Friday, July 13, 2012

«ክስን፤ ጥቆማንና ዳኝነትን ለይቶ ያልወሰነ ስብሰባ!»


የታመመ ሰው ሕክምና የሚሄደው ለሕመሙ ተገቢውን ህክምና ለማግኘት ነው። ሐኪሙ፤ ከታማሚው የሚያገኘውን የቃል መረጃና በምርመራ ያገኘውን ውጤት አንድ ላይ አዋሕዶ ካልሰራ በስተቀር ፈዋሽ መድኃኒት ማዘዝ አይችልም። ቢያዝ እንኳን ለማያውቀውና መርምሮ ላልደረሰበት በሽታ የሚሰጠው መድኃኒት ከፈዋሽነቱ ይልቅ ጎጂ እንደሚሆን ሳይታለም የተፈታ ይሆናል።
እንደዚሁ ሁሉ በጥቅምት ወር 2004 ዓ/ም ላይ የቤተክርስቲያን መሪዎች ሊቃነ ጳጳሳት ስብሰባ ተቀምጠው ነበር። ታማሚውን፤ የሕመሙን ዓይነትና ለሕመሙ የተስማማ መድኃኒት ለይቶ ለመስጠት በተሰየመ አጀንዳ ላይ ውይይት አድርጎ ማዘዙን የተመለከተ መረጃ «አባ ሰላማ» በድረ ገጹ አስነብቦናል። ይህንኑ ተመልከተን አንዳንድ ጥያቄዎችን አጫረብንና በዚያ ላይ የተድበሰበሰውን አካሄድ ለመግለጥና  «ሲያውቅ የተኛ ቢጠሩት አይሰማም» እንዲሉ  መደረግ የነበረበትን አካሄድ ሁሉ ለማኅበረ ቅዱሳን ደስታ ሲባል የተተወ መሆኑን ብናውቅም ለታሪክና ለትውልድ ትልልቁን ግድፈት ለማሳየት ወደድን።

1/ የቀረበው ክስ ነው ወይስ ጥቆማ?

ሀ/ ክስ ፤/accusation/
ክስ /accusation/ በእንግሊዝኛው ፍቺ፤ አንድ ሰው ወይም ቡድን በሌላ ሰው ወይም ቡድን ላይ ሕገ ወጥ ነገር ፈጽሟል ብሎ የሚያቀርበው የሕግ መብትን የማስከበር አቤቱታ ነው።
ይህንኑ ቃል አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ እንዲህ ሲሉ በመዝገበ ቃላቸው ላይ ፈትተውታል።
«ከሰሰ- በዳኛ ተማጠነ፤ እገሌን አቅርብልኝ፤ ዳኘን አለ። በደሉን፤ ግፉን ተናገረ፤ አመለከተ፤ ጠላቱን አሳጣ» በማለት ተርጉመውታል።
ክስ በሚለው ቃል ላይ እንደ አስረጂ በቀረቡት ትርጉሞች ላይ ከተግባባን  በማኅበረ ቅዱሳን ከሳሽነት እና በተከሳሽ 7 ድርጅቶችና 16 ግለሰቦች  መካከል  ለተቀደሰው ጉባዔ ቀርቦ የታየ ነገር ነበርን? ብለን ብንጠይቅ አዎ ለማለት የሚያስችል ጭብጥ የለንም። ምክንያቱም «ክስ» የሚለውን ዐውደ ቃል ሊያሟላ የሚችል ሂደት አልነበርምና ነው። ይሁን እንጂ የሊቃነ ጳጳሳቱ ስብሰባ የሰጠው ውሳኔ እንዲህ ሲል ይናገራል።

«………….7 ድርጅቶችና 16 ግለሰቦች የቀረበባቸው ክስ በተጨባጭ በመረጋገጡ» ይላል። ማን ከሳሽ? ማን ተከሳሽ? ማን መርማሪ? ምን ዓይነት መልስና ማስረጃ ቀረቦ ታየ? የሚታወቅ ነገር የለም። በክስ አግባብና  አካሄድ ያልሄደ ሆኖ ሳለ እንዴት ነው በተጨባጭ የሚረጋገጠው? እዚያው ፍጪው! እዚያው አቡኪው! ከመሆን የዘለለ አልነበረም። ስለዚህ በየትኛውም መመዘኛ «ክስ» የሚለውን ስያሜ ለመያዝ የሚያበቃው ስላልሆነ ይህንን ስም ሲያነሱት ሊያፍሩ ይገባቸዋል። በዚህ ዘመን በተደበላለቀ ጫወታ/game/፤ ትላልቆች የተቀመጡበትን ሥፍራ ለሌሎች ዓላማ መሳካት ማዋል ያስተዛዝባል። ያሳዝናልም።

Wednesday, July 11, 2012

የግንቦቱ ሲኖዶስ ካወገዛቸው ግለሰቦች መካከል ሦስቱ ውግዘቱን በመቃወም ጠቅላይ ቤተክህነቱን ይግባኝ ጠየቁ


(ደብዳቤ የጻፉት / አሸናፊ መኮንን፣ / አግዛቸው ተፈራ እና መምህር ጽጌ ስጦታው መሆናቸው ታውቋል)
የጽሑፍ ምንጭ፤ አባ ሰላማ ድረ ገጽ
(ደብዳቤ የጻፉት / አሸናፊ መኮንን፣ / አግዛቸው ተፈራ እና መምህር ጽጌ ስጦታው መሆናቸው ታውቋል)
የግንቦቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ቤተክርስቲያንን የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ በማድረግ ያዋረደበትን ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡ ይህን የራሱን ክብር የቀነስበትን፣ በታሪክ ተወቃሽ የሚያደርገውንና ብዙዎችን ያሳዘነውን፣ የቤተክርስቲያንን ሕግና ስርአት ባልተከተለና፣ በየትኛውም መስፈርት ሲመዘን ሕገ ወጥ ሆኖ የተገኘውን ውግዘት፣ «ተወጋዦቹ» እየተቃወሙት ነው፡፡ አንዳንዶቹም ይግባኝ እየጠየቁበት መሆኑ ተሰምቷል፡፡ እስካሁን ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ለጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤትና ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት በጻፏቸው ደብዳቤዎች ተቃውሟቸውን ያሰሙትና የተላለፈባቸው ሕገወጥ ውግዘት እንዲነሳና ጉዳያቸው እንደገና እንዲታይ የጠየቁት / አሸናፊ መኮንን፣ / አግዛቸው ተፈራ እና መምህር ጽጌ ስጦታው መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ለዛሬው የዲ/ አሸናፊ መኮንንን ደብዳቤ እናቀርባለን (ሙሉውን ደብዳቤ ከዚህ ጽሑፍ በታች ያገኙታል)፡፡
እንደሚታወቀው / አሸናፊ መኮንን  እስካሁን 16 መንፈሳዊ መጻሕፍትን በመጻፍ ለበርካታ ምእመናን መጽናናትን ያመጣና እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ያስነሳው እውነተኛ የቤተክርስቲያን ልጅ ነው፡፡ መጻሕፍቱ በአብዛኛው መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ያተኮሩ፣ እየጣፈጡ የሚነበቡ፣ ሕይወትን የሚፈትሹና ለብዙዎች የመንፈስ እርካታን ያመጡ በመሆናቸው በየቤተክርስቲያኑ ደጅና የኦርቶዶክስ መጻሕፍት በሚሸጡባቸው የመጻሕፍት መደብሮች ውስጥ እየተሸጡ ለምእመናን በቅርበት የሚደርሱ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥም በስፋት የሚነበቡና የማኅበረ ቅዱሳንን የተረት መጻሕፍት ከገበያ እያስወጡ ያሉ መጻሕፍት መሆናቸውን ብዙዎች የሚመሰክሩት ሐቅ ነው፡፡
/ አሸናፊ በጻፈው ደብዳቤ በሲኖዶሱ ውሳኔ ከልብ ማዘኑን የገለጸ ሲሆን፣ የተላለፈው ውግዘት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ትምህርት ያልተከተለ፣ የቤተ ክርስቲያኗን ህግና ስርአት ያፈረሰ፣ ታሪክን ያላገናዘበ መሆኑን አትቷል፡፡ ደብዳቤው በምድራውያን ፍርድ ቤቶች እንኳ የከሳሽ ክስ ብቻ ተሰምቶ ብይን እንደማይሰጥና ለተከሳሽም ቃሉን የሚሰጥበት እድል እንደሚሰጥ ጠቅሶ፣ «ውግዘት የተካሄደው የቤተክርስቲያን እምነትና ቀኖና ተነክቷል ተብሎ ከሆነ ይህ አካሄድም የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና ያፈረሰ ነው» ሲል ይሞግታል፡፡ እርሱ አንቀጸ ብርሃን የሚባል መንፈሳዊ ማኅበር የሌለውና ዳንኤል ተሾመ የሚባልና በተሐድሶ ዙሪያ መጽሐፍ የጻፈ ሰው እንደማያውቅ የገለጸ ሲሆን፣ ማኅበረ ቅዱሳን ግን እርሱን በኑፋቄ የሚከስበት ነጥብ ሲያጣ እንዲህ አይነቶቹን የሐሰት መረጃዎች በማቀበል ሆነ ብሎ ሲኖዶሱን አሳስቷል፡፡ ማንንም ለማነጋገር የፈራ የሚመስለው ሲኖዶስም ሁሉንም ሳይጠራና ሳያነጋግር፣ ተከሳሾቹም ስለቀረበባቸው መረጃ ምላሽ እንዲሰጡ ሳያደርግ በጭፍንና በጅምላ ማውገዙ እንደዚህ ያሉ ታሪካዊ ስሕተቶችን እንዲፈጽምና ራሱ እንዲገመትበት አድርጓል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን / አሸናፊን ለመክሰስና ለማስወገዝ የተንቀሳቀሰው በዋናነት የእርሱ መጻሕፍቱ በቤተክርስቲያን ውስጥ በስፋት በመነበባቸውና ለብዙዎች የመንፈስ እረፍትንና እርካታን በማምጣታቸው ቀንቶና ተመቅኝቶ እንደሆነ ለማኅበሩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እየተናገሩ ነው፡፡ / አሸናፊ እስካሁን የጻፋቸውን 16 መጻሕፍት በግንቦት 2003 . በብፁዕ አቡነ ገሪማ ፊርማ ለሊቃውንት ጉባኤ በተጻፈ ደብዳቤ የሊቃውንት ጉባኤው ለሥራ እንዲጠቀምባቸው መመሪያ ተላልፎ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎም ማኅበረ ቅዱሳን ነገር እየሰራ / አሸናፊን ለማስወገዝ፣ ከፓትርያርኩ ጋር ግጭት ውስጥ የነበሩትን ጳጳሳት በማሳደም ውስጥ ለውስጥ ብዙ ሴራ ሲጎነጉን መቆየቱ ታውቋል፡፡ ከሰሞኑ አንዳንድ የማቅ ቀንደኛ ጳጳሳት ለምሳሌ አባ ጢሞቴዎስና አባ ዮሴፍ በሰዎች ፊት፣ አሸናፊን ያወገዙት እንደተባለው ኑፋቄ ስለተገኘበት ሳይሆን እርሱን ከፓትርያርኩ ለመነጠል በማሰብ እንደሆነ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ በተለይ አባ ጢሞቴዎስ እንዳሉት «ዲያቆን አሸናፊን ያወገዝነው ምንም ለማይጽፈው ለገብረ መድኅን (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ነው) ጽሑፍ እየጻፈለት ስለሆነ ይህን ለማስቆም ነው፡፡ በተጨማሪም / እጅጋየሁ የጻፉትንና ያሳተሙትን መጽሐፋቸውን «የጻፈው አሸናፊ ስለሆነ ነው» በማለት ማቅ የሰጣቸውን የተሳሳተ መረጃ እንደወረደ በማስተጋበት ይህም ለማውገዝ ሌላው ምክንያት እንደሆናቸው ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡ በዚህም ቤተክርስቲያኗን እንመራለን የሚሉ አንዳንድ ጳጳሳት በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ መገመት ይቻላል፡፡
ከዚህ ቀደም እውነትን በመመስከራቸውና ተከሰው ቀርበውና ተከራክረው በመርታታቸው «ጥፋተኛ» ተብለውና ቀኖና ተቀብለው ያለበደላቸው ደብረ ሊባኖስ ተልከው የነበሩትን መምህር ጽጌ ስጦታውንና መምህር ግርማ በቀለን፣ እንደ እስጢፋኖስ በድንጋይ ከወገሯቸው መካከል አንዱ የነበሩትና ዛሬ በሰዎች ፊት ያን አሳፋሪ ስራቸውን እንደጽድቅ እያወሩ የሚገኙት፣ አሁንም ከተወገዙት መካከል አንዱን ቢያገኙትም በድንጋይ እንደሚወግሩት እየዛቱ ያሉት የያኔው መነኩሴ የአሁኑ ጳጳስ አባ ዮሴፍም «/ አሸናፊ የተወገዘው እርሱን ከፓትርያርኩ ለመነጠል ተፈልጎ ነው» በማለት በሰዎች ፊት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ከዚህ ሁሉ ድራማ በስተጀርባ ማህበረ ቅዱሳን የራሱን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሯሯጥ፣ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎቹም አንዳንድ ጳጳሳት በአንድ በኩል ነውራቸውን ማቅ እንዳያወጣባቸው እርሱን ለማስደሰት፣ በሌላ በኩል አቡነ ጳውሎስን ያለ ሰው በማስቀረት በእርሳቸው ላይ ያሻቸውን ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን እንደሚያሳይ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ ያሉ ወገኖች ይናገራሉ፡፡
በሕገ ወጥ መንገድ ውግዘት ያስተላለፈው ሲኖዶስ ከሕገ ቤተክርስቲያን ውጪ ማውገዙና ሕግ ማፍረሱ ሳያንስ፣ በመግለጫው መጨረሻ ላይ የተወገዙት ይቅርታ ከጠየቁ ቤተክርስቲያን በሯ ክፍት ነው ማለቱ የተወገዙትን ወገኖች በእጅጉ እንዳሳዘነ እየተነገረ ነው፡፡ ለሕገ ወጥ አሰራሩ ይቅርታ መጠየቅና ውግዘቱን ማንሳት ያለበትም ራሱ ሲኖዶሱ ሊሆን ይገባል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ የሌሎቹን ወንድሞች ደብዳቤዎች ይዘትና ደብዳቤዎቹን በቀጣይ እናቀርባለን፡፡
የዲ/ን አሸናፊ መኰንን ማመልከቻ ለማንበብ ( እዚህ ይጫኑ )
  የሌሎቹን ወንድሞች ደብዳቤዎች ይዘትና ደብዳቤዎቹን በቀጣይ እናቀርባለን፡፡

«ቤተክርስቲያንህን እወቅ» የሚለው መጽሐፍ፤ የማኅበረ ቅዱሳን የመጽሐፍ ምንተፋ (plagiarism) ውጤት ነው


ስለማኅበረ ቅዱሳን ማንነት ገና ብዙ እንጽፋለን። የተገኙ መረጃዎችን ሁሉ እናስነብባለን። ምክንያቱም ማኅበረ ቅዱሳን ያልሆነውን ሆኖ በመታየት የዋሃንን የሚያሳስት፤ የተሳሳቱትን ወደእውነት ማወቅ እንዳይደርሱ በሩን የሚዘጋ የእውነት ሁሉ እንቅፋት ስለሆነ ነው። ከዚህ ቀደም እንደምንለው ሁሉ በቅንነትና ለቤተክርስቲያን በመቆርቆር እየተከተሉ ያሉትን የዋሃንን ሳንጨምር ነው።
ብልጣብልጦቹና መሰሪዎቹ ሲነግዱም ሆነ የሰው እውቀት ሲዘርፉ ራሳቸውን የሚደብቁት፤ ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩ አፍላ የወጣቶች ማኅበር ተደርገው እንዲታሰቡ ማታለያን በመጠቀም ሲሆን በግብር ግን ከዚህ በታች እንደቀረበው ጽሁፍ የሌላውን እውቀትና ሀብት ያለምስክር በመዝረፍ እንደራሳቸው ፈጠራ ገበያ ላይ አውጥቶ በመቸብቸብ ነው።
 የሙት ወቃሽና ከሳሽ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን እነ አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ፤ እነ ነጋድራስ ባይከዳኝ፤ እነ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ አጽማቸው እንዳያርፍ ስማቸውን በማኩሰስ ከሙት ዓለም እየጠራ መወንጀሉ ሳያንስ፤ እነዚህ ሊቃውንት አባቶች ካካፈሉን የእውቀት ማእድ እየሰረቀና በስሙ መጽሐፍ እያሳተመ ሲሸጥ ሃፍረት ያልፈጠረበት ኅሊና ቢስ ማኅበር መሆኑ ከምንም በላይ አረጋጋጭ ነው።
 ማኅበሩ ከእነዚህ መናፍቃንና ተሐድሶ በማለት ከሚከሳቸው ምሁራን መጻሕፍት ውስጥ ለምን መስረቅ ፈለገ? ቃል በቃል ከሰረቀስ በኋላ ለምን ያገኘበትን ምንጭ ያልጠቀሰ? ብለን ብንጠይቅ፤ ድሮውን ሲፈጠር ጀምሮ ማኅበሩ እውቀት በዞረበት ያልዞረ፤ በብልጣብልጥ ዘመንኛ ጥበብ የሚሸቅጥ፤ ግብረ እኩይ ማንነቱን በሚያጣፋው ነጠላ የሚሰውር፤ ከዚህም ቡጭቅ፤ ከዚያም ቡጭቅ አድርጎ የሚኖር  የዋህ መሳይ አውደልዳዮች የተሰባሰቡበት ማኅበር ስለሆነ ብቻ ነው። በአንድ ወቅት ከፕሮቴስታንቱ ከዶ/ር መለሰ ወጉ መጽሐፍ ላይ ገልብጦ አቶ ማኅበረ ቅዱሳን ስለጻፈው ጽሁፍ «አባ ሰላማ ብሎግ» በመረጃ አጣቅሶ አስነብቦን ነበር። አሁን ደግሞ  ሙት ከሳሹ አቶ ማኅበረ ቅዱሳን፤ ተሐድሶ ናቸው ይወገዙልኝ ካላቸው ከብላቴን ጌታ ኅሩይ መጽሐፍ ውስጥ እውቀት በመስረቅ ምንጩን ሳይጠቅስ ቃል በቃል በመገልበጥና ፊደላትን በማስተካከል ብቻ አሳትሞ የነገደበትን መጽሐፍ በመንቀስ «ዓውደ ምሕረት» ብሎግ እነሆ ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ይህ ነው ተዋወቁት ይለናል። በግብሩ የምትደግፉትም እፈሩ! ያፈራችሁበትም ተሸማቀቁ! ግብሩን አይታችሁ የተለያችሁትም ጥሩ ውሳኔ አድርጋችኋል። ንስሐ ማለት ከክፉ መሸሽ ነውና።
መልካም ንባብ!!

 ማኅበረ ቅዱሳን ከሚታወቅበት የክፋት ሥራዎቹ መካከል አንዱ የሰውን ጽሑፍ በመስረቅ እና የራሱ ሀሳብና እቅድ አድርጐ በሚያሳትማቸው መጽሔቶቹ፣ ጋዜጦቹ መጽሐፍቶቹ ላይ በማውጣት ነው፡፡ አንባቢ ከኔ ወዲህ ላሳር ብሎ የሚያምነው ይህ ማኅበር አይታወቅብኝም ብሎ የሰው ሥራ እየመነተፈ ከሳተማቸው መጽሐፍት መሀል ለዛሬ አንዱን እናያለን።
ይህ ሊቅ የማያስወድድ ባህሪው እያንደረደረ እና እያንቀዠቀዠ ወስዶ ይወገዙልኝ ካላቸው በርካታ ግለሠቦች መካከል የሀገራችንን የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ እድገት እዚህ ደረጃ ያደረሡ፣ 42 የሚደርሡ መጽሐፍቶችን የዳሰሱ ይልቁንም እንደነ ጎህ-ጽባሕ እና አዲስ ዓለም የተሠኙ መጻሕፍቶችን የደረሱ እና ባለ ትልቅ ራዕዩና ከዘመናቸው ቀድመው የተፈጠሩት ታላቅ ሰው ይጠቀሳሉ። እኚህ ታላቅ ኢትዮጵያዊና ኦርቶዶክሳዊ (በማ.. አጠራር ፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ ተብለው የተፈረጁ) ክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ይባላሉ፡፡ እኚህ ታላቅ አባት ከነ ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ከነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ከነ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም እና ከነ ፕሮፌስር ጌታቸው ኃይሌ ጋር ፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ ተብለው የተፈረጁ ሲሆን ማኅበሩ ይህን  ስም የሰጣቸው ስራዎቻቸውን ሁሉ ካስወገዘ በኋላ በስሙ ለማሳተም ፈልጎ ነው ወይ የሚል ጥያቄ ያስነሳል።


ማኅበሩ 1988 . ከእርሳቸው ገልብጦ ባሣተመውቤተ ክርስቲያንህን እወቅየሚለው መጽሐፍ በተለይ የቅ/ጳውሎስንና የቅ/ጴጥሮስን ታሪክ ከእነሙሉ ሥራቸው ብላቴን ጌታ ኅሩይነቅዕ ንጹህ- ዜና ሐዋርያትብለው 1923 . ካሣተሙት ወስዶ ተጠቀሞበታል። ለማሳያ ያህል የሚከተሉትን ታሪኮች እናቀርብላችኋለን፡-
1.     ዜና ሐዋርያት ገፅ 324 (1923)
Ø ቅዱስ ጴጥሮስ ፊቱ ሰፊ ሆኖ ሪዛም ነበር፣ ቁመቱም ካጭር የረዘመ ከረዥም ያጠረ መካከለኛ ነበር፡፡
v ቤተ ክርስቲያንህን እወቅ ገፅ 65 (1988)
Ø ቅዱስ ጴጥሮስ ፊቱ ሰፉ ያለ ሲሆን ረዥምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ሰው ነው፡፡
2.    ጥሩ ምንጭ ገፅ 330
Ø ቅዱስ ጳውሎስ መልኩና ሠውነቱ የምሥራቅ ሊቃውንት ቃል ለቃል ተያይዞ እንደመጣላቸው ከጻፉት መጻሕፍት ያገኘነውን ከዚህ ቀጥለን እንጽፋለን፡- ጭንቅላቱ ትልቅ ሆኖ ራሡ በራ ነበር፡፡ የሁለቱም ሽፋሉ ጠጉር የተጋጠመ ያውም የረዛዘመ ነበር፡፡ ዓይኖዋ ሰማያዊ ቀለም የመሠሉ ብሩሀን ነበሩ፡፡ አፍንጫውም ትልቅና ቀጥ ብሎ የወረደ ጉንጭና ጉንጩ የሮማን ፍሬ የመሠሉ ነበር፡፡ ጽሕሙና ሪዙም ረጃጅም ነበር፡፡ ጽሕም ማለት ከአገጭ ላይ በቅሎ ወደ ታች የሚወርደው ነው፡፡ ሪዝ ማለት ግን ከላይ ከራስ ጠጉር ተያይዞ የበቀለና ወደ ታች በጉንጭ ላይ ወርዶ ከጽሕም ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ አንገቱ አጠር ያለው ሆኖ ትከሻው ክብና ጎባጣ ነበር፡፡ እግሮቹ ከጉልበቱ ላይ የተቃረቡ ሆነው ከቅልጥሙ በታች የተራራቁ ነበሩ (ወርኃ ነበር ማለት ነው)፡፡ ቁመቱ ግን ከረዥም አጠር ያለ ከድንክ ረዘም ያለ ለአኃውን አሳቻ ነበር፡፡