Thursday, December 29, 2011

እውነትም ፍቅር ትቀዘቅዛለች!


ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጵያ ውስጥ እስላሙ በክርስትያኑ ላይ «የአላሁአክባር» ዘመቻውን በደንብ እያስፋፋው ስለመገኘቱ ከታች ባለው ርእስ የተመለከተው የቪዲዮ ምስል ማሳያ ነው። እራሱ ክርስቲያን ነኝ የሚለው ኦርቶዶክሱ እርስ በእርሱ እየተባላ፣ እየተካሰሰ፣ የአሸናፊነት ከበሮ ለመደለቅ በአንድ ወገን ሲኖዶሱ እርስ በእርስ፣ በሌላ ወገን ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ በእነ በጋሻው ላይ የተያዘ የሞት ሽረት ትንቅንቅ፣ በእስልምናው በራሱ የሱኒና የሐነፊ ሽኩቻ በመጨረሻው ዘመን የተነገረው ትንቢት እየደረሰ ይሆን? ያስብላል። «ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል» ማቴ 24፣7ከሁሉ የሚገርመውና ትንቢቱን በትክክል የሚያረጋግጥልን ነገር ክርስቶስ በተወለደበት ቤተልሔም መቅደስ የፈረንጆቹ ገና በሁለት ወገን ጦርነት ደምቆ መዋሉ ነው። ኳኳታና የሰው ግንባር ፍንዳታ በተሰማበት አዲስ ዜማ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ክርስቲያን ቀርቶ አረሚ የማያደርገውን ፈጽመው አክብረው ዋሉ። እውነትም «ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች» ማቴ24፣12 ያለው ደርሷል። ግሪኮችና አርመኖች ተፈጣፈጡ!!