Tuesday, September 15, 2015

ተከስተ ጌትነት ለተወራበት የወሲብ ቅሌት፤ ዋሽንግተን ዲሲ ለሚታተመው ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ የሰጠው ምላሽ

እኔ ወ/ሮ ሆሳዕናን አስገድጄ አልደፈርኩም። በፍርድ ቤትም አልተከሰስኩም። ለዚህም ማስረጃ አለኝ።”
የወ/ሮ ሆሳዕና ባለቤት ባለፈው በቪ ኦ ኤ በቀረበው ፕሮግራም መግቢያ ላይ “በሚስቴ ላይ የጾታ ጥቃት ተፈጽሞባታል” ያለውና ወይዘሮ ሆሳዕናም በዚያው ፕሮግራም ላይ ቀርባ “ጉዳዩ በህግ የተያዘ ነገር ነው” ያለችው ነገር ሙሉ በሙሉ ውሸት ነው። እኔ ማንንም ሰው አስገድጄ አልደፈርኩም ምንም አይነት ክስም አልቀረበብኝም። ከወንጀል ነፃ መሆኔን የሚያሳይ ህጋዊ ማስረጃ በአሜሪካን አገር ጉዳዩ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት በጠበቃዬ አማካይነት ያገኘሁት እሷ በአሜሪካን ድምፅ ሬድዮ ቀርባ ከስሸው ጉዳዩ በህግ ተይዟል ብላ በተናገረች በሚቀጥለው ቀን ነው።

 ይባስ ብሎ በአሜሪካን ድምፅ ሬድዮ ፓስተር ተከሰተ ባለትዳር ሴት ደፍሮ ተከሰሰ የሚለውን ዜና ውሸት እና የፈጠራ ወሬ መሆኑን የሚያሳየው እኔ እነሱ ከሚኖሩበት ሚንያፖሊስ ከተማ እኔ ወደምኖርበት ወደ ዋሽንግተን ስመለስ ወደ አውሮፕላን ጣቢያ የሸኘችኝ እራስዋ ወይዘሮ ሆሳዕና ነች። በብዙ ጭቅጭቅ የ1000 (አንድ ሺህ) ዶላር የእጅ ሰዓት በራስዋ ክሬዲት ካርድ ገዝታልኛለች። ለዚህም ሌላ ህጋዊ ማሰረጃ አለኝ። በዚያን ሰአት እንኳን ልትከስኝ ቀርቶ ለወንድ ልጅ ሰዓት መስጠት እወዳለሁ ብላ እኔ ሰአት አልፈልግም እያልኳት እሷ ግን እኔ የወንድ ልጅ ሰዓት ስለሚስደስተኝ ልግዛልህ። አንተ ብትፈልግ ወደፊት በሌላ ነገር ቀይረው በማለት ከነደረሰኙ ሰጠችኝ።

አንተና ወይዘሮ ሆሳዕና እንዴት ተገናኛችሁ ጉዳዩስ እንዴት እዚህ ደረጃ ደረሰ? ብለን ላቀረብነው ጥያቄ የሰጠው ምላሽ፡ ወ/ሮ ሆሳዕናና የእኔ ባለቤት የአንድ ሰፈር ሰዎች ናቸው። ከዚያም በራስዋ በወይዘሮ ሆሳዕና ተደጋጋሚ ግፊትና ጥረት ተቀራረብን። የቤተሰባችን አካል ሆነችና አገልግሎትህን ስለምወድ እንድደግፍ ጌታ አሳሰበኝ በሚል መንፈሳዊ አካሄድ ለእኔና ለቤተሰቦቼ በተለያየ ጊዜ ስጦታ ሰጥታናለች። የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በምዕመናን በጎ ፈቃድ የፍቅር ስጦታና የአገልግሎት ድጋፍ ማግኘት የተለመደ ስለሆነ እኔም በአገልግሎት ዘመኔ እኔንና አገልግሎቴን የሚደግፉ ብዙ ደጋግ ሰዎች ስላጋጠሙኝ ወይዘሮ ሆሳዕና ያለችውንም በቅንነት ተቀበልኩት። በመጨረሻም እኔ ባለቤትህና አንተ ለምን የጋራ ቢዝነስ አንጀምርም? እኔ ገንዘብ አለኝ፣ የቤተሰብ የቢዝነስ ልምዱም ስላለኝ አንተ ደግሞ ኢትዮጵያ ታዋቂ ስለሆንክ ሦስታችን አብረን ኢትዮጵያ ቢዝነስ ብንሰራ ሊሳካልን ይችላል ብላ ጠየቀችን። እኔም ማንኛውም ዘማሪ አንደሚመኘው ከቤተክርስቲያን ምንም ነገር ሳልጠብቅ ራሴን እና ቤተሰቤን በግሌ እየሠራሁ በማስተዳደር በነፃ የማገልገል ከፍተኛ ፍላጎት ስለነበረኝ እኔና ባለቤቴ በሀሳቡ ተስማማን። እኔ እነሱ ወደሚኖሩበት ከተማ የሄድኩት እና ሆቴል ያረፍኩት ራስዋ ወይዘሮ ሆሳዕና በአሜሪካን ድምፅ ሬድዮ ቀርባ እንደተናገረችው በጋራ ስለምንጀምረው ቢዝነስ ለመነጋገር ነበር። ይህን ሀሳብ ያመጣችው እራሷ ወይዘሮ ሆሳዕና ነች።

በራሷ ገንዘብ የአውሮፕላን ትኬት ቆርጣ እራሱዋ ሆቴል ይዛ፣ (ለዚህም ማስረጃ አለኝ)። ከዚያ በኋላ አሁንም ራሷ በአሜሪካን ድምፅ ቀርባ እንደተናገረችው ያረፍኩበት ክፍል ውስጥ ገብታ ልብሷን አወለቀች። ብዙ ተፈታተነችኝ። የምሄድበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነና ሆን ተብሎ የገባሁበት ወጥመድ እንዳለ ሲገባኝ ፍላጎቱ ባይኖረኝም እሷን ሳላሳዝን ሞራልዋን ሳልነካ በሰላምና በእርጋታ ለመውጣት “በቃ አሁን እኔ መረጋጋት አልቻልኩም ፍላጎቱ የለኝም ሌላ ጊዜ ተመልሼ ልምጣና ያንቺን ፍላጐት አሟላለሁ” ብዬ ቃል ገባሁ። እሷም ተመልሼ ወደእሷ ከመጣሁና መሻቷን ከፈጸምኩ አብረን ልንሠራ ከተነጋገርንበት ቢዝነስ በተጨማሪ ለግሌ ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደምትሰጠኝ ነግራኝ ተለያየን። ካረፍኩበት ሆቴል ወደ አውሮፕላን ጣቢያ ስንሄድ ለወንድ ልጅ የሰዓት ስጦታ መስጠት ያስደስተኛል ብላ ከላይ እንደጠቀስኩት የአንድ ሺህ ዶላር ሰዓት መንገድ ላይ ወደሚገኝ ሞል ኦፍ አሜሪካ የገበያ ማዕከል ውስጥ ሜሲስ የሚባል ስቶር ወስዳ ገዛችልኝ።

አየር ማረፊያ አውርዳኝ ስንለያይ ለመጀመርያ ጊዜነጻነት ተሰማኝ። ዋሽንግተን ዲሲ ተመልሼ እቤቴ ስገባም የሆነውን ነገር ሁሉ ለባለቤቴ አንድም ነገር ሳልደብቅ ነገርኳት። ከዚያም እንደ አንድ ክርስቲያን እና እንደ አንድ አገልጋይ ከእኔ የማይጠበቅ ነገር አድርጌአለሁ ብዬ ያለማንም አስገዳጅነት በራሴ ፈቃድ ለቤተክርስቲያን ተናግሬ ወዲያውኑ ራሴ አገልግሎት አቆምኩ። በራሴ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የአሜሪካን ክፍለግዛቶች በሚገኙ አብያተክርስቲያናት እንዳገለግል የተጋበዝኩባቸውን አገልግሎቶች በሙሉ በራሴ ፈቃድ ሰረዝኩ። እኔ ወደዋሽንግተን ከመጣሁ በኋላ ወይዘሮ ሆሳዕናም እኔን በስልክ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ አደረገች ግን አልተሳካላትም። ከዚያ በኋላ የበቀል እርምጃው ግራ በሚያጋባ መልኩ መጣ።
መጀመሪያ ለእኔ ባለቤት ለወ/ሮ የምስራች ባለቤቱዋ አቶ መላኩ ደውሎ ሚስቴ ከአንቺ ባል ጋር አብራ ስለተኛች ይቅርታ ልትጠይቅሽ ነው ብሎ ስልኩን ለወይዘሮ ሆሳዕና ሰጣት። ወይዘሮ ሆሳዕናም እኔ ከባለቤትሽ ከተከስተ ጋር ተኝቻለሁ ይቅርታ አድርጊልኝ ብላ በስልክ ለእኔ ባለቤት የድምፅ መልእክት ተወችላት (ደውለው ለባለቤቴ የተውት የእሱም የእሷም የድምፅ መልዕክት ማስረጃው አለኝ)። ከዚያ ደጋግመው ደውለው ባለቤቴን አገኟትና ባልሽ ከሚስቴ ጋር ተኛ ብሎ ነገራት። ባለቤቴም በቃ ካጠፉ ይቅር እንበላቸው እና ነገሩ ይቁም አለችው።

ባለቤቴም ሁሉንም ነገር አልቀበል ስትል ወደ ቤተክርስቲያን ሄዱ። አቶ መላኩ ቤተክርስቲያን ሄዶ ፓስተር ተከስተ ከሚስቴ ጋር ተኝቷል አገልግሎት ማቆም አለበት ይቅርታ መጠየቅ አለበት አለ። እኔም የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው እና መንፈስ ቅዱስ እንደሚወቅሰኝ ከአንድ አገልጋይ የማይጠበቅ ጥፋት አጥፍቻለሁ። እግዚአብሔርንም በድያለሁ ለዛም እራሴን ከአገልግሎት አስቁሚያለሁ። እናንተንም ይቅርታ እጠይቃለሁ አልኩኝ። ሰዎቹ ዓላማቸው ክርስቲያናዊ ዕርቅ እንዳልሆነና አሳባቸውን በመቀየር ለሌላ ለተሻለ የበቀል እርምጃ ሊጠቀሙበት እንደሆነ አስቀድሜ ለሦስቱ ሽማግሌዎች ነግሬአቸው ነበር። ነገሩ በሰላም እንዲያልቅና ክርስቲያናዊ አካሄድ ነው ብዬ ስለማምን ሙሉ ኃላፊነት ወስጄ ይቅርታን ጠይቄአለሁ። አቶ መላኩ ግን የግብረሥጋ ግንኙነት ፈጽመሃልና እመን የሆነውንም ዝርዝር ነገር ንገረኝ ብሎ ጠየቀኝ። እኔም ሙሉ ኃላፊነት ወስጄ ይቅርታንም ጠይቄ የወይዘሮ ሆሳዕናን ስሜትና ስብእና የሚነካ ዝርዝር ነገር ውስጥ ግን እንደማልገባ አሳወቅሁኝ። ምክንያቱም እንደዚህ ዓይነት ነገር ያልተለመደ በመሆኑና አቶ መላኩ ማወቅ የሚፈልገውን መረጃ በሙሉ ከገዛ ሚስቱ ማግኘት ስለሚችል ነው። ቤተክርስቲያንም ፓሰተር ተከስተ ከአንድ አገልጋይ የማይጠበቅ ጥፋት አጥፍቻለሁ ብሎ በራሱ ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ገብቶአል አገልግሎትም አቁሞአል ፣አንተንም ይቅርታ ጠይቋል ነገሩ እዚህ ጋር ይለቅ ብለው ጠየቁት ። እነሱ ግን እኔን ለማጥፋት ቆርጠው ስለተነሱ ነገሩ እንዲቆም አልፈለጉም።

ቤተክርስቲያን መጥተው ያሰቡትን ያህል እኔን የጎዱኝ እና ያዋረዱኝ ስላልመሰላችው ቪ ኦ ኤ ሄደው ፓስተር ተከስተ አስገድዶ ደፍሮኛል ጉዳዩም በህግ ተይዞአል የሚል በሽምግልናው ወቅት በጭራሽ ያልተነሳ ሌላ ተጨማሪ የውሸት ታሪክ ፈጠሩ። ይህን አላማ እንዲያስፈጽም ጋዜጠኛ አዲሱ አበበን ይዘው መጡ። አቶ አዲሱ ጋር ስንነጋገር ሆን ብሎ እኔን ለማጥቃት እንዳሰበና እውነቱን ማወቅ እንደማይፈልግ ስለገመትኩ በጉዳዪ ለይ ምንም አይነት ኢንተርቪው ላንተ አልሰጥም፣ ጉዳዪም በቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ተይዟል አልኩት። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና ጉዳዩን የያዙትም ሽማግሌዎችም አቶ አዲሱን ይሄ የቤተክርሰቲያን ነገር ነው በዚህ ነገር ላይ ምንም አይነት ፕሮግራም በሬዲዩ ላይ መሥራት የለብህም ብለው እየነገሩትና እየተለመነ በማን አለብኝነት ጉዳዩን አጣሞ ሁላችሁም እንደሰማችሁት እኔን በሚያዋርድ ፣ስሜን በሚያጠፋ፣ ሕይወቴንና አገልግሎቴን በሚያበላሽ መልኩ ፕሮግራሙን ሰርቶ በሬድዮ አቀረበው። አሁንም የምለው እኔ የበደሉኝን ሁሉ ይቅር ብያለሁ። እንደ ክርስቲያንና እንደ አገልጋይ አጉድዬ በተገኘሁባቸው ጉዳዮች ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምህረትን ከባለቤቴና ከቤተክርስቲያኔ ደግሞ ይቅርታን አግኝቻለሁ። ዛሬ ደግሞ በእኔ ምክንያት ያዘናችሁትን ሁሉ ይቅርታ እጠይቃለሁ ብሏል።
አሁን እያሳየኸኝ ያለውን ማስረጃ ይዘህ ለማስተባበልና በሕግ ለመፋረድ እስከዛሬ ለምን ሙከራ አላደረግህም? ለሚለው ጥያቄም መልስ ሰጥቷል።

ሥሜንና ክብሬን በተመለከተ እኔ ሥምና የሚዋረድ ክብር የለኝም። እኔን ከጎዳና ላይ አንስቶ ሰው ያደረገኝ እግዚአብሔር ነው። ከእርሱ ውጭ በሰው የሚዋረድም የሚከብርም ማንነት የለኝም። ፍትህን በተመለከተ ደግሞ የምንኖርበት አሜሪካ የፍትህ አገር መሆኑን አውቃለሁ። የትኛውም ድርጅት፣ ባለሥልጣንም ሆነ ግለሰብ ከሕግ በታች መሆኑንም አውቃለሁ። ወንጌል አምኖ እንደዳነ ክርስቲያን ግን እግዚአብሔር ሁሉንም በጽድቅ ስለሚፈርድ ፍትህን ከእግዚአብሔር እንጂ ከማንም ሰው አልጠብቅም። ባለቤቴም ቢሆን ሁሉም ነገር በሰላምና በይቅርታ እንዲያልቅ ስለምትፈልግ ወደ ፍርድ ቤትም አልሄድንም። በዚህ አጋጣሚ ሳሚ በማያውቀውና በሌለበት ነገር በኔ ምክንያት ስለተሰቃየ ና በውሽት ስሙ ስለጠፋ በጣም ያዘንኩ መሆኔን እገልጻለሁ።

Thursday, September 10, 2015

ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ሰዎች በሁሉም ሥፍራ በአንድ ጊዜ መገኘት ይችላሉን?

ክፍል ሁለት
በክፍል አንድ ያቆምንበትን ሃሳብ ይዘን ከመቀጠላችን በፊት አንዳንድ ተቺዎች ባነሱልን ሞገት ዙሪያ ለዛሬ ጥቂት ማለት እንደሚያስፈልግ ስላመንን በዚያ ዙሪያ እንቆያለን።
 ሞጋቾቹ የሚያቀርቡት ማስረጃ በመዝሙር 34፤7 ላይ ያለውን ጥቅስ ነው።

«የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል»

ይህንን ጥቅስ በመያዝ ቅዱሳኑ መላእክት ሁልጊዜ በሰዎች ዙሪያ ሰፍረው ስለሚገኙ ማዳን፤ ጸሎት መቀበልና መልስ መስጠት የዘወትር ሥራቸው ነው ይላሉ። በሌላ ደግሞ መላእክት የሚኖሩበት ከተማ ኢዮር፤ ራማና ኤረር እንደሆነም ይናገራሉ። መላእክት ዘወትር በዚህ ምድር ባሉ ሰዎች ዙሪያ ሰፍረው የሚገኙ ከሆነ በኢዮር፤ ራማና ኤረር የሚኖሩት መላእክት ምንድናቸው? ወይስ መላእክት በሰማይም በምድርም በአንድ ጊዜ ይገኛሉ ማለት ነው? ተብለው ሲጠየቁ የመላእክትን ውሱን ተፈጥሮ ለማመን ይዳዳሉ። ነገር ግን በተግባር ይህንን ይቃረናሉ። ለምሳሌ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በተፈጥሮ ሥፍራው በሰማይ እያመሰገነ ሳለ በማእዘነ ዓለሙ ሁሉ ስሙን የሚጠሩትን  ሰዎች ልመና ይሰማል? መልስም ይሰጣል ወይ? ተብለው ሲጠየቁ አዎ ይሰማል ለማለት አያፍሩም። እንዲያማ ከሆነ ቅዱስ ሚካኤል በአንድ ጊዜ በሁሉም ሥፍራ ይገኛል ማለት ነው። ይህ ደግሞ ትልቅ ስህተት ነው። ፍጡር በተፈጥሮው ውሱን የመሆኑን ማንነት ይንዳል።

  እርግጥ ነው፤ ቅዱሳኑ መላእክት ሰዎችን ይራዳሉ፤ ያግዛሉ። ይህንን ስንል መጋቤ ፍጥረታትየሆነውን  እግዚአብሔርን በሥራ ያግዙታል ማለት አይደለም።  ይህች ያለንባት ምድር ትሁን ዓለማት በሙሉ የሚተዳደሩት በእግዚአብሔር ብቃትና ሥልጣን እንጂ በመላእክት አጋዥነት አይደለም። እግዚአብሔር ብቻውን በቂ ነው። ሁሉን ተአምራት የሠራ እርሱ ብቻውን ነው።
«እርሱ ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና» መዝ 136፤4
የተአምራትና የድንቅ ነገር ሁሉ ባለቤት እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለሆነም መላእክቱ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ አንጻር ያደረጉትን እያየን መላእክቱን በውዳሴና በስባሔ የምናቀርብላቸው አምልኮ የለም። ደግሞም ቅዱሳኑ መላእክት የሚኖሩባቸውን ዓለመ መላእክት ትተው በዚህ ምድር የሚዞሩበትም ሁኔታ እንዳለ መጽሐፍ ቅዱስ አይነግረንም። ይልቁንም ይህችን ምድር ያለመታከት የሚዞርባት ሰይጣን ብቻ ነው።
 ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የፈረጠጠ እሱ ብቻ ስለሆነ ተቆጣጣሪ አልቦ ሆኖ ይኖራል። በራሱ ፈቃድ የት፤ የት እንደሚዞር ለፈጣሪው እንዲህ ሲል እናገኘዋለን።
«እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ከወዴት መጣህ? አለው። ሰይጣንም፤ ምድርን ሁሉ ዞርሁአት፥ በእርስዋም ተመላለስሁ ብሎ ለእግዚአብሔር መለሰ» ኢዮብ 1፤7
ምድርን ለመዞር፤ በእሷ ላይም ለመመላለስ ፈቃድ አይጠይቅም። «ከወዴት መጣህ?» የሚለው የእግዚአብሔር ጥያቄ የሚያስረዳን አፈንጋጭና በፈቃዱ ያለትእዛዝ የሚዞር መሆኑን ነው። ቅዱሳን መላእክቱ ግን እንደዚህ አይደሉም። በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ሥራ አላቸው፤ ትእዛዝ ይቀበላሉ፤ ትእዛዝ ይተገብራሉ እንጂ እንደሰይጣን በሰዎች ስለተጠሩ ወይም ባይጠሩም ስለፈለጉ የትም አይዞሩም፤ ያለትእዛዝም አይንቀሳቀሱም። በሁሉም ሥፍራም በምልዓት አይገኙም።

  መጽሐፍ ቅዱስ በትንቢተ ዳንኤል ላይ የመላእክትን ውሱንነት፤ መውጣት፤ መውረድ በደንብ የሚያስረዳን ቃል እንዲህ ይላል።
«እነሆም፥ አንዲት እጅ ዳሰሰችኝ፥ በጕልበቴና በእጄም አቆመችኝ። እርሱም፦ እጅግ የተወደድህ ሰው ዳንኤል ሆይ፥ እኔ ዛሬ ወደ አንተ ተልኬአለሁና የምነግርህን ቃል አስተውል፥ ቀጥ ብለህም ቁም አለኝ። ይህንም ቃል ባለኝ ጊዜ እየተንቀጠቀጥሁ ቆምሁ። እርሱም እንዲህ አለኝ። ዳንኤል ሆይ፥ አትፍራ ልብህ ያስተውል ዘንድ፥ ሰውነትህም በአምላክህ ፊት ይዋረድ ዘንድ ካደረግህበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ቃልህ ተሰምቶአል እኔም ስለ ቃልህ መጥቻለሁ። የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት» ዳን 10፤10-13
ነቢዩ ዳንኤል ያከናወነው መንፈሳዊ ተጋድሎ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለተወደደ ስሙ ያልተጠቀሰ አንድ መልአክ የተሰጠውን መልእክት ሊነግረው መጥቷል።   መልእክቱ ለዳንኤል ከመድረሱ በፊት የፋርስን መንግሥት የተቆጣጠረው የተቃዋሚ መንፈስ አለቃ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላከውን መልአክ 21 ቀን መንገድ ላይ እየተዋጋ አዘግይቶታል። ያንንም የእግዚአብሔር መልአክ ሊያግዘው ቅዱስ ሚካኤል እንደመጣና ውጊያው ከቅዱስ ሚካኤል በዚያ እንደተወውና ወደእርሱ እንደወረደ መልአኩ ለቅዱስ ዳንኤል ሲነግረው እናነባለን።

ከዚህ ምንባብ የምንረዳው ፤
1/ መላእክት የሰዎች መልካም ሥራና ተጋድሎ በእግዚአብሔር ሲወደድ የማናውቀው መልአክ ሊረዳን፤ ሊያግዘን፤ ሊያድነን ከእግዚአብሔር ዘንድ ሊላክ እንደሚችል፤
2/ መላእክቱን ለእገዛና ለረድኤት የሚያመጣቸው የኛ ስራ በመላእክቱ ዘንድ ተቀባይነትና ተወዳጅነት በማትረፉ እንዳልሆነ፤
3/ አንድ መልአክ ወደተላከበት ስፍራ ሲሄድ የነበረበትን ሥፍራ እንደሚለቅ፤ በቦታ እንደሚወሰን፤ ባለጋራ ሊዋጋው እንደሚችል፤
4/ መላእክት እንደሚተጋገዙ፤ አንዱ ከአንዱ በኃይልና በሥልጣን እንደሚበልጥ፤
5/ መውጣትና መውረድ እንዳለባቸው፤ በሁሉም ስፍራ እንደማይገኙ ያስረዳናል።
ስለሆነም ቅዱሳን መላእክት ይራዱናል፤ ያግዙናል፤ ያድኑናል ሲባል ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር ባላቸው ግንኙነት የተነሳ በተልእኮ ሲመጡልንና ሲደርሱልን ብቻ ነው። ከዚያ ባሻገር ሰዎች ስም እየመረጡ፤ የኃይል ሚዛን እያበላለጡ ስለጠሯቸው የሚመጡ አይደለም።
እነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የሚያስረዱን በእግዚአብሔር ትእዛዝ የሚላኩ መሆናቸውን ነው።
«የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር፥ እርሱ መልአኩን በፊትህ ይሰድዳል» ዘፍ 24፤7  «እግዚአብሔር መልአኩን ከአንተ ጋር ይልካል፥ መንገድህንም ያቀናል»ዘፍ 24፤40  «እግዚአብሔርም መልአኩን አዘዘው፥ ሰይፉንም በአፎቱ ከተተው» 1ኛ ዜና 21፤27  «እግዚአብሔርም ጽኑዓን ኃያላኑንና መሳፍንቱን አለቆቹንም ከአሦር ንጉሥ ሰፈር እንዲያጠፋ መልአኩን ሰደደ» 2ኛ  ዜና 32፤21  «መልአኩን የላከ፥ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ» ዳን 3፤28  «አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶችን አፍ ዘጋ» ዳን 6፤22
አምላክ፤ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የማልኮስን ጆሮ ለቆረጠው ጴጥሮስ እንዲህ ብሎት ነበር። «
«ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን?» ማቴ 26፤53
 ለኢየሱስ በስቅለቱ ሰሞን የመያዝ፤ የመገፋት፤ የመንገላታት የመገረፍ መከራ ሁሉ ከአብ ዘንድ ትእዛዝ ሳይወጣ የሚያግዙት መላእክት አይመጡም ነበር። ፈቃዱን ሳይሆን የአብን ፈቃድ ለመፈጸም የመጣውም ይህንን ሁሉ ሊቀበል ነውና። ከዚህ ከኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት የምንረዳው እውነታ ቅዱሳን መላእክቱ ከአብ ትእዛዝ ሳይሰጣቸው የትም መሄድ የማይችሉት ወልድ የመጣው የአብን ፈቃድ ሊፈጽም ስለሆነ ነው። ተገቢ ለሆነው የሰዎች ልመናና ጸሎት የሚያስፈልገውን የሚያደርገው ሁሉን አዋቂ በሆነው በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሲላኩ ብቻ ነው።
የሰዎች ድርሻ ወደእግዚአብሔር መጮኽና መለመን ሲሆን ምላሹን ደግሞ የሚያውቀው እርሱ ብቻ ነው። «መላእክቱን በስማቸው ስንለምንና ስንማጸናቸው ይሆንልናል፤ ይደረግልናል»የሚሉ ሰዎች ቆንጽለው የሚያቀርቧት የመዝሙር 34፤7 ጥቅስ «የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል» የሚለውን ነጥለው በማውጣት ቢሆንም የዚህ አጋዥ መከራከሪያ ጥቅስ ሙሉ ማስረጃ ግን ከላይ ከፍ ባለው ቁጥርና ከታችም ዝቅ ብሎ በተጻፈው የምንረዳው፤ እግዚአብሔር ላይ ብቻ እንድንታመን የሚያደርጉ ናቸው። ሙሉ ጥቅሱ ይህንን ይመስላል።
«ይህ ችግረኛ ጮኸ፥ እግዚአብሔርም ሰማው፥ ከመከራውም ሁሉ አዳነው።
የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።
እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።
የሚፈሩት አንዳችን አያጡምና ቅዱሳኑ ሁሉ፥ እግዚአብሔርን ፍሩት» መዝ 34፤ 6-9

ነቢዩ ዳዊት በደረሰው ችግር ወደእግዚአብሔር ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤ ከመከራውም አዳነው። የእግዚአብሔርም መልአክ እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ በታዘዘም ጊዜ ያድናል። ምክንያቱም በእግዚአብሔር የሚታመኑና እሱንም የሚፈሩት አንዳች አያጡምና። ቁጥር 8 እና 9  በእግዚአብሔር መታመንና መፍራትን ገንዘብ ያደረጉ ሁሉ ምላሽ እንደሚያገኙ ያስረዳናልና።

«ቅዱሳን መላእክቱ በዚህ ምድር እየዞሩ ለሰዎች የሚራዱና የሚያግዙ በመሆናቸው በስማቸው የሚደረገውን የሰዎችን ልመናና ጸሎትም ይሰማሉ» የሚል ክርክር የሚያነሱ ሰዎች መላእክቱ በቀጥታ ታዘው ያደረጉትን መነሻ በማድረግና በማድነቅ እንጂ ቅዱሳኑ መላእክት ራሳቸው ምሥጋናንና ውዳሴን ተገቢያቸው እንደሆነ ሽተው እግዚአብሔርን ከሚያውቁ ሰዎች ሲቀበሉ አናይም። እንዲያውም በራእይ መጽሐፍ ላይ እንደምናነበው ቅዱስ ዮሐንስ፤ እግዚአብሔር በመልአኩ በኩል ስላደረገለት፤ ስለነገረውና ስላሳየው ነገር ሁሉ በፊቱ ወድቆ በሰገደ ጊዜ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ እንዲህ የሚል ነበር።

«ልሰግድለትም በእግሩ ፊት ተደፋሁ። እርሱም፦ እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር የኢየሱስም ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና አለኝ»       ራእ 19፤10
ዛሬ ግን ሰዎች «ለእግዚአብሔር ስገድ» የሚለውን የመልአኩን የማስጠንቀቂያ መልእክት ወደጎን ትተው «ለመልአኩም ስገድ» እያሉ ሲሰብኩ ይገኛሉ። መልእክት አድራሹ መልአክ ከዮሐንስ በተሻለ ስለመልእክቱ ምንነት እውቀት እንዳለው እርግጥ ነው። ከዐውደ ንባቡ እንደምንገነዘበውም ስለመልአኩ ቢያንስ ሁለት ዐበይት ነገሮችን እንረዳለን። አንድ፤ መልእክቱን በቀጥታ ከእግዚአብሔር እየሰማ ለዮሐንስ የሚያደርስ መሆኑን። ሁለትም፤ መልአክቱ ከዮሐንስ ዘንድ ከመድረሱ በፊት በመልአኩ ዘንድ የተሰማና የታወቀ መሆኑን ነው። ስለሆነም ዮሐንስ ስግደትን ለመልአኩ መስጠት የፈለገው መልአኩ የፈጣሪ የቅርብ ባለሟል በመሆኑና የሚያየውን ግርማ በመፍራት እንዲሁም ይዞለት የሚመጣው መልእክቶቹ እጅግ ከባድና ከዚህ በፊት በሕይወቱ ሰምቶአቸው የማያውቅ ከባድ የሕይወት ልምምድን የሚያሳዩ በመሆናቸው የተነሳ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል።
ስለዚህ «ተጠንቀቅ» ያለውን ቃል መጠበቅ ብልህነት ነው።
ክፍል ሦስት ይቀጥላል …..

Saturday, September 5, 2015

ባለቤቴን አፈቅረዋለሁ ትዳራችንም ፅኑ ነው !!


ከዚህ በፊት ስለተከስተ ጌትነት የአሜሪካው አማርኛ ድምጽ አየር ላይ ካዋለው መረጃ ተነስተን ዐመጻውን በንስሐ እንዲተው የሚያሳስብ ዘገባ አውጥተን ነበር። በንስሐ ስለመመለሱ እየተናገረ ባለበት ሁኔታ የባለቤቱን ጽናትና ያላትን የይቅርታ ልብ ተመልክተን ወደፍቺና የግድያ ተግባር ላለመሄድ የተጓዘችበትን የክርስትና አርአያነት «አሌክስ አብርሃም» የዘገበውን ልናስነብባችሁ ወደድን።
 


ባለቤቴን አፈቅረዋለሁ ትዳራችንም ፅኑ ነው !!
 (አሌክስ አብርሃም )

ይቅርታ መቸም እንደሚወራው ቀላል ነገር አይደለም !! በተለይም በባልና በሚስት ማሃል በአንድኛው ወገን ለትዳር አለመታመን ሲከሰት የተበደለው አጋር ይቅር ለማለት ይቸገራል …እንዲህ አይነቱ ነገር ሲከሰት ሚስት ባሏን በመፍለጫ …በተኛበት አቅምሳው እጇን ለመንግስት የሰጠችበት ዜና ሰምተናል ….ባልም በገጀራ ሚስቱን አመሳቅሎ ዘብጥያ የወረደባቸውን በርካታ ዜናዎች በቲቪ ተመልክተን አማትበናል ! የራሱ ጉዳይ ያሉም ትዳራቸውን በትነዋል !
ይህን ነገረ ካለነገር አላነሳሁትም …. በዚያ ሰሞን ከወደአሜሪካ የሰማነው ዜና የሚታወስ ነው …..ዘማሪ ተከስተ ጌትነት ሚስቴን አማግጦብኛል ያለ አንድ ሰው በየሚዲያዎቹ ቀርቦ ፍረዱኝ ሲል ሁላችንም ሰምተን ጉድ ጉድ ብለናል ! ማገጠች የተባለችውም ሴት በየሚዲያው እንዴት ካንድ አይሉ ሁለት ሶስት ጊዜ ወዳረፈበት ክፍል ጎራ እያለች ‹‹ሳትፈልግ ›› አብረው እንደተኙ በዝርዝር መግለፅዋ ይታወሳል ….ፓስተር ተከስተ ጌትነትም ይህንኑ አምኖ ይቅርታ መጠየቁ እንደዛው ..ሚዲያውም እስኪበቃው አናፍሶታል !ዘማሪ /ፓስተር ተከስተ በሚያገለግልበት ቤተክርስቲያንም አገልግሎቱን እንዳቆመ ተዘግቦ ነበር !!
ታዲያ ያኔ አገር ይያዝ ያለው ሚዲያ ለዚችኛዋ ዜና ጭጭ ማለቱ ስለገረመኝ …ያው ችግሩን ካወራን መጨረሻውስ ምን ሆነ የሚለውን ዝም ማለቱ ተገቢ አይደለም በሚል ይችን ፅሁፍ እነሆ አልኩ ……. ትላንት ‹‹የእውነት ቃል ጎስፕል ሚዲያ›› ‹‹የእንደገና አምላክ›› በሚል ርእስ እንደዘገበው ከሆነ ዘማሪ ጌትነት ባለፈው ቅዳሜ በምእመኑ ፊት ቁሞ ስለሁኔታው ምስክርነቱን ሰጥቷል … ባለቤቱ የምስራችም የሆነውን ሁሉ ይቅር እንዳለች በሚገልፅ አጭር ቃል እንዲህ ብላለች ‹‹ ባለቤቴን አፈቅረዋለሁ ትዳራችንም ፅኑ ነው ›› ፓስተር ጌትነትም ወደአገልግሎቱ ተመልሷል !! መቸስ ይቅርታ ጥሩ ነው … መልካም የትዳርና የአገልግሎት ጊዜ ይሁን እያልኩ ….ምንም እንኳን የመጀመሪያ ተጎጅዋ እርሷ ብትሆንም እንዲህ በችግር ጊዜ የራሷን ብሶት ትታ ከባሏ ጎን የምትቆም ሚስት ማግኘት መታደል ነው የሚል የግል አስተያየቴን ጨምሬ ላብቃ !!

Wednesday, August 26, 2015

በአመልካች ጣትህ ሌላው ላይ ስትጠቁም፤ ሦስቱ ጣቶችህ ይመሰክሩብሃል!





  አንዳንድ ሰዎች የራሳቸውን ግፍ፤ ዐመጻና ኃጢአት ለመሸፈን የአቻቸውን በደልና ዐመጻ በማቅረብ ለመደበቅ ይሞክራሉ። ነገር ግን የሌላው ሰው ዐመጻና በደል መቁጠር የራስን የኃጢአት ደብዳቤ አይፍቀውም። በየትኛውም ማእዘን የሚገኙ ዐመጸኞች ከዐመጻቸው እስካልተመለሱ ድረስ ዐመጻቸው ሰላማዊውን ሊያጠፋ ይችላል።  ከኋላ ይሁኑ ከፊት ዐመጸኞች የቆሙበት ሥፍራ ብቻውን ንጹሐን አያደርጋቸውም። ይልቁንም ሰላማዊው ላይ በሽታቸው እንዳይጋባ ቢቻል ሸክማቸውን በንስሐ እንዲያራግፉ ሊነገራቸው፤ ሸክሙ ተስማምቶናል ካሉም ራሳቸው ተሸክመው ገለል እንዲሉ ሊደረግ ይገባል።  ተፈጥሮ የሰጣትን ሁለት መልክ በመጠቀም ለማሳሳት ሞክራለች ተብሎ በምሳሌ እንደሚነገርላት የሌሊት ወፍ ከአይጦች ዘንድ ሄዳ ጥርሷን በማሳየት «እኔ የእናንተ ወገን ነኝ» ካለች በኋላ ከወፎችም ማኅበር ተቀላቅላ ክንፏን እያራገበች «የተከበራችሁ ወገኖቼ እንደምን አላችሁ!» እንዳለችው እንስሳ በሁለት ገጽ ለማታለል የሚሞክሩ የዘመኑ ተለዋዋጮች ራሳቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ሸክም ሆነው ሳሉ የችግሯ ደራሽ ለመምሰል መሞከራቸው በዚህ ዘመን እንደማይቻል በግልጽ ሊያውቁት ይገባል።

   ሰሞኑን የምንመለከተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደአዞ ሐረግ በጎን በቅሎ በዋናው ግንድ ላይ የተጠመጠመው በቅዱሳን ስም የሚጠራው ማኅበር ተራራ የሚያክል የራሱን ኃጢአትና ዐመጻ ላይደበቅ ሸሽጎ የሙስና ተዋጊና የቤተ ክርስቲያኒቱ አዳኝ ለመሆን ሲታትር እያየን ሲሆን በሞት የሚፈላለጋቸውንም ፓትርያርክ በማወዳደስ ላይ መጠመዱ «ቁርበት አንጥፉልኝ» የተባለውን ብሂል እንድናስታውስ አድርጎናል።

  እኛም ነገሩ ቢገርመን «አመልካች ጣትህን ስትጠቁም፤ ሦስቱ ጣቶችህ በራስህ ላይ ይመሰክሩብሃል» ልንለው ወደድን። ሙሰኞቹም፤ ማኅበሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠንቅ ከመሆን ባለፈ አንዳቸው የአንዳቸው አጣሪ፤ ጠቋሚና አባራሪ ሊሆኑ በፍጹም አይችሉም። ከዚህ በፊት በማኅበሩም ላይ ሆነ በነፍሰ በላ ሙሰኞቹ ላይ ተከታታይ ጽሁፍ በማቅረብ ሁሉ አጥፊዎች  መሆናቸውን በግልጽ ተናግረናል። አሁንም የምንናገረው ያንኑ በመድገም ነው። የምናሰምርበትም እውነት «ከማኅበሩና ከሙሰኞቹ የትኛው በመወገድ ሊቀድም ይገባል? የሚለው ካልሆነ በስተቀር በሁለቱም አላስፈላጊነት ላይ አንዳችም ብዥታ የለንም»

   ስለሆነም በማኅበሩ ላይ ከዚህ በፊት በፓትርያርኩ የተያዙ አቋሞች በሙሰኞች ማጥራት ሽፋን የሚታለፍ ወይም የሚቀየር ከሆነ ከሁለት ጅቦች መካከል አንዱን ጅብ ምርጫ የመውሰድ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመታደግ የሚደረግ እንቅስቃሴ አይደለም እንላለን። በመካከላቸው የመጠንና የዓይነት ካልሆነ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኒቱን በሚግጡ ጅቦች መካከል የተግባር ልዩነት ስለሌለ ሁሉም ቦታቸውን ሊይዙ የሚገባቸው የጥፋት ኃይሎች መሆናቸው አያጠያይቅም። እንደምንመለከተው ያለው መገፋፋት በሦስት የሚከፈል ይመስለናል።

  1ኛው- ጫንቃው የደነደነ ማኅበር ከቦታው ሊወገድ የተገባው ቢሆንም  የተወሰኑ አስተዳዳሪዎችና ከታች ያሉ ዘራፊዎች፤ ቅዱስ ነኝ የሚለውን ማኅበር የሚጠሉት ማኅበሩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ስላደረሰው በደልና ግፍ በመቆርቆር ብቻ ሳይሆን በስለላ መረቡ ስለተጠለፉና እዳ በደላቸው ስለተጻፈባቸው፤ ከሚከተላቸው ፍርሃትና ድንጋጤ ለመገላገል ሲሉ በሐቅ ከሚታገሉት ጋር በኅብረት የሚጮኹ አንድ ቡድን ናቸው።

 2/ ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያኒቱን መስሎና አኅሎ በላይዋ ላይ ነግሶ በስሟ መነገዱ የታያቸው፤ በመንገድ ላይ ቆሞ እንቅፋት የሆናቸው፤ ለስውር ዓላማው የስለላ ቡድኑን ያወቁ፤ የቤተክርስቲያኒቱን ልጆች ለራሱ መመልመሉ የቆጫቸው፤የገቢ አቅሙን እያደለበ፤ ሀብቷን ለራሱ ዓላማ ሲጠቀም የተመለከቱ፤ የኃጢአት በደል ጸሐፊ፤ ለሲኖዶስ ክፍፍል ረጅም እጅ ያለው መሆኑን የተረዱ በትክክል አምነው የሚታገሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች በሁለተኛ ረድፍ አሉ። ይህ ረድፍ ድምጹን የሚሰማና የሚያስተባብረው የበላይ አመራር ቢኖር ኖሮ ውጤታማ ሥራ ለመስራት የሚችልና በሙሰኛ አስተዳዳሪዎችም ይሁን በማኅበሩ ተግባር የመረረው ቡድን ነው ።

  3/ ራሱን ቅዱስ፤ ጻድቅና የቤተ ክርስቲያኒቱ መድኅን አድርጎ የተነሳ፤ በገንዘቡ፤ በኃይሉ፤ በአስተዳደሩ፤ በሴራ መዋቅሩና በእንቅስቃሴው አደገኛ የሆነ፤ የራሱን የሲኖዶስ አባላት ያደረጃ፤ ስለቤተክርስቲያኒቱ ሳይሆን ከጥቅሙ ጋር ለቆመ ሰይጣንም ቢሆን የሚተባበር፤ ሰዎችን በማጥመድ አገልጋይ ለማድረግ የሚተጋ፤ የሰዎች የእዳ በደል መዝጋቢ፤ ሰላይ፤ በዝሙት የረከሰ፤ ነጋዴ፤ አስመሳይና አታላይ ነገር ግን በሩቅ ሲያዩት ቆዳው ከእባብ የለሰለሰ ማኅበር፤ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባለው በሦስተኛ ረድፍ አለ።
በዚህ መካከል ከወዲህም ከወዲያም የሚዘምቱ፤ ነገር የሚያማቱ፤ የሚያወሻክቱ፤ የአስመሳዮች ቡድን እንደወቅቱ ሁኔታ፤ ኃይል ወዳጋደለበት የሚያጋድሉ የአስተሳሰብ ድሆች ከሲኖዶስ ጀምሮ በየደረጃው ቢኖሩም ተጽእኖ ፈጣሪ ሆነው ለእክል የሚበቃ አቅም የላቸውም።

 በሦስቱ ረድፎች ያለውን የኃይል አሰላለፍ ተመልክቶ ተገቢ ከሆነው ወገናዊ ኃይል ጋር በመቆም እንቅስቃሴ መውሰድ የተገባ ቢሆንም እስካሁን ከወሬ ባለፈ የሚታይ እርምጃ ብዙም ሲወሰድ አይታይም።
ወቅቱ በፈጠረው የቤተክርስቲያኒቱ ተግዳሮትና የችግር እሳት መካከል የተገኙትት ፓትርያርክ ማትያስ ምን ዓይነት እርምጃ፤ መቼና ከማን ጋር ሆነው መውሰድ ይችላሉ? የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚያሻው ወቅታዊ ጉዳይ ይመስለናል። አካሄዱን በሳተ፤ ውጤቱም ምን ሊሆን እንደሚችል ባልተጠና ውሳኔ የሚወሰድ እርምጃ ከጥቅሙ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል። ስለሆነም በገበያ ግርግር መካከል የሚዘለው ማኅበር የራሱን የቤት ሥራ ሳይጨርስ «ከፓትርያርኩ ጋር አለሁ፤ አለሁ» የሚለው ጉዳይ አሳሳቢ ነው።
ስለማኅበሩም ይሁን ማኅበሩን በሚደግፉ ነገር ግን ብዙ ችግር ባለባቸው ሰዎች ዙሪያ ትንፍሽ የማይለው «ሐራ» የተባለው ብሎግ የማኅበሩ ቀኝ እጅ ስለሆኑት አባ ማቴዎስ ለሙስና ውጊያ የመዘጋጀታቸውን ዜና መስራቱ እንዲሁም የፓትርያርኩን ፈቃደኝነት አደበላልቆ ማቅረቡ ችግሩን ለመቅረፍ ሳይሆን የማኅበሩን ጉዳይ ለመሸፈን አጋጣሚ ማግኘቱን የሚያመለክት ነው።
 ስለሆነም ለፓትርያርኩ የመፍትሄ ሃሳብ ሊሆኑ የሚችሉ ነጥቦችን ለመጠቆም እንወዳለን።

  1/ በቅድሚያ ፓትርያርኩ ብቻቸውን ተንቀሳቅሰው፤ ብቻቸውን ጮኸው፤ ብቻቸውን ታግለው የሚያመጡት ውጤት እንደሌለ በመረዳት የተሻለ ግንዛቤ፤ እውቀትና የአስተዳደር ክህሎት ያላቸውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር ግድ የሚላቸውን ሰዎች በሥራ አጋርነት በዙሪያቸው ማሰባሰብ ያስፈልጋቸዋል። ከጳጳሳቱም ብዙዎቹ በማኅበሩ የተጠለፉ ወይም ከሙስናና ከዘረኝነት ጋር የተሳሰሩ ስለሆነ ከጳጳሳቱም ሆነ ከበታች ሹማምንት መካከል ጥንቃቄ የታከለበት ምርጫ መደረግ አለበት። የፓትርያርኩ ልዩ ፀሐፊ፤ የፕሮቶኮል ሹም፤ የውጪ ግንኙነት ክፍል፤ የፓትርያርኩ ቢሮ ኃላፊ እና ሌሎች ተጨማሪ ክፍሎችን ማደራጀት ያስፈልጋል። የፓርትያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት በሆነው አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ሥራ አስኪያጅ፤ የሀገረ ስብከቱ ፀሐፊ፤ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ወዘተ ክፍሎች ፓትርያርኩ ለሚያደርጓቸው ቀጣይ እርምጃዎች ወሳኝ ስለሆኑ ይህንን በተጠናና መልኩ እንደገና ማዋቀር የግድ ይላል። የፓትርያርኩ ጽ/ቤት የየዕለት የሥራ ውሎ ከበታች ክፍሎች ሪፖርት በመቀበልና ለፓትርያርኩ በማቅረብ ተከታታይ የሥራ መመሪያና ትእዛዝ በማስተላለፍ ያልተቋረጠ ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል።

2/ እንደአጭር ጊዜ የማስተካከያ እርምጃ  ከላይ በተራ ቁጥር 1 በተመለከተው ነጥብ ውስጥ ያሉ አካሎችና ሌሎች አጋዦች ያሉበት አጣሪ ኮሚሽን በማዋቀር በሚያደርጉት ምርመራ በሙስና የከበሩ፤ ከሌላቸው ደመወዝና ልዩ ገቢ ውጪ ሃብት ያከማቹ፤ አላግባብ የበለለጸጉ፤ የገንዘብ ብክነትን ያስከተሉ አሰራሮች ሁሉ ዝርዝር መረጃቸውና ከነመፍትሄ ሃሳቦቻቸው በማቅረብ ማስተካከያና የሕግ እርምጃ በማስወሰድ በፍጥነት መግታት ተገቢ ወቅታዊ እንቅስቃሴ መሆን አለበት እንላለን። ነገር ግን እንደረጅም ግብ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ በፓትርያርኩ የሚመራ የመዋቅር ጥናትና ማሻሻያ መምሪያ በማቋቋም ከዘመናዊ አስተዳደር ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማዘመን የመዋቅር ማሻሻያ ጥናት መደረግ ይገባል። 

ከዚያ ባሻገር በማኅበሩ ግፊት፤ በአስፈጻሚ ጳጳሳቱ በኩል ሙስናን እናጣራለን ማለቱ «በቆሻሻ መጥረጊያ ቤት መወልወል ይሆናል»

3/ ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ በፊት እንደተወሰነው ሀብትና ንብረቱን እንዲያስመዘግብ፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሞዴላ ሞዴሎች እንዲጠቀም፤ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ያለውን ሂሳብ በቤተ ክርስቲያኒቱ ኦዲት እንዲያስመረምር፤ ለወደፊትም በቤተ ክርስቲያኒቱ ተወስኖ በሚሰጠው ደንብ እንዲመራ የተላለፈውን ውሳኔ ያለምንም ማመንታት ተግባራዊ ማድረግ የግድ ይላል። በዚህ ዙሪያ ፓትርያርኩ የገቡትን ቃል በመጠበቅ ማስፈጸም እንዳለባቸው እናምናለን።
ስለሆነም ስለሙስናና ስለገንዘብ ብክነት ለመናገር በዘረኝነትና በእከከኝ ልከክህ የተሳሰሩ የጥቅም ተጋሪ ጳጳሳቱና ከኋላ በሚገፋቸው ማኅበር ሳይሆን እጃቸው ንጹህ የሆነ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን የጣሪያ ሳር ያልመዘዙ ልጆችዋ በኩል በመሆኑ ፓትርያርኩ ቆም ብለው በአስተውሎት እንዲመለከቱት ልናሳስብ እንወዳለን። እርግጥ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን ችግር ላይ ነች። ነገር ግን ችግሯን ተተግነው ደረስንላት የሚሉ ሁሉ የየራሳቸውን ስውር ዓላማ ደብቀው የተነሱ ስለሆነ ጥንቃቄ መወሰድ ይገባዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፤ 

በቅንነት የምንገልጽልዎ ነገር የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር የሚያንገበግባቸው፤ በታማኝነት፤ በፈሪሃ እግዚአብሔር ለማገልገል መንፈሳዊነቱም ፈቃደኝነቱም ያላቸው የተማሩ ልጆች ስላሉአት በጥንቃቄ አጥንተው ለቀጣይ እርምጃ እንዲበራቱ እንጠይቃለን። ማኅበሩም አጋጣሚዎችን ለራሱ በሚመቸው መልኩ እየተጠቀመ፤ የተወሰነበትን ውሳኔዎች ለማስቀልበስ የሚሄድበትን መንገድ ሊዘነጉ አይገባም። ቁርጠነቱ ካለ ሙሰኞችንም፤ ማኅበሩንም ቦታ ቦታቸውን ለማስያዝ ሰውም፤ ጊዜም፤ ኃይልም አለ!!

Saturday, August 22, 2015

ዘማሪት ዘርፌ ከበደ በማኅበረ ቅዱሳን ከተጠመደባት ወጥመድ በእግዚአብሔር ርዳታ ዳነች!


ባለፈው እሁድ ማለትም 10/12/2007 ዓ/ም በአዳማ ከተማ፣ በሥላሴ ቤተክርስቲያን፣ በተካሄደው ታላቅ ጉባኤ ዘማሪት ዘርፌ ከበደን በሕዝብ ሁሉ ፊት ‹‹በድንጋይ ወግሮ ማስወገርን›› ዓላማ አድርጎ ወደ ጉባኤው በነጎደው ማህበር ቅዱሳን ወጥመድ፤ እግዚአብር በችሎቱ ያዳናት፡፡ ይህ የጥፋት ማኅበር በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ጠብንና ሁከትን በምዕመናኑ መካከል የመፍጠር አጀንዳ ከመሸከሙ የተነሳ እንዲህ ዓይነት የወረደ አህዛባዊ ወጥመድ አጥምዶ በእግዚአብሔር ጉባኤው ውስጥ መግባቱ ለብዙዎች ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳን ያነገበ ጽንፈኛ ማህበር መሆኑን ፍንትው አድርጎ ያሳየ ሆኖል፡፡

    ዘማሪት ዘርፌ ከበደ በቤተክርስቲያናችን ደንብና ስርዓት በመዘመር በሕዝብ ሁሉ ፊት በአንድ ልብ በአንድ መንፈስ እግዚአብሔርን እያከበረች ባለበት ወቅት ነው፤ ባለ-ጊዜ በሆነ አንድ የማህበሩን ራዕይ በሚያራምድ ግለሰብ፤ መድረክ ላይ በእጇ የጨበጠችውን ማይክ በመንጠቅ፣ በግብዝነት በነሆለለ አዕምሮ ቢስነት በጥፊ ለመምታት ሙከራ ያደረገው፡፡ በሰዓቱ በሺዎች የሚቆጠር ምእመናን በመንፈስ መቃኘት ተወስኖ፣ በቅድስት ቤተክርስቲያን ዐውደ ምህረት ተሰባስቦ፣ የአንድነት የምስጋና ድምጽ ወደ ክቡር ዙፋን፣ ወደ ጸባኦት እንዲህ ሲል ይዘምር ነበር፡-

‹‹የማልደራደርበት የማልቀብረው እውነት፣ አንገት የማያስደፋ የማላፍርበት፣ ኢየሱስ የሚለው ስም እስትንፋሴ ነው፣ እውነቱ ይሄ ነው››፡፡ አስከትሎም ደግሞ በዚሁ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ኢየሱስን በሚያከበረው መንፈስ በመቀጣጠል ይሄው ሕዝብ፡- ‹‹የኔ ናርዶስ የኔ ቤዛ፣ በመዓዛው ልቤን ገዛ፣ ያንን መዳፍ ተመልክቼ፣ ተከተልኩት ሁሉን ትቼ"

 እያለ በአንድ ልብ እያመሰገነ ባለበት ቅጽበት ነው እግዚአብሔር ሲከብር በአንዳች ቁጣ የሚሞላው፣ በአንዳችም ሽንፈት ወራዳ ሥራን ሲሰራ የሚታወቀው፣ የጨለማው ዓለም ገዥ ዲያብሎስ በአደራጃቸው ጋሻ ጃግሬዎቹ በማኅበረ ቅዱሳን በኩል በስጋ አካል መዋጋት የጀመረው፡፡ በዚህ ሽብር መሐል ነው መጋቢ ምስጢር ቀሲስ ገብረሚካኤል የማነ በመነሳት ከወጋሪዎቿ እጅ ባላቸው የቤተክርስቲያኒቱ ስልጣንና አክብሮት በመንጠቅ ሥራ ተጠምደው ሳሉ፤ የአዳማ ከተማ ፖሊስ በስፍራው ደርሶ ዘማሪት ዘርፌን ከጽንፈኛው ማህበር ወጥመድ ያያዳኗት፡፡ መጽሐፍ እንደሚል፡- ‹‹ነፍሳችን እንደ ወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች። ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን።›› መዝ 124፡-7፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን የተመለከቱ፣ በዚህ አንካሳ ማኅበር ሽብር ክፉኛ ልባቸው የተሰበረ ምዕመናን ‹‹በጉባኤው ውስጥ በሐዘን እንባ ፊታቸው›› ሲታጠብ ተስተውሏል፡፡ ማህበረ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን የወቅቱ ፈተናና መከፋፈል ምክንያት መሆኑ አሁን አሁን በግላጭ መታየት ጀምሯል፡፡

    እንዲህ ዓይነት የወረደ ግብር በማኅበረ ቅዱሳን ሁከት ፈጣሪነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናንና ብርቅዬ አገልጋዮቿ ላይ መፈጸሙ እንግዳ እንዳልሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ ለዛም ነው ብዙዎች የደብር አለቆችና ካህናት በአንድ ድምጽ ማኅበሩ ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳውን በቤተክርስቲያኒቱ ስም እየፈጸመ እንዳለ የመሰከሩትን በማስረጃነት በመጥቀስ ሆነ ብሎ ‹‹ቤተክርስቲያኒቱን በሽብር ለማናጥ እየሰራ›› ነው ሲሉ የሚከሱት፡:

    ከዚህ በፊትም ይሄው ማህበር ባሰለፋቸው ጨካኝ ወንቤዴዎቹ በመታገዝ፤ ግንቦት 8 ቀን 2005 ዓ/ም በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ የቀሲስ ሊቀ መዘምራን ትዝታው ሳሙኤልን ደም ማፍሰሳቸውንና በአምቡላንስም ለፈጣን ህክምና ሆስፒታል ድረስ ለመሄድ ተገዶ እንደነበር የምናስታውሰው ነው፡፡ ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ ቀሲስ ትዝታው ሳሙኤል በማኅበረ ቅዱሳን በኩል በቅድስት ቤተክርስቲናችን ላይ እየደረሰ ስላለው እኩይ ተግባር ለአባ ሰረቀ ብርሃን ያቀረበውን ግልጽ ጥያቄ  ማየት ይችላሉ፡-

    በቅርቡ አፍሪካ ሕብረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን፣ በሴኔ ወር 12 ቀን 2007 ዓ/ም እንዲሁ በደቀመዝሙር ዘማሪ ዲያቆን ከፍያለው ቱፋ ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸሙና ለቀናት ያክል በህክምና ሲረዳ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ድብደባቸው ሳይሆን የሚገርመው ቅድስት ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ በማን አለብኝነት መፈንጨታቸና አገልጋዮችን እየደበደቡ ሞባይል ቀፎና ገንዘብ የመዝረፋቸው ነገር ነው የሚደንቀው፡፡

ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ዲያቆን ከፍያለው ቱፋን ደብድበው ከጣሉት በኋላ የ4500 ብር ስማርት ፎንና ገንዘብ ሰርቀው ሲያበቁ ‹‹አንተ ተሐድሶ፣ አንተ ጴንጤ፣ ደበደብንህ፣ ምንትሆን እንግዲህ›› እያሉ መንፈሳዊ መስለው መቆማቸው ነው፡፡ እግዚአብሔር ከዚህ ዓይነቱ አዕምሮ ቢስነትና ድንዛዜ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ምዕመን ይጠብቅልን!
ይህን መረጃ ያቀበላችሁኝ የአዳማ ሥላሴ ቤተክርስቲያን መዘምራንን እግዚአብሔር አምላክ ይባርካችሁ! የጨለማውን ሥራ እንዲህ በብርሃን ጸዳል መግለጡ ተገቢ ነውና!
ከውስጥ አዋቂ ምንጭ

Wednesday, August 19, 2015

ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ሰዎች በሁሉም ሥፍራ በአንድ ጊዜ መገኘት ይችላሉን?


1/ እንደመግቢያ፤

   መላእክትና ሰዎች በእግዚአብሔር ግብር የተፈጠሩ ፍጡራን ናቸው።  በኦሪት ዘፍጥረት የመጀመሪያዎች ሁለት ምዕራፎች እንደተመለከተው በላይ በሰማይ፤ ከታች በምድርና በጥልቅ ውሃማ አካሎች ሁሉ እግዚአብሔር በለይኩን ቃሉ (ከአዳም በስተቀር) የፈጠራቸውን ሥነ ፍጥረቶች እናገኛለን። በመሠረተ እምነት ደረጃ ፍጡር ስንል ፈጣሪ ወይም አስገኚ ያለው ነገር ማለታችን ነው። መፍጠር ወይም የሌለውን ነገር ማስገኘት ማለት አንድን ነገር መሥራት ወይም መፈብረክ ማለት አይደለም። የነገረ መለኮት ምሁራን መፍጠርን ወይም ማስገኘትን ሲገልጹ «from nothing to something» በማለት ይገልጹታል። «ከምንምነት ወደአንድ ነገርነት» ማምጣት ማለት ነው።  እግዚአብሔር ለመፍጠር መነሻ ሃሳብ ወይም ጥሬ ነገር /substance/ አያስፈልገውም።  

   ፍጡራን ግን ይህንን ማድረግ አይቻላቸውም። ለምሳሌ ወንበር የሠራ ሰው ፈበረከ ወይም ሠራ ቢባል እንጂ «ፈጠረ ወይም አስገኘ» ሊባል የተገባው አይደለም ይላሉ ምሁራኑ። ምክንያቱም «ወንበር» የተባለውን ቁስ ለመሥራት  አንዳንድ ነገሮች «something» የግድ ያስፈልጉታልና ነው። ይህም የሥራ ጉዞ «from something to something» በቅርጽ፤ በመጠንና በይዘት ይለውጠዋል እንጂ /from nothing to something/ ከምንም ነገር ሳይነሳ «ወንበር» የተባለውን ቁስ ማቅረብ አለመቻሉ የጉድለቱ አንድ አስረጂ እንደሆነ በአመክንዮ ያቀርባሉ።  ያንንም ወንበር እንኳን ለመሥራት ወይም ለመፈብረክ የግድ የሚያስፈልጉት ጥሬ ሀብቶች /raw materials/ የሠራተኛው የራሱ ግኝቶች አይደሉም። 

   ስለሆነም ፍጡራን በሙሉ ያላቸው ሁኔታ፤ ችሎታና ብቃት ያልተወሰነ፤ በአፈጣጠር ያልተገደበ አይደለም። በሥራቸው ሁሉ ምሉዕነት ያለው፤ ጉድለት አልቦነትም የማይጎበኘው አይደለም። መላእክትና ሰዎች መነሻም፤ መድረሻም አላቸው። መነሻና መድረሻ ያለው ፍጥረት ደግሞ በአንድ ጊዜ በስፍሐትና በምልዓት በሁሉ ሥፍራ መገኘት አይችልም። በሥራው ሁሉ በብቃትና በራሱ ኃይል የማከናውን ፍጹምነት የለውም።

 የእግዚአብሔር ባህርይ ግን ከዚህ የተለየ ነው። እግዚአብሔር የሁሉ ነገር ፈጣሪና አስገኚ ስለሆነ መነሻም መድረሻም የለውም። ኋለኛ የሌለው ፊተኛ፤ ፊተኛም የሌለው ኋለኛ እሱ ብቻ በመሆኑ አልፋና ኦሜጋ እንለዋለን።
መጽሐፍ ቅዱስ « በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ» ዘፍ 1፤1 ሲል እግዚአብሔር ከምንም ነገር «from nothing to something»  ለመፍጠር ወይም ለማስገኘት ምንም ተጨማሪ ነገር እንዳላስፈለገውና እሱ ብቻ እንደተቻለው እንረዳለን። ሰማይና ምድርን ግን የፍጥረት መነሻ ሆነው ተከስተዋል። ሁለቱም በሥፍራ፤ በቦታና በሁኔታ ተወስነዋል። ምድር በውስጧ የተገኙት ፍጥረታትም ሁሉ መነሻና መድረሻ፤ መጠነ ውሱንነትና መጠነ አኽሎኝነት ይዘው መገኘታቸውን በእያንዳንዱ የሥነ ፍጥረታት ጠባይዓት ላይ እንመለከታለን። ከፍጥረታት አንዱ ክፍል የሆነው የሰው ልጅን ብንመለከት በፍጥረተ ጠባዩ  የአስተሳሰብ፤ የአፈጣጠርና የማንነት ብቃት በተሰጠው እሱነቱ ልክ ተወስኖ ይገኝበታል።

  እርግጥ ነው፤ ስለሃይማኖት ጥሩ ግንዛቤ ያለው ሰው ያለብዙ ምክንያታዊ ውጣ ውረድ «ፍጡራን በአንድ ጊዜ በሁሉ ሥፍራ መገኘት አይችሉም!» ብሎ መልስ ሊሰጥ ይችላል። ደግሞም የሚሠመርበት እውነት፤ በሁሉ ሥፍራ፤ በአንድ ጊዜ፤ በስፍሐትና በምልዐት  (በምሉዕ ኵለሄነት) የመገኘት ብቃት ከእግዚአብሔር በስተቀር ለፍጡር አይቻለውም የሚለውን እውነት አምኖ መቀበል ነው። ሁሉን ቻይነት/Omnipotence/ ከእግዚአብሔር በቀር ለማን ይቻለዋል? ለማንም!!

«ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?» ኢሳ 44፤24

በላይ በሰማይ፤ በታች በምድር በሁሉም ሥፍራ ያለና የሚኖር፤ የሚሰማም፤ መልስ የሚሰጥም እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ቅዱሳን መላእክት ይሁኑ ቅዱሳን ሰዎች በሰማይ ሥፍራቸው ሳሉ በምድር የሚደረገውን ሁሉ ያውቃሉ? ያያሉ? ይሰማሉ? በፍጹም አያውቁም፤ አያዩም፤ አይሰሙም።  በሰማይ ሳሉ በምድር ያለውንም የሚያውቁ ከሆነ በስፍሐትና በምልዓት ይገኛሉ ማለት ነው። ይህ ደግሞ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ያለ ስህተት ነው። ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ የመገኘትን ብቃት የፈጣሪ እንጂ የፍጡራን እንዳልሆነ የገለጽነውን እውነታ የሚጻረር ይሆናል።  

2/ «እግዚአብሔር ብቻውን በሁሉ ሥፍራ አለ» የምንለው ለምንድነው?

መልሱ አጭር ነው። እግዚአብሔር በላይ በሰማይ፤ በታች በምድርም፤ በሁሉ ሥፍራ መገኘት የሚችለው በላይ በሰማይ ይሁን በታች በምድር ላለው ነገር ሁሉ ፈጣሪና አስገኚ ስለሆነ ነው።
 ከባዶነት ወደአንድ ነገርነት ማምጣት የቻለ ፈጣሪ፤ በፈጠረው ነገር ሊገደብ፤ ሊወሰን፤ ሊከለከል አይችልም። ፍጥረታት ግን በዚህ ብቃት ውስጥ ሊገቡ አይችሉም። ምክንያቱም ፍጥረታት በቦታ፤ በሁኔታና በአፈጣጠር ውሱን ስለሆኑና ከፈጣራቸው እግዚአብሔር ጋር ሊስተካከሉ ስለማይችሉ ነው። የቅዱሳን መላእክትና የቅዱሳን ሰዎች ብቃት እግዚአብሔር በሰጣቸው መጠንና ፈቃድ የተወሰነ ነው።  መላእክቱ ይሁኑ ሰዎች ፍጡር እንጂ ፈጣሪዎች ባለመሆናቸው ፍጥረተ ዓለም ይወስናቸዋል። እግዚአብሔር ግን እንዲህ አይደለም። በትንቢተ ዳንኤል ላይ እንዲህ እንደተመለከተው፤
«በምድርም የሚኖሩ ሁሉ እንደ ምናምን ይቈጠራሉ፤ በሰማይም ሠራዊት በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም ምን ታደርጋለህ? የሚለው የለም» ዳን 4፤35

3/ የቅዱሳን መላእክት ውሱንነትና በስፍሐት አለመገኘት

እያየን በመጣነው ከእግዚአብሔር ስፉሕነትና ከፍጥረታት ውሱንነት የተነሳ መላእክት በምልዐት በሰማይም በምድርም ሊገኙ እንደማይችሉ  እናምናለን። ነገር ግን ከላይ የገለጽነውን ጉዳይ ዳግም ማንሳት ያስፈለገን ዐቢይ ምክንያት ብዙ ሰዎች የመላእክትን ውሱን መሆን፤ በሁሉ ሥፍራ በአንድ ጊዜ አለመገኘት አምነው ሲያበቁ  ከዚህ ተቃራኒ በሆነ አቋም  ቅዱሳን መላእክት በአንድ ጊዜ በሰማይና በምድር የመገኘት ብቃት እንዳላቸው የሚያስተምሩና አምነው የሚያሳምኑ  ሰዎች በመኖራቸው  ነው። 

   ሰው በአንድ ጊዜ አማኝም፤ ከሀዲም መሆን አይችልም። ምክንያቱም  ጣፋጭ ፍሬ የሚሰጥ ዛፍ ፤ በጭራሽ መራራና ጣፋጭ ፍሬ በአንድ ጊዜ ማፍራት እንደማይቻለው ሁሉ በእምነት የቅዱሳን መላእክትንም ሆነ የቅዱሳን ሰዎችን የውሱንነት ተፈጥሮ ካመንን በኋላ በምንም ዓይነት መንገድ ከዚህ በተጻራሪ መቆም ስለማይቻለን ነው።
ብዙ ጊዜ ሰዎች አምኛለሁ ባሉበት እምነት ውስጥ ክህደት መሰል ነገር የለም ብለው የሚከራከሩት ስላመኑት እምነት በቂ እውቀትና ግንዛቤ ስለሌላቸው ነው። ለዚህ ጥሩ አብነት የሚሆነን ነጥብ፤ በአንድ ወቅት ሰዱቃውያን ወደ ጌታችን፤ አምላካችንና መድኃኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ቀርበው ትንሣኤ ሙታንን ለመቃወም «በምድር ሰባት ባል ያገባች ሴት በሰማይ ለማንኛቸው ትሆናለች?» ብለው በጠየቁት ጊዜ የሰጣቸው መልስ  በየትኛውም ዘመንና ጊዜ ለሚነሳ ጥያቄ እንደአስረጂ አቅርበን እዚህ ላይ ብንጠቅሰው ተገቢ ይመስለናል።
«ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ» ማቴ 22፤29 አላቸው።

  እግዚአብሔርን የሙታን ብቻ አምላክ አድርጎ መንሥኤ ኃይሉን መካድ ከባድ ስህተት ነው። መጻሕፍት የሕያዋን አምላክ ብለው ሲመሰክሩ ይህንንም አለማወቅ ስንፍና ነው። ለዚህ ሁሉ ምክንያቱ አንድ ነው።
  ሰዎች «እናምንበታለን» ባሉት ነገር ውስጥ የሚገቡ ስህተቶች ሁሉ ተቀባይነት አግኝተው ሃይማኖታዊ ካባን የሚላበሱት «መጻሕፍቱንና የእግዚአብሔርን ኃይል» በደንብ ካለመረዳታቸው በሚመጣ ጉድለት እንደሆነ ሁሉ፤ በዚህም ዘመን ያሉ ስህተቶችን እንዲሁ እንገነዘባቸዋለን።  ሰዱቃውያን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በእጃቸው ይዘው ሲያበቁ ስለትንሣኤ ሙታን አለመኖር አምነው መቀመጣቸው ላያስገርም ይችላል። ምክንያቱም ሰዎች የእግዚአብሔር ኃይል መገለጫ መንገዶችን ወደሚናገሩ ወደ ቅዱሳት መጻሕፍቱ ይሄዳሉ እንጂ መጻሕፍቱ ወደሰዎቹ ሊመጡ አይችሉም ነው።  በእጃቸው ያለው መጻሕፍትማ  የሚሉት እንደዚህ ነበር።

«ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም»  እያለ እውነቱን ቢናገርም እያየበቡ ስለማያስተውሉ የትንሣውን ኃይል ክደዋል (ማቴ 22-31-32 ፤  ዘጸ 3፤6 )

ሰዱቃውያኑ ከተቀበሏቸው መጻሕፍት ውስጥ የተጻፈውን አለማወቃቸው የሚያስረዳን ነገር መጻሕፍትን በመያዝ ወይም በማንበብ  እውነት ሁልጊዜ ይገለጣል ማለት አይደለም።  መረዳቱ ካላቸው ሰዎችም ዘንድ ለኛ ያልተገለጠን እውነት ስለሚኖር ሌሎችን በመጠየቅ ወይም የሚሉትን በማስተዋልና እንደእግዚአብሔር ቃል በመመርመር ወዳልደረስንበት እውነት ልንደርስ እንችላለን። እንደዚሁ ሁሉ በዚህ ዘመንም ያሉ ሰዎች የቅዱሳን መላእክትንንና የቅዱሳን ሰዎችን ውሱንነትና በምልዐት ያለመገኘት ተፈጥሮ አምነው ሲያበቁ በተግባር ግን ከዚህ አስተሳሰብ በተቃራኒ ቆመው የመገኘታቸው ነገር በመጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነታ ውስጥ ለመኖር ካለመቻል የመጣ እክል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። 

4/ በሰማይ ሥፍራ ያሉ ቅዱሳን በዓለመ ምልዓትይገኛሉን?

ፍጡራን ውሱንና በሁሉ ሥፍራ የመገኘት ብቃት እንደሌላቸው ከላይ በተደጋጋሚ ለማሳየት በሞከርነው ላይ ካመንን በዓለማት ሁሉ በምልዓት ሊገኙ አይችሉም ብለን ደፍረን መናገር እንችላለን። እንደመላእክቱ ሁሉ ቅዱሳን ሰዎች በተወሰነ ሥፍራ፤ በተወሰነ  መጠንና  በተፈቀደላቸው ዓለም የሚኖሩ እንጂ ምሉዕ በኵለኄ ስላይደሉ እንደፈጣሪ ሁሉን አዋቂነት የላቸውም ብንልም ስህተት አይደለም። ከዚህ በተለየ አስተሳሰብ ላይ ከሆንን ደግሞ ሊሆን የሚችለው ነገር ሁሉን ቻይ በሆነው በእግዚአብሔር ኃይልና ፍጡር በሆነው ፍጥረት መካከል ያለውን ልዩነት አለመረዳት ስለሚሆን እምነቱ በክህደት የተሞላ ይሆናል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የፈጣሪን ኃይል ለፍጡራን ከመስጠት የበለጠ ክህደት የለም። እግዚአብሔርን የሚመስል ምንም ነገር ሊኖር አይችልምና።

«አቤቱ የእስራኤል አምላክ ሆይ፥ በሰማይ ወይም በምድር አንተን የሚመስል አምላክ የለም፤ በፍጹም ልባቸው በፊትህ ለሚሄዱ ባሪያዎችህ ቃል ኪዳንንና ምሕረትን የምትጠብቅ» 2ኛ ዜና 6፤14

መላእክት ቅዱሳን በመሆናቸው ወይም ቅዱሳን ሰዎች አምላካቸው ስላከበራቸው እግዚአብሔርን የሚመስል ባህርይ እንዳላቸው አድርጎ ማሰብ  አስነዋሪ ነገር ነው። ቅዱሳን በዓለመ ሥጋ ሳሉ ወይም በዓለመ መላእክት የሚገኙ መላእክት የሚሠሩት ሥራ በእግዚአብሔር ፈቃድና በተሰጣቸው ጸጋ ይወሰናል። በዚህ ምድር የሚኖሩ ቅዱሳን ሙት ቢያስነሱ፤ ደዌ ቢፈውሱ ከተሰጣቸው ጸጋ አኳያ እንጂ በተፈጥሮ ካላቸው ብቃት የተነሳ አይደለም።  በዚያም ጸጋ ቢሆን የሚመሰገነውና ሊመሰገን የተገባው የጸጋው ባለቤት እግዚአብሔር ብቻ ነው። ቅዱሳኑን ማክበር አንድ ነገር ነው፤ ነገር ግን በማክበር ሽፋን ወይም እግዚአብሔር በነሱ በኩል በሠራው አስደናቂ ነገር የተነሳ ለእነሱ ምሥጋናና ውዳሴ እንድንሰጥ የሚያደርገን አንዳችም መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ የለም። ጸጋ ማለት እግዚአብሔር በወደደው መንገድ የራሱን ሥራ የሚሠራበት ኃይል እንጂ ሠራተኞቹ ይመሰገኑበት ዘንድ የተሰጠ የውዳሴያቸው መሣሪያ አይደለም።

«አሁንም ጸጋን ይሰጠን ዘንድ እግዚአብሔርን ለምኑ፤ ይህ ከእጃችሁ የተሰጠ ሲሆን ከቶ ፊታችሁን ይቀበላልን? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር» ሚል 1፤9

ጸጋ የሚሰጥ፤ የሚከለከል ኃይል ነው። ጸጋ ሰጪው በፈቀደው መጠን ለፈቀደው ጉዳይ የሚሰራበት መንገድ እንጂ ወሰን የሌለውና ሁሉን ለማድረግ ክበበ ተፈጥሮን አልፎ የሚሄድ ምሉዕ ኃይል ያለው ማለት አይደለም።

«እንደ ተሰጠንም ጸጋ ልዩ ልዩ ስጦታ አለን» ሮሜ 12፤6


«ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤ በሁሉም ላይ ታላቅ ጸጋ ነበረባቸው» የሐዋ 4፤33

በአንድ ወቅት ሐዋርያው ጳውሎስ ልስጥራን በሚባል ሀገር በገባ ጊዜ በልስጥራን የተባለ ከልጅነቱ ጀምሮ እግሩ ሽባ የሆነና የሰለለ ሰው አግኝቶ በኢየሱስ ስም ከፈወሰው በኋላ  አማልክት ከሰማይ ወርደዋል ብለው ሲያበቁ ሕዝቡና የድያ ካህን ኮርማ ሊሰዋላቸው ፈለገ። ጳውሎስና በርናባስ ግን ልብሳቸውን ቀደው እንዲህ አሉ።

«እንዲህም አሉ። እናንተ ሰዎች፥ ይህን ስለ ምን ታደርጋላችሁ? እኛ ደግሞ እንደ እናንተ የምንሰማ ሰዎች ነን፥ ከዚህም ከንቱ ነገር ሰማይንና ምድርን ባሕርንም በእነርሱም ያለውን ሁሉ ወደ ፈጠረ ወደ ሕያው እግዚአብሔር ዘወር ትሉ ዘንድ ወንጌልን እንሰብካለን» የሐዋ 14፤14-15

የቅዱሳን መላእክትም ይሁን የቅዱሳን ሰዎች ዋና የእምነታቸው ማእከል ራሳቸውን በምሥጋናውና በተሠራው ቦታ ማስቀመጥ ሳይሆን እግዚአብሔር በእነሱ በኩል እንዲከብር ማድረግ ነው።  ከጳውሎስ ተአምራት የተማርነው ነገር ተአምራቱን የሠራው ጳውሎስ ሳይሆን መክበር ያለበት የተአምራቱ ባለቤት እግዚአብሔር ብቻ እንዲከብር ሰዎች ሁሉ ዓይናቸውን በእግዚአብሔር ላይ እንዲጥሉ በኃይለ ቃል ሲናገራቸው የምናነበውም ለዚህ ነው።

5/ በሰማያት ሥፍራ ያሉ ቅዱሳኑ መላእክትና ቅዱሳን ሰዎች የሰዎችን ልመናና ጸሎት ሰምተው ምላሽ ሊሰጡ ይችላሉን?

የቅዱሳኑን ውሱንነትና በምልዓት ያለመገኘት ብቃት መመልከት ያስፈለገን ከዚህ በታች ለምናቀርባቸው ጭብጦች ገላጭ አስረጂ እንዲሆኑን ከመፈለግ የተነሳ ነው። ውሱንነትና በምልዓት አለመገኘት ማለት ከታች ለሚነሱት ነጥቦች መልስ ይሰጡናል።
እዚህ ላይ ሁለት የተለያዩ ነጥቦችን ልናነሳ እንገደዳለን። አንደኛው ቅዱሳን መላእክት በሰማያት ባለ የምሥጋና ዓለም እያሉ በምድር የሚደረገውን ነገር ሁሉ ያውቃሉ ወይ? የሚለውንና በገነት ያሉ ቅዱሳን በምድር የሚደረገውን ሁሉ ማየት ወይም መስማት ይችላሉ ወይ? የሚለውን ነጥብ ለይቶ መመልከት ተገቢ ነው።
 ከቅዱሳን መላእክትና ከቅዱሳን ሰዎች ተፈጥሮ የተነሳ በምልዐት ያለመገኘትን ጉድለት የተነሳ በገነት ወይም በዓለመ መላእክት ያሉ ቅዱሳን በዚህ ክበበ ዓለም ያለውን ነገር ሁሉ በአንዴ ሰምተው፤ በአንዴ አውቀው፤ ምላሽ ሊሰጡ አይችሉም። በወሰነ ነፍሳዊ አካል በገነት ሳሉ በዚህ ምድርም የመገኘት ብቃት የሌላቸው ከመሆኑም ባሻገር በተፈጥሮአቸውም  በገነት ሳሉ  በምድር ያሉ ሰዎችን ጸሎት በብቃት በመስማት ምላሽ ለመስጠት  ስላይደለ የሁሉን አዋቂነትና ሰሚነት ችሎታ የላቸውምና በምድር ላይ ሆነን በገነት ይሰሙናል ልንል የተገባ አይደለም። ይህን የማድረግ ባህርይ የእግዚአብሔር የብቻው ነው። 

   በዚህች ባለንባት ምድር በየትኛውም ማእዘነ ዓለም በስማቸው የሚደረገን ልመና በገነት ሳሉ ይሰማሉ ማለት ፈጣሪ ናቸው ብሎ በክህደት አዘቅት ውስጥ መውደቅ ማለት ነው።
ቅዱሳን መላእክትን እግዚአብሔር ለፈለገው ዓላማ ሲልካቸው ወይም እንዲገኙ በተሰወነላቸው ሥፍራ ከመገኘት በስተቀር በፈቃዳቸው ወይም ሰዎች ስለጠሯቸው እንደፍላጎታቸው ሊሄዱ አይችሉም፤ ያልተወሰነ የመስማት ብቃትም የላቸውም።  በኢጣሊቄ ይኖር ለነበረ ጭፍራ፤ የመቶ አለቃ የሆነው ቆርኔሌዎስ ጸሎቱና ምጽዋቱ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለተወደደ ስሙ ያልተገለጸ የእግዚአብሔር መልአክ በተልእኰ መጥቶ መልእክት ማድረሱንና ማድረግ ስለሚገባው ነገር ሲናገረው እናነባለን።

እዚህ ላይ ሊሠመርበት የሚገባቸው ነጥቦች ሦስት ናቸው።

ሀ/ የመልአኩ ድርሻ  ማንነቱን ማስተዋወቅ ወይም የራሱን ሃሳብ መግለጽ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላለፈውን መልእክት ማስረዳት ብቻ ነው። ከነበረበት ሰማያዊ ሥፍራም በተልእኰ ወደቆርኔሌዎስ ሲሄድ የነበረበትን ዓለመ መላእክት ለቆ ይወርዳል እንጂ በስፍሐት በነበረበት ቦታም በተመሳሳይ ሁኔታ ሊገኝ አይችልም። መውጣትና መውረድ ያስፈለገውም ለዚህ ነው።
ለ/ መልአኩ ከቆርኔሌዎስ ቤት የተገኘው መልአኩ በስሙ ስለተደረገው ጸሎትና ምጽዋት ምላሽ ሊከፍለው መምጣቱን ለመንገር ሳይሆን ቆርኔሌዎስ በአምላኩ ስም ያደረገው ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ማግኘቱን  በመግለጽ የእግዚአብሔር መልእክት ለማድረስ ብቻ ነው።
ሐ/ በዚህ ሥፍራ ስሙ ያልተገለጸውን የመልአክ ስም በምትሃት ጠቅሰን በመናገር መልእክት አድራሽነቱን እንደባለቤት ቆጥረን እንድናመሰግነው የሚያደርገን አንዳች ነገር የለም።

 ይሁን እንጂ በዘጸአተ እስራኤል ታሪክ ላይ ያልተገለጸው መልአክ፤ ሚካኤል እንደመራቸው ተደርጎ የተጠራውና በትንቢተ ዳንኤል መጽሐፍ ውስጥ እንደተመለከተውም፤ ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳናቸው፤  እግዚአብሔር ባወቀ ያልገለጸውን የመልአክ ስም በመስጠት ሚካኤልና ገብርኤል ናቸው እያሉ የስህተት ትምህርቶች ምሥጋናውን ሁሉ  ከእግዚአብሔር ላይ ለመውሰድ የተደረገ ትግል ከመሆን አያልፍም። በእግዚአብሔር ሥፍራ ላልተገለጹ መላእክት ክብርና ምስጋናን በመስጠት እግዚአብሔርን ማስቀናት የጠላት ሴራ ውጤት ነው። በእርግጥም ይህንን የሚያደርገው ሰይጣን ነው።  ምክንያቱም በቅዱሳን መላእክት ስም ተሸሽጎ ሰዎችን ከእግዚአብሔር ፈቃድ ለማስወጣት የብርሃን መልአክ ነኝ ቢል ማስመሰል የቆየ ተግባሩ ነው።  በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ  ሳይገልጽ በዝምታ ያለፈውን ነገር እንዳለ ለሱ በመስጠት በዝምታ እንደመተው የመሰለ ማለፊያ እውቀት የለም።

   እንደዚሁ ሁሉ ወደቆርኔሌዎስ የተላከውን መልአከ ማንነት እግዚአብሔር ብቻ ባወቀው ሁኔታ ስላልተገለጸ ከዝምታ ባለፈ ወደስም ገላጭነት የሚያሸጋግረን ምክንያት የለም። «እንደአናንያ፤ እንደአዛርያ፤ እንደሚሳኤል፤ አድነን ገብርኤል» እንድንል የሚያደርገን ከመጽሐፉ ባለቤትም የተሻለ እውነት እኛ ዘንድ የለም።
ስለሆነም ቅዱሳን መላእክቱ ሰዎች ወደእግዚአብሔር በሚያቀርቡት ልመናና ጸሎት ወይም እግዚአብሔር እንዲራዱ፤ እንዲታደጉ ሲልካቸው በትእዛዝ ብቻ ተልእኰአቸውን ለመፈጸም ከሚመጡ በስተቀር ሰዎች ስማቸውን ስለጠሩ፤ በስማቸውም ስለተማጸኑ፤ ለዚያ የሚሆን ዋጋ ለመስጠት ደስ ተሰኝተው፤ ላደረጉትም ትድግና ምስጋና ለመቀበል ሽተው በጭራሽ አይመጡም። ምክንያታችንም ከላይ ስንገልጽ እንደመጣነው መላእክቱም ይሁኑ ቅዱሳኑ በሰማይ ሳሉ በምድር ላይ በስማቸው የተደረገውን የሰዎችን ሁሉ ልመና መስማት፤ መቀበልና ምላሽ የመስጠት ብቃት ስለሌላቸው ነው። በምልዓት ተገኝቶ የመስማትና ጸሎት የመቀበል ችሎታ የእግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ!!

ክፍል ሁለት ይቀጥላል ….

Saturday, August 1, 2015

ኤሎሄ ኢየሱስ!

እንደምነህ ጌታ፤ ቸሩ ፈጣሪያችን፤
እኛማ አለነው፤ ከተባለ ኖርን።  
አልደላን፤ አልሞቀን በርዶን፤ አልተመቸን፤  
መግባትና መውጣት፤
ማልቀስና ማዘን ድሩን አድርቶብን፤                                                                                                                        
አንዱ ሲወጣብን፤ አንዱ ሲሄድብን።                                                                                                     
እነሆ አለነው፤ የሰው መንገድ ሆነን።

በናፍቆት ስንጠብቅ፤ ኑረትን የኖርነው
ሌሎች የገቡባት ሰማይ ቤት እንዴት ነው?
እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ  ምነው ?
እኛማ .....እኛማ
ለሹመኛ አለቃ፤ ማመልከቻ ፅፈን
ለወፈ ሰማይ ሕዝብ፣ መድረክ ላይ ለፍፈን
ጸሎት ቤታችንን፤ እኛው ላይ ቆልፈን
የምድር አተካራ፤ ህግጋቱን አልፈን                                                                                                                                    
ቢጨንቀን፤ቢጠበን
ሁለት ሽህ ዘመን፤ እነሆ አለፈን     
ስጋችንን ለብሰህ፤ ካየነው ዐይንህን።

የመምጣትህ ተስፋ ርቆ እየዳመነ                                                                                                       
እምነት ተስፋ ፍቅር እየመነመነ
ቢዘገይ ሰዓቱ ...እምነትን ዘንግተን                                                                                                                           
የልባችን ምኞት፤ ቢያይል መሻታችን                                                                                                       
የሰጠኸውን ትተን ያላልከውን ሆንን                                                                                                         
ችላ ብለን አደርን፤ ረሳንህ ጌታችን
ጠብቀን ጠብቀን ሁለት ሽህ ዘመን።

ሲሰግዱ ሰግዳለሁ፤ ሳይታጎል ጾሜ                                                                                                      
ሲበሉም በላለሁ፤ ልማዴን ደግሜ                                                                                                                                              
እልልታም፤ ዝማሬም ሲነቅፉም ቀድሜ                                                                                                                         
ምሰሶ ዐይኔ ውስጥ እኔም ተሸክሜ፤                                                                                                      
እነሆ አለሁኝ በዘልዛላ እድሜ።
የንስሐ ዘመን ቢኖረኝ ጥቂት                                                                                                                     
የቀረህ መሰለኝ ያንተ መዘግየት
ጥቂት ልጠይቅህ አቤቱ ጌታ ሆይ                                                                                                                              
ከነቅዱሳንህ አንተ ደህና ነህ ወይ?
ከምር እንደሚያሙት ምጽአት ቀረ እንዴ ?
በቶማስ ልቡና ጠረጠርኩ አንዳንዴ !                                                                                                                                  
ታውቀዋለህና ያለውን በሆዴ።
መጠርጠሬስ በእውነት ከእምነቴ ነው እንጅ፤                                                                                                 
አይደለም ከክዳት ለመውጣት ከደጅ፤                                                                                                       
ዘመኑን ከፋና እድሜን የሚፈጅ፤                                                                                                         
ኃጢአት ነገሰ፤ ለጠላትም ወዳጅ                                                                                                                    
ባየኸው ትውልዱን ሆኖልህ የማይበጅ።                                                                                                             
አንተ የሰጠኸው ረዳቱ ቀረና                                                                                                                
ራሱን አወቀ አሉ፤ ወንዱንመረጠና፤                                                                                                                                                                                                                       
ይሄ ሁሉ ሆነ ረዝሞ መዘግየትህ                                                                                                                
ኧረ መቼ ይሆን የመምጫ ዘመንህ?
የሆነስ ሆነና ሰማይ ቤት እንዴት ነው
አብረሃም ሰላም ነው ...
እዛስ ቤት ገነባ? ወይስ በድንኳን ነው ?
እኛማ ይሄውልህ ...
በቤት ኪራይ ችንካር እየተሰቀልን
‹‹ኤሎሄ›› እንላለን ጎጆ እንድጥልልን ....
ወደላይ ገነባን ወደጎን አሰፋን
ወደላይም ከላይ ወደጎንም ከጎን
እንደጉድ ተገፋን
ቤት ለእንግዳ ማለት ጭራሹኑ ጠፋን !!
አባታችን ሙሴ እንዴት ነው ለክብሩ
ውቅያኖስ መክፈያው ደህና ናት ብትሩ ?
እኛማ ይሄውልህ ....
እንጀራ ፍለጋ ባህር ስናቋርጥ
የተስፋዋን ምድር ቀን ሞልቶ ሳንረግጥ
የትም ውሃ በላን የትም አሳ ላሰን
ን ገ ር ል ን ና ብትሩን ያውሰን ....
በትር ያለው መሪ መቼም አላገኘን፤                                                                                                              
ዘመን የሚያሻግር እባክህ ላክልን።
እናልህ ጌታ ሆይ ....
ከተስፋዋ ምድር ወደሌላ ተስፋ አለን እየኳተን
መሄጃው ሲገርመን
መመለሻ መንገድ መቆሚያ ቦታ አጥተን ...!
ላባታችን ሙሴ እንደምትልልን ...
የመሄድ ዘመን ነው
ባህር የሚያሻግር
በትርህን ላክልን ...

ሰማይ ቤት እንዴት ነው ? ...                                                                                                                                                         
ዳዊትስ ደህና ነው ?
ዛሬም ይዘምራል ..መሰንቆበገና?                                                                                                                                            
ሃሌ፤ ሃሌ ሉያ የሰማይ ምስጋና፤                                                                                                         
ጎልያድስ የት ነው? በዚያ በቁመና።
እኛማ እኛማ
እልፍ አላፍ ጎልያድ ከቦን ሲደነፋ
ወንጭፉን ጠቅልሎ ምነው ዳዊት ጠፋ?
ብሎሃል በልልን
 ጌታ ሆይ ከሰማህ                                                                                                                                         
ከዘመን ጎልያድ ታደገን እባክህ                                                                                           
ሙተናል፤ ቆስለናል፤                                                                                                                            
ወንጭፍ እምነታችን ተጠቅልሎ ወድቋል።
ለረከሰ ጠጠር ለሞላ ወርዋሪ
‹‹ወንጭፍህን ስጠው ለዚህ ታሪክ አውሪ››

እንዴት ነህ ጌታ ሆይ ... ሰማይ ቤት እንዴት ነው ?
የሙሴ አልጋ  ወራሽ  ኢያሱ ሰላም ነው ....?
ያቆማትን ፀሐይ ግቢ ቢላት ምነው ...?
ያው እንደምታውቀው
ዐሥራ ሦስት ወር ፀሐይ                                                                                                                     
ወርኀ ክረምት ሸሸ፤ እየበዛ ሀጋይ                                                                                                            
ራሳችን ፈረሰ፤ምድሪቱ ደረቀች፤                                                                                                               
ወንዙ መነመነ፤ ባዶ እርቃን ቀረች።                                                                                                         
እባክህን ጌታ ሆይ ወይ ቶሎ ናልን፤                                                                                                   
ምትቆይ ከሆነም ኤልያስ ይምጣልን                                                                                                             
በጻድቅ ጸሎቱ ዝናም ያውርድልን፤                                                                                                           
በጎ ሰው ከጠፋ ዘመናት አለፈን።

ወራቱ በሙሉ ፀሐይ እያዘለ
የተሾመው ሁሉ ‹ፀሐይ ነኝ› እያለ
የሰው ጀምበር በዝቶ
ባቃጠላት ምድጃ አገር
ምን ታምር ይኖራል .... በዚህኛው ዘመን፤                                                                                                            
ታሪክ አውሪ ትውልድ፤ ኤልያስ የለውም፤                                                                                                              
ሹመቱ ምድራዊ፤መንፈሱም ሥጋውም።

ኧረ ጌታ ናልን  በናትህ ....በውድህ
በጭንቅ አላማጇ፤ ለአቅሌሲያ ብለህ
ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሁነህ ና
ማጣፊያው አጠረን፤ ሙቀት ገደለና !

ሔዋንስ ደህና ናት ?
ያው የልጅ ልጆቿ
በእግሯ ተተክተን፤
የፍሬው ሲገርምህ
ግንዱንም አንክተን፤
ፍጥረተአዳም                                                                                                                                                               
ገምጠነዋል ሥሩን።
                                                                                                                                             
የባሰ ሳይመጣ ቶሎ ድረስልን፤                                                                                                                        
አንድም ሰው አታገኝ የቆየህ እንደሆን                                                                                                        
ማራናታ እያልን ይኼው እንጮሃለን
አውራ እንደሌለው መንጋ ተበትነን
ቀበሮ ጨረሰን፤ ፈጀን፤ አቃጠለን                                                                                                                  
ኤሎሄ ኢየሱስ ቶሎ ድረስልን።

(ከጌታቸው ይመር ግጥሞች ለንባብ እንዲመች ተደርጎ በመካነ ጦማሩ የተስተካከለ)

Wednesday, July 22, 2015

" እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች"

ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ፣ ኦርቶዶክስ ብንባልም የእምነታችን ጀማሪና ፈፃሚ ግን ያው አንዱ ክርስቶስ ነው። በዚህ ዘመን ይቅርና በሐዋሪያት ዘመን እንኳ ክርስቲያኖች እርስ በእርስ በመከፋፈልና በመገፋፋት ያስቸግሩ ነበር። ጴጥሮስ (ኬፋ) ያስተማራቸው፣ ጳውሎስ ያስተማራቸው እንዲሁም ሌሎች ያስተማሩዋቸው ክርስቲያኖች ለየብቻቸው መደራጀታቸውና መራራቃቸው ሐዋሪያው ጳውሎስን አስመርሮት እንዲህ ብሎ ፅፎላቸው ነበር፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥ 10 "ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። ወንድሞቼ ሆይ፥ በመካከላችሁ ክርክር እንዳለ ስለ እናንተ የቀሎዔ ቤተ ሰዎች አስታውቀውኛልና። ይህንም እላለሁ። እያንዳንዳችሁ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ። ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስስ ስለ እናንተ ተሰቀለን? ወይስ በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን?"

በእኛ ዘመንም ቢሆን ክርስቶስ አልተከፈለም። በመካከላችንም ወይ በፕሮቴስታንት ወይ በኦርቶዶክስ ወይ በካቶሊክ ስም የተጠመቀ የለም። የተሰቀለውም አንድ ሲሆን፣ በታዘዝነው መሰረት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሁላችን ተጠምቀናል። ክርስትና አንድ ሲሆን አብያተክርስቲያናት ግን እንዳመለካከታችን መጠን ብዙ ናቸው። ልዩነት ችግር የሚሆነው እኛ ስናደርገው ነው፣ ካወቅንበት ግን ዉበት ነው።

============================
አለም ላይ እንዳለው ብዛት እና ተፅዕኖ የመፍጠር አቅም የትና የት መድረስ ይችል የነበረው የተከበረው ሐይማኖታችን፣ በኋላቀር አስተሳሰባችንና እኔ ብቻ ልደመጥ ባይነታችን እርስ በእርሱ ተጠላልፎ ወደ ፊት ዳዴ እንኳን ማለት ተስኖታል። ለዚህ ሁሉ ተጠያቂ እኛው ነን። ጥፋታችንን ሳንቀበል መፍትሄ ማምጣት አይቻልም። ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች በየቦታው ተበታትነናል። ለአንድ ዓላማ ልንቆምለት የምንችለው ትልቅ ሐይማኖት እና እውነት ይዘን፣ ነገር ግን እንደ ህፃናት በተገኘችው ጥቃቅን ቀዳዳ ሁሉ መበጣበጥ በጣም አሳዛኝ ነገር ነው። ተልኮአችንን ረስተነዋል። ውጪ ያሉትን ለክርስትና መማረክ ሲገባን የራሳችንን ወንድም በመታገል ጉልበታችንን እዛው ቤት ውስጥ እያፈሰስነው ነው። የራሳችንን ቤት እኛው እያፈረስነው ነው። ወደ ፍቅር እንመለስ!!

==========================
ማቴዎስ 12፥ 25 " እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም።"

===========================
መዝሙረ ዳዊት 133 ፥ 1 "ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።"

===========================
ዮሐንስ 17፥ 20-23 "ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።"

===========================
ስለ ክርስቲያኖች አንድነት ብዙ የተባለ ቢኖርም ለዛሬ እነዚህን አይተናል። ስህተትን ማረም ከሁሉም ይጠበቃል። በየአብያተክርስቲያናቱ ያሉ መሪዎችም ራሳቸውን መፈተሽ እና ከሚከፋፍል እና ከጥላቻ የራቀ ትምህርት ማስተማር ይኖርባቸዋል። እንዲያ ካልሆነ ግን እግዚአብሔርን ማገልገልም ሆነ መከተል ከንቱ ነው። የፍቅርና የአንድነት አምላክ እንጂ የጥላቻ እና የመከፋፈል አይደለምና። ወንድሙን ጠልቶ እግዚአብሔርን እወዳለሁ የሚል እራሱን ያታልላል።

እያልኩ ያለሁት ያሉንን አብያተክርስቲያናት አፍርሰን አንድ ቤተክርስቲያን እናቋቁም ሳይሆን፣ በያለንበት ህብረት ማድረግ ይቻላል። ከልዩነቶቻችን በላይ አንድነታችንን እናጉላው የሚል ነው።

እንግዲህ በመካከላችን ያለውን አላስፈላጊ ርቀት እናጥብብ፣ ህብረት እናድርግ፣ እንፈላለግ፣ ይቅር እንባባል። አንድነት ውስጥ ያሉ የአመለካከት ልዩነቶች ውበት ናቸው እንጂ በራሳቸው ችግር አይደሉም። መንገዳችንንም እናስተካክል፣ እግዚአብሔርንም በአንድነት እንፈልግ።

===========================
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 7፥ 14 "በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።"
===========================

በዚህ መልእክት የምትስማሙ መልእክቱን ለሌሎች ወንድሞችና እህቶች ሃሳቡን ለሌሎች አካፍሉ። እንዲህ ባለው ሀሳብ ደስተኛ የማይሆኑ አንዳንድ ግለሰቦች በየአብያተክርስቲያናቱ ቢኖሩ ለጊዜው ነው ተዋቸው፣ እግዚአብሔርን በሚገባ እስኪያውቁት ነው።


Lewi Ephrem's

Thursday, July 9, 2015

የኦሮሞ ኢስላሚስቶች ለአረፋ በዓል ሄደው በሳዑዲ ያደረጉትን ይመልከቱ!

  
    በኦሮሚያ ክልል የተነሱ የአብዱል ወሀብ ጥራዝ ነጠቅ  ተከታይ ወሀቢስቶች በጅማ፤ በኢሉባቦር፤ በአርሲና በባሌ የተለያዩ ቦታዎች በኦፊሴል የተነገረና ያልተነገረ የሽብር እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በአማራ ክልል ደግሞ የወሎ አክራሪ ወሀቢስቶች ቤተ ክርስቲያን ከማቃጠል አንስቶ ሰው እስከመግደል መድረሳቸውን በማስረጃ የተረጋገጠ እውነት ነው። በስልጤና ወራቤ የከተሙ አሸባሪ ፋናቲኮች ተመሳሳይ ድርጊት ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውም ፀሐይ የሞቀው፤ ሀገር ያወቀው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሱሪያቸውን የሚያሳጥሩ፤ ካልሲያቸውን የሚያሳዩ፤ የአፍንጫቸውን ስር ጸጉር ሙልጭ አድርገው በመላጨት ጢማቸውን የሚያሳድጉ፤ ግንባራቸው ላይ የተነቀሱ እስኪመስል ድረስ ከመሬት ሲጋጩ የጠቆረ ሰውነት ከማንነት ጋር የተሸከሙ አክራሪዎች የሌላውን መብት እስካልነኩ ድረስ ተቃውሞ የማይቀርብበት ቢሆንም የድርጊታቸው ዋነኛ ምስክር ግን ለማሸበር ልዩ ምልክታቸው ሆኖ መገኘቱ ነው። ወሀቢስቶች ከሱኒና ከሱና ውጪ ያለው ሁሉ ካፊርና ከሀዲ ነው።          ለዚህም ዓላማ ግብ መንታት መታገል፤ መዋጋትና መግደል ብሎም መሞት ጂሀድ ነው። በዚህ ዓላማ ላይ መሞት በጀና/ ገነት/ ልዩ ዓለም የሚያስገኝ ሲሆን 72 ደናግላን ሴቶች ድንግላቸውን በጂሀድ ለሞተው አሸባሪ ለማስረከብ በጥቋቁር ቀሚስ ተሸፋፍነው እንደሚጠብቋቸው ያምናሉ።
ከዚህ በታች የሚታየው ቪዲዮ በሳዑዲ የአረፋ በዓል ለማክበር የሄዱ አክራሪዎች የወቅቱ የኢትዮጵያ ባንዲራ የሆነውን ዓርማ ከተሰቀለበት አውርደው የኦነግን ባንዲራ ሲሰቅሉ ያሳያል። «ሱባንአላህ» የሚለው የኦሮሞ ኢስላሚስት አክራሪ የአማራ ባንዲራ ወርዶ የኦሮሞ መንግሥት በቅርቡ በኦሮሚያ ይቋቋማል ይላል። በዚህ ዓይነት ኦነግ አሸባሪ አይደለምን?
እንግዲህ እነዚህ የመሳሰሉ አሸባሪዎች ናቸው፤ ኢትዮጵያ ተመልሰው ሕዝብን ከሕዝብ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ሲያጋጩ የሚስተዋለው።
ደግመን ደጋግመን የምንለው እውነታ ቢኖር ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ ሁኔታ ጠፍቶ እንጂ ለቁጥር የሚያታክቱ አሸባሪዎች አሉ። «አስቀድሞ ነበር፤ መጥኖ መደቆስ፤
አሁን ምን ያደርጋል፤ድስት ጥዶ ማልቀስ»
እንዳይሆን ሰላምን፤ ፍቅርን፤አንድነት፤ ኅብረትንና በጋራ አብሮ መኖርን በሚፈልጉ የእስልምና እምነት ተከታዮች በኩል አካባቢንና ውስጥን የማጥራት ሥራ ከታችኛው እርከን አንስቶ እንዲደረግ ከዚህ በፊት ስንለው እንደቆየነው ሁሉ አሁንም ደግመን ለማስታወስ እንወዳለን።