይኑን እንዳበራለት እንደሚያውቅ ሊገባቸው በሚችል ቋንቋ በግልጽ ተናግሮ ሳለ መልሰው በጥያቄ ሲያደርቁት ይታያሉ። ዳኅጸ ልሳን በመፈለግ ለመክሰስና ሸንጎ አቁሞ ለማስወገዝ ወይም ለማስደብደብ ካልሆነ በስተቀር ወደእውነት ለመመለስ ለቀና ነገር ቀና ልብ መቼም የሌላቸው ናቸው።
«ደግመውም። ምን አደረገልህ? እንዴትስ ዓይኖችህን ከፈተ? አሉት» ዮሐ 9፤26 ዓይኑ የበራለትም ሰው ነገረ ስራቸው ሁሉ አስገርሞትና እንደዚህ አብዝተው ጥያቄ መጠየቃቸው በተደረገው ተአምር ተስበውና በኢየሱስ የማዳን ፍቅር ተሸንፈው ደቀ መዛሙርቱ ለመሆን የፈለጉ መስሎት በመሰላቸት ስሜት እንዲህ ሲል መለሰላቸው።
«እርሱም መልሶ፦ አስቀድሜ ነገርኋችሁ አልሰማችሁምም፤ ስለ ምን ዳግመኛ ልትሰሙ ትወዳላችሁ? እናንተ ደግሞ ደቀ መዛሙርቱ ልትሆኑ ትወዳላችሁን? አላቸው» ዮሐ 9፤26
ካህናቱ ነገረ መጻሕፍትን አዋቂዎች ናቸው፤ እድሜአቸውን ሁሉ በመቅደሱ ሲያገለግሉ ኖረዋል፤ በዚያ ላይ ዓይናቸው አልታወረም። በእርግጥም መጠየቃቸው ደቀመዛሙርት ለመሆን ከመፈለግ የተነሳ ሊሆን እንደሚችል ቢገመት ስህተት ላይሆን ይችላል። ስህተቱ ግን ካህናቱ ክርስቶስን ለማወቅ አለመቻላቸው ብቻ ሳይሆን ለማወቅም አለመፈለጋቸውን አለመረዳት ነው። ልበ ዕውራኑ ካህናትም ሲመልሱ እንዲህ አሉ።
«ተሳድበውም። አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ፥ እኛ ግን የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን፤ እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ተናገረው እኛ እናውቃለን፥ ይህ ሰው ግን ከወዴት እንደ ሆነ አናውቅም አሉት» ዮሐ 28-29
ዕውር ሆኖ የተወለደውን ሰው ዓይኑ ብርሃን ስለማግኘቱ ለማወቅ አንድም ቦታ መፈለጋቸውን አናነብም።  ዓይነ ብርሃኑ የተመለሰለትን ሰው በጥያቄ ከማሰለችታቸው በላይ ተመጣጣኝ መልስ ቢሰጣቸው ካህናት ሆነው ሳለ የምላሻቸው ማሟሺያ ስድብ ጭምር ማከላቸው በእርግጥም እውቀት በተለይም መንፈሳዊ እውቀት ከላይ ከሰማይ ካልተሰጠ በስተቀር በትምህርትና በክህነት ማዕርግ ሊገኝ እንደማይችል ያረጋግጥልናል። ይህንንም እውነት ጌታችን ራሱ እንዲህ ሲል መናገሩ የታሪኩን እውነታ ያሳያል። «የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም» ዮሐ 6፤44  ለሰው ልጅ ትምህርትና እውቀት አስፈላጊ የለውጥ መሣሪያዎቹ እንደሆኑ ባይካድም  ከላይ ካልተሰጠ በስተቀር ይህ በራሱ ወደእውነተኛ መገለጥ ሊያደርስ አይችልም። ብዙ አዋቂዎች ባለማወቅ ደመና ተሸፍነው መገኘታቸው ዘወትር የምንመለከተው ሐቅ ነው።
ካህናቱ ዓይነ ስውሩን ከሰደቡት በኋላ «አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ፤ እኛ ግን የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን» አሉት።  የኢየሱስ ደቀ መዝሙር መሆን የተናቀ ደረጃ ሲሆን የሙሴ ደቀ መዝሙር መሆን መቻል በካህናቱ ዘንድ ትልቅ እድገትና እውቀት መሆኑ ነው። ዛሬም «የእርቃችን መንገድና እውነት፤ መድኃኒትና በር ኢየሱስ ብቻ» ብሎ መጥራት ያስነቅፋል። በዚህ ላይ ልዩ ልዩ የመዳኛ መንገዶችን፤ ብዙ ብዙ አማላጆችን ካልያዝክ በስተቀር  «ኢየሱስ» በሚለው ስም ላይ ብቻ መታመን ዋስትና እንደሌለው የሚያስተምሩ ካህናት አሉ። «ፊት የማያስመልሱ፤ አንገት የማያስቀልሱ» ብዙ የቃል ኪዳን ባለቤቶችን ከፊትህ ካላደረክ ገነትን በኢየሱስ ይቅር ባይነት ላይ ብቻ ታምነህ እንዲህ በቀላሉ አታገኝም! የሚሉ መምህራንና ካህናት አሉ። «ስድስቱን ቃላተ ወንጌልንና ዐሠርቱ ቃላተ ኦሪትን» ለመፈጸም ከመፈለግ ይልቅ «ተአምሯን ለመስማት ተሽቀዳደሙ» የሚለውን ማደንዘዣ ዘወትር የሚያነበንቡ ልበ እውራን ካህናት አሉ። «ኢየሱስ ጌታ ነው»  (1ኛ ቆሮ 12፤3) ብሎ መጥራት ይህ የመናፍቅ አባባል ነው የሚሉና ይህንንም በመፍራት በአፋቸው የማስገቡ ካህናት አሉ።
ካህናተ ቤተ መቅደስ፤ ዓይነ ብርሃኑ የተመለሰለትን ሰው ከሰደቡ በኋላ «አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ» ብለው ለእነሱ ጸያፍ የመሰላቸው፤ ነገር ግን የኢየሱስ ደቀ መዝሙር መሆን ከመቻል የተሻለ እድል እንደሌለ ስለማያውቁ ራሳቸውን የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ከመሆን አግልለው «እኛ የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን» ማለታቸው ትልቁንና የተሻለው መጣላቸው መሆኑን አላወቁትም። እናውቃለን ይላሉ፤ አያውቁም፤ እናያለን ይላሉ እውራን ናቸው። አብ ስለወልድ ማንነት የገለጠላቸው ግን «ኢየሱስ ጌታ ነው» ሲሉ አያፍሩም። «በሩ እኔ ነኝ» ስላለ ዕለት ዕለት ያንን በር ብቻ ያንኳኳሉ። «አንኳኩ ይከፈትላችኋል» ያለው ቃል ስለማይታበል ተስፋቸው እሱ ነው።  የሌሎችን በር በመደብደብ፤ እባካችሁ ሂዱና ያንን «በሩ እኔ ነኝ» ያለውን ጌታ አስከፍቱልን ብለው በማስቸገር ባልተነገረ ድካም ውስጥ ራሳቸውን ሲያሽከረክሩ አይገኙም። እሱን በቀጥታ ለለመኑት አምላካችን የማያሳፍር በቃሉ የታመነ ተለማኝ ነውና።
«እኔም እላችኋለሁ። ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል»   ሉቃ 11፤9
የሚገርመውና የሚደንቀው ነገር ካህናተ ሌዋውያኑ «ይህ ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን እናውቃለን» ሲሉ ቆይተው የደቀ መዝሙርነት ጉዳይ ሲነሳ የተናገሩትን ቃል ሸምጥጠው በመካድ «ይህ ሰው ከወዴት እንደሆነ አናውቅም» ሲሉ መገኘታቸው ነው። «እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ተናገረው እኛ እናውቃለን፥ ይህ ሰው ግን ከወዴት እንደ ሆነ አናውቅም አሉት» ዮሐ 9፤29  ከወዴት እንደሆነ ካላወቁት ከምን ተነስተው ነው « ይህ ሰው ኃጢአተኛ እንደሆነ እናውቃለን» ብለው ለመናገር ድፍረት ያገኙት?  ለዚህ ሁሉ ያላዋቂ ሳሚ ዓይነት ምላሻቸው ዋናው ምክንያት ካህናቱ ራሳቸውን የሚስሉት ከሌላው የተሻለ እውቀትና ማንም ያልደረሰበት ትምህርት እንዳላቸው ስለሚያስቡ ብቻ ነው። እውነትና ከአብ ዘንድ ስለወልድ ያለው መገለጥ ከሌላ ከማንም ዘንድ ሊኖር ይችላል ብለው በፍጹም አያስቡም። ቢኖር እንኳን ከእነሱ የተለየውን ሁሉ እንደኑፋቄና ክህደት ይቆጥሩታል።
በዘመናችን የወልድን መሲህነት፤ ብቸና አዳኝነትና ከምድር እስከሰማይ የተዘረጋውን ሕያው መሰላል በማንሳት ሌሎችን በምትክነት አበጅተው፤ ለምትክነቱም የሚጠቅም መከላከያ ምሽግ ቆፍረው የሚሟገቱ ካህናትና አዘጭዛጭ ማኅበራት አሉ።  «እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው» ዮሐ 1፤52  የሚለውንና ከባለቤቱ ከራሱ የሰማነው ቃል አይበቃንም፤ የግብጻዊው መነኩሴ የህርያቆስም ይጨመርልን፤ አብሮም ይዳበል በማለት «አንቲ ውእቱ ሰዋስዊሁ ለያዕቆብ» መላእክት የሚወጡባትና የሚወርዱባት መሰላል አንቺ ነሽ (ቅዳሴ ማርያም) የሚሉ ካህናትና አዘጭዛጮች አሉ። ይህንን የቃል ልዩነት ለማስማማት ሲሉ አንዴ እናውቃለን፤ አንዴ ደግሞ አናውቅም የሚሉ ልበ እውራን አሉ። ራሳቸውን ከክርስቶስ ደቀ መዝሙርነት ሰልፍ አውጥተው እኔ የተክልዬ ልጅ፤ የሳማ ሰንበት፤ የዜና ማርቆስ፤ የአርሴማ፤ የሙሴ…………..የሚሉ አሉ። የአጵሎስና የኬፋ ዓይነት መሆኑ ነው።
«ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥ በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥በገበያም ሰላምታና። መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ» ማቴ 23፤2-7 ዛሬም በተግባር አለ። ካህናቱ ያውቃሉ ግን እውነትን አያውቁም!!

Monday, July 1, 2013

በጎልጉል ድረ ገጽ በቀረበው ''አንተ ማነህ?'' ጽሁፍ ላይ አቶ የኑስ (ዮናስ - በመጽሐፍ ቅዱስ) ላቀረቡት የግል ወቀሳ ጽሑፈ የተሰጠ ምላሽ


አቶ የኑስ (ዮናስ) የተባሉት - በመጽሐፍ ቅዱስ) ላቀረቡት የግል ወቀሳ፤
አቶ ዮናስ !!!
አሁንም

ስላም ይብዛልዎት እያልኩ ነገርን ነገር ያነሰዋልና ባላሰብኩት ነገር ላይ በሰነዘሩብኝ የሃሰት ክስ ላይ ተመስርቼ አንዳንድ የጋራ ጥያቂዎችን እንዳቀርብ ይፍቅዱልኝ???
1) የሙስሊሙ ጥያቄ በአገሪቱ ውስጥ በሙሉ መልካም አስተዳደር እንዲመጣ ነው ወይስ በእኛ ላይ ብቻ በደል ስለደረሰብን ትግላችን ለሙስሊሙ መብት ብቻ የሚል ነው?
2) በየቦታውና በየጊዜው በሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ዘዎትር የሚሰማው መፈክር 'መሪዎቻችን ይፈቱ' እንጂ በታሰሩ ጋዜጠኞች፤ ፖለቲከኞች፤የመብት ተከራካሪዎችና በአጠቃላይ ፍትህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ስትሉ ሰምቼ አላውቅምና ይህ ከምን የመጣ ነው?
3) ያስታውሱ እንደሆነ ''ሰማያዊ ፓርቲ'' ባዘጋጀው ሰልፍ ላይ አዘጋጆች ከተከሰሱበት ምክናያት አንዱ በሰልፉ ላይ አንዳንድ ሙስሊም ወገኖች ባቀረቡት ጠበብ ያለ ግለኛ መፈክር ምክንያት ነበር ታዲያ በቅንነት ለአንድ አገርና ሕዝብ በተሰለፈ ሁሉን አቀፍ ሰልፈኛ መካከል እንዲህ ዓይነቱ ሥራና ዝንባሌ የት የሚያደርሰን ይመስልዎታል?
4) ጥያቄዎቼ የሁላችንንም የወደፊት የጋራ ጉዳይ የሆነውንና አገርን ለመልካም አስተዳደር ለማብቃት ከሚደረገው አጠቃላይ እንቅስቃሴ አንጻር ሊኖረው የሚገባውን ፋይዳ ከወዲሁ ቆም ብለን ለማሰብ እንድንችል በማሰብ የተሰነዘሩ መሆናቸውን ከወዲሁ አስበው በቅንነት እንዲመልሱልኝ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት በትህትና እየጠየኩ ባለፈው እንደነካኩት እንደ ሃይማኖት ልዩነትና ክርክር አድርገው የሚቆጥሩት ከሆነ ግን ለፍላጎትዎ ማርኪያ የሚሆንዎን ጥሩና መሰረት ያለው ክርክር ወይም በመረጃ የተደገፈ ማስረጃ በክርስትናና በእስልምና መካከል አገሪቱ ባፈራቻቸው ምሑራን በአማርኛ በስፋት የሚቀርበውን ''Аnswering Islam ''  ድህረ ገጽ ቢከታተሉ ለችግርዎ የተሻለ መልስና ግንዛቤ ሊያገኙ ይችላሉና ትኩረትዎን ወደ እዚህ ድህረ ገጽ ቢያደርጉ ይሻልዎታል ማለት እወዳለሁ። ለአገራችን ጠቅላላ ችግር ብዙ የሚሠራ ሥራ ስላለ እኔን ለጊዜው ቢተውኝ??? አሁንም ጨዋ ሙስሊም ወገኖቼን እወዳለሁ። ክፋትን ተላብሰው ባልሆነ ነገር በመካፋፈል ለትውልድ መርዝ የሚረጩትንና እየረጩ ካሉ የእኛው ጉዶች ጋር ግን ምንጊዜም ስምምነት እንደሌለኝ ላሳውቅዎት እወዳለሁ። ደግሞም አንዳንዶች በመድረክ ላይ እየወጡ ''አላህ ወ-አክብር'' እንደሚሉት ዓይነት ማስመሰል ጨርሶ አላውቅበትምና በዚህ አይገምቱኝ። ደግሞም የእኔን እምነት መከተል አለባችሁ በማለት ከፍቅር ሌላ ሰይፍ አላነሳም። ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ስለሚጠፉ!!!

አሁንም ለጋራ የአገራችን ችግር
በጋራ አብረን በቅንነት እንሰለፍ!!!

ምድራዊ አገራችንን ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ያስባት!!!

አሁንም አክባሪዎ

በይስሃቅ በኩል የአብርሃም ዘር

ተናገር ነኝ

Saturday, June 29, 2013

ከሰዓሊና ገጣሚ ገ/ክርስቶስ ደስታ የግጥም ስብስቦች


The painter-poet, was born in 1932 in the Eastern province of Harar, Ethiopia, to father Aleka Desta, a clergyman, and mother W/o Atsede Mariam Wondimagegnehu. Gebre Kristos completed his elementary education in his native town of Harar, and attended the Haile Sellassie 1st School and General Wingate High School. He later joined the Science Department at Haile Sellassie 1st University, presently Addis Ababa University. Gebre Kristos did not pursue a career in his field of study, scientific agriculture, but instead studied art and painted in his spare time. Initially, Gebre Kristos was a self-taught artist, but in his sophomore year, his predilection for art won out, and Gebre Kristos abandoned his studies in hope of becoming a full-time artist.

Sunday, June 23, 2013

በሰማንያ ወአሀዱ ሽፋን የተፈጸመው የጠላት ሴራ ሲገለጥ (ክፍል ሦስት )



ከባለፈው ክፍላችን የቀጠለውን በሰማንያ ወአሀዱ ሽፋን ጠላት አስርጎ ያስገባውን የስህተት መንፈሱን አሰራር በቀጣይነት እንመረምራለን። ጥንተ ጠላታችን በእግዚአብሔር ዋና ቃል ውስጥ ጥቂት የስህተት ቃላትን ሰንቅሮ ማስገባት መቻሉ ጠቅላላ የአምልኮ ሥርዓታችንን እንደፈለገ ለማናጋት በር ስለሚያገኝ በዚህ ዙሪያ አጥብቆ ይሰራል። ይህንን እስትንፋሰ እግዚአብሔር የሆነውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ከአበው ሲወርድ እዚህ ዘመን የደረሰውን ጠብቆና ጠንቅቆ በማቆየት፤ ስህተት ሲገኝ በማቃናት፤ የጎደለውን በማረም፤ የሁል ጊዜ አዲስነቱን እንደያዘ፤ ትውልዱን እያደሰ መቀጠል እንዲችል የማድረግ ኃላፊነቱ የቅዱስ ሲኖዶስና የሊቃውንት ጉባዔው ሥልጣን ቢሆንም ምሁራኑ በዐረፍተ ዘመን በሞት ጥላ ሥር አርፈው ቦታቸውን በመልቀቅ ለጊዜው ጥሬ ትርጉሙን እንኳን ለመረዳት አቅሙ በሌላቸውና «ከተንስኡ ለጸሎት» በዘለለ ቃለ እግዚአብሔርን ለመመርመር ድክመት ቤቱን የሰራባቸው ወንበሩ ላይ ያለአቅማቸው በመቀመጣቸው ቅዱሱ መጽሐፍ ሊበረዝ ችሏል። ሊቃውንቱ ወደዳር ተገፍተው በደጀ ጠኝነት ያንጋጥጣሉ።፤ ገሚሱም በጋዜጣ አዟሪነት ያለቦታቸው ተሰማርተዋል። እነ «በአፍ ጤፍ ይቆሉ»  በሊቃውንት ስም የቤተክህነትን ገበያ ያደራሉ። መጋቤ ብሉይ ሠይፈ ሥላሴን የመሳሰሉ ሊቃውንት የደረሱበትን እውቀትና እውነት እንዳይተነፍሱ በድንቁርና መዶሻ ተመትተው እስከወዲያኛው አሸለቡ። ድኩማነ አእምሮዎች ሲያዋክቧቸው የቆዩት ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ እንኳን በዚህ በጎጋ ጉባዔያተኛ መካከል ባገኙት መንገድ ሁሉ ያካፈሉት ቃለ እውነት ብዙ ዘር ያፈራ ቢሆንም የተመኙትን ያህል ሳይሰሩ ያንን ሁሉ እውቀት ይዘውት የሄዱት ለቤተክርስቲያን ትልቅ ጉዳት መሆኑን እያየነው ነው። 
   እንደው ለመሆኑ ከእሳቸው ወዲያ በነገረ መጻሕፍትና ትርጉም አዋቂነት የሚጠራ ጳጳስ ማን ይሆን? ከተረትና ከእንቆቅልሽ በዘለለ ቃለ እግዚአብሔርን በምልዓትና በስፋት ማስተማር፤ ማረቅ፣ ማቃናት የሚችል አንድም ጳጳስ በዚህ ዘመን አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን የሚቆጨውም ሰው አለመገኘቱ በጣም አሳሳቢ ነው። ሊቃውንት ጉባዔ የተባለው የእነ ክንፈገብርኤል አልታዬና የሊቀ ሥዩማን  ራደ መሥሪያ ቤት ሊቅነቱን ሳናይለት ዘመኑን ፈጠመ።  የሚብሰው ደግሞ ትልቁንና ዋናውን ቃለ እግዚአብሔር/መጽሐፍ ቅዱስ/ ጥንታዊውን የአበው ትርጉምና ሕግጋት ጠብቆ እንደንጹህ የምንጭ ውሃ ኮለል ብሎ የምእመናን የልቡና ጥማት እንዲያረካ ማድረግ አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን የነበረውን መጽሐፍ አደፍርሰው፤ በጥብጠውና ከመርዝ ጋር ደበላልቀው በማቅረብ ሊቃውንት የሚባለውን ክብር ትቢያ ላይ ወድቆ እንዲቀር ማድረጋቸው ሌላው አሳዛኙ ገጽታቸው ነው። 
የሊቃውንት ጉባዔነትን ሥልጣን ተሸክመው የራሳቸውን ግዙፍ ድክመትና ስህተት በማየት ከማረም ይልቅ  የመንደር ላይ ጽሁፎችንና በራሪ ወረቀቶችን እየለቀሙ  አብረዋቸው የሌሉ ሰዎችን በማውገዝ መጠመዳቸው የሊቅነት ስያሜ  አቅጣጫው የጠፋ ይመስለናል። በየተአምሩ፤ በየድርሳኑ፤ በየገድላቱ፤ በየመጽሐፍ ቅዱሱ የተሰነቀረውንና ማን እንዳስገባው የማይታወቀውን ከእግዚአብሔር ቃል ሃሳብና ትርጉም የማይስማማውን እየመረመሩ ማስተካከል ሲገባ ሊቃውንት ጉባዔው የተኛበትን ሥራ በፈቃዳቸው ተረክበው «ይህ፤ ይህ ግድፈት ነው፤ ሊታረም ይገባል፤ የቀደምት አበው አስተምህሮ ሥፍራውን ይያዝ » በማለት በማስረጃ አስደግፈው የጠቆሙ ሰዎችን ጽሁፍ እየለቀሙ አውግዘናል ማለቱ ሊቃውንት ጉባዔው ኮምፓስ እንደሌለው መርከብ ውቅያኖስ ላይ መንሳፈፉን ራሱ አረጋግጧል። ሰዎቹ ይታረም ያሉት የተጻፈውን ስህተት አንስተው እንደ ወንጌል ቃልና እንደአበው አስተምህሮ ይታረም ማለታቸው ወንጀል ሆኖ ሊያስወግዝ ቀርቶ እኛ መሥራት ያቃተንን ስለሰራችሁልን እናመሰግናለን ሊባሉ ይገባ ነበር።
እኛም አቅማችንና ችሎቻን የፈቀደውን ያህል በመረጃና በማስረጃ አስደግፈን  ሁሉም እንዲያውቀው በሰማንያ ወአሀዱ ሽፋን ጠላት አስርጎ ያስገባውን የስህተት ቃል ለማሳየት እንሞክራለን። 

1/ የብቻችን መጽሐፍ እንዴት?

በባለፈው ክፍል ሁለት ጽሁፋችን ለመጠቆም እንደሞከርነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊት እንደትርፍ የቀኖና መጻሕፍት ትቆጥራቸው የነበሩትና ከ2000 ዓ/ም መጽሐፍ ቅዱስ ህትመት በኋላ ግን እንደዋና  የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የደመረችው የመቃብያን መጻሕፍት ሦስት ክፍሎች ከአይሁዳውያን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ቁጥር ውስጥ የሌለ መሆኑን ለማሳየት ሞክረናል። በ3ኛውና በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ትንቢተ ሚልክያስ ያሉትን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በ39 ክፍል መድበው ትክክለኛ የእግዚአብሔር ቃል የሆኑ የአይሁዳውያን መጻሕፍትን ሙሉ በሙሉ መቀበላቸውም ታሪክ ያስተምረናል። ከዚህ ውጪ የአይሁዳውያን መጻሕፍት ያልነበሩትን የኦሪት መጻሕፍት እንደብሉይ ኪዳን ለመቀበል የሚያስችል ሌላ ምክንያት የለም። ለእስራኤል ዘሥጋ የተሰጡ የእግዚአብሔር ቃል መጻሕፍት ሙሉ በሙሉ በአዲስ ኪዳን ዘመን ተቀባይነት አግኝተዋል። እነዚህንም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብለን እንጠራቸዋለን። ነገር ግን ለሕዝበ እስራኤል ያልተሰጡና በብሉይ ኪዳን መጻሕፍትነት ያልተመዘገቡ መጻሕፍት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከየት አምጥታ እንደብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ቆጠረቻቸው? ምንጫቸው ከየት ነው?  እነዚህንም በትርፍነት የያዘቻቸው በእርግጥ ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሰጥ የለም። ስማቸውን ዘወትር የምታነሳቸው ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን/ እነአትናቴዎስ/ የማያውቋቸውና ዛሬም ድረስ እናቴ የምንላት የኮፕት ቤተ ክርስቲያን የማታውቃቸውን መቀበላችን ለምን? ብለን መጠየቅ አግባብነት አለው። ደግሞም በዓለማችን ላይ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በአንዱም ውስጥ የሌለ መጽሐፈ መቃብያን ለኢትዮጵያ ብቻ የተሰጠው ከሰማይ ነው ወይስ ከምድር? መቼና እንዴት? ለሚሉት ጥያቄዎች በእርግጥ በቂ መልስ የሚሰጥ የለም።

2/ዲያብሎስ ከክብሩ የወደቀው ለአዳም ስገድ ተብሎ አልሰግድም በማለቱ ነው። 

መጽሐፈ መቃብያን ምንጩ ያለመታወቁ አንዱ ምክንያት የያዘው ሃሳብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑ ነው። ዲያብሎስ ከክብሩ የወረደው እግዚአብሔር ለአዳም ስገድ ባለው ጊዜ ለሚዋረድልኝ ለአዳምስ አልሰግድም ብሎ እምቢተኛ በመሆኑ ነው ይለናል። ዲያብሎስ ራሱ ይህንን ቃል ሲናገር ያዳመጠው ሰው ማን እንደሆነ ለጊዜው ባይገለጽም መቃብያን ግን የዲያብሎስን ንግግር የሰማ ያህል እንዲህ ሲል አስፍሮታል።
«የሚጠፉ በኔም የሚስቱ ሰዎች ፈጽመው ይበዙ ዘንድ የአዳምም ልጆች ይጠፉ ዘንድ ይህንን በተናገሩ ጊዜ እኔ ደስ ይለኛል። ለሚዋረድልኝ ለአዳም አልሰግድም በማለቴ እግዚአብሔር ስለአባታቸው ስለአዳም ከማዕረጌ አዋርዶኛልና« 3ኛ መቃ 1፤15

ዲያብሎስ ራሱን ከፍ ከፍ ስላደረገና አምላክነትን ስለፈለገ ከማዕረጉ እንደተዋረደ የምታስተምር ቤተ ክርስቲያን፤ የለም ዲያብሎስ የወደቀው ለአዳም ስገድ በተባለ ጊዜ አልሰግድም በማለቱ ነው የሚለውን የመቃብያን መጽሐፍ፤ እስትንፋሰ እግዚአብሔር ያለበት የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ነው በማለት ከ 81 ዱ ጋር አዳብላ ልትቆጥረው እንዴት ቻለች? ጥያቄአችን ነው። አይሁዶቹም እንደብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ያልቆጠሩት፤ ኮፕቶችና ሌሎቹም አብያተ ክርስቲያናት የማያውቁትን ይህንን መቃብያንን ከብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ጋር እንድንደምረው የሚያስገድደን መንፈሳዊ ይዘቱ ምንድነው? ስለ ሰማንያ ወአሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ ስንናገር አሰሱንና ገሠሡን ሁሉ በመቆጠር ሊሆን አይገባውም። የአንድ መንፈሳዊ መጽሐፍ ልኬታ ምንጩ፤ መንፈሳዊነቱ፤ ተቀባይነቱና አገልግሎቱ ካልተመዘነ የጠላት አሰራር መግባቱ አይቀሬ ይሆናል። 

3/ ሳምራውያን ትንሣዔ ሙታን የለም ብለው ያምኑ ነበር ወይ?

ስለሰዱቃውያንና ስለፈሪሳውያን ትምህርተ ሃይማኖት የምናገኘው ማስረጃ ያለው በአዲስ ኪዳን ውስጥ ብቻ ነው። ሁለቱም የካህናተ ኦሪት ወገን ቢሆኑም  ሰዱቃውያን ከሞት በኋላ ስላለው ትንሣዔም ሆነ ዘላለማዊነት በፍጹም እምነት የላቸውም። ትንሣዔም፤ መላዕክትም የለም ባዮች ናቸው። ፈሪሳውያን ግን መላእክትም፤ ትንሣዔ ሙታንም መኖሩን  ቢያምኑም ይህ የሚሆነው ለአይሁዳውያን ብቻ ነው የሚል የትምክህት አስተምህሮ ስለነበራቸው ኢየሱስ ለክርስቲያኖች እንዲህ ሲል አስጠንቅቋል።
«ኢየሱስም፦ ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ አላቸው። ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ እንድትጠበቁ ብዬ ስለ እንጀራ እንዳልተናገርኋችሁ እንዴት አታስተውሉምን? እነርሱም ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ትምህርት እንጂ ከእንጀራ እርሾ እንዲጠበቁ እንዳላላቸው ያን ጊዜ አስተዋሉ» ማቴ 16፤6-12 የአዲስ ኪዳን የትንሣዔ አዋጅ ለተወሰነ ሕዝብ ስላይደለ የፈሪሳውያንን አስተምህሮ ክርስቲያኖች መቀበል ስለሌለባቸው ከዚህ ክፉ እርሾ እንዲጠበቁ አሳስቧል። እንደሰዱቃውያንም ትንሣዔ የለም ከሚል ትምህርትም ራሳቸውን እንዲጠብቁ ጳውሎስ  ሲያስረዳ የስንዴ ቅንጣት እንዴት ፈርሳና በስብሳ  ፍሬ እንደምታፈራ ትንሣዔውን በምሳሌ ሲያስተምር «አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም» 1ኛ ቆሮ 15፤36 ይለናል።
እዚህ ላይ ስለሰዱቃውያንና ስለፈሪሳውያን የትንሣዔ ሙታን እምነት ማንሳት ያስፈለገው ከላይ በቁጥር 3 ላይ ላመለከትነው የጥያቄ ኃይለ ቃል መንደርደሪያ እንዲሆነን ነው። ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን ስለትንሣዔ ሙታን ያላቸው እምነት ከላይ እንደገለጽነው የአዲስ ኪዳን አስረጂ ከሆነ ሳምራውያን የሚባሉት ሕዝቦች ትንሣዔ ሙታን የለም ያሉት መቼ ነው? ብለን እንጠይቃለን። ምክንያቱም መጽሐፈ መቃብያን ሳምራውያን ትንሣዔ ሙታን የለም ብለዋል ይለናልና። 

አጭር ታሪክ፤

ሴኬም የያዕቆብ ምንጭ ያለባት የዐሥሩ ነገድ ሰሜናዊው እስራኤል መቀመጫ ከተማ ነበረች። የሰሎሞን መንግሥት በልጁ በሮብዓም/ ሁለት ነገድ/ በኢየሩሳሌም እና በአገልጋዩ በናባጥ ልጅ በኢዮርብዓም /ዐሥር ነገድ/ በሴኬም ከተከፈለ ( 1ኛ ነገ 12፤20) በኋላ ቆይቶ የሰማርያ ታሪክ ይጀምራል። እሱም የአክአብ አባት ዘንበሪ ሳምር ከሚባለው ሰው ላይ ከሴኬም ከተማ በስተቀኝ ያለውን ተራራ በሁለት መክሊት ከገዛ በኋላ በባለቤቱ በሳምር ስም ተራራ ላይ ቤት ሰርቶ ቦታውን ሰማርያ ማሰኘቱን መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። 1ኛ ነገ 16፤24 ከተማው እያደገ፤ ሀገሩም እየሰፋ ሰማርያ ስያሜውን ይዛ ዛሬም ድረስ አለች። ሰማርያ ገሪዛንና ጌባል የሚባሉ የአምልኮ ኮረብታዎቿን ይዛ በመገኘቷ ከሁለቱ ነገድ መዲና ከሆነችው ከኢየሩሳሌም ጋር ኅብረት ያልነበራቸው ከዚያን ጊዜ አንስቶ ነበር። ስለዚህም ጌታችን ከኢየሩሳሌም ወደሰሜናዊ የገሊላ አውራጃ ለመሄድ አማራጭ መንገዱ ሩቅ ስለሆነና የመጣበትም ዓላማ ስለነበረው በዚህች ከይሁዳውያን ጋር ኅብረት ባልነበራት በሰማርያ ማለፉን እናነባለን። (ዮሐ 4፤4)

ሰማርያውያን የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ ስፍራ ገሪዛን ተራራ እንጂ ኢየሩሳሌም አይደለችም ከማለታቸው በስተቀር፤ የትንሣዔ ሙታንና የገነትንም መኖር ያምናሉ። ይሁን እንጂ መጽሐፈ መቃብያን የተባለው የአዲስ ኪዳኑን ታሪክ እንደብሉይ ኪዳን ዘመን ትረካ ወደኋላ ጎትቶ የሌለውን ነገር ያስነብበናል።
«ሳምራውያን ግን ሥጋችን ትቢያ ይሆናል፣ አይነሳም ይላሉ» (2ኛ መቃ 14፤1-3) እዚህ ላይ ጥያቄ የሚያስነሳው መቃብያን የተባለው መጽሐፍ በአዲስ ኪዳን የተጻፈውንና ጌታችን ያስተማረውን ታሪክ ስለሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን ይዞ መገኘቱ አንዱ ነጥብ ሲሆን ትንሣዔ ሙታን የለም ያላሉትንና የማይሉትን ሳምራውያንን ከሰዱቃውያን ጋር አብሮ መጨፍለቁ ታሪኩን አስገራሚ ያደርገዋል። ምክንያቱም ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን ስለትንሣዔ በጠየቁት ጊዜ ሳምራውያን ያልነበሩ ሆነው ሳለ መቃብያን ግን ልክ እንዳሉ ቆጥሮ፤ ያልተናገሩትን ስለመናገራቸው መዘገቡ ምን ይባላል? ሳምራውያን የብሉይ ኪዳን እምነት ተከታዮች ስለትንሣዔ ሙታን ያላቸው እምነት ግልጥ ነው። መቃብያን ግን የትም ያልተጻፈውን አንስቶ ይለጥፍባቸዋል።
ዛሬ በቁጥር ከ 800 የማይበልጡ ሳምራውያን በትንሣዔ ሙታንም በመላእክትም መኖር የማመን ጥንታዊ እምነታቸውን ያልተዉ የ10ሩ ነገድ ዘሮች በሰማርያ ይኖራሉ። መቃብያን ግን ይዋሽባቸዋል። ለምን?
(ይቀጥላል)

Sunday, June 16, 2013

«መድኃኒት መልካም ነው፤ መድኃኒትን አላግባብ መጠቀም ግን አደጋ አለው»



(በ2002 ዓ/ም በሳይበር ኢትዮጵያ ድረ ገጽ አባ /ትንሣዔ ላደረጉት ሃይማኖታዊ ክርክር፤ ተሳታፊ ከሰጣቸው መልስ ተስተካክሎ የተወሰደ)
 «የሞኝ ለቅሶ መልሶ፤ መልሶ» እንዲሉ ስንት ያውቃሉ ተብሎ የሚነገርላቸው ትልቅ ሰው የባልቴት ወሬ ሲያንስነብቡን ይገርማል። በመሰረቱ ቅድስት ማርያም እሙ ለእግዚእነ፤ በኅቱም ድንግልና ወለደችው ብሎ ማመን ከመጽሐፍ ቅዱስ የተገኘ እንጂ ከመጽሀፈ ባልቴት የተወረሰ አይደለም። እናትህና «አባትህን አክብር»ያለው መጽሀፍ ቅዱስ የኢየሱስ ክርስቶስን እናት ክብር ዝቅ ማድረግ ጤናማነት አይደለም። ችግሩ ግን ያለው ማርያም ክርስቶስን በሥጋ ስለወለደችውና ይህንን የመመረጥ ጸጋ ለማጉላትና በጣም የሚወዷት አድርጎ ለመሳል የተሞከረበት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነና ይህንኑም «ትንሽ ዱቄት ይዘህ ወዳለው »ተጠጋ እንዲሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነውን እና እሱን የሚያፈርሰውን ሃይለ ቃል ሁሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እየለቀሙ ይሄ ይደግፈናል፤ ይሄ ይረዳናል የሚል ለራስ ማሳመኛና ሌላውን በራስ ትርጉም መከራከሪያ አድርጎ ማቅረብ ምን ይሉታል? እስኪ አባ ከላይ የሰጡበትን የሞገት ሂደቶች እንቃኝ። ተዓምረ ማርያም አባ ገብርኤል አባ ሚካኤል በተባሉ የግብጽ ጳጳስት ዘመን፤ ቆስጠንጢኖስ ብሎ ራሱን በሰየመው ዘርዓ ያዕቆብ በነገሰ በ7ኛው ዐመት ከዓረብኛ ወደ ግዕዝ ተተረጎመ ይላል የተዓምር መቅድም። እውነቱ ይሄ ሆኖ ሳለ አባ ወ/ትንሳዔ ተዓምረ ማርያም ከዘርዓ ያዕቆብ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደነበረ አድርጎ ማቅረብን ምን ይሉታል? አባ በእርግጥ እውነቱን ያውቁታል፤ ችግሩ ግን በስብከተ ወንጌል የካቡት ስምና ክብር ተዓምር በሚሉት መጽሐፍ ልቡ የተሰረቀው ወገን ባንድ ሌሊት ዓይናቸውን ላፈር እንደሚላቸው ስለሚያውቁ ይህንኑ ጠብቆ ለመኖር ስሉ ብቻ ነው ብሎ መገመት ይቻላል። እናም አባ ተዓምር ተብዬው መጽሐፍ ኢትዮጵያ የገባው በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ንግስና መሆኑን ከተዓምር መቅድም አንብበው ይመኑ እንልዎታለን። የሚገርመው ግን ተዓምር ተብዬው መጽሀፍ ከግብጽ መጣሁ ብሎ መቅድሙ ላይ ይቀባጥር እንጂ ይህንን የተዓምር መጽሐፍ የግብጽ (ኮፕቲክ) ቤተክርስቲያን የማታውቀው መሆኑ ነው። ግብጽ የራስዋ የሆኑ  መጻሕፍቶችዋንም እንደዚህ እንደእኛ በማውገዝና በማስፈራራት በ «አሌ ለከ» በወየውልህ ማስፈራሪያ  የማያውቀውን ንባብ እንዲሰማ በማይፈታ ሥልጣን በጽኑ አወገዝን እያሉ የፍርሃት ቀንበር በግድ አይጭኑም። በየትኛውም የግብጽ ቤተክርስቲን ከሰሜን አሌክሳንድሪያ እስከ ደቡባዊ ለክሰር ከተሞች ብንሄድ የኢትዮጵያው ተአምር ተመሳሳዩ በግብጽ የለም። ካይሮ በሚገኘው የኮፕቲክ ቤተመጽሃፍት ውስጥ ከኢትዮጽያ የመጣ ተብሎ በግዕዝ እንደተጻፈ ተቀምጦ ይገኛል። በለንደን ብሪቲሽ ሙዚየም ከግዕዝ በስተቀር የሌላ የማንም ምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት አይገኝም። ታዲያ ዘርዓ ያዕቆብ ከየት አመጣው? ምንአልባት ለእግዚአብሔር እኛ ልዩ ህዝቦች ስለሆንን ከሰማይ ወርዶልን ይሆን? ምን አለበት የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት ለእኛ እንደሚስማማን አድርገን እየተረጎምን አዎ! ወርዶልናል ብንል!! አባ ሌላው መከራከሪያ ነጥባቸው «በክርስቶስ ያመኑቱ ኃይል ይከተላቸዋል» የሚለው የወንጌል ቃል ነው። ስለሆነም የተደረገውን ተዓምራት ሁሉ ልንቀበል እንዲገባን ይመክሩን ዘንድ መሻታቸው ነው። በእርግጥ በክርስቶስ ያሉ ቅዱሳን ድንቅ ተዓምርን ሰርተዋል፤ዛሬም ይሰራሉ። ሌላው ይቅርና አባ እርስዎም የእግዚአብሔር መንፈስ ካደረብዎ ብዙ ተአምራትን ሊሰሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ማንኛውም ተአምር በስመ ክርስቲያን ስለተሰራ እንዳለ ለመቀበል የማንችለው፤
1/በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ሲመዘን የሚጋጭ ሆኖ መገኘት የለበትም።
2/በተደረገው ተዓምር ክብሩ ሁሉ ኃይልን ለሰጠ ለክርስቶስ መሆን አለበት። (የሐ/ሥራ14፤15)
3/ ተዓምር ሁሉ እውነት ስላይደለ የእምነትና የምግባር ሚዛኑ መለካት አለበት።(1ኛ ዮሐ4፤1)
ሀ/ ከዚህ አንጻር አጼ ዘርዓ ያዕቆብ የተዓምር መጽሐፍ ሲመዘን በቅድሚያ ጠላቶችችሁን ውደዱ፤ የሚሰድቧችሁን መርቁ የሚለውን የወንጌል ቃል ሽሮ አናምንም፤ አንቀበልም ያሉትን አባ እስጢፋኖስንና ደቀመዛሙርቱን አፍንጫቸውን ፎንነው(ቆርጠው) ጉድጓድ ቆፍረው እስከአንገታቸው በመቅበር ከብት እንደነዱባቸው፤ አስቃይተው ስለገደሏቸው ይህም ታላቅ የጽድቅ ስራ እንደሆነ ተቆጥሮ የዚህን በረከት አሳድርብን ብሎ ሰው ሁሉ እንዲቀበል በውግዘት ያስገድዳል። ይህ እንግዲህ የዘርዓ ያዕቆብን የመግደልና የማሰቃየት ተዓምር፤ ተዓምረ ማርያም በተባለው መጽሐፍ ውስጥ ማርያም ደስ መሰኘቷን ተጽፎ ይገኛል።  በቅዱስ ወንጌላችን ውስጥ ክርስቲያኖች ስለእምነታቸው መገደላቸውን እንጂ ለማሳመን ሰው ገደሉ የሚል አንድም ቦታ ተጽፎ አናገኝም። ስለዚህ ተዓምረ ማርያም መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም ብሎ መደምደም ይቻላል። ሰውን መግደል ለእውነተኛ ክርስቲያኖች እንደክርስናትያናዊ ተአምር አይቆጠርም። ድንግል ማርያምም ሰው የገደለውን ሰው ቅዱስ ትለዋለች ብለን አናምንም። አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ግን ቅዱስ ተብሎ ቤተክርስቲያን ታንጾለት፤ ስም አጠራሩ ጳጉሜን 3 ቀን ይከበራል።
ለ/ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ጅግራ ናት ብለው ይከራከራሉ እንዲሉ አምልኮ ስዕልን ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ የኦሪቱን የሚናተፍ አውራ ዶሮ አስመስሎ ሙሴ ሁለቱን ኪሩብ እንዲቀረጽ የተነገረውን ቃል ሁሉም ኦርቶዶክሳዊያን መምህራን ሳይጠቅሷት እንደማያልፏት ሁሉ አባም ያቺኑ ጭምብል ብቅ አድርገዋታል። ሙሴ አስመስለህ ቅረጽ የተባለው ለምንድነው? አስመስሎ መቅረጽን የታዘዘው ሙሴ ብቻ ነው ወይስ ሕዝቡ ሁሉ? አስመስሎ የተቀረጸው ምስል የሚቀመጠው በየሰዉ ቤት ወይስ ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ብቻ? አስመስሎ የሚቀረጸው ምስል ዓይነት ኪሩብ ወይስ የሰው ምስል? በቁጥርስ ስንት? አጠቃላይ የብሉይ ኪዳን ሕግ ለም? እንዴት? ለማንና መቼ?  የሚለውን አመክንዮአዊ ሕግ ባለማየት የራስን የልብ መሻት ከልብ ለማድረስ መጠቃቀሱ ተገቢ አይደለም እንልዎታለን። በአዲስ ኪዳን ስለምስል የተነገረን ሳይኖር እናድርግ ብንል እንኳን የሙሴ የቅድስተቅዱሳን ኪሩብ ሳይሆን ልባችን ያፈለቀውንና በጭብጥ አልባ ምትሀት(illusion) የምንስላቸውና የምንቀርጻቸውን ሁሉ በህዝበ እስራኤል ዘንድ እንደተደረገ አድርጎ መቁጠር ዋሾ ቀጣፊ ያሰኛል።
     ሙሴ እንዳደረገው እናድርግ ብንል እንኳን  ሙሴ በሚናተፍ አውራ ዶሮ ዓይነት የቀረጸው ኪሩብ የተቀመጠው በመንበሩ ላይ በቅድስተ ቅዱሳን እንጂ በሕዝበ አስራኤል ድንኳን ሁሉ አይደለም። አንድም ቦታ ሕዝቡ የሙሴን ኪሩብ ምስል ሰርቶ በየቤቱ አስቀመጠ የሚል ጽህፉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የለም። ስለዚህ ሙሴን እንደምሳሌ ማቅረብዎ ከጠላት የተገኘ ምክር እንጂ የመንፈስ ቅዱስ አይደለም። ለሀገር ለመንደሩ፤ለደጅ ለሰፈሩ በመፍቀድ ምንጭና ባለቤት የሌላቸውን ሰዓሊ፤ ጠራቢ ያልሕግ የሰውን ልብ ሊያማልል፤ ዋጋ ገበያ እንዲያወጣለት የሚያጓጓ አድርጎ የሳለውን ሁሉ ሰው እየገዛ እንዲያመልክ እንዲሰግድ ማስተማር የጤንነት አይደለም። ሙሴም ይህንን አላደረገም፤ አላስተማረምም። የስዕልና የምስል አምልኮ መቼ እንደተጀመረ? ማን እንደጀመረ? ሊቃውንቱን ስንት እንዳከራከረ ተጽፎ ይገኛል። ወደኢትዮጵያም ቤተክርስቲያን መቼ እንደገባ ይታወቃል።
        ስዕል መሳልና ለስዕል መስገድ ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ስለዚህ የዛሬዎቹ ሰዎች ስለምስል ሙሴን አግዘን ብለው ኪሩብን ከመጥቀሳቸው በፊት ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ውስጥ ምስልና ስዕል በስግደት የማይታወቅበት ጊዜ ነበር። በዚህ ጉዳይ ሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ። የሚገርመው ደግሞ ስዕልና ምስል በሙሴ ተፈቅዷል ባዮች ህዝብ እንዲሳሳት ማድረጋቸውን አለማወቃቸው የሚያሳየው በዛሬዋ ቤተክርስቲያን መቅደስ ውስጥ የሚናተፉ አውራ ዶሮ የሚመስሉ ሁለቱ የሙሴ ኪሩብ አለመኖራቸው ነው። ምነው የሙሴን የኪሩብ ምስል ከቤተመቅደሱ አስወገዳችሁት? ሙሴን እንደአጋዥ ምክንያት ስታቀርቡ ሙሴ ያደረገውን መተዋችሁ ለምነው? ወይስ ሙሴ አሻሽሉት የሚል ሕግ ትቶላችሁ ነበር?
      ለህዝቡ በምክንያትነት ኪሩቦቹን ስትጠቅሱ እናንተ የሱን አርአያና ምሳሌ ተከትላችሁ ቤተመቅደሱ ውስጥ እንደሚናተፍ አውራ ዶሮ ግራና ቀኝ አለማስቀመጣችሁ የናንተ ሥራ ከሙሴ ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ምስክር ነው። ስዕልም ይሁን ምስል ለታሪክ አስረጂ፤ ለመረጃ፤ ለትምህርት አስረጂና ጠቃሚ ሊሆን ከሚችል በላይ በየቤታችን ወይም በየመቅደሱ እጣን እንድናጥን፤ እንድንሰግድ፤ ከፊት ለፊታችን አስቀምጠን እንድንጸልይባቸው አንድም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት የለንም። እግዚአብሔር የሚገለጥበትን መንገድ ለሙሴ በብሉይ ኪዳን ተናግሯል። በአዲስ ኪዳንም በጾም፤ በጸሎት፤ በምጽዋትና በክርስቲያናዊ ምግባር ከተጋን የእግዚአብሔርን መልስ ለማግኘት፤ መልዕክት ለመቀበል፤ የሚገለጥበት መንገድ ያለራሱ ማንም አያውቀውም። እግዚአብሔርን ለመለመን በቅዱስ ሚካኤል ስም ካቶሊካዊው ጉይዶ ሬኒ በ1636 ዓ/ም በልቡ አቅንቶ፤ ችሎታውን ተጠቅሞ የሳለውን ስዕል ከገበያ ገዝቶ በመስገድ ወይም በእጣን ማጠን በዚያ በኩል እግዚአብሔርን መፈለግ እብደት ነው። ጉዶ ሬኒ ዛሬ ላይ ይህንን ቢያይ ኖሮ ምን ይል ይሆን?

                                 (www.artcyclopedia.com)
ሐ/ ሌላው ችግራችሁ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት አለቦታው በመጠቀም የልባችሁን መሻት ሁሉ በእሱ ቻይነት ካባ ለመሸፈን መሞከር ነው። ተአምር ሁሉ እውነት አይደለም ያልኩበት 3ኛው ነጥቤ ወንጌል፤ አባት አባ ያለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማይ የሚገባ አይደለም እንዳለው ሁሉ ተዓምር ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው ብለን አንቀበልም። በዚህ ዓለም ብዙ መናፍስት ገብተዋልና። ሲሞን መሰርይ የሰማርያ ከተማ ድንቅ ተዓምር ሰሪ ነበር። ግን ተዓምሩ ከእግዚአብሔር መንፈስ አልነበረም። ታዲያ እነዚህ የኛ ሰዎች እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ስለሆነ በኛ ተጽፈው የተገኙትን ተአምራት ሁሉ ድንቅ ስራ እያላችሁ ተቀበሉ ይሉናል። እስኪ አንዱን እንመልከት፤ በገድለ ተ/ ሃይማኖት የተሰራ ተዓምር ነው። አባ ተ/ ሃይማኖት «ባህር አልቅም» የተባለ ሰይጣን በመስቀል ምልክት አማትበው ከያዙት በኋላ አሳምነው፤ አስተምረው፤ አጥምቀው፤ እግዚእ ኀረዮ ብለው ስመ ክርስትና ሰጥተው ካበቁ በኋላ አመነኮሱት የሚል አስነብበበውናል። በእነሱ እንዴት ብሎ መጠየቅ አይቻልም፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነዋ!!! ጥሩ የበደል መሸፈኛ ምክንያት!!
እኛ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት ብናምንም ከሃሌ ኵሉነቱን አለአግባብ ሲጠቀሙበት ማየት ስለማንፈልግ እንዲህ እንጠይቃቸዋለን።
1/ ሰይጣን ስጋና ደም አለው ወይ? ሲገርዝስ ደም ይፈሰዋል? ግርዛትስ ክርስቲያን ለመሆን መመዘኛ ነው? «በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና» ገላ 5፤6
2/ ሰይጣን ንስሃ ይገባል ወይ? በወንጌልስ ሊያምን ይችላል?
3/ የክርስቶስ ሞትና ትንሳዔ (ሎቱ ስብሐት) ሰይጣናትን ያካትታል ወይ? ሰይጣን ዘላለማዊ ህይወትን ወርሶ ገነት ገባ የሚሉ ሰዎችን አባ፤ ምን ይሏቸዋል?
መቼም በዚህ ላይም ጉድ እንዲያስነብቡን እንጠብቃለን። በበኩሌ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት አለቦታው መጠቀም በእግዚአብሔር ላይ ከማሾፍ የተለየ አድርጌ አላየውም። መጠያየቅና እውነቱን ከመረዳዳት ባሽገር ጴንጤ፤ተሃድሶ፤ካቶሊክ፤መናፍቅ ወዘተ መባባል የትም አያደርስም። መድኃኒት መልካም ነው፤ መድኃኒትን አለቦታው መጠቀም ግን አደጋ አለው፤ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት ለልባችን መሻት ሁሉ ማዋላችን ይብቃ። ከእውነቱ እንታረቅ። አስተዋይ ልቦና ይስጠን።

Wednesday, June 12, 2013

ጥያቄ፤ በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?






       ምንጭ፤    (michaelyemane.blogspot.com) 


ጥያቄ፤ በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?
መልስ፤ በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ ይረዳን ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ የተለያዩ መንገዶችን ያቀርባል፡፡ በዚህ ዕድሜ በኃጥአት ላይ ፍጽሞ በሚገባ ባለድል አንሆንም (1ኛ ዮሐንስ 1፡8)፤ ነገር ግን ያ አሁንም የእኛ ግብ ሊሆን ይገባል፡፡ በእግዚአብሔር ዕርዳታ እና የቃሉን መርሆች በመከተል በሂደት ኃጥአትን ማሸነፍ እና በበለጠ ክርስቶስን መምሰል እንችላለን፡፡
በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሰው የመጀመሪያው መንገድ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል ስለዚህም በክርስትና ህይወታችን ባለድል መሆን እንችላለን፡፡ እግዚአብሔር ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡16-25 ውስጥ የሥጋ ሥራዎችን ከመንፈስ ፍሬዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ በዚያ ምንባብ ውስጥ በመንፈስ እንድንሄድ ተጠርተናል፡፡ ሁሉም አማኞች አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ምንባብ ለእሱ ቁጥጥር እየተገዛን በመንፈስ መሄድ እንደሚገባን ይነግረናል፡፡ ይህ በቋሚነት መንፈስ ቅዱ በህይወታችን ውስጥ ሥጋን ከመከተል ይልቅ በተከታታይ የመንፈስ ቅዱስን ምሪት መከተል መምረጥ ማለት ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ ማድረግ የሚችለው ልዩነት፤ በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላቱ በፊት ኢየሱስን ሦስት ጊዜ በካደው በጴጥሮስ ህይወት ታይቷል፤ እናም ከዚህ በኋላ ክርስቶስን እስከሞት ድረስ እንደሚከተለው ተናግሮ ነበር፡፡ በመንፈስ ከተሞላ በኋላ በጴንጤቆስጤ በዓል ላይ በአደባባይ በድፍረት ለአይሁዶች ነገራቸው፡፡
የመንፈስን ምሪት ላለማጥፋት ለመሞከር በመንፈስ እንሄዳለን (በ1ኛ ተሰሎንቄ 5፡19 እንደተነገረው) እና በምትኩ በመንፈስ መሞላትን እንፈልግ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21)፡፡ አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ እንዴት ይሞላል? በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደነበረው ከሁሉ በፊት የእግዚአብሔር ምርጫ ነው፡፡ እሱ እንዲከወን የፈለገውን ሥራውን የሚያስፈፅሙ ግለሰቦችን መረጠ እና በመንፈሱም ሞላቸው (ኦሪት ዘፍጥረት 41፡38፤ ኦሪት ዘፀአት 31፡3፤ ኦሪት ዘዳግም 24፡2፤ 1ኛ ሳሙኤል 10፡10) በእግዚአብሔር ቃል ራሳቸውን እየሞሉ ያሉትን እነዚያን ሊሞላቸው እንደሚመርጥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21 እና ወደ ቆላስያስ ሰዎች 3፡16 ውስጥ ማረጋገጫ አለ፡፡ ይሄ ወደ ሁለተኛው መንገድ ይመራናል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል፤ መጽሐፍ ቅዱስ፤ እግዚአብሔር ለየትኛውም በጎ ሥራ ሁሉ እኛን ለማስታጠቅ ቃሉን ሰጥቶናል ይላል (2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16-17)፡፡ እንዴት መኖር እንዳለብን እና ምን ማመን እንዳለብን ያስተምረናል፣ የተሳሳቱ ጎዳናዎችን በመረጥን ጊዜ ይገልጥልናል፣ ወደ ትክክለኛውም ጎዳና እንድንመለስ እና በዚያ ጎዳና እንድንቆይም ይረዳናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሕያው እና የሚሰራ እንደሆነ፣ ሥር ለመስደድ ወደ ልቦቻችን ዘልቆ ለመግባት እና ጥልቅ የሆኑትን የልባችንን ኃጥአቶች እና አመለካከቶችን ማሸነፍ እንደሚችል ወደ ዕብራውያን ሰዎች 4፡12 ይነግረናል፡፡ ዘማሪው በመዝሙረ ዳዊት 119 ውስጥ ስለ እሱ የህይወት ቀያሪነቱ ኃይል በጥልቀት ይናገራል፡፡ ኢያሱ ጠላቶቹን የማሸነፍ ውጤታማነት ቁልፉ ይህንን መንገድ ያለመርሳት እንዳልሆነ ነገር ግን በምትኩ በቀን እና በማታ ማሰላሰል እና እሱን መታዘዝ እንደሆነ ተነግሮታል፡፡ እግዚአብሔር ባዘዘ ጊዜ እንኳ በውትድርናው ስሜት የማይሰጥ ነገር ባይሆንም ይህን አደረገ፤ እና ይሄ ለተስፋይቱ ምድር ላደረገው ጦርነት የድሉ ቁልፍ ነበር፡፡
እኛ ራሳችን ብዙውን ጊዜ በቀላሉ የምናየው መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱሶቻችንን በመሸከም ወይም የቀን ጥሞና ወይም በቀን አንድ ምዕራፍ እያነበብን ምልክታዊ አገልግሎት እንሰጣለን፣ነገር ግን እሱን ማሰቡን ፤ እሱን ማሰላሰሉን ወይም በኑሮዎቻችን ላይ ተግባራዊ ማድረጉን ትተናል፣ እሱ የሚገልጣቸውን ኃጥአቶቻችንን መናዘዝ ወይም ለእኛ ለሚገልጣቸውን ስጦታዎች እግዚአብሔርን ማመስገን ትተናል፡፡ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ በሚመጣበት ጊዜ እኛ ብዙውን ጊዜ ምግብ ያስጠላቸው ወይም አመጋገባቸው የተዛባብን ነን፡፡ ከቃሉ በመመገብ በመንፈሳዊው እንዲያው በህይወት እንዲያቆየን ያህል (ነገር ግን ጤናማ እና የሚፋፉ ክርስቲያኖች እንድንሆን ፈጽሞ የሚበቃንን ያህል አንበላም) ወይም ብዙ ጊዜ ልንመገብ እንመጣለን ነገር ግን መንፈሳዊ ምግብን ከእሱ ለማግኘት ለረጅም ጊዜ በፍጹም አናሰላስለውም፡፡
እሱ ጠቃሚ ነው፣የእግዚአብሔርን ቃል በየቀኑ የማጥናትና የማሰላሰል ልምድ ካላደረግህ ያን ማድረግ ትጀምራለህ፡፡ ጥቂቶች የሚረዳ ጅማሬ ሆኖ አግኝተውታል፡፡ ከእሱ ያገኘኸውን አንድ ነገር እስከምትጽፍ ድረስ ቃሉን ላለመተው ልምድ አድርገው፡፡ ጥቂቶች እነርሱን በተናገራቸው ዙሪያ ይለወጡ ዘንድ እንዲረዳቸው በመጠየቅ ወደ እግዚአብሔር የሚደረጉትን ፀሎቶች ይመዘግባሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሕይወታችን ውስጥ መንፈስ የሚጠቀምበት መሳሪያ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡17)፤ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ውጊያዎቻችንን እንድንዋጋ የሰጠን ጠቃሚ እና ዋነኛ የጦር ዕቃ አካል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡12-18) ነው፡፡
በኃጥአት ላይ ለምናደርጋቸው ውጊያዎቻችን ሦስተኛው ዋነኛ መንገድ ፀሎት ነው፡፡ አሁንም ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች የከንፈር አገልግሎት የሚሰጡበት መንገድ ነው ነገር ግን ጥቅሙን ደካማ ያደርጋል፡፡ የፀሎት ስብሰባዎች፣ የፀሎት ጊዜያቶች ወ.ዘ.ተ. አሉን ነገር ግን ጸሎትን የጥንቷ ቤተክርስቲያን በምትጠቀምበት መንገድ አልተጠቀምንበትም (የሐዋርያት ሥራ 3፡1፣4፡31፣6፡4፣13፡1-3)፡፡ ጳውሎስ ያገለግላቸው ለነበሩት እንዴት ይፀልይ እንደነበር በተደጋጋሚ ይጠቅሳል፡፡ እግዚአብሔር ጸሎትን በተመለከተ የሚያስደንቁ ተስፋዎችን ሰጥቶናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7-11፣ የሉቃስ ወንጌል 18፡1-8፣ ዮሐንስ ወንጌል 6፡23-27፣ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)፣ እና ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ውጊያ በመዘጋጀት ምንባቡ ውስጥ ፀሎትን ያካትታል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡18)፡፡
በኑሮዎቻችን ኃጥአትን በማሸነፉ ፀሎት እንዴት ጠቃሚ ነው? ልክ ከጴጥሮስ ክህደት በፊት በጌተሰማኔ የአትክልት ሥፍራ ለጴጥሮስ የክርስቶስ የሆኑ ቃላቶች አሉን፡፡ ኢየሱስ እየጸለየ ጴጥሮስ እየተኛ ነው፡፡ ኢየሱስ አነቃውና እናም አለው “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።”(የማቴዎስ ወንጌል 26፡41) እኛ እንደ ጴጥሮስ ትክክል የሆነውን ማድረግ እንፈልጋለን ነገር ግን ጥንካሬውን እያገኘን አይደለም፡፡ መፈለጋችንን ፣ ማንኳኳታችንን፣ መጠየቃችንን ለመቀጠል የእግዚአብሔርን ተግሳጽ መከተል ያስፈልገናል እናም ያ የምንፈልገውን ጥንካሬ ይሰጠናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7)፡፡ ጸሎት ምትሃታዊ ዘይቤ አይደለም፡፡ ጸሎት በቀላሉ የእኛን የራሳችንን ድክመትና የእግዚአብሔርን የማይወሰነውን ኃይል ማረጋገጥ እና እኛ ማድረግ የምንፈልገውን ሳይሆን እሱ እንድናደርገው የሚፈልገውን ለማድረግ ለዚያ ጥንካሬ ወደ እሱ መዞር ነው (1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)
ኃጥአትን ለመማረክ በምናደርገው ጦርነታችን ውስጥ አራተኛው መንገድ፤ የሌሎች አማኞች ህብረት፤ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን በላከበት ጊዜ ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው (የማቴዎስ ወንጌል 10፡1)፡፡ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ያሉ ሚሲዮኖች በአንድ ጊዜ አንድ ሆነው አልወጡም ነበር ነገር ግን ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆነ ማህበር ነበር፡፡ ኢየሱስ አንድ ላይ መሰብሰባችንን እንዳንተው ነገር ግን ያን ጊዜ በፍቅር እና በመልካም ሥራዎች እርስ በራሳችንን ለማበረታታት እንድንጠቀምበት አዞናል (ወደ ዕብራውያን ሰዎች 10፡24)፡፡ አንዳችን ለአንዳችን ስህተታችንን እንድንናዘዝ ይነግረናል (የያዕቆብ መልዕክት 5፡16) በብሉይ ኪዳን በጥበብ መጽሐፍ ውስጥ ብረት ብረትን እንደሚስል ተነግሮናል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ሌላውን ይስላል (መጽሐፈ ምሳሌ 27፤17)። በቁጥሮች ውስጥ ጥንካሬ አለ (መጽሐፈ መክብብ 4፡11-12)፡፡
ብዙ ክርስቲያኖች የሚከብዱ ኃጥአቶችን በማሸነፉ ረገድ ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ መኖር በጣም ትልቅ ጥቅም መሆን እንደሚችል ያን አግኝተዋል፡፡ ከአንተ ጋር ሊያወራ፤ ሊፀልይ፣ ሊያበረታታህ፤ እና እንዲያውም የሚገጽህ የሚችል ሌላ ሰው ማግኘት ትልቅ ዋጋ አለው፡፡ ፈተና ለሁላችንም ያለ ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 10፡13) ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ ወይም ኃላፊነትን የሚወስድ ማህበር መኖሩ እንዲያውም በጣም ከባድ የሆኑትን ኃጥአቶችን ለማሸነፍ የሚያስፈልገንን የመጨረሻውን የማበረታቻ እና የመነሳሳት መጠን ሊሰጠን ይችላል፡፡
አንዳንድ ጊዜ በኃጥአት ላይ ድል መንሳት በፍጥነት ይመጣል፡፡ ሌላ ጊዜ ድል በጣም በዝግታ ይመጣል፡፡ እግዚአብሔር የእሱን መንገዶች ስንጠቀም ለውጥን በህይወታችን በሂደት እንደሚያመጣ ቃል ገብቷል፡፡ ኃጥአትን ለማሸነፍ ጥረታችንን በቀጣይነት መቀጠል እንችላለን ምክንያቱም እሱ በቃሉ ታማኝ እንደሆነ እናውቃለን፡፡

Thursday, June 6, 2013

የፕሬዚዳንት ሞርሲና የፓርቲዎች ጉባዔ በዐባይ ጉዳይ


መምሪ በተባለው የግብጽ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት የተደረገ ውይይት) 

የነጻነትና ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር እንዲህ አሉ፤ 

«ድምጼን አሰምቼ በግልጽ መናገር የምፈልገው ነገር ሁሉም አማራጮች ለእኛ አስፈላጊዎች መሆናቸውን ነው። እናም ሁሉንም አማራጮች እንደግፋለን፤ ነገር ግን ሂደቱ በየደረጃው መሆን ይገባዋል። የንግግር ግንኙነታችን ሂደቱን መቀየር ካልቻለ ወደዓለም ዐቀፉ የግልግል አካል እናቀርበዋለን። ይህም ካልተሳካ ማንም ሊገምተው እንደሚችለው የውሃ ዋስትናችንን ለመከላከል ወደሌላ አማራጭ እንገባለን። ምክንያቱም የውሃ ዋስትና  ለእኛ የሞት ወይም የሕይወት ጉዳይ ነውና።


የአልኑር ፓርቲ ፓርቲ ሊቀመንበር በተራቸው እንዲህ አሉ፤

አሁን እየተካሄደ ባለው የዐባይ ስምምነት ማዕቀፍ ላይ ግብጽ ከተስማማች አደገኛ ስትራቴጂካዊ ስህተት መፈጸሟ ነው። ምክንያቱም በዚህ ጉዳይ ላይ አሜሪካ፤ እስራኤልና ኢትዮጵያ ከጉዳዩ ጀርባ አሉና። ምክንያቱም በዚህ ስምምነት ግብጽን በመጉዳት ርካሽ የፖለቲካ ጫና ለማሳረፍ ሲሉ ነው። እኛም እንደእነሱ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 35%  ኦሮሞ ስለሆነና ኦሮሞም ለመገንጠል የሚዋጋለት ኦነግ የሚባል ድርጅት ስላለው ለእሱ ሁለመናዊ ድጋፍ ማቅረብ አለብን። በሀገር ቤት ያለው ፖለቲካዊ የተቃውሞ መድረክ ደካማና ልፍስፍስ ስለሆነ ለመገንጠል በሚዋጉት እንደኦጋዴን ነጻነት ግንባር ያሉትን መደገፍ ይገባናል። ይህም በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የተቀናጀ ጫና እንድናሳርፍ ያስችለናል። ይህ ሁሉ ተደርጎ  ውጤት ካላስገኘልን ሌላው አማራጭ ለግብጽ ኅልውና አደገኛ የሆነ ማንኛውንም ግድብ ለማውደም የምንችልበት ሁኔታ መፍጠር ነው። ለዚህም አስተማማኝ የደኅንነት መረጃ መኖር አለበት። ምክንያቱም አንዳንድ ጠበብቶች ግድቡን መጀመር በራሱ አደገኛና ጦርነት የማወጅ ያህል እንድንቆጥር በቂ ማስረጃ ነው እያሉን ነውና።

የአል አዝሃር ዩኒቨርሲቲ የሃይማኖት መምህር የሆኑት ደግሞ በተራቸው፤

አስታውሳለሁ፤ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ግብጽ በመጣበት ወቅት በግብጽ ሕዝብ ላይ አላግጦ ነው የሄደው። ዐባይ ክንፍ የለውም፤ ወደእስራኤልም አይበርም አለ፤ ነገር ግን ማንኛውም ህዝብ እንደሚያውቀው የግብጽ ሕዝብም ያውቃል። የዓባይ ወንዝ በቀይባህር ስር የሚሄድበት የራሱ የቧንቧ መስመር ስውር ክንፍ አለው። ማንም ሀገር በቧንቧ መስመር ውሃ ወደሀገሩ እንደሚያስገባ ይታወቃል፤ ሲሉ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን በመቃወም ዐባይ ክንፍ አለው ብለዋል።  

የገድ አልተውራ ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ተራቸውን ጠብቀው እንዲህ አሉ፤

እንደዚህ ይባል ወይም አይባል እንደሆነ አላውቅም፤ ነገር ግን አንዱ ጓደኛዬ ቅድም እንዳለው ኢትዮጵያ ብዙ ተቃዋሚዎች እንዳሏት ይታወቃል፤ እዚያም የተለየ እንቅስቃሴ እያየን ነው። የግብጽ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖሩ ምን ያደርግልናል? አስፈላጊ ነገር አሁን የፖለቲካና የመረጃ ክፍሎቻችን ብቻ ናቸው። በኢትዮጵያ ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመርኩዘን ሚና መጫወት አለብን። ይህንን ማስኬድ መቻል በትንሽ ወጪ ብዙ መስራት የሚያስችለን ሲሆን አጸፋዊ አደጋውም የቀነሰ ነው። በደንብ አድርገን በውስጥ ጉዳያቸው ብዙ መስራት ከቻልን ማዳከም ይቻለናል። አንድ የኢትዮጵያ ጋዜጣ እንዲህ አለ፤ ግብጽ የጦርነት ሃሳብ የላትም። ይህንን የማድረግ ብቃት የላትም፤ ሚሳይል የላትም፤ አውሮፕላን የላትም፤ ቢኖራትም ሱዳን በክልሏ ላይ ይህ እንዲደረግ አትፈቅድም ብሏል። በእርግጥም የሱዳኖች ሁኔታ ለእኛ በጣም የሚያሳምም ነው። ሁኔታዋ ማድረግ ከሚገባት አንጻር ሲታይ በጣም ደካማ ነው።  በእኛም በኩል መረጃ ፍሰት ችግር አለ።  ግብጽ የጦር አውሮፕላን ልትገዛ ነው፤ በአየር ላይ ነዳጅ መሙላት የሚችል አውሮፕላን አላት ወዘተ የሚሉት መረጃዎች መውጣት አለባቸው፤ በእርግጥ ባይሆንም እንኳን መረጃው በዲፕሎማሲያዊ ጥረታችን ላይ የራሱን ተጽዕኖ ያሳርፋል።

የሪፎርምና ደቨሎፕመንት ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ተራውን ተረክበው እንዲህ ዶለቱ፤

እኛ ባለን ግንዛቤ የብሔራዊ ቡድናችን ኢትዮጵያ ሄዶ ባደረገው ጫወታ ተጽእኖ በመፍጠር ማሸነፍ መቻሉን ነው። ብሔራዊ ቡድናችን የአፍሪካ ሻምፒዮን መሆኑና እጅግ በአመርቂ ውጤት ጫና መፍጠር መቻሉ በራሱ የሚያሳየው እውነትም ግብጻውያን ጫና የመፍጠር ጥበብ እንዳለን ነው። ትልቅም ተጽዕኖ የመፍጠር አቅም አለን። የግብጽን ቤተክርስቲያንና የአልሃዛር ስኮላሮችን በዚህ ጉዳይ መጠቀም እንችላለን። አንዳንዶች የጦርነት አማራጮች ሊኖር እንደሚችል ያወራሉ። የሚወራውን ነገር ለመተግበር አስቸጋሪ ነው። እንደዚህ ዓይነቱን እሳቤ መነቀፍ ይገባዋል። ከዚህ ይልቅ የግንኙነት ምህዋራችንን ከኤርትራ፤ ከሶማሊያና ከጅቡቲ ጋር ብናደርግ ለደኅንነታችን ክፍሎች ትልቅ መስክ ነው።  ይህንን ማድረግ ጥሩ ከመሆኑም ባሻገር ግንኙነት የማድረግ መብታችንም እንደመጠቀም ስለሆነ ተገቢ ነው። ተስፋችን ሲጨልም ደግሞ ሃሳባችንን መፈጸም የምንችልባቸው በተዘዋዋሪ አንድ መቶ መንገዶች ስላሉን ሁሉንም እናደርጋለን።

የኢስላሚክ ሌበር ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ምኞታቸውን ከፍ አድርገው ተናገሩ፤

እኔ ከጠላቶቻችን ጋር ጦርነት የምናደርግበት ቀን ናፍቆኛል፤ በእርግጥም ከእስራኤልና ከአሜሪካ ጋር። ጦርነቱ ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎ ተገቢውን ፍትህና እርጋታ የሚያመጣ መሆን ከቻለ። ምንም እንኳን ይህ ውይይት ምስጢራዊ ውይይት እንደመሆኑ ሁሉንም ነገር በምስጢር መያዝ ይገባናል። ውይይታችን ወደሚዲያ ሾልኮ መውጣት የለበትም። በእህታችን በባኪናም በኩል በግልጽ ከሚወጣው በስተቀር። ሕዝባዊ የሀገራዊ ደኅንነት እቅድ በግልጽ እንዲኖር እንፈልጋለን። እኛ እንዲህ ቢሆንም እንኳን………. (አቋረጡ) ቀጠሉና እሺ…..መልካም………እኔ የማነሳቸው ነጥቦች አግባብ ከመሆናቸው ጀርባ በእርግጥም ምንም ምስጢርነት የላቸውም። ውጊያችን ከአሜሪካና ከእስራኤል ጋር እንጂ ከኢትዮጵያ ጋር አይደለም። ስለዚህ ውጊያችንን ለማስኬድ ፤ ይህ የኔ ሃሳብ ነው……….( ፕሬዚዳንት ሙርሲ ጣልቃ ገቡና፤ ይህ ውይይት እኮ በቀጥታ ስርጭት እየሄደ ነው ያለው! አሉ) የኢስላሚክ ፓርቲው ሊቀመንበርም፤ እኔም የምስጢር እቅድ ወይም ፕላን ማብራሪያ እየሰጠሁ አይደለም!  ሲሉ በጉባዔው ሳቅ ሆነ።  ቀጥለውም «እኔ ያልኩትን እኮ ማንም ሀገር የሚያደርገው ነው፤ በሌሎችም ሲባል የቆየ ነው» አሉ። (የጉባዔው ረጅም ሳቅ!!)
ማንም ሀገር ለከባቢያዊ ጥቅሙ የሚያደርገው ነው። እኔ ለግብጽ ሕዝብ የምለው ማንም ተነስቶ የውሃ አቅርቦትህን ሊዘጋ አይችልም ነው። የግብጽን ሕዝብ የዓለም አደገኛው የጽንፈኝነት መንገድ እንዲገባ ካልፈለጉ በስተቀር ይህን አያደርጉም። እስኪ አስቡት 80 ሚሊዮን ግብጻዊ ውሃ ሲዘጋበት በአሜሪካና በእስራኤል ላይ ምን የሚያደርግ ይመስላችኋል?

ፕሬዚዳንት ሙርሲ፤ የልባቸውን በልባቸው ይዘው፤ በዲፕሎማሲያዊ  ቋንቋ ደስ የተሰኙበትን ገታራ ውይይት አለዝበው እንዲህ ሲሉ ደመደሙ።  

«እኛ ለሰሜንና ደቡብ ሱዳናውያን የከበረና የተትረፈረፈ አክብሮት አለን» አሉና የሱዳንን ዳተኝነት ሸነገሉ። «ውሳኔዎቻቸውን ሁሉ እናከብራለን» ሲሉ በማሞካሸት ጠላት ማፍራት እንደማይገባ በውሰጠ ታዋቂ ጠቆሙ። እንደዚሁም ሁሉ «ለኢትዮጵያ ሕዝብም ያለን አክብሮት ተመሳሳይ ነው!» አሉና ዙሪያ ገባህን እሳት እንለኩሳለን ሲል ለቆየው ጉባዔ ማለስለሻ ቫዝሊን ቀቡት። እኛ የትኛውንም ጀብደንነት ጀማሪዎችና በማንም ላይ አሳቢዎችም አይደለንም አሉ። ነገር ግን አሉ ፕሬዚዳንት ሞርሲ፤ ነገር ግን መታወቅ ያለበት  እያንዳንዷን የዐባይ ውሃ ጠብታ ለመከላከል እጅግ የጠነከረ እርምጃ የምንወስድ መሆናችን ነው። ለእያንዳንዷ ጠብታ ውሃ!
(ተፈጸመ)