Showing posts with label ታሪክ. Show all posts
Showing posts with label ታሪክ. Show all posts

Sunday, April 7, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ (ክፍል አምስት)



 የጽሁፉ ባለቤቶች (ለእስልምና መልስ አዘጋጅዎች ነው)
አንደኛው፡
የጥንቱ የመጨቆንና የማንቋሸሽ መንገድ እንደገና ተጀመረ፣ እነዚህ መንገዶች ከጣሊያን ወረራ ጥቂት ቀደም ብሎ በተከሰተው ምስጢራዊው የልጅ ኢያሱ ሞት አበቁ፡፡
ሁለተኛው፡
ሙሉ ለሙሉ አዲስ ወደ ሆነ አቀራረብ በድንገት ቀልበስ ማለት ነበር፡፡ ስለዚህም በ1935 በመጀመሪያዎቹ አካባቢ ንጉሱ ኃይለስላሴ እራሱን የተለያየ ማህበረ ሰብ አካላት መሪ አድርጎ ማቅረብ ጀመረ፡፡ እርሱም በተለያዩ ቦታዎች ላይ በታላቋ ኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት እኩልነት እንደሚኖር ንግግር አደረገ፡፡ አያይዞም በግንቦት 22 1935 ለሐረር የማህረሰብ መሪዎች ንግግርን አደረገ፡፡ የንጉስ ኃይለስላሴም ዋና መልእክት የነበረው ሁሉንም ሃይማኖቶች፣ ሁሉንም ጎሳዎች፣ በአዲሲቱ የኢትዮጵያ ሞዴል ማለትም “ክርስትያን ባልሆነው ነገር ግን ከልዩ ልዩ አካል በተውጣጣው የኢትዮጵያ ሞዴል” ውስጥ ለማካተት መሞከር ነበር፡፡ እርሱም የሁሉም ሃይማኖት እኩልነት ያለበት ህገ መንግስትን እንደሚያወጣ ቃል ኪዳንን ገባ፡፡ ሙስሊሞችን የማባበሉ የእርሱ አዲሱ ጥረት ያካተተው በአዲስ አበባ ውስጥ የአረብ ቋንቋ ጆርናል እንዲታተም እና በሚኒልክ ትምህርት ቤት ውስጥ አስተማሪ በነበረው ግብፃዊ አማካኝነት እንዲዘጋጅ የተደረገው እርምጃ ነበረበት፡፡ በመጨረሻም ቀደም ሲል በአፄ ሚኒሊክ በ1904 ቃል የተገባበትን የታላቁ መስጊድን ግንባታ ፈቀደ፡፡ በዚህም መሰረት እና በመሐመድ አሊ ኩባንያ ተፅዕኖ መሰረት የአረብ-እስላማዊ የንግድ ማዕከል በአዲስ አበባ መርካቶ ኢትዮጵያን በመደገፍ የድጋፍ መግለጫን አወጣ፡፡ በግንቦት 30 1935 በመሐመድ አል ሳዲቅ “የአገሪቱ የሙስሊም ኮሙኒቲ መሪ” በነበረው የተሰጠውን መግለጫ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት በጋዜጣው ላይ አውጥቶታል፡፡
ሦስተኛው፡
በኃይለስላሴ ተደርጎ የነበረው ሦስተኛው እርምጃ በአረብ አገሮች ውስጥ እርዳታን መፈለግ ነበር፡፡ በ1935 ውስጥ ወደ ግብፅ፣ ሊቢያና አረቢያ መልእክተኞችን ላከ፡፡ የእርሱም ዓላማ የወታደርና ሌላም ዓይነት የቁሳቁስ እርዳታን ለመጠየቅ አልነበረም፡፡ እርሱ ፈልጎ የነበረው ለእርሱ የኢትዮጵያ አዲስ ሞዴል ማለትም የሐበሻ ሕዝቦች መንግስት የስምምነት (የተቀባይነት) ምልክት እንዲሁም ከሙሶሊኒ ጋር ለሚያደርገው ትግል የሙስሊም ሕዝቦችን ድጋፍ ለማግኘት ነበር፡፡ እርሱም የተደባለቀ ውጤት ነበረው፡፡ በሊቢያ የነበረው ሚሽን ያልተሳካ ነበር ምክንያቱም የሳኑሲ የፀረ ጣሊያን እንቅስቃሴ ተደምስሶ ነበርና፡፡ በጣም ጠቃሚው ደግሞ የግብፅ ሕዝብ ነበረ፡፡ በእርግጥ ግብፃውያን በሙሶሊኒ በኩል ሊከፈት ስላለው ጦርነት ያን ጊዜ አስታዋሽ አያስፈልጋቸውም ነበር፡፡ በ1935 የኢትዮጵያና የእርሷ እጣ ፈንታ፣ በግብፅ፣ እንዲሁም በሶርያ በኢራቅና በፍልስጥዔም ውስጥ የሕዝብን አመለካከት በመካፋፈል ዋና ጉዳይና አጀንዳ ነበር፡፡
በአጠቃላይ የመካከለኛው ምስራቅ የፓን አረብ አገሮች አገር ወዳድነት እንዲሁም የእስልምና በፖለቲካው መድረክ ውስጥ መነቃቃት፤ “የኢትዮጵያ ጥያቄ” እንዲሁም ከእርሱ ጋር አብሮ ያለው ያልጠራ አመለካከት ከዚህ እንቅስቃሴ ማዕከል ውስጥ እና የማንነት ትርጉም ውስጥ ገብቶ፤ የፖለቲካ መረጋጋት በሌለበት ሰዓት እንደገና ሊተረጎም ነበር፡፡ እጅግ ብዙ የሚሆኑት ግብፃውያን ብሪቴንን ከሚያዳክም ማንኛውም ነገር ጋር ተባብረው ነበር፡፡ ብዙዎች ሌሎች ደግሞ ሙሶሊንን በመደገፍ ዝግጁዎች ሆነው በክርስትያን ኢትዮጵያ ላይ መጥፎውን ሁሉ ይመኙ ነበር፡፡ መጽሐፎችና ጽሑፎች የኢትዮጵያን ወንጀል በመግለፅ ተጻፉና በጊዜው የነበረውን የንጉሱን የኃይለስላሴ የመጨረሻ ደቂቃ ንቃት ላይ ማላገጣቸውን ቀጠሉ፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያን ይደግፉ የነበሩትም ቀላል ቁጥር አልነበራቸውም በተለይም ሳይጠቀስ የማይቀረው እና የአገሪቱን ጠቃሚ እገዛ ያመጣው በግብፅ ውስጥ “ኢትጵያን የሚመክት ኮሚቴ” መቋቋሙና መንቀሳቀሱ ነበር፣ እርሱም ሊበራሎችና አክራሪ ያልሆኑ የካይሮ ሙስሊሞች አንድነት ድርጅት ነበር፡፡ 

Wednesday, April 3, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ (ክፍል አራት)


   የጽሁፉ ባለቤቶች፤ (ለእስልምና መልስ አዘጋጅዎች ነው)

የሙሶሊኒ ግመሎች

በታዋቂው የአፍሪካ ቀንድ የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ኤሪሊች ሃጋይ በ2007 ከተጻፈውና Saudi Arabia & Ethiopia [ISLAM, CHRISTIANITY & POLITICS ENTWIND] ከተሰኘው መጽሐፍ ምዕራፍ አንድ ላይ የተቀናበረ ታሪካዊ ጽሑፍ፡፡
የክርስትያን ኢትዮጵያ መንግስት በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ጊዜ ከጣሊያን ወረራ በፊት በሰኔ 1934 ከሳውዲው ኢማም ያህያ ጋር የድሮውን ነገር ግን በጣም ጥሩ ያልነበረውን ግንኙነታዊ ድልድይ ለመመስረት ጥረት አድርገው እንደነበር ታሪኩ ይገልጣል፡፡ በአፍሪካ ቀንድ ላይ ያሉትን እስላማዊ ማህበረ ሰቦችን ያገናኘው ቀይ ባህር ከክርስትያን ኢትዮጵያ መንግስት ጋር ብዙ ግንኙነትን ለማሰራት ባለማስቻሉ፡፡ በኢትዮጵያ ነገስታትና በተለያዩ የአረብ አገር መሪዎች መካከል የነበረው የታሪካዊ ግንኙነት ታሪካዊ ዘገባ የሚመስለው ጥቂት ነበረ በማለት የታሪክ ተመራማሪው ያስረዳል፡፡ የዚህ ሰንካላ ግንኙነት እና ወዳጅነት ስምምነት መጥፋትም ዋናው ምክንያት የኢትዮጵያ መንግስት ሃይማኖት ነው፡፡
ለዚህ የወዳጅነት አለመኖር ችግር በተመለከተ የሚገኘው ታዋቂ ታሪክ በአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በንጉስ ፋሲለደስ የተሞከረው ሙከራ እንደነበረ ጸሐፊው ታሪካዊውን ማስረጃ ያቀርባል፡፡ ንጉሱ ከየመኑ ኢማም አል-ሙታዋኪ አላ አል-አላህ ጋር (በመልእክተኞቻቸው አማካኝነት) ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ውይይቱም ያጠናከረው ነገር በኢትዮጵያና ከቀይ ባህር ማዶ ባሉት አጎራባች አገሮች መካከል ጥልቅ የሆነ መሰረታዊ ችግር የመኖሩን እውነታ ብቻ ነበር፡፡ የየመኑ ኢማም የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበውን የንግድና የፖለቲካ ትብብር ጥያቄ አልቀበልም ብሎ ነበር፡፡ ምክንያቱ ምን ነበር? የየመኑ ኢማም ከኢትዮጵያ መንግስት የጠየቀው ጥያቄ ነበር፣ ጥያቄውም የሃይማኖት ለውጥ ነበር፣ ፕሮፌሰር ኤርሊች ማስረጃውን ጠቅሶ እንደሚከተለው እንደነበር አስቀምጦታል፡ ገዢውም ያለው “የኢትዮጵያው ንጉስ” ማለትም ፋሲለደስ “በቅድሚያ የነጃሺን ፈለግ መከተል አለበት” ነበር፡፡ በመሆኑም የወዳጅነት ስምምነቱ እንዲኖር ንጉሱ በቅድሚያ ሃይማኖቱን “ወደ እስልምና መለወጥ አለበት” የሚል ሰበብ ነበር፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ መሰረታዊ ችግር ነው ጥልቅ የሆነ ዘላቂ ችግር ከውጭ ብቻ ሳይሆን ከውስጥም አገሪቱን የከበባት መሆኑን የሚያሳየው፡፡

በ1930ዎቹም ውስጥ በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ለሳውዲው ንጉስ ለኢብን ሳውድ የቀረበው ጥያቄም በጣም የማይሆን እድል አጋጥሞት ነበር፡፡ በእርግጥ በዚያን ጊዜ ኢትዮጵያ ጠንካራ የሆነች የክርስትያን አገር ሆና ነበር፡፡ ስለዚህም በዋሃቢያ እምነት ላይ የተመሰረተው የሳውዲ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት የእነተባባር ትያቄ ሊቀበለው አልቻለም ነበር፡፡

ነገር ግን የአፍሪካን ቀንድና አረቦችን ቀይ ባህር ያገናኛል የሚለው ፅንሰ ሐሳብ ለጣሊያን ቅኝ ገዢዎች በጣም ጠቃሚ የነበረ ስልት ነበር፡፡ ከ1890 ዓም ጀምሮ የራሳቸውን አካባቢያዊ ማህበረ ሰብ በኤርትራ ውስጥ መስርተው የነበሩት ጣሊያኖች ማህበረሰባቸውን በቀይ ባርህ ስም ላይ የተመሰረተና “ማሬ ኤሪትርየም” የሚል ስያሜ ሰጥተውት ነበር፡፡ ጣሊያኖቹ በሁለቱም የባህሩ አካባቢ አገሮች ላይ ተፅዕኖአቸውን ለማምጣት አልመው ነበር፡፡ ስለዚህም በሙሶሎኒ ስር ይህ ረቂቅ ሃሳብ በጣም ንቁ የሆነ ፖሊሲ ሆኖ ነበር፡፡ በ1926 ሙሶሊኒ የጣሊያንን ማህበረ ሰብ በዲክታተሪያል ቁጥጥር ስር ካደረገ በኋላ ያወጀው የመጀመሪያው ነገር “የናፖሊዮናዊ ዓመትን” ነበር፣ በዚህም የፋሽስቱ መንግስት እራሱን የሚያረጋግጠው በሜዲትሬኒያን ባህር እና በቀይ ባህር ላይ እንደነበር ይፋ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በጣም ሃይለኛ የኤርትሪያ ገዢ የነበረው ጃኮቦ ጋስፓሪኒ ሁለት መልክ ያለውን ተግባሩን ጀመረ፡፡ በአንድ በኩል ጣሊያን በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገባበትን ነገር ሲያጠብቅ በሌላ ጎኑ ደግሞ ከአረቢያኖች ጋር ትብብርን ለመመስረት ጥረትን አደረገ፡፡ 
በመስከረም 1926 ላይ ጋስፓሪኒ ከየመኑ ኢማም ያህያ ጋር የትብብር ስምምነትን ፈረመ ይህም ጣሊያኖች የመኖችን እንዲያስታጥቁ መንገድን ከፈተ፡፡ 

Thursday, March 28, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ

                                        
                       (የጽሁፉ ባለቤቶች ለእስልምና መልስ አዘጋጅዎች ነው)
( ክፍል ሦስት )

መሰረታዊና ታሪካዊ ጥያቄ፡

የሼክ አብደላ ርዕዮተ ዓለም በሌላው ዓለም ውስጥ ተቀባይነት ሲያገኝና ዓለም አቀፍ ሲሆን በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዘንድ  ተቀባይነት ስለምን ሊያገኝ አልቻለም? ይህ ጥያቄ በኢትዮጵያውያን መካከል መነሳትና መብላላት ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ጥያቄ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሁሉ ሊጠየቁበት የሚገባው ጥያቄ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ጥያቄው በምንም መልኩ ቢላመጥና ቢገላበጥ የሚሰጠው መልስ ከሚከተሉት ከሁለቱ መልሶች መካከል ከአንዱ በፍፁም ሊዘል አይችልም፡
አንደኛ፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የእስልምና እምነት በጣም ጥንታዊ ወይንም የተለምዶ ብቻ ስለሆነ ነው፡ አል-አሕበሽን አይቀበልም፤ ወይንም፤
ሁለተኛ፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ስር የሰደደውና ብዙዎች የሚከተሉት የእስልምና እምነት ርዕዮተ ዓለም የዋሃቢው አክራሪ እስልምና ስለሆነ የአል-አሕበሽን ትምህርት አይቀበልም የሚሉት ብቻ ናቸው፡፡
እንግዲህ በአሁኑ ጊዜ የተነሳው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በማነው የተነሳው፣ ማን መራው፣ ዓላማው እና የወደፊት ግቡ ምንድነው የሚሉት ሁሉ መልሳቸውን የሚያገኙት ከዚህ መሰረታዊና ታሪካዊ ጥያቄ ጋር ተያይዘው ሲታዩ ብቻ ነው፡፡ ይህ ነጥብ ነው ለምናደርገው ነገርና ለምንሰጠው ድጋፍ ጥንቃቄ እንድናደርግ የሚጠራን፤ ይህ ነጥብ ነው ዛሬ ተቀምጠን የሰቀልነው ነገ ቆመን የማናወርደው እንዳይሆን የሚመክረን፣ ይህ ነጥብ ነው የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው የሚለውን አባባል አቁመን አሁን አርቀን ለማሰብ መነሳት አለብን የሚለን፡፡

የአል-አሕበሽ መሰረታዊ እምነቶች

የአል-አሕበሽ መሪ ሼክ አብደላ ለተከታዮቹ ካደረጋቸው ንግግሮች ውስጥ በአንዱ እንቅስቃሴው የሚከተለውን መሰረታዊ ርዕዮተ ዓለም ለማስቀመጥ እንደሞከረና በዚያም ውስጥ ከዋነኛው ተቃዋሚ እራሱን ለይቶ እንዳስቀመጠ ፕሮፌሰሮቹ አመልክተዋል ንግግሩም፡-
 “እኛ እስላማዊ ማህበር ነን፣ (ማህበራችን) የሚወክለውም ምንም ዓይነት የፈጠራ ልዩነት የሌለበትን ነው፣ ማለትም እንደነዚያ ከሃምሳ፣ ሁለት መቶ ወይንም ስድስት መቶ ዓመታት በፊት እንደተጨመሩት ዓይነት አይደለንም፡፡ የመጀመሪያዎቹ የሳይድ ካታብ ሐሳቦች ናቸው ... ሁለተኛዎቹ ደግሞ የመሐመድ ኢብን አብድ አል-ዋሃብ ናቸው፣ ሦስተኛዎቹ ደግሞ  የኢብን ታይሚያ ናቸው ከእነዚህ ነው አብድ አል-ዋሃብ ሐሰቦቹን ያመጣቸው፡፡ (የወሰዳቸው)፡፡ እኛ ግን አሻሪስ እና ሻፊዎች ነን፡፡ የእምነታችንም መሰረት አሻሪያ ሲሆን ሻፊያ ደግሞ የየዕለቱ መለያችን ነው፡፡” የሚል ነበር፡፡
በንግግሩ ውስጥ የጠቀሳቸውን ሰዎች እንደ ዋነኛ ጠላቶች አድርጎ ለምን እንደመረጣቸው እና ምክንያቱንም ሊቃውቱ ሲያስረዱ የሚከተሉትን ከታሪክ አቅርበዋል፡ ሳይድ ኩታብ የግብፅ እንቅስቃሴ መሪና ሊቅ ሲሆን፣ በእስልምና የፖለቲካል ሐሳቦች ላይ ሥራን በመስራት በሙስሊም ወንድማማችነትና በዋሃቢዝምን መሰረታዊ ነጥቦች መካከል ድልድይ የሰራውን መጥቀሱ እንደሆነ፡፡ ሼኩ አል-ዋሃብን እና ኢብን ታይሚያምን ሲጠቅስ ደግሞ የዋሃቢዝም መስራችና የትምህርቱ ታሪካዊ አነሳሽንና ምንጭን ማለትም ግልፅ የሆነውን ነገር ማንሳቱ ነበር ይላሉ፡፡ ኢብን ታይሚያ የ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊቅ ነበር፡፡ ዘመናዊው የፓኪስታን ፈላስፋ አቡ አል-አላ አል-ማውዱዲ የተነሳሳው በኢብን ታይሚያ እና በሳይድ ኩታብ በተሰጠው በዋሃቢያ ትምህርት ነው፣ እርሱም የሙስሊም ወንድማማቾችን የሃይማኖታዊ ሕጋዊነት በመስጠት ከ1960 ጀምሮ ወደ አክራሪ እንቅስቃሴነት የመቀየር ህጋዊነት አምጥቷል ይህም እስላማዊ ያልሆኑትን እና መሰረታዊ ያልሆኑትን ትምህርቶችና ነገሮች በማስወገድ እስልምናን ለማጥራት ተብሎ ነበር፡፡ የአል-አሕበሽ መሪ እነዚህን አስተማሪዎችና መሪዎች ከታሪካዊ አስተምህሮአቸው በመነሳት የጠቀሰበት ዋናው ምክንያት እዚህ ላይ ግልፅ ነው፣ እርሱም እነርሱ በሙሉ ያራምዱት የነበረው እስልምና ከሌሎች ጋር በሰላም ለመኖር የሚፈልግም የሚችልም እንዳይደለ ነው፡፡

Monday, March 25, 2013

በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት


ፕሮፌሰር መሥፍን ወ/ማርያም
(ክፍል ሁለት)

የዛሬዎቹ ባለሥልጣኖች በደርግ ጊዜ አልነበሩም፤ የደርግን ስሕተት በማየት አልተማሩም፤ ትምህርታን አቋርጠው ወደጫካ የገቡት ከትምህርት የሚበልጥባቸው ምኞት አጋጥሟቸው ነው፤ የትምህርት ገዜያቸውን በጫካ ባለሥልጣን በመሆን፣ እነሱው ሕግ አውጪና ዳኛ፣ እነሱው የጫካ አስፈጻሚ ሆነው ቀዩ፤ ደርግ በጠራራ ጸሐይ የሚሠራውን እነሱ በጫካ ጭለማ ሲሠሩ ቆዩ፤ በሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላም በጣም ቆይተው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን በትንሹ ተገነዘቡ፤ በጣም የተማሩ ሰዎች ጋር ሲገናኙ ማፈር አስጨነቃቸው፤ ስለዚህም ቀላሉ ነገር የተማሩ ሰዎችን አለማቅረብ፣ ትምህርታቸውን በጠባያቸው ካላጠቡ የተማሩ ሰዎች ጋር በቀር አለመገናኘት፣ እንዲያውም የትምህርትን ዋጋና ጥራት በማዋረድ አዲስ የሚመረቁት ሁሉ ለባለሥልጣኖች አንገታቸውን የሚደፉ ዓይነት እንዲሆኑ ማድረግ ዓላማ ሆነ።
የተማሩና የሠለጠኑ የጦር መኮንኖችም ተሸናፊዎች በመሆናቸው ትምህርታቸው ዋጋ እንደሌለው ማረጋጋጫ እያደረጉ የወያኔ መሪዎች በአደባባይ ተናገሩ፤ ትንሽዋ ቢምቢ ሰውን መግደል እንደምትችል ያልተገነዘቡት ከጫካ የመጡ ሰዎች በመግደል ማሸነፍን የትምህርትን ዋጋ-ቢስነት ማረጋጋጫ አደረጉት፤ የተማሩ ሰላማዊም የጦር መኮንኖችም ዋጋ-ቢስነታቸው ኑሮአቸውን በማናጋቱ በችግር ወደሌላ ሥራ ተሰማሩ፤ ወይም አገር ጥለው ተሰደዱ፤ በሰላማዊውም ሆነ በፖሊስና በጦር ሠራዊቱ የተማረ ሰው እጥረት መፈጠሩ ለወያኔ መግቢያና መደላደያ ምቹ ሁኔታን ፈጠረ።

በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት

መስፍን ወልደማርያም

ጥር 2005

ክፍል አንድ

በአለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ አንድ ልብ ያላልነው መሠረታዊ ለውጥ አለ፤ እንዲያውም የመከራችን ሁሉ ምንጭ ነው ለማለት ይቻላል፤ የመሪዎቻችን አለመማር ብቻ ሳይሆን ትምህርትን መናቅ ወይም ጭራሹኑ መጥላት ዋና ባሕርያቸው ሆነ፤ እስከደርግ ዘመን የነበሩት የአገር መሪዎች ቢያንስ የአንደኛ ደረጃውን (ዳዊት መድገም) የአገሩን ባህላዊ ትምህርት ያከናወኑ ነበሩ፤ ከዚያ በኋላ ለጨዋ ቤተሰብ ልጆች ትምህርት ማለት በቤተ መንግሥት በመዋል የሚገኝ ልምድ ነበር፤ ተፈሪ መኮንን በአሥራ ሦስት ዓመቱ ደጃዝማች የሆነውና ሥልጣን ላይ የወጣው በመወለድ ያገኘውን ዕድል በልምድ እንዲያዳብረው ነበር፤ ተክለ ሐዋርያት ከአሥር ዓመታት በላይ ሩስያ ተምሮ ሲመለስ ተፈሪ ያገኘውን አላገኘም።

በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ትውልድ ለሥልጣን መነሻ አይሆንም ነበር ባይባልም፣ ለእድገት ትምህርት አስፈላጊ መሆኑ በመታመኑ የዓየር ኃይል እጩ መኮንኖችም ሆኑ መኮንኖቹ ከደብረ ዘይት እየተመላለሱ ይማሩ ነበር፤ በማታው ትምህርት ብዙ የፖሊስና የጦር ሠራዊት መኮንኖች (ኮሎኔል ሚካኤል አንዶም ጭምር) ይማሩ ነበር፤ ማታ ከተማሩት የፖሊስ መኮንኖች ውስጥ ሁለቱ አምባሳደሮችም ሚኒስትሮችም ሆነው ነበር፤ ከሐረር አካደሚ የወጣ መኮንንም አምባሳደር ሆኖ ነበር፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አገዛዝ የደሀ ልጆች ወደሥልጣን ወንበሩ አልተጠጉም የሚሉ ካሉ የማያውቁ ናቸው፤ ትምህርታቸውን በታማኝነት ከፍነው ቀብረው ሚኒስትርና ሌላም ሹመት ያገኙ የደሀ ልጆች ብዙዎች ናቸው።

Friday, March 22, 2013

«እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ» ክፍል ሁለት


ሁለቱ እስላማዊ ርዕዮተ ዓለሞችና ትግላቸው (ጽሁፍ በእስልምና መልስ አዘጋጅዎች)

በወቅቱ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የሙስሊሞችን እንቅስቃሴ፣ ለመደገፍ፣ ወይንም ዝም ብሎ ለማየት ወይንም ለመቃወም የሚቻለው እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ምን ይመስል እንደበረ በትክክል በመገንዘብ ነው፡፡ የአሁኑ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በእርግጥ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነውን? ብዙዎችን መስሏቸዋል፡፡ በጣም የቅርቡ በኢትዮ ሚዲያ የድረ-ገፅ ጽሑፎች ላይ የቀረበው የኦክላንድ መግለጫ እንዲሁም  www.ethiomedia.com/2012_report/4059.html የቀረበው የነጃሺ ካውንስል መግለጫ፣ አሜሪካ ውስጥ ባለው በኢትዮጵያ ክርስትያንና እስላም ካውንስል በJuly 26 2012 በኢትዮ ሚዲያ ላይ የወጣው www.ethiomedia.com/2012_report/4097.html ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሁም በሌሎች ድረገፆች ላይ በተደጋጋሚ የተሰጡት መግለጫዎች በሙሉ ሁኔታውን ያቀረቡት የእምነት ነፃነት ተደፈረ ከሚል አመለካከት የተነሳ ነው፡፡
ይህንን በተመለከተ የሚጻፉትም የተለያዩ ጽሑፎች አስገራሚዎች ሆነው አግኝተናቸዋል፤ በተለይም በዚያው በኢትዮ ሚዲያ ላይ Standing up with our Moslem citizens በሚል ርዕስ በይልማ በቀለ የቀረበው ጽሑፍ ለምሳሌነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ሙሉ ጽሑፉን www.ethiomedia.com/2012_report/4554.html ማንበብ ይቻላል፡፡ አቶ ይልማ በቀለ የሙስሊሞችን እንቅስቃሴ እንደ እውነተኛ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ የገዚው ፓርቲ እነርሱን ለማፈን አንዳንድ የፈጠራ ፕሮፓጋንዳዎችን እንደተጠቀመ በማድረግ አስቀምጦታል፡፡ በእርግጥ ይልማ በቀለ እንዳለው ኢትዮጵያን የምንመኛት የሁሉም እምነት ተከታዮች በነፃነት የሚኖሩባት አገር እንድትሆን ነው፡፡ የሙስሊሞች ጥያቄና የዘመናት ዕቅድ ግን በእርሱና በመሰሎቹ ዘንድ የታየው ላይ ላዩን ከሚሆነው ነገርና  ከሞኝነትም ጭምር የተነሳ ነው ምክንያቱም ነገሩ ሁሉ እነሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡
ሙስሊሞች በተለይም በአሁኑ ተቃውሞ ውስጥ የተሳተፉት መሰረታዊ ፍላጎታቸው በእርግጥ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነውን? የአንድ አገር መንግስትስ  በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ ለመግባታ ስለምን ይገደዳል? በስልጣን ላይ ያለ አንድ መንግስት በሃይማኖት ስም የተቀነባበረና አገሪቱን ችግር ውስጥ የሚጥል አደጋ ሲመጣ እያየና መረጃዎችና ማስረጃዎች እያለውና እያወቀ ዝም ሊልስ ይገባዋል ወይ? ለዚህ ነው የተሰጡት መግለጫዎች እና ይልማ በቀለን በመሳሰሉ ሰዎች የቀረቡት ጽሑፎች ሚዛን የጎደላቸውና ታሪካዊ ምንጮችን ያላገናዘቡ የሆኑት፡፡
የዚህ ድረገፅ አዘጋጆች ካለው ውዥንብርና መወናበድ ባሻገር ያሉትን ታሪካዊ ምርምሮችን እና አቅጣጫ ጠቋሚ እውነታዎችን ማሳየት የተገደዱት ለዚህ ነው፡፡ ከገዢው ፓርቲ መርሆ የተነሳ በአገሪቱ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ የመናገርና የመጻፍ ነፃነት በእርግጥ አለ ማለት አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው ብዙ ጋዜጠኞች በእስር ላይ የሚገኙት፡፡ ሰዎች የፈለጉትን እምነት የመከተልም ነፃነት በመጠኑ የለም ማለት ይቻላል፣ ይሁን እንጂ የአሁኑ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቃውሞ እንቅስቃሴ መሰረታዊው ጥያቄ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ሊሆን አይችልም፣ ምክንያቱም የሃይማኖት ነፃነት አልተነፈጋቸውምና፡፡ እንዲያውም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሙስሊሞች ነፃነት ያገኙት በመለስ ዜናዊ አገዛዝ ስር መሆኑ ለማንም ግልፅ ነው፡፡ ታዲያ ለሙስሊሞች እንቅስቃሴ መሠረታዊው ምክንያት ምንድነው?


Friday, March 15, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ



ፎቶ ከ /britainfirst.org/


ኢህአዴግ ችግሮችን ለመፍታት የሚሞክርባቸው ጥሩ ያልሆኑ መንገዶቹና ሌላውን ለማሳመን የሚጓዝባቸው የህጻናት ጫወታ ዓይነት ስልቶቹ፤  እንከን ሲለቅም ለሚኖር ለሌላ ወገን ቀርቶ ዳር ቆሞ በአንክሮ ለሚታዘበውም ሰው ሳይቀር የሚያሳፍር ሆኖ ይገኛል። ሕዝቡ በፍርሃት ቆፈን ውስጥ ወድቆ፤ «ዝምታ ቤቴ» ቢል የወደደው መስሎት ከሆነ የውድቀቱ መጀመሪያ መሆኑ ማወቅ ይገባዋል። ለሀገርም፤ ለወገንም የማይበጅ ፍጻሜ ይኖረዋል።  የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ባደረገው ጥናትና የመረጃ ትንተና ውጤት መሠረት 2030 በዓለም ላይ በውስጣቸው በሚነሳ ሽኩቻና በአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ምክንያት ሊፈራርሱ ከሚችሉ ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ  ናት ሲል ያወጣውን መረጃ ሟርት ነው ብሎ የሚያልፍ ከሆነ ውስጡን ማየት አቅቶታል ማለት ነው። መልኳን በመስታወት ውስጥ ያገኘችው ዝንጀሮ «አቤት የፊቷ ማስቀየም፤ በዚያ ላይ የመቀመጫዋ መመለጥ» ብላ አክፋፍታ መናገሯ የሚያመለክተው ራሷ ምን እንደምትመስል ምንም ግንዛቤ የሌላት በመሆኑ ነው። የኢህአዴግም የቁጣ ፊት እያስቀየመ፤ መቀመጫው ሁሉ እየተመላለጠ መጥቶ ሳለ የሌላውን በማየት ሲሳለቅ ሀገሪቷን ይዞ እንዳይወድቅ እንሰጋለን። በተለይም በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ለፖለቲካው የሚመች ሥራ ለመሥራት ብቅ ጥልቅ ማለቱ ከእሳት ጋር መጫወት ይሆናል። ኦርቶዶክሱ ውስጥ ውስጡን ቆስሏል። የእስልምናውንም አያያዝ «ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ፤ አሁን ምን ያደርጋል፤ ድስት ጥዶ ማልቀስ» በማለት እየተናገርንበት ነው። ጀሃድ በለው፤ ግፋ በለው፤ እሰር በለው የትም አድርሶ አያውቅም። መንግሥት ሰከን ብሎ በማስተዋልና በጥበብ መጓዝ ካልቻለ ስለወደድነው አይቆምም፤ ስለጠላነው አይሞትም። ተግባር ራሱ ወደመጨረሻው ምዕራፍ ይገፋዋልና ያንን ስንመለከት የሚያሳስበን ብዙ ነገር አለ።   
ምንም እንኳን በመንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ብታተኩርም ሀገራችን ለእግዚአብሔር መንግሥት የምትታዘዝ፤ ሰላምና ፍቅር የሰፈነባት፤ ሕዝቦች በነጻነት የሚኖሩባት ሀገር እንድትሆን ካለን ዓላማ አንጻር ማኅበራዊው፤ ፖለቲካዊውና ኢኮኖሚያው ሁኔታ ያሳስበናልና እንደዜጋ በዚህ ላይም ከወገንተኝነት በጸዳ ያለውን እውነታ ብሎጋችን ትናገራለች። ኢህአዴግ እንደፖለቲካ ሽንፈት ሳይሆን ለሀገር ሰላምና መረጋጋት ሲል በየምክንያቱ ያሰራቸውን ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ሰዎች በመፍታት ትኩሳቱን ያብርድ እንላለን። አሁን ባለው ሁሉን ነገር የመቆጣጠር ግትርነትና ሥነ ልቡና ሰልቦ አደብ የማስገዛት ስልት ወንጀለኛ ቢሆን እንኳን እንደትክክል ቆጥሮ የሚያምነው ወገን ማግኘት ከማይችልበት ደረጃ ደርሷል። «ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው» እንዲሉ ከኑሮው ውድነት ጋር ተስፋ አድርጎ «ሌላ ቀንም አለ» እያለ በተስፋ የሚኖርበትን ሃይማኖት በሆነ ባልሆነው እየነካኩ ዝም ብሎ የተኛውን መቆስቆስ  ወደበጎ አያደርስም።  ለማንኛውም መንግሥት ወደክንዱ ሳይሆን ወደልቡ ይመለስ።  «እመ እግዚአብሔር ኢሐነጸ ቤተ፤ ከንቶ ይጻምዉ እለ የሐንጹ። እመ እግዚአብሔር ኢዐቀበ ሀገረ ከንቶ ይተግሁ እለ ይኄልዉ»   «እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል» መዝ ፻፳፯፤፩ ጉልበት ብቻውን ልብ ለሌለው ደርግም አልጠቀመም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከታች ለማንሳት ወደፈለግነው ጉዳይ እናመራለን። ኢህአዴግ ከሚታማበት ችግሮች አንዱ እስከአሁን ድረስ በየሚዲያው የምንሰማቸውና የምናነባቸው ነገሮች የእስልምና ሃይማኖት መብት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደተረገጠ እያስተጋቡ ሆነው መገኘታቸው ነው። ከዚህ በፊት በዚህ ጉዳይ ላይ በሁለት ክፍል ብሎጋችን ጽፋለች። እውነት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሌሎች ሃይማኖት በተለየ የእስልምና ሃይማኖት ጭቆና አለ? ብለን ጠይቀናል። ከዚያም በተለየ መልኩ በአፍሪካው ክፍለ አህጉር የእስልምና አክራሪነት እየሰፋ አልመጣም? ኢትዮጵያስ ከእስልምናው የአክራሪነት መንፈስ እንቅስቃሴ ውጪ የሆነች ሀገር ናት? ብለንም ጠይቀናል። ኢህአዴግን በመጥላት ወይም የሚጓዝባቸውን መጥፎ ስልቶች በመመልከት ብቻ ያፈጠጠውን ሀቅ መካድ ይቻላል? ብለናልም። የኢህአዴግን ድርቅናና ግትርነት ለመነቅነቅ አሁን ካለው የትኛውም አኩራፊ ኃይል ጋር አንድ መሆን ነው የሚል መርህ እውነቱን በመጨፍለቅ ወደእርስ በእርስ ፍጅት ሊያስገባን ይችላል። ስለዚህም በኢትዮጵያችን ውስጥ ስላለው የእስልምና እንቅስቃሴ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጠባዩን የተመለከተ የጥናት ጽሁፎችን የዳሰሱ መረጃዎችን ለአስተዋዮች ለማቅረብ ወደናል። እውነታውን ማሳየት ችግሩን አውቆ በጋራ የምንኖርበትን ሀገር ለመገንባት ይረዳናል። ምድሪቱን እንድንጠብቃትና እንድንንከባከባትም ከእግዚአብሔር አደራ አለብን። ዘፍ ፪፤፲፭
እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ በሚል ርዕስ ከሚቀርበው ሦስት ሰፋፊ ተከታታይ ጽሁፎች ውስጥ የመጀመሪያውን እነሆ ብለናል።

ክፍል  
             የጽሑፉ ባለቤቶችለእስልምና መልስ» አዘጋጆች ነው)