Wednesday, March 14, 2012

ሃይማኖት፤ፍልስፍናና ሳይንስ!

ሃይማኖት፣ፍልስፍና እና ሳይንስ ምንና ምን ናቸው?

የካቲት 28/2012
ሃይማኖት፣ ፍልስፍና እና ሳይንስ ግኑኝነት ያላቸው ፅንሳተ ሐሣባት ናቸው ወይስ የተለያዩና የማይገናኙ? ተያያዥ ፅንሳተ ሐሣብ ከኾኑ ግኑኝነታቸው እንዴት ነው? በተመጋጋቢነት ወይስ በሌላ? በተመጋጋቢነት ከኾነ የትኛው መሠረት የትኛው ደግሞ ቅርንጫፍ ይሆናል? (የትኛው ለየትኛው መጋቢ ይሆናል?) የተለያዩ ከኾኑስ ተቃራኒ ናቸው ወይስ ሌላ ነው የመለያየታቸው ምሥጢር?
የሃይማትን፣ የፍልስፍናን እና የሳይንስን ግንኙነትና መለያየት ለማሳየት ብዙዎች ሦስቱን የሥነ አመክንዮ ሕግጋት እንደሚጠቀሙ ይታወቃል፡፡ በተለይም ሃይማኖትን ከፍልስፍና እና ከሳይንስ ጋር ይቀረናል ለማለት የሚጠቀሙት ያለ መቃረን ሕግን (Law of non-contradiction) ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ጽሑፍ መጀመሪያ የፍልስፍናን እና የሃይማኖትን ልዩነትና አንድነት በእነዚህ ሕግጋት በመገምገም፤ የሳይንስንና የሃይማትን ወይም የፍልስፍናንና የሳይንስ ግንኙነት በዚያ መንፈስ ወስደን አጠቃላይ ያላቸው ግንኙነት ምን እንደሚመስል በማነጻጸር እንመለከታለን፡፡
በዚህ መሠረት ሦስቱን የሥነ አመክንዮ ሕግጋትን በመጠቀም የሃይማትንና የፍልስፍና ግንኙነትና ልዩነት ምን እንደሚመስል እንቃኝ፡፡ ለማስታወስ ያህል እነዚህ የሥነ አመክንዮ ሕግጋት ሦስቱ የአስተምህሮ ሕግጋት (Laws of thought) በመባል ይታወቃሉ፡፡ በእንጊሊዘኛው በአንድነት አስቀምጠን ብናያቸው ‹‹“A” is “A” or “A” is not “non-A” but “A” can not be “A” and “non-A” at the same time and the same respect.›› የሚል ዐ.ነገር ይኖራቸዋል፡፡
  1. የኑባሬ ሕግ- Law of identity
በዚህ ሕግ መሠረት አንድ ነገር በተመሳሳይ ጊዜ፣ ኹኔታና ቦታ መኾን የሚችለው ያው ራሱን ብቻ ነው፡፡ በፊደል ብንወክለው ‹ሀ› ማለት ‹ሀ› ነው ማለት ይሆናል፡፡ ወይም ‹‹“A” is “A” or “A” is not “non-A”›› ማለት ነው፡፡
በዚህ ሕግ መሠረት ሃይማኖትና ፍልስፍና የሚኖራቸው ገለጻ ‹‹ሃይማኖት› ማለት ሃይማኖት ነው፡፡›› የሚል ወይም ‹‹ፍልስፍና› ማለት ፍልስፍና ነው›› የሚል ይዘት ነው፡፡ በሌላ በኩልም ቢኾን ‹‹ሃይማኖት› ማለት ‹ሃይማኖት ያልኾነ› ማለት አይደለም፡፡›› ተብሎ ሊገለፅ ይችላል፡፡ ‹ሃይማኖት ያልኾነ አይደለም› ማለት ‹ሃይማኖት ነው› ማለት ነው፡፡ የፍልስፍናም በዚህ መልክ ይገለጻል፡፡ ስለኾነም ሕጉ የሚገልጸው አንድን ፅንሰ-ሐሳብን ብቻ ነው፡፡ በዚህ ሕግ ተመሥርቶም የሃይማኖት ምንነት ብቻ ወይም የፍልስፍና ምንነት ብቻ ማብራራት ይቻላል እንጂ ሁለቱን ፅንሳተ-ሐሳብ በማነፃፀር ወይም በማቃረን መግለፅ አይቻልም፡፡ ይህ በመኾኑም ይህንን ሕግ ተጠቅመን ሃይማኖትና ፍልስፍናን መከፋፈል አንችልም፡፡
  1. ያለ መቃረን ሕግ- Law of non-contradiction
አንድ ነገር (ሰው፣ ፍጥረት፣ ክስተት፣…) በአንድ ጊዜ፣ ኹኔታና ሥፍራ ራሱንና ሌላውን መኾን አይችልም፡፡ በፊደል ሲቀመጥ ‹‹ሀ› ራሱን ‹ሀ›ን እና ‹ሀ ያልኾነ›ውን መኾን አይችልም፡፡› ማለት ይሆናል፡፡ ወይም ‹‹“A” can not be “A” and “non-A” at the same time and in the same respect.›› የሚል ገለጻ አለው፡፡
በዚህ ሕግ መሠረት ሃይማትና ፍልስፍና የሚኖራቸው ግኑኝነት‹‹ሃይማኖት›ራሱን ሃይማኖትና ‹ሃይማኖት ያልኾነ› መኾን አይችልም፡፡› ወይም ‹‹ፍልስፍና› ራሱን ፍልስፍና እና ‹ፍልስፍና ያልኾነ›ን መኾን አይችልም›› ማለት ይሆናል፡፡ ብዙን ጊዜ ግን በተለምዶ ‹ፍልስፍና እና ሃይማኖት ተቃራኒ ናቸው› በሚል ለመከራከር ይህንን ያለ መቃረን ሕግ ሰዎች ይጠቀሙበታል፡፡ አቃርኖ ማስቀመጥ ግን ትክክል አይደለም፡፡ ምክንያቱም፡-
i. ‹ሃይማኖት ያልኾነ› የሚለው ሐረግም ከሃይማኖት ውጭ ያሉ ፅንሳተ-ሐሳብን ይወክላል እንጂ ‹ፍልስፍና› ማለትን ብቻ አይገልፅም፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ‹ፍልስፍና ያልኾነ› የሚለው ፅንሰ-ሐሣብም ከፍልስፍና ውጭ ያሉ ፅንሣተ-ሐሣብ ሁሉ ይወክላል እንጂ ‹ሃይማኖት› ማለትን አይገልፅም፡፡ ‹ፍልስፍልና ያልኾነ ሃይማኖት ነው› ወይም ‹ሃይማኖት ያልኾነ ፍልስፍና ነው› ማለትም ሕጋዊ አገላለጽ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ‹ሀ ያልኾነ› ‹ለ› ነው ማለት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ‹ሀ ያልኾነ› ማለት ከ‹ሀ› ውጭ ያሉትን ሁሉንም ወይም የተወሰኑትን ፊደላት ሊወክል ይችላልና፡፡ ስለዚህ የፍልስፍና እና የሃይማኖት ፅንሣተ ሐሳብን በተቃራኒት መግለፅ መርሃዊ አጠቃቀም አይደለም፡፡
ii. ፍልስፍና እና ሃይማኖት ተያያዥ ፅንሣተ ሐሣብ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ሥነ መለኮት (Theology) የሚባለው የሃይማት አስተምህሮ ከፍልስፍና ትምህርት ክፍላት አንዱ መኾኑ ይታወቃል፤ ሞራላዊነትም የሃይማኖት ክፍል የኾነ የፍልስፍና ቅርንጫፍ ነው፤ እንዲሁም በምሥጢረ ህላዌ(Ontology) ሁለቱም ፅንሣተ ሐሣብ ግንኙነታቸው የጠበቀ ነው፡፡ ይህ በኾነበት ምንም ዓይነት የፅንሠ ሐሣብ ግንኙነትና አንድነት የሌላቸው አድርጎ ‹ፍልስፍና ያልኾነ ሃይማኖት ነው› ወይም ‹ሃይማኖት ያልኾነ ፍልስፍና ነው› የሚል አቀራረብ አግባባዊ የኾነ ያለ መቃረን ሕግ መሠረት የለውም፡፡
  1. የማዕከል መገለል ሕግ- Law of excluded middle
አንድ ነገር ወይ እሱው ያ ነገር ነው ወይም እርሱን ያልኾነ ነገር ነው፡፡ በፊደል ሲቀመጥ ‹‹ሀ› ወይ ‹ሀ› ወይም ‹ሀ ያልኾነ› ነው›› የሚል ይሆናል፡፡ በእንግሊዘኛው ለማሳየት ‹‹“A” is “A” or “non-A”›› የሚል ዐ.ነገር ይሠጠናል፡፡ ስለዚህ አንድ ነገር ወይ ራሱን መኾን ወይም ያለመኾን ኹለት አማራጮች ብቻ ይኖሩታል ማለት ይሆናል፡፡ የዚህ ሕግ ፅንሠ ሐሳብ ከሁለት አማራጮች ውጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ በመለያየት ያስቀምጣል፡፡ ለምሳሌ ‹ጥቁር ወይም ጥቁር ያልኾነ›፣ ‹ወይ እውነት ወይም ሐሰት›፣ ‹ሃይማኖት ወይም ሃይማኖት ያልኾነ›… ዓይነት አገላለፅ ነው ያለው፡፡
ይህንን ሕግ ተጠቅሞም ሃይማኖትና ፍልስፍናን መለያየት አስቸጋሪ ነው የሚኾነው፡፡ ምክንያቱም የሁለቱን ፅንሣተ ሐሣብ ግንኙነትና መለያየት በአግባብ ለማስቀመጥ አያስችልም፡፡ ‹ሃይማኖትና ፍልስፍና ግንኙነት አላቸው ወይስ የላቸውም?› የሚል ጥያቄ ብናነሣ መልሳችን ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም የሚል ሊኾን አይችልም፡፡ የተወሰነ ግንኙነት የሚኖራቸው ከኾነም ሕጉ የሃይማኖትና ፍልስፍናን መገናኛ በጥሶ አንዱን እውነት ሌላውን ግን ሐሰት በማለት ማስፈረጅ አያስችልም ማለት ነው፡፡ ፍልስፍና እና ሃይማኖት ደግሞ (ከላይ በመቃረን ሕግ እንደጠቀስነው) የሚገናኙባቸው የዕውቀት (አስተምህሮ) ክፍሎች አሏቸው፡፡ ስለዚህ ሌላ ፅንሠ ሐሣብ እንደሌለ በመቁጠር ሁለቱን ብቻ ባማራጭነት ወስዶ አንዱን እውነት ሌላውን ግን ሐሰት፤ አንዱን ትክክል ሌላውን ግን ስህተት አድርጎ መፈረጅ አግባብነት የለውም፡፡
ከዚህ በላይ ባየነው መሠረት ሃይማኖትና እና ፍልስፍናን አቃርኖ መከራከር አይቻልም፡፡ ስለዚህ ሥነ አመክንዮዊ የአስተምህሮ ሕግጋት ተጠቅሞ ሃይማኖትና ፍልስፍና የሚቃረኑ ወይም ምንም ግንኙነት የሌላቸው አስመስሎ ማቅረብ አግባብ አይደለም፡፡ ምክንያቱም አንደኛ ሕግጋቱ የአንድን ፅንሠ ሐሣብ ኑባሬ፣ ከሌሎች ፅናሣተ ሐሣብ መለየትና ያለውን አማራጭነት ያስቀምጣሉ እንጂ ከሌላ አንድ ፅንሠ ሐሣብ ጋር የሚኖረውን የግንኙነት መስተጋብር እና ቀጥታ መቃረን መቻል አይገልፁም፡፡ ስለዚህ ሃይማኖትና ፍልስፍና ይቃረናሉ፣ ፍልስፍና ካነበብክ ሃይማኖትህን ትክዳለህ እና የመሳሰሉ ገለጻዎች ሥነ አመክንዮአዊ መሠረት የሌላቸው ያለማወቅ አገላለፆች ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ በዚህ መልክ ‹የሃይማኖትንና የሳይንስን›፣ ‹የፍልስፍና እና የሳይንስን› ፅንሣተ ሐሣብ መተንተንና ማብራራትም ይቻላል፡፡ ኾኖም ያንንም ከዚህ በላይ በተመለከትነው መንፈስ መቃኘትና መረዳት ይገባናል፡፡ ያለበለዚያ የአገላለፅ ድግግሞሽ ይኾንብናል፡፡ ዋናው የሕግጋቱን አጠቃቀም መረዳት ነው፡፡
ይህ ከኾነ የሃይማኖት፣ የፍልስፍና እና የሳይንስ ግንኙነት ምን ይመስላል?› ለሚለው ጥያቄ የሚከተለው ሰንጠረዥ በማነፃፀሪያነት ማየት ይቻላል፡፡
መሠረቱ
ሃይማኖት
ፍልስፍና
ሳይንስ
መሠረታዊ ትርጉሙ
መሠረታዊ ትርጉሙ ማመንና መታመን ነው፡፡
ጥበብን (እውነትን፣ ዕውቀትን) ማፍቀርና መሻት ወይም በጥበብ መደነቅ ነው፡፡
የቁስ አካል አፈጣጠርንና አሠራርን የማስተዋል፣ የመፈተንና የመተንተን ሥርዓታዊ አስተሳሰብ ነው፡፡
መሠረታዊ ጥያቄው
በማን?› በሚል ጥያቄ መልስ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
ምን?› የሚለው ጥያቄ መነሻው ነው፡፡
እንዴት?› የሚለው የፍልስፍና ጥያቄ መልስ ማረጋገጪያ ነው፡፡
የጥናት ወሰኑ (አድማሱ)
ረቂቃንና ግዙፋን አካላት መኖራቸውን ይቀበላል፡፡ እምነትን፣ ዕውቀትን፣ ሥነ-ምግባርንና አተገባበሩን ያጠቃልላል፡፡
የጥናቱ መሠረት ምሥጢረ ህላዌ (ontology)፣ የጥናት ስልቱ የሥነ አመክንዮ ሕግጋት፣ መቋጫውም ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ያለው መልስ ነው፡፡ መልስ ላልተሰጠው ለየትኛውም የሳይንስ ዕውቀት መሠረት ነው፡፡
የግዙፋን አካላት (ፍጥረታት) መኖርና ቁሳዊ ጥቅሞች ላይ ብቻ ያተኩራል፡፡ የእነሱም ዕውቀትና አተገባበር ያካልላል፡፡
የዕውቀት ምንጩ
ዕውቀት የሚገኘው በራስ በሚደረግ ምርምር ብቻ ሳይኾን በአምላክ ገላጭነትም ጭምር ነው ይላል፡፡
እንደይታው ይሆናል፡- በሰው ልጅ ላይ ቀድሞ ተጽፎበታል ወይም በልምድ ይሰበስበዋል ወይም በሁለቱም ማግኘት ይችላል የሚል፡፡
ዕውቀትን ማግኘት የሚቻለው በራስ በሚደረግ መመራመር ብቻ ነው ብሎ ያምናል፤ በተለይም በልምድ በመሰብሰብ፡፡
የመኖር ዋስትናው (ግቡ)
ከሞት በኋላ ሕይወት ይኖራል ይላል፡፡
በአብዛኛው እርግጠኛ መኾን አይቻልም፡፡
ከሞት በኋላ ሕይወት መኖሩን አይቀበልም፡፡
መሠረታዊ ዶግማዎች
ቋሚ የማይለወጡ ዶግማዎች አሉት፡፡ ለምሳሌ የእግዚአብሔር መኖር፣ ፍጥረትን መፍጠሩ፣ ጠባቂነቱና መግቦቱ፡፡
በየትኛው ነገር ህልውና፣ ተፈጥሮ፣ አሠራር እና አረዳድ (ዕውቀት) ላይ ጥያቄ ያነሳል፡፡ እርግጠኛ ባለመኾን በሃይማትና በሳይንስ መሃል ይዋዥቃል፡፡
እንደ ሁኔታው መሻሻል ወይም መለወጥ መሠረታዊ መርሁ ነው፡፡

Tuesday, March 13, 2012

ፕሬዚዳንት ግርማ አረፉ? ወይስ ዳኑ?



አዲስ አበባ ሲቲ ኦንላይን እንደዘገበው ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በተወለዱ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ዘግቧል።(አዲስ ነገር ኦንላይን ዘገባውን ከደረገጹ ከሰዓታት በኋላ ሰርዞታል)
በተለያዩ ድረ ገጾች ማለትም ኢሳት ቲቪ፣ድሬ ትዩብ፣ ኢትዮ ትዩብ፣ ደ ብርሃን፣ዘሐበሻ ብሎግና የቦ የመሳሰሉት ድረ ገጾች ፣ከአዲስ አበባ ኮሪያ ሆስፒታል ወደሳውዲ አረቢያ መጓዛቸውና እዚያው እንዳረፉ ያወጡት ዘገባ እስካሁን እንዳለ ነው።
ይሁን እንጂ የመንግሥት የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቃለ አቀባይ ለቪኦኤ አሁን ማምሻውን በሰጠው መረጃ ፕሬዚዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የገለጸ ሲሆን በመንግስታዊው ቴሌቪዥኑ ደግሞ በቅርቡ እንደሚመለሱ ተነግሯል።


ሰበር ዜና; ነጭ ለባሹ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሠራዊት አቡነ ገብርአልን ለማስወገድ የመከረ አስቸኳይ ስብሰባ አካሄደ



በሀዋሳ የተሰደዱት ምዕመናንና ምዕመናት ላይ አስቸኳይ ርምጃ ለመውሰድ ዝቷል

"ማኅበረ ቅዱሳን" የልዩ ልዩ የጥዋ ማኅበራት ሰብሳቢዎችን (ሙሴዎችን) እና የሀዋሳ ማዕከል ኃላፊዎችን ያካተተ ነጭ ለባሽ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሠራዊት ባደረገው ድንገተኛ አስቸኳይ ስብሰባ፣ አቡነ ገብርአልን ለማስወገድ ሤራ መቋጨቱን ውስጥ ዐዋቂ ምንጮች ከወደ ሥፍራው መረጃ አድርሰውናል፡፡ ትላንት ከምሽቱ ከ12፡00 እስከ 3፡00 ሰዓት  በሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የክርስትና ማጥመቂያ አዳራሽ ውስጥ በተካሄደው ስብሰባ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ይትባረክ ታጠቅ ተገኝተዋል፡፡

መልአከ ብርሃን ይትባረክ ታጠቅ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባልና የ"ማኅበሩ" ልሳን የሆነው የስምዓ ፅድቅ ጋዜጣ ተከፋይ ዐምደኛ መሆናቸው ሲታወቅ "ማኅበረ ቅዱሳን" በድርጅታዊ አሠራር አቡነ ገብርኤልን ካስመጣ በኋላ ለሥራ አስኪያጅነት አጭቶ ያሾማቸው ምርጥ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ተላላኪ ናቸው፡፡