Thursday, August 28, 2014

«ፍትሕን ለግል ስሜት መወጫ ማድረግ የቱን ያህል ለትውልድ መተዛዘቢያ ሆኖ የተሰወረ ሊሆን አይችልም» አምባሳደር ብርሃኑ ድንቄ ለአፄ ኃ/ሥላሴ በ1957 ዓ/ም ከጻፉት ደብዳቤ







ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ

አዲስ አበባ

ግርማዊ ሆይ፣

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ማኅበራዊ ሕይወት የሚታየውን ምሬትና ግፍ፣ የፍትሕም መጓደል ምክንያት በማድረግ ወደ አገሬ ለመግባት ያለኝን አሳብ ማቆየት ግድ እንደሆነብኝ ለግርማዊነትዎ መግለጥ አስፈላጊ መስሎ ታይቶኛል፡፡ ይህ ሁኔታ የሚታረምበትን በኅብረት ለመሥራት ባንሞክር ታላቅ ብጥብጥ እንደሚያስከትልብን ከታሪክ መማር ካልቻልን፣ ከተከታዩ መቅሰፍት የምናመልጥበትና የምንከለልበት ሰው ሠራሽ ዘዴ ይገኝለታል ብሎ ራስን መደለል በሕልም ዓለም ውስጥ ለመኖር እንደ መፈተን ይቆጠራል፡፡
ከዚህም በቀር ለተተኪው ትውልድ አቋም ይሆናሉ ብለን ተከባክበን ልናሳድጋቸው አላፊነት ያለብንን ሕፃናትና ውለታ ትተው ለማለፍ የተደራጁትን ሽማግሎቻችንንም ደህና ዕረፍት እንዳያገኙ ከአገሪቱ በተፈጥሮ ያገኙትን ዕድል መንፈግ ያሰኛል፡፡ በዚህም ምክንያት በፈጸምነው ስህተት ታሪክ ምሕረት ሊያደርግልን በፍጹም አይችልም፡፡
ይህን የመሳሰለው ሁኔታ በብርቱ የሚያሳስበን መሆኑን ስንገልጥ ምንም እንኳ አንዳንድ ሰዎች ‹‹አንተ ምን አገባህ?›› በማለት በጉዳዩ ባለቤትነት ክፍያ ድርሻችንን ለማሳነስ ቢሞክሩም በኢትዮጵያዊነት ትክለኛ መብት ላይ አጥብበው ያሰመሩትን የወሰን ክልል አሜን ብሎ ለመቀበል ከቶ ስለሚያስቸግር እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አላፊነቱን የማስወረድ ተግባር እንዳለበት አይካድም፡፡ እኔም ይህን ምክንያት አድርጌ በአሁኑ የመንግሥት አስተዳደር የደረሰውን ሕገ ወጥ አፈጻጸም ሁሉ ለማረምና ፍትሕን ለማደላደል የሚቻልበትን አሳብ በነፃ ለመግለጥ ስል እውጭ አገር መቆየትን መረጥሁ፡፡
በአሁኑ አያያዝ እንዲቀጥል የተተወ እንደሆነ በኢትዮጵያ የወገን መለያየትና የደም መፍሰስ እንደሚያሠጋ የመላው ኢትዮጵያውያን ግምት የወደቀበት ነው፡፡ ዋናው አላማ ይህ እልቂት የሚወገድበት መድኃኒቱ ምንድነው? ለተባለው ጥያቄ ለመመለስ እንደሆነ ጥርጥር የለውም፡፡ መቸም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በሚመስለውና በሚያምንበት ረገድ መልሱን ለመስጠት ሞክሯል፡፡ አሁን የጐደለ መስሎ የሚታየው ከዙፋኑ በኩል የሚጠበቀው ይሁንታ ብቻ ነው፡፡ ነገሩን በመጠኑ ለማብራራት ያህል በሚከተሉት መስመሮች አስተያየቴን ለመግለጥ እሰነዝራለሁ፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዙፋኑ የሰጠው ልባዊ አክብሮት ዘላቂ ሆኖ በታሪካዊ ቅርስነት እንዲጠበቅ በቤተ መንግሥቱ በኩል አልታሰበበትም ለማለት ያስደፍራል፡፡ ባለፈው ‹‹መለኮታዊ መብት›› የተባለው የዘውድ ቴዎሪ የተሳሳተ መሆኑን ቢረዳውም፣ ሕዝቡ፣ ዘውዱን ታሪካዊ ሲምቦል ወይም ምሳሌ አድርጐ በክብር ሊያኖረው ሲፈቅድ ወደ መለኮታዊ መብት አስተያየት እንደገና እንዲመለስና ጣኦታዊ ስግደት እንዲያደርግ ማስገደድ፣ በእልህ ዘውዱን ለማስረገጥ ካልሆነ በቀር ለሌላ አያገለግልም፡፡
ጃንሆይ፣ ባለዘውድ፣ አስተዳዳሪ፣ ሕግ አውጭ፣ ዳኛ፣ ምስለኔ፣ ፖሊስ፣ ጭቃ ሹም ሆኜ ልሥራ ሲሉ፣ በ፳ኛው [20ኛው] ክፍለ ዘመን የሚገኝ ሕዝብ ይህን መብት አጠቃሎ በፈቃዱ ለዘውዱ ብቻ ይለቃል ማለት የማይታመን ነው፡፡ መቸም እየተደጋገመ የሚሰጠው ምክንያት ‹‹ሕዝቡ ኃላፊነትን ለመቀበል አልደረሰም›› የሚል መሆኑን በየጊዜው ሰምተናል፡፡ በውነቱ ከአፍሪካና ከኤሻ ሕዝብ መካከል አልደረሰም ተብሎ በኢትዮጵያ ሕዝብ መፍረድ ይገባልን? ደግሞስ ያለመድረስ ትርጓሜው ምንድነው? ምናልባት የማሰብ፣ የመምረጥ፣ የማመዛዘን፣ የመፍረድ ሴንስ አልተፈጠረለትም ማለት ነው? እንደዚህማ ከሆነ በ፫ሺሕ [በ3 ሺሕ] ዘመን ውስጥ ለዚህ ሕዝብ ጭንቅላት ሆኖ ያሰበለት፣ ዓይን ሆኖ ያየለት፣ ጆሮ ሆኖ የሰማለት የዛሬው ዘውድ ነው ማለት ነዋ! የሚፈተነው ይህን የመሰለ አስተያየት ለማቅረብ እንደሆነ ምሕረት የሌለው በደል ነው፡፡
ይልቁንስ ጃንሆይ የሕግ ጠባቂነትን ልብስ ተጐናጽፈው በዚህ መንፈስ ፍትሕን ከሚያጓድሉ፣ ሥልጣኑን ለሕዝብዎ ሰጥተው እርሱ ቢጨነቅበት እንደሚሻል ጥርጥር የለውም፡፡ ያለዚያ ከዚህ ማስታወሻዬ ውስጥ ለስማቸው እንኳ ሥፍራ ለመስጠት ዋጋ የሌላቸውና ሕሊና ቢሶች የሚያቀርቡልዎትን ‹‹ደህና ታይቷል›› እያሉ ፍትሕን ለግል ስሜት መወጫ ማድረግ የቱን ያህል ለትውልድ መተዛዘቢያ ሆኖ እንደሚኖር የተሰወረ ሊሆን አይችልም፡፡
ይህን ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ለማሻሻል የሚቻለው ጃንሆይ ዘውዱን ለራስዎ አስቀርተው አስተዳደሩን ለሕዝብ በመስጠትና የዴሞክራሲን መንፈስ በማስገባት ነው፡፡ ነገር ግን ይህ አስተያየት ለግርማዊነትዎ ሰውነት አለርጂ ሆኖ ቢያስቸግርም እንኳ ሌላ ማማረጫ ይኖራል፡፡ ይኸውም ዘውዱን ለልዑል አልጋ ወራሽ ማስተላለፍና አብዲኬት ማድረግ ነው፡፡ እርሳቸው ሕገ መንግሥት ጠብቀው ለመኖር ፈቃደኛ እንደሆኑ አያሌ ሰዎች ሲመሰክሩላቸው ሰምቻለሁ፡፡ ያለዚያ ተከታዩ ትርምስና ደም መፋሰስ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም፡፡
ይህ አቤቱታ ከኔ ብቻ የቀረበ አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍርኃት ታፍኖ ነጋም መሸም የሚያጕተመትመው ይህንኑ ነው፡፡ ድምፁን ከፍ ለማድረግ ግን አካባቢው አልፈቀደለትም፡፡ እኔም ከርሱ የተለየሁ መስዬ ታይቼ እንደሆነ ያጋጣሚ ነገር ብቻ ነው፡፡ አዲስ አበባ የታፈንኩትን ያህል እዚህ ከተነፈስሁ በኋላ ወደ አገሬ እንድመለስ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ምናልባት ይህን አቤቱታ በመጻፌ እወነጀል ይሆናል፡፡ ግድ የለም፡፡ የሆነ ሆኖ በትእዛዝ ሳይሆን በነፃ የሚፈርድና በግልጽ የሚያስችል ፍርድ ቤት ተቋቁሞ ራሴን በሕጋዊ ጠበቃ አማካይነት ለመከላከል ጃንሆይ የሚፈቅዱልኝ ከሆነ በአገሬ ውስጥ ለመተንፈስ ዕድል ተሰጠኝ ማለት ነው፡፡
ከዚህም ሁሉ ጋር ላስታውሰው የምፈቅደው፣ ይህን ማስታወሻ በመጻፌ ተቀይመው የእኔን ሕይወት ለማስጠፋት በሺሕ የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚወጣ ጥርጥር የለውም፡፡ አዝናለሁ፡፡ እኔ ለሞት የተዘጋጀሁ ስለሆነ ገንዘቡ ባይባክንና ለነፍሰ ገዳይ በመስጠት ፈንታ ለጦም አዳሪ ችግረኛ ቢውል የበለጠ እንደሚጠቅም ጥርጥር የለውም፡፡ በበኩሌ በአገራችን ሬሾሉሽን እንዲነሣና የማንም ደም እንዲፈስ አልፈቅድም፡፡ በዚህ ባቤቱታዬ የምወተውተውም ሰላማዊ ለውጥ እንዲሆንና የምንፈራው ደም መፋሰስ እንዳይደርስ ስለሆነ ጃንሆይ አንድ ቀን ‹‹ለካ ብርሃኑ ውነቱ ኖሯል!›› ሳይሉ አይቀርም፡፡
እንኳን ዘውድ የጫነ ሰውነትንና ማናቸውንም ሰው የማክበር ልምድ ስላለኝ፣ ይህ አቀራረቤ ክብርን ለመድፈር እንደማያስቆጥርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ውነት ሁል ጊዜ መራራ ናት፡፡ የመድኃኒት ፈውሱ እንጂ ምሬቱ አይታሰብም እንደተባለው ይህ በቅን ልቡና የቀረበው ውነተኛ አቤቱታዬ የግርማዊነትዎን ልብ አራርቶ ለኢትዮጵያ ማኅበራዊ ሕይወት አንድ ፈውስ እንዲያመጣለት ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ጃንሆይ! በኢትዮጵያ ወጣቱ ሽማግሌው ሴቱ ወንዱ የአኗኗሩ ዘዴ ውሉ ተዘባርቆበታል፡፡ አምላካችን፣ ፈጣሪያችን እያለ ቢደልልዎት አይመኑት፡፡ ጨንቆት ነው፡፡ ከልብ የሚመርቅዎት ግን ራስህን አስተዳድር ብለው አርነት ሲያወጡትና ወደ ዴሞክራሲ ሲመሩት ነው፡፡ ይህንንም ስል ሕዝብ በራሱ ሲተዳደር ችግር አይገጥመውም ማለቴ አይደለም፡፡ እስከዚህ አልሳሳትም፡፡ ነገር ግን ሌላው ለፍቶ ከሚጥለውና ላንሣህ ከሚለው፣ ራሱ ወድቆ በራሱ መነሣትን ይመርጣል፡፡ ይኽም በሥሕተት መማር ይባላል፡፡ ስለዚህ ጃንሆይም ተሳሳቱ እያለ ከሚከስዎት እርሱ ለሥሕተት እንዲጸጸትና እንዲማር ቢያደርጉት ትልቅ ውለታ ይቆጠራል፡፡
የዛሬው ሕገ መንግሥት ዴሞክራሲን ለማስገንባት የሚረዳ ካለመሆኑም በላይ ያንኑም ቅሉ አክብሮ ለመጠበቅ በአንቀጽ ፳፩ [21] እንደተመለከተው ከንጉሠ ነገሥቱ በመሐላ የተሰጠው ቃል ፈርሷል እያሉ አያሌ ኢትዮጵያውያን እንደሚያማርሩ ግርማዊነትዎ ሳይሰማው አይቀርም፡፡ መቸም ሕገ መንግሥቱን፣ ለመጣስ አንድ የጽሕፈት ሚኒስቴር ደብዳቤ ይበቃል፡፡ እንግዴህ ሕዝቡ ወይም ሹማምቱ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝ ነኝ እያሉ ቢምሉም፣ ንጉሠ ነገሥቱ በበኩሉ መሐላውን የሚጠብቅ ካልሆነ በመሐላቸው ታስረው እንደማይኖሩ በልጅ ኢያሱ ጊዜ የደረሰው ሁኔታ ምሳሌ ሊሆን ይችል ይመስለኛል፡፡
በአሁኑ ጊዜ የገጠመንን ፕሮብሌም እንደ መጠኑ ለመግለጥ ‹‹በግርማዊነታቸው መንግሥት ያገኘሁት ኤክስፔሪያንስ›› የሚለው መጽሐፌ በሙሉ ታትሞ እስከወጣ ድረስ ፲፪ኛውን [12ኛውን] ምዕራፍ ከዚህ ጋር አያይዤ ለግርማዊነትዎ በትህትና አቀርባለሁ፡፡

                          ዋሽንግተን ግንቦት ፳፭/፶፯ [ግንቦት 25/57]
                                ከታላቅ አክብሮታዊ ፍርሐት ጋራ
                                          ብርሃኑ ድንቄ


Friday, August 22, 2014

ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብ

 (ዘርዓ ያዕቆብ ፈላስፋ

ስለ አምላክ  ሕግና ስለ ሰው ሕግ

እግዚአብሔር  የገዛ  ሕዝቡን  እንዲያስቷቸው  ስለምን  ዋሾ  ሰዎችን  ይተዋል  ብዬ  አሰብኩ፡፡  እግዚአብሔር  ግን  ለሁሉም
ለእያንዳንዱ  እውነትንና  ሐሰትን  እንዲያውቅ  ልቦና  ሰጥቶናል፡፡  እውነት  ወይም  ሐሰት እንደፈቃዱ  የሚመርጥበት
መምረጫም ሰጠው፡፡ እውነትን ብንወድ ለፍጥረት ሁሉ አስፈላጊና ተገቢ የሆነውን እርሱም እንድናይበት እግዚአብሔር
በሰጠን ልቦናችን ውስጥ እንፈልጋት፡፡ ሰው ሁሉ ዋሾ ነውና እውነትንም በሰዎች ትምህርት አታገኟትም፡፡ ከእውነት ይልቅ
ሐሰትን ብንመርጥ ስለዚህ እኛ በስህተታችን እንጠፋለን እንጂ ለፍጥረት ሁሉ የተሰራው የፈጣሪ ሥርዓትና ሕግ አይጠፋም፡፡
እግዚአብሔር ማንንም በሠራው ሥራ ይጠብቀዋል፡፡ ከሰው ሥራ ግን የእግዚአብሔር ሥራ ይጸናል፡፡ የሰው ሥራ ሊያጠፋው
አይችልም።  ስለዚህም  ከጋብቻ  ይልቅ  ምንኩስናን  ይበልጣል  ብለው  የሚያምኑ  እነርሱ  በፈጣሪ  ሥራ  ጽናት  ወደ  ጋብቻ
ይሳባሉ፡፡ ፆም ነፍስን እንደሚያፀድቅ የሚያምኑ እነርሱ ደግሞ ረሃብ በበዛባቸው  ጊዜ ይበላሉ፡፡ ገንዘቡን የተወ ፍፁም
እንዲሆን  የሚያምኑ በገንዘብ  ለሚያገኙት   ጥቅም  ወደ  ገንዘብ  መፈለግ  ይሳባሉ፡፡  ብዙዎች  የሀገራችን  መነኩሴዎችም
እንደሚደርጉት ከተዉት በኋላ እንደገና ይፈልጉታል፡፡ እንደዚሁ ዋሾዎች ሁላቸው የተፈጥሮን ሥራ ሊያፈርሱ ይፈልጋሉ፡፡
ነገር ግን ደካማነታቸውን ያሳያሉ እንጂ አይችሉም፡፡ ፈጣሪም ይስቅባቸዋል፡፡ የፍጥረት ጌታም በላያቸው ይሳለቅባቸዋል፡፡
እግዚአብሔር የእግዚአብሔርን ፍርድ ማድረግ ያውቃልና ኃጥአንም በእጁ ሥራ ወጥመድ  ተጠመደ፡፡ ስለዚህም የጋብቻን
ሥርዓት የሚያስነውር መነኩሴ በክፉ በሽታና ፍጥረቱ ባልሆነ በሌላ የሴት አበሳ በዝሙት ተጽዕኖ ይጠመዳል፡፡ ገንዘባቸውን
የሚንቁ  ገንዘብ  እንዲያገኙ  በሀብታሞችና  በነገሥታት  ዘንድ  ግብዞች  ይሆናሉ፡፡  ለእግዚአብሔር  ብለው  ዘመዶቻቸውንም
በሽምግልናቸውና በችግራቸውም ረዳት ባጡ ጊዜ የተዉ በነሱ ሽምግልና ጊዜ ሰውና እግዚአብሔርን ወደ ማማት፤ መሳደብ
ይደርሳሉ፡፡  እንደዚሁም  የፈጣሪን  ሥርዓት   የሚያፈርሱ  ሁሉ  በእጃቸው  በሰሩት  ወጥመድ  ይወድቃሉ፡፡  እንደገናም
እግዚአብሔር  ክፋትን፤ ስህተትን  በሰው  መካከል  ይተዋል፡፡  ነፍሶቻችን  በዚህ  ዓለም  የእግዚአብሔር ጥበብ  የፈጠረውን
የፈተና ቀን ይኖራሉ፡፡

ጠቢቡ ሰለሞን

"እግዚአብሔር  ፃድቃንን  ፈተናቸው፡፡  ወርቅ  በእሳት  እንደሚፈተን  ይፈትናቸዋል፡፡  ለእርሱ  የተዘጋጁ  ሆነውም
አግኝቷቸዋልና፡፡ እንደተወደደ ዕጣን መዐዛም ይቀበላቸዋል" ይላል፡፡
ከሞታችን በኋላም ቢሆን ወደፈጣሪያችን በገባን ጊዜ እግዚአብሔር በእውነትና በትልቅ በጥበብ ከሠራው ሁሉ እውነትና ቅን
የሆነውን መንገድ ሁሉ እንለያለን፡፡ ነፍሳችንም ከሥጋዊ ሞታችን በኋላ እንደምትድን ይታወቃል፡፡ በዚህ ዓለም ውዴታችን
አይፈፀምምና የሌላቸው ይፈልጋሉ፤ ያላቸው ባላቸው ላይ እንደገና ሊጨምሩ ይፈልጋሉ፡፡ሰው በዚህ ዓለም ያለው ሁሉ
እንኳን  ቢኖረው  እንደገና  ይወዳል  እንጅ  አይጠግብም፡፡  ይህም  የፍጥረታችን  ጠባይ  ለሚመጣው  ንብረት  እንጂ  ለዚህ
ዓለም ንብረት ብቻ እንዳልተፈጠርን ያመለክታል፡፡ በዚያውም የፈጣሪያቸውን ፈቃድ የፈፀሙ ነፍሳት ፍፁም ይጠግባሉ
እንጂ ከእንግዲህ ሌላ አይወዱም፡፡ አለዚያ ግን የሰው ፍጥረት አስፈላጊውን ሁሉ አላገኝምና ጎዶሎ በሆነ ነበር፡፡ እንደገናም
ነፍሳችን  እግዚአብሔርን  ማሠብ  ትችላለችና  በሃሳቧም  ታየዋለች፡፡  እንደገናም  ለዘላለም  መኖር  ማሰብ  ትችላለች፡፡
እግዚአብሔርም ይህን ማሰብ በከንቱ አልሰጣትም፡፡ ነገር ግን እንደሰጣት ልታስብና  እንድታገኝም ሰጣት፡፡ ደግሞ በዚህ
ዓለም ፅድቅ ሁሉ አይፈፀምም፡፡ ክፉ ሰዎች ከዚህ ዓለም መልካም ይጠግባሉ፡፡ ደጋጎች ይራባሉ፡፡ የሚደሰት ክፉ አለ፣
የሚያዝን ደግ አለ፣ የሚደሰት ዐመፀኛ አለ፣ የሚያለቅስ ፃድቅም አለ፣ ስለዚህም  ከሞታችን በኋላ ለሁሉ እንደየምግባሩ
የሚከፍለው  ሌላ  ኑሮና  ፍፁም  ፅድቅ  ያስፈልጋል፡፡  በብርሃን  ልቦናችን  ተገለፀላቸው፡፡  የፈጣሪን  ፈቃድ  የፈፀሙና
በተፈጥሯቸውም ፀባያዊ ህጉን የጠበቁ ዋጋቸው ይከፈላቸዋል፡፡ የተፈጥሮን ሕግ ከመረመርን የተረጋገጠ መሆኑን ልቦናችን
በግልፅ  ይነግረናል፡፡  ነገር  ግን ሰዎች  ሊመረምሩ  አልፈለጉምና  የፈጣሪያቸውን  ፈቃድ በእውነት  ከመፈለግ  የሰዎችን  ቃል
ማመን መረጡ፡፡

 ስለ ባህሪያዊ ዕውቀት

የፈጣሪ ፈቃድ ግን ለእግዚአብሔር ለፈጣሪህ ስገድ ፣ ሰውንም ሁሉ እንደነፍስህ አፍቅር ይላል፡፡ ይህ በልቦናችን እውነት
መሆኑ  ይታወቃል፡፡  እንደገናም  በልቦናችን  እውነትነቱ  የሚታወቅ  ሌላ  እውነት  "ሊያደርጉብህ  የማትፈልገውን  በሰው
አታድርግ፡፡  ላንተ  ሊያደርጉልህ  የምትፈልገውን  አድርግላቸው"  ይላል፡፡  የሰንበትን  ማክበር  የሚለው  ካልሆነ  በቀር  ዐሥሩ
የኦሪት  ትዕዛዛት  የፈጣሪ  ናቸው፡፡  ሰንበትን  ለማክበር  ግን  ልቦናችን  ዝም  ይላል፡፡ ልንገድልና  ልንሰርቅ፣  ልንዋሽና  የሰው
ሚስት  ልንሰርቅ  ይህን  የሚመስለውን  ልናደርግ  እንደማይገባን  ልቦናችን  ይነግረናል፡፡ እንዲሁ  ስድስቱ  የወንጌል  ቃላት
የፈጣሪ  ፈቃዶች  ናቸው፡፡  እኛ  ይህን  የምህረት  ሥራ  ሊያደርጉልን  እንፈልጋለን፡፡  በሚቻለን  ለሌሎች  ልናደርግላቸው
ይገባናል፡፡ ደግሞም በዚህ ዓለም ሕይወታችን፣ ንብረታችን እንድንጠብቅ የፈጣሪ ፈቃድ ነው፡፡ ከፈጣሪ ፈቃድ ወጥተን
በዚህ ሕይወት እንኖራለን፡፡ በተቀደሰ ፈቃዱ ካልሆነ በቀር ልንተወው አይገባንም፡፡እርሱ ፈጣሪያችን ለሁሉ ልቦናና ችሎታ
ስለሰጠ ኑሯችንን በዕውቀትና በሥራ እንድናሳምረው ይፈቅድልናል፡፡ ይህ ካልሆነ በቀር የሕይወታችን ፍላጎት አይገኝም፡፡
እንዲሁ  አንዱ  ካንዷ  ጋር  መጋባትና  ልጆች  ማሳደግን  ፈቅዷል፡፡  ደግሞም  ከልቦናችን  ጋር  የሚስማማ  ለህይወታችንም
ለሁሉም  የሰው  ልጆች  ኑሮ  የሚያስፈልጉ  ሌሎች  ብዙ  ሥራዎች  አሉና  የፈጣሪ  ፈቃድም  እንዲሁ  ስለሆነ  ልንጠብቀው
ይገባናል፡፡ እግዚያብሔር ፍፁማን አድርጎ እንዳልፈጠረን ልናውቅ ይገባናል፡፡ ለመፈፀማችን የተዘጋጀን አዋቂዎችና በዚህም
ዓለም  እስካለን  ድረስ  እንድንፈፅምና  ፈጣሪያችን  በጥበቡ  ላዘጋጀልን  ዋጋ  የተዘጋጀን እንድንሆን  አድርጎ  ፈጠረን፡፡  በዚህ
ምድር ፍፁማንና ብፁዓን አድርጎ ሊፈጥረን ለእግዚአብሔር ይቻለው ነበር፡፡ ነገር ግን ለመፈፀማችን የምንዘጋጅ አድርጎ
ፈጠረን እንጅ እንዲሁ ሊፈጥረን አልፈቀደም፡፡ ከሞታችን በኋላ ፈጣሪያችን ለሚሰጠን ዋጋ የተዘጋጀን ፍፁማን እንድንሆን
በዚህ የፈተና ዓለም መካከል አኖረን፡፡ በዚህ ዓለም እስካለንም ወደ እርሱ እስኪወስደን ድረስ እየታገስን ፈቃዱን እየፈፀምን
ፈጣሪያችን  ልናመሰግነው  ይገባል፡፡  የፈተናችንንም  ጊዜያቶች  እንዲያቀልልን  ባለማወቃችን  ሠራነውን  የእብደት  አበሳ
እንዲተውልን የተፈጥሮ ሕግጋትን አውቀን እንድንጠብቃቸው ልቦና እንዲሰጠን ወደቸርነቱ እንለምን፡፡ ፀሎት ደግሞ ላዋቂ
ነፍስ  አስፈላጊ  ነውና  ዘወትር  ልንፀልይ  ይገባናል፡፡  አዋቂ  ነፍስ  ሁሉን  የሚያውቅና ሁሉን  የሚጠብቅ  ሁሉን  የሚገዛ
እግዚአብሔር እንዳለ ታውቃለች፡፡ ወደ እርሱ እንድትፀልይም ከእርሱ መልካም እንድትለምን፣ ከክፉ እንድትድንና ሁሉን
ወደሚችል እጅ እንድትማፀን ወደ እርሱ ትሳባለች፡፡ እግዚአብሔር ምሁርና ትልቅ ነው፡፡ የሚሳነውም የለም፡፡ ከበታቹ
ያለውን ያያል፣ ሁሉንም ይይዛል፣ ሁሉን ያውቃል ፣ ሁሉን ይመራል፣ ሁሉን ያስተምራል አባታችን ፈጣሪያችን ጠባቂያችን
ነው፡፡  የነፍሳችን  ዋጋ  ቸርና  ይቅር  ባይ  ችግራችንን  ሁሉ  የሚያውቅ  ነው፡፡  ለሕይወት  እንጂ  ለጥፋት  አልፈጠረንም፡፡
በትዕግስታችን ይደሰታል፡

Thursday, August 14, 2014

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሥርዓተ አልበኝነት ነግሷል!

  • የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሲፈራርስ ዝምታው እስከመቼ?
  •  
  •  ቅዱስ ፓትርያርኩ በዚህ ጉዳይ ምላሻቸው ምን ይሆን?

ዛሬ ዛሬ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የሚለው ቃል ከወረቀት ባለፈ በመሬት ላይ ተፈሚነቱ የሚታየው በጣም በጥቂቱ ነው። በተለይም ቤተ ክርስቲያኒቱ አለኝ በምትለው ማእርገ ክህነት በኩል ዲቁና፤ ቅስና ( ምንኩስና) ቁምስና በሙሉ የሚሰጠው ለማንና መስፈርቱ ምን እንደሆነ በማይታወቅ መልኩ ሥርዓተ የለሽ ሆኖ ይታይበታል። እነ መቶ አለቃ ግርማ ወንድሙ ሳይቀሩ በር የሚዘጋ መስቀል ተሸክመው እያሳለሙ በአጥማቂነት ተሰማርተው ገንዘብ ይሰበስባሉ። ከዚህ በፊት ወደእስራኤል አቅንቶ የነበረው ግርማ ወንድሙ ገና ገንዘብ መሰብሰብ ሲጀምር አንዷን ሴት ሲያጠምቅ ጎረቤቷ ቡዳ ሆና በላቻት በማሰኘቱ፤ ቡዳ ናት የተባለችው ሴት ፍርድ ቤት በስም አጥፊነት ከሳው መጥሪያ ብታመጣበት ሌሊቱኑ ፈርጥጦ ወደኢትዮጵያ ማምለጡን ጉዳዩን በቅርበት ከሚያውቁ ሰምተን ተገርመን ነበር። ባለቤት የሌላትን ቤተ ክርስቲያን እየተዘዋወረ በክፉ መንፈስ የሚበጠብጠው ግርማ አሁን ደግሞ ወደአውሮፓ ዘልቆ በጣሊያን የዘረፋውንና የቡዳ በላሽ ዜማውን እያስነካው ይገኛል። እነባህታዊ ገብረ መስቀል ማርያምን ተገለጸችልኝ እያሉ ህዝቡን ሲያጭበረብሩ እንዳልነበር ብህትውናውን እርግፍ አድርገው ቆንጆ መርጠው ሚስት አግብተው ልጆች ወልደው ማርያም ተገለጸችልኝ፤ ገብርኤልን አየሁት ከሚል ማደናገሪያ ነጻ ወጥተዋል። ከማጭበር በር ይህኛው የተሻለ አማራጭ ይመስለናል።
ይህ ማእርገ ክህነት የሚባለው ሹመት በአንዳንዶች ዘንድ የክብር ዶክትሬት ይመስል ከስም ባለፈና የሕዝቡን ግንባር ከሚገጩበት በስተቀር እንደማኅበረ ቅዱሳን ባሉ ማኅበራት ዘንድም የአገልግሎት ዋጋ የሌለው መሳሪያ ሆኖ ይገኛል። በየትኛውም ቤተ ክርስቲያን ሲያገለግሉበት አይታይም። የማዕረጉን ስም የሚፈልጉት ክህነት የላቸውም እንዳይባሉና በክህነት ሽፋን በሚገኘው ክብር የመበለቶችን ቤት ለመዝረፍ ስለሚረዳ እንጂ ከመጀመሪያው በድንግልና ጸንተው ለማዕርገ ዲቁና በቅተው «ተንሥኡ፤ ጸልዩ» እያሉ ሲያገለግሉበት ቆይተው፤ በኋላም በስርዓተ ቤተ ክርስቲያን በተክሊል በድንግልና የጸናች አግብተው አይደለም። ሲጀመር ጀምሮ ዲቁናም ይሁን ቅስና የተቀበሉት ሰዎች ድንግላቸው የፈረሰበትን ጊዜ ራሳቸው በትክክል አያውቁትም። ራሳቸው በድንግልና ሳይቆዩ፤ ድንግልና እንደፈንጣጣ በጠፋበት ዘመን ድንግል አግብተው አይቀስሱም።  በተለይ ወንዶቹ አጭበርባሪዎች፤ ቀሳጮችና መልቴዎች ናቸው። በዚህ ዙሪያ ሀገር ሰፈሩን ሲያዳርሱ የኖሩ የዘመኑ ቀሳውስትና መነኮሳት ነን ባዮች ቅስናን እንደማጭበርበሪያ ይጠቀሙበታል። ቅዱስ በተባለው መቅደስ ገብተው በርኩስናቸው ሕዝቡን ያታልሉበታል። ይህ ዐመፃና ማታለል በሀገር ላይ ጥፋትን፤ በሕዝብ ላይ ቁጣን ማምጣቱ አይቀርም። ማንም እመራበታለሁ ብሎ ላወጣው ለራሱ ሕግ የማይታዘዝ ከሆነ የሚጠፋው በዚያው በራሱ ሕግ ነው።
«ያለ ሕግ ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለ ሕግ ደግሞ ይጠፋሉና፤ ሕግም ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል» ሮሜ 2፤12
ዛሬ ሁሉም ከዚህ ከራሳቸው የሕግ ክብር ስለወረዱ ማንም ምንንም አይቆጣጠርም። ሥርዓት ፈረሰ፤ ሕግ ተጣሰ የሚል አንድም ስንኳ የለም። «ኩሉ ዐረየ፤ ወኅቡረ ዐለወ» እንዳለው ዳዊት በመዝሙሩ ሁላቸውም ተሳስተዋል፤ ሁላቸውም በዐመጻ ስለተስተካከሉ ዲቁና ሰጪውም ተቀባዩም ከሥርዓት ውጪ ሆነዋል።  ከዚህ በታች የቀረበውም ጽሁፍ ይህንን መሠረት ያደረገ ነው።
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነን «እንበለ አሐዱ ኄር፤ ኢይኀድጋ ለሀገር» ለሀገር እንዲሉ አንድ ተቆርቋሪ ኤርትራዊ ቄስ ከሀገረ እስራኤል-ቴል አቪቭ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ለልዩ ልዩ ድረ ገጾች በግልባጭ ሲልክ ለእኛ የደረሰውን ጽሁፍ እንዳለ አቅርበነዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምን ሆነች?

በታሪክ አጋጣሚ ኢትዮጵያና ኤርትራ ከመለያየታቸው በስተቀር በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነት ዛሬም ድረስ አንድ ነን። ሥርዓቱና ሕግጋቱ የተለያየ አይደለም። በማዕረገ ክህነት አሰጣጥ ልዩነት ያለን አይመስለንም።  ነገር ግን እጅግ አሳዝኝና አስገራሚ ነገር ስናይ የምንጠይቀው አጥተናል። በተደረገው ሁኔታ እኛ በእስራኤል የምንገኝ ኤርትራውያን በተደረገው አድራጎት ተጎድተናል። ይኸውም ለሰሚ የሚከብድና ከምናውቃት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ህግጋት ውጪ ማዕረገ ክህነት በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳም ውስጥ ሲሰጥ በማየታችን በጣም አዝነናል። ነገሩን በአጭሩ አስረዳለሁ።
ሰውየው በትግራይ ክፍለሀገር ሰንቃጣ እንደተወለደ አውቀነዋል። ስሙም ሓጎስ አስገዶም ይባላል። በትግራይ ክፍለ ሀገር ይህ ሓጎስ አስገዶም የተባለ ሰውዬ አባ ሰላማ የሚባል ማኅበር አቁሞ ህዝብ ለህዝብ ሲያጋጭ ተይዞ ሶስት አመት ወኅኒ ታስሮ ነበር። በአቡነ መርሐ ክርስቶስ ማኅበሩ በትእዛዝ ፈረሰ። በሲኖዶስም ተወሰነበት። ተስፋ ያልቆረጠው ይህ ሓጎስ አሰገዶም የተባለ ሰውዬው ወደ ሽመልባ የኤትራውያን ስደተኛ ካምፖ በመግባት ባሕታዊ ወልደ ሥላሴ እባለሎህ በማለት ማደናገር ጀመረ።
ባህታዊ ነኝ የሚለው ሓጎስ አስገዶም

በዚያም በእሱ የተጀመረ ረብሻ በሽመልባ ባሉ የኤርትራ ቤተክርስቲያን በመበራከቱ ጥቂት ተከታዮች አስከትሎ በሱዳን አድርጎ ሊቢያ ገባ። ሊቢያ ሲገባም አባ ሰላማ መልዕክት ነግረውኛል ከዛሬ ጀምሮ አንተ ሞኖክሴ ነህ ብለውኛል ብሎ አባ ሳሙኤል ነኝ አለ። ከዚያም ይህ ሓጎስ አስገዶም ከሊቢያ ወደእስራኤል ሀገር ከኤርትራውያን ጋር ገብቶ ኤርትራዊ ነኝ ብሎ የስደተኛ ወረቀት ከወሰደ በኋላ ሳይሞኖክስ አባ ሳሙኤል ተብሎ እየተጠራ ቆየ። አጠምቃለሁ እያለ ሲያታልል፤ ህዝብ ሲያሳብድ፤ ገንዘብ ሲሰበስብ ቆይቶ ብዙ ኤትራውያን ደግሞ አንተ ሞኖክሴ አይደለህም፤ ለምን አባ ትባላለህ። ክህነት የለህም ለምን ታሳልማለህ።  ንስሀ ለምን ትሰጣለህ ስንለው የእኔ ክህነት በአባ ሰላማ ፍሬምናጦስ አማላጅነት ከሰማይ ነው የተሰጠኝ፤ የእናንተ ክህነት ግን ከኃጢአተኛ ጳጳስ እጅ የተሰጠ ነው እያለ ሲሳደብ በማየታችን ህዝቡ በዚህ አታላይ ሰው እንዳይታለል ስናስተምር ተናዶ ወደኢየሩሳሌም በመሄድ ከኢትዮጵያ ሊቀጳጳስና አንዳንድ መነኮሳት ጋር በስውር መገናኘቱን ቀጠለ።
ባህታዊ ወልደ ሥላሴ ነኝ እያለ በሽመልባ ሲያታልል

 ከዚያም ከሊቀ ጳጳሱ አባ ዳንኤል ዘንድ ዲቁና ተቀበልኩ አለና በአስማቱ ለሚያታልላቸው ደጋፊዎቹ  ማዕረጉ ሲሰጠው የሚያሳይ ፎቶና ፊልም አሳየ። ትንሽ ቆይቶ ሞኖኮስኩኝ ብሎ እንደቦብ ማርሊ ያሳደገውን ጸጉሩን ቆርጦ ጥቁር ቆብና ቀሚስ አድርጎ መጣ። አንተን አመነኮሰች ቤተ ክርስቲያን? ብለን አዘንን። አለቀስን።
በአባ ሳሙኤል ስም ቄስና መነኩሴ ነኝ አለን ደግሞ

ከሱ ጋር የነበሩና ስናስተምራቸው የተመለሱ ሁለት ዲያቆናት ለመመንኮስ 50 ሺህ ሼቄል ከፍሏል አሉን። ለሊቀ ጳጳሱና ከመነኮሳቱ መካከል አባ ፍስሐና አባ ብርሃና መስቀል የተባሉም ገንዘብ መቀበላቸውን አሁንም ይመሰክራሉ። የሰው ማስረጃ አለን። ሌሎችም መነኮሳት የተቀበሉ አሉ። ይህ አታላይ አባ ሳሙኤል የተባለው ትንሽ ቆይቶ የቅስና ማዕረግ ከአባ ዳንኤል ተሰጠኝ ብሎ በደብረ ገነት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ሥርዓት በቢዲዮና በፎቶ  ቴልአቪቭ አምጥቶ ለተከታዮቹ አሳየ። ይህ ሁሉ ማስረጃ በእጃችን ይገኛል።
ምንም የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሙያ ለሌለው፤ ዲቁና ሳይኖረው  ለሓገስ አስገዶም ቅስና ሲሰጡት አቡነ ዳንኤል ናቸው

 የዚህ ሁሉ አስተባባሪ አባ ፍስሐ ይባላሉ። አባ ብርሃነ መስቀል የተባሉት፤ አባ ተወልደ የተባሉትም አብረውት አሉ። ገንዘብ የተቀበሉ መኖክሴዎች ዝርዝር በእጃችን አለ። በቁጥር ትንሾች ቢሆኑም የቤተ ክርስቲያን ስርዓት ጠፋ ብለው የተናገሩ ቢኖሩም የሰማቸው የለም።  ገንዘብ የሁሉንም አፍ ዝም አሰኝቷል።



 እኛ የምናዝነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ሹማምንት በገንዘብ ስልጣነ ክህነት እየሰጡ ለምን ቤተ ክርስቲያንን ያሰድባሉ? የኢየሩሳሌም ገዳም ሞኖክሴዎችስ ለምን በገንዘብ ይደለላሉ? ክህነት እንደዚህ ነው? ሙንኩስናስ እንደዚህ ነው? በበኩላችን ይህን ሰውዬ ያለአግባብ እያታለለ ከኤርትራውያን እጅ የወሰደውን በብዙ መቶ ሺህ ሼቄል ለማስመለስና በህግ ፊት ለማቆም ማስረጃዎቻችንን ይዘናል። እናንተ በሰጣችሁት ክህነት አንታለልም። አንታወክም። ለነገሩ ቤተ ክርስቲያንን አዋርዳችሁታል። ሓጎስ አስገዶም ቄስ ሆነ? ሚስቱንም አምጥቶ አመነኮሰ። አንድ ቤት አንድ ላይ ይኖራሉ። አይ ኦርቶዶክስ፤ እንደዚህ መሆና ያሳዝናል። ሕግ ካለ፤ ዳኛ ካለ ኢየሩሳሌም ያሉ ሞነኮሳትን ከገዳሙ ማባረር ነበር። ለሓጎስ አስገዶም ቅስና የሰጡ ሊቀጳጳሱም መቀጣት ነበረባቸው።
ያሳዝናል። ያሳዝናል። በትክክልም ዘመኑ ተጨርሷል። ክህነትና ሙንኩስና  በገንዘብ ሆነ። ኤሎሄ ኤሎሄ ይባላል።

ለምእመን በገንዘብ ክህነት እንዲያገኝ ያደረጉ አባ ብርሃነ መስቀል የሚባሉት በቀኙ፤ አባ ፍስሐ የሚባሉት አባ ፍስሐ የሚባሉት በግራ በመሀል አቡነ ዳንኤልና ሲሆኑ በደብረ ገነት ቤተመቅደስ ውስጥ ሓጎስ አስገዶም ፤ ወልደሥላሴና አባ ሳሙኤል የተባለው ቅስና ሲቀበል የሚያሳይ ፎቶ። የዚህ ሥርዓት ሙሉ ቪዲዮ በእጃችን አለን።
             
                     ፍትዊ አንገሶም ቴልአቪቭ

Monday, August 11, 2014

ትክክለኛው ሃይማኖት የቱ ነው?



 ቀልጣፋ ሬስቶራንቶች በቀላሉ የሚስቡን የፈለግነውን ምግብ በምንወደው መንገድ እንድናዝ መንገድ ስለሚከፍቱልን ነው። ጥቂት ካፌዎች ደግሞ ከመቶ በላይ የተለያዩ የቡና ጣዕም እንደሚያቀርቡ በጉራ ይናገራሉ። መኖሪያ ቤቶችና መኪናዎችን ስንገዛ እንኳ የምንፈልገው ምርጫ እንዲያሟላ እንሻለን። በቼኮላት፣ በቫኒላና በእንጆሪ ዓለም ታጥረን መኖር አንፈልግም። ፍላጎት ንጉሥ ነው! እንደግላዊ ፍላጎትህና ምርጫህ የምታገኝበት ሁሉ የተሟላበት ዘመን ነው።
ለአንተ ብቻ ትክክለኛ ሃይማኖት የማግኘቱ ሁኔታስ ምን ይመስላል? ወቀሳ አልባ፣ ብዙ ጫና የሌለውና ይህንን አድርግ አታድርግ እያለ የማያስቸግር ሐይማኖት ብታገኝስ? ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት ያውና እዚያ አለ ነገር ግን ሃይማኖት እንደሚወዱት አይስክሬም የሚመረጥ ነው እንዴ?
ትኩረታችንን ለመሳብ የሚሻሙ በርካታ ድምፆች ስላሉ ለምን ብሎ ነው አንድ ሰው ኢየሱስን ከሌሎች ማለትም ከመሐመድ ወይም ከኮንፊሸየስ፣ ከቡድሐ ወይም ቻርለስ ቴዝ ራስል ወይም ከጆሴፍ እስሚዝ አስበልጦ የሚመርጠው? ዞሮ ዞሮ ሁሉም መንገዶች የሚያደርሱት ወደ መንግስተ ሰማይ አይደለም እንዴ? በመሰረቱ ሁሉም ሃይማኖቶች አንድ አይደሉም እንዴ? እንደ እውነቱ ከሆነ ሁሉም ሃይማኖቶች ወደ መንግስተ ሰማይ አያመሩም። ሁሉም መንገዶች ወደ ኢንዲያና መቼም አያደርሱም።
ኢየሱስ ብቻውን በእግዚአብሔር ሥልጣን ይናገራል።
1/  ምክንያቱም ኢየሱስ ብቻ ነው ሞትን ያሸነፈው። እስካሁን ድረስ መሐመድ፣ ኮንፊሸየስና ሌሎች በመቃብር በስብሰው ይገኛሉ። ነገር ግን ኢየሱስ በራሱ ስልጣን በጨካኙ የሮማውያን መስቀል ከሞተና ከተቀበረ ከሦስት ቀን በኋለ መቃብሩን ፈንቅሎ ተነስቶአል። በሞት ላይ ስልጣን ያለው ማንኛውም ሰው ትኩረታችን ሊስብ ግድ ይላል። ማንም በሞት ላይ ስልጣን ያለው ግለሰብ ሲናገር ልናደምጠው አስፈላጊ ነው። ሞትን ማሸነፍ የቻለ ከፍጥረታት መካከል ማንም የለም። ከሰማይ የመጣው ብቻ ሞትን አሸንፎ ወደሰማይ ወጥቷል።ስለዚህ እንዲህ ያለው አሸናፊ የተናገረው የእምነት መሠረት መሆን አለበት። ሰው ሟች መሆኑን ያውቃል። ሟች ደግሞ ከሞት ለማምለጥ የሚችለው በሞት ላይ ባለሙሉ ሥልጣን በሆነ ክንድ ላይ ሲያርፍ ነውና ኢየሱስን ማመን የግድ ይለዋል። ሌላ ማንም አዳኝ የለም።
2/ የኢየሱስ ሕይወትና ትንሣዔ ምስክር ያለውና እውነት ነው።  የኢየሱስን ትንሣዔ የሚደግፈው መረጃ የሚያጥለቀልቅ ነው።   ሮማውያንና ሰቃልያኑ ካህናት የኢየሱስን መቃብር ማስጠበቅ ያስፈለጋቸው «በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ» ያለውን ቃሉን ይዘው እንጂ የሞተ ሰው መቃብር ስለሚጠበቅ አልነበረም።  አዎ ትንሣዔውን ለመከላከል ወታደሮች ከመቃብሩ ማንም እንዳይወጣ፤ ወደመቃብሩም ማንም እንዳይደርስ አድርገው አስጠብቀው ነበር። ነገር ግን የመቃብሩ ቦታ ባዶ ሆኗል!  እንደተናገረው አልተነሳም እንዳይሉ የኢየሱስ ጠላቶች ያን ሁሉ ስለትንሣዔው የተነዛውን ወሬ ለማክሸፍ የበሰበሰውን አካሉን በማቅረብ በቀላሉ ያስታግሱት ነበር። ግን አልቻሉም፤ መላው ሲጠፋባቸው ደቀመዛሙርቱ ሬሳውን ሰርቀውት ይሆን? አሉ።  ከሐዋርያቱ መካከል ከዮሐንስ በስተቀር ሌሎቹ የሸሹት በጊዜ ነው። የሸሹ ሰዎች ተመልሰው ከሮማ ወታደሮች ጋር ተዋግተው ሰረቁት ማለት የማይመስል ነገር ነው። ቀላሉ ሃቅ ግን የኢየሱስ ትንሳኤ እንዲሁ ተነግሮ ተገልፆ የሚያልቅ መች ሆነና! ትንሣዔውን ያለምስክር ያልተወ ኢየሱስ ግን በአንድና በሁለት ሰዎች ፊት ብቻ ሳይሆን በአምስት መቶ ሰዎች ፊት ትንሣዔውን አስመስክሯል።

«መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤ ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ» 1ኛ ቆሮ 15፤4-8

ስለዚህ ሰዎች ኢየሱስን ለማመን የሚያስችላቸው በቂ የእምነት ማስረጃ ስላላቸው ነው። በዚህ ምድር ላይ ካሉ ሃይማኖቶች ውስጥ እንደኢየሱስ ሞትን ያሸነፈ፤ ትንሣዔውን በምስክር ያረጋገጠ ማንም የለም። ስለዚህ በሞት ላይ ሥልጣን ያለው ማንም ሰው ሊደመጥ ይገባል። ኢየሱስ በሞት ላይ ያለውን ሥልጣን አረጋግጧል። ስለዚህ የሚናገረውን መስማት ይገባናል። ለድነት ብቸኛው መንገድ ኢየሱስ መሆኑን ራሱ ይናገራል።(ዮሐንስ 14፡ 6)። ካሉትም ብዙ መንገዶች አንዱ አይደለም። ኢየሱስ ብቸኛ የድነት መንገድ ነው። ሌላ መንገድ ሁሉ በትንሣዔና በሕይወት ላይ ሥልጣን የሌለው የሞት መንገድ ነው።
3/ ኢየሱስ ከሸክም ያሳርፋል። በዚህ ምድር ላይ ከሸክም አሳርፋችኋለሁ ብሎ ቃል የገባ አንድም ሥጋ ለባሽ የለም። ይህ ብቸኛ ኢየሱስ እንዲህ ይላል “እናንተ ደካሞች፤ ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፣ ወደእኔ ኑ፣ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” (ማቴዎስ 11፡ 28)። ሕይወትም አስቸጋሪ ነው። ብዙዎቻችን ደምተናል፣ ቆስለናል፣ ጦርነትንም እንፈራለን። ዓለምም አስጨናቂ እየሆነች ነው። ስለዚህ የሚያሳርፈንን ብንፈልግ ተገቢ ነው። ነገር ግን ከኢየሱስ በቀር ሸክም የከበዳችሁ ወደእኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ ያለ ማንም ሌላ የለም። በትንሣዔውና በሕይወቱ የታመነ ኢየሱስ ይህንን የማለት ብቃት ስላለው በእርሱ ላይ ማረፍ ከአስጨናቂው ዓለም ለመዳናችን ዋስትናችን ነው።
ስለዚህ ምን ትፈልጋላችሁ? ከኃጢአት፤ ከድካም፤ ከተስፋ መቁረጥ በንስሐ መታደስ ወይስ  የአንዱ ሃይማኖት አባል በመሆን ብቻ መኖር? ሕያው የሆነ አዳኝ ወይስ “ከሞቱት በርካታ ነቢያት ወይም ጻድቅ” አንዱን ተስፋ ማድረግ? ትርጉም ያለው ግንኙነት ወይስ ተራ የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት መከተል?
ኢየሱስ አማራጭ ሳይሆን ምርጫ ነው! ሃይማኖት ማለት አንድ መንፈሳዊ ድርጅት ወይም የአንዱ ተቋም ስያሜና የዚያ አባል ሆኖ መኖር ማለት አይደለም።  ከእግዚአብሔር  አብ ጋር ትርጉም ያለው ግንኙነት ትፈልግ እንደሆን ሃይማኖትህ ኢየሱስን ማመን ነው። «በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው»  ይላል መጽሐፍ። (ዮሐንስ 3፡ 36) አንዳንዶች ይህንንማ እናምናለን ነገር ግን ትክክለኛው እምነት ያለው በኛ ሃይማኖት ውስጥ ስለሆነ አባል ሁነን ይላሉ። መጽሐፍ ቅዱስ በማኅበር ስለመጸለይ ይነግረናል እንጂ ኢየሱስን ለማመን የዚህ ወይም የዚያ ሃይማኖት ተቋም አባል ሁን የሚል ትዕዛዝ የለውም። ኢየሱስ በሱ የሚያምኑ ሁሉ እንዲድኑ እንጂ የሃይማኖት ድርጅት ሊመሠረት አልመጣም።

«የምንለምነውንም ሁሉ እንዲሰማልን ብናውቅ ከእርሱ የለመነውን ልመና እንደ ተቀበልን እናውቃለን» 1ኛ ዮሐ 5፤15

(www.Gotquestions.org)ተሻሽሎ የተወሰደ

Friday, August 1, 2014

ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብ

(ዘርዓ ያዕቆብ ፈላስፋ) ክፍል ሁለት

የሰው  ፍጥረት  ታካችና  ደካማ  መሰለኝ፡፡ ሰው  ግን ፍቅርን  ቢወዳትና  በጣም  ቢያፈቅራት  የተሸሸገውንም  ፍጥረትን  ቢያውቅ ይወዳል፡፡ ይህም  ነገር  እጅግ  ጥልቅ  ነውና  በትልቅ  ድካምና  ትዕግስት  ካልሆነ  በስተቀር  አይገኝም፡፡ ጠቢቡ ሰለሞን፡ “ከፀሐይ  በታች  ስለተደረገው  ሁሉ  ጥበብን  ለመፈለግና  ለመመርመር  ልቤን  ሰጠሁ፡፡  እግዚአብሔር  ለሰው  ልጆች  እንዲደክሙበት የሰጣቸውን  ክፉ  ስራ  አየሁ”ይላል፡፡

   ስለዚህ  ሰዎች  ሊመረምሩት  አይፈልጉም፡፡  ሳይመረምሩ  ከአባቶቻቸው  የሰሙትን  ማመን  ይመርጣሉ፡፡  ነገር  ግን እግዚአብሔር  ሰውን  የምግባሩ  ጌታ  ክፉ  ወይም  መልካም  የፈለገውን  እንዲሆን  ፈጠረው፡፡  ሰውም  ክፉና  ዋሾ  መሆንን  ቢመርጥ ለክፋቱ የሚገባውን  ቅጣት  እስኪያገኝ  ድረስ  ይችላል፡፡ ነገር  ግን  ሰው ሥጋዊ  ነውና  ለሥጋው  የሚመቸውን  ይወዳል፡፡ ክፉ  ይሁን  መልካም  ለስጋው  ፍላጎት የሚያገኝበትን  መንገድ  ሁሉ  ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር  ሰው  የፈለገውን  እንዲሆን  ለመምረጥ  መብት  ሰጠው  እንጂ  ለክፋት  አልፈጠረውም፡፡ ስለዚህ  መምረጥ  ክፉ  ቢሆን  ለቅጣት  መልካም  ቢሆን  ደግሞ  የመልካምነት  ዋጋ  ለመቀበል  የተዘጋጀ  እንዲሆን  እድል  ሰጠው፡፡

  በሕዝብ  ዘንድ  ክብርና  ገንዘብ  ለማግኝት  የሚፈልግ  ዋሾ  ሰው  ነው፡፡  ዋሾ  ሰው  ይህን  በሐሰተኛ  መንገድ  ሲያገኝ  እዉነት አስመስሎ ሀሰት  ይናገራል፡፡ ሊመረምሩ  የማይፈልጉ  ሰዎች  እውነት  ይመስላቸውና  በእርሱ  በጽኑ  ሃይማኖት  ያምናሉ፡፡ እስኪ  ሕዝባችን  በስንት  ውሸት  ያምናል?  በጽኑ  ሃይማኖት  ያምናል፡፡  በሃሳበ  ከዋክብትና  በሌላም  አስማት፣  አጋንንት  በመሳብና በመርጨት፣ አስማት በማድረግ፣ በጥንቆላ  ሁሉ  ያምናሉ፡፡ ይህንን  ሁሉ  መርምረው  እውነቱን  አግኝተው  አያምኑም፡፡ ነገር  ግን  ከአባቶቻቸው  ሰምተው ያምናሉ፡፡ እነዚያስ  የፊተኞቹ  ገንዘብና  ክብር ለማግኝት  ካልሆነ በቀር ስለምን  ዋሹ?  እንዲሁ  ህዝብን  ሊገዙ  የሚፈልጉ  ሁሉ  እውነት  እንነግራቸኋለን  እግዚአብሔር  ወደናንተ  ላከን  ይሏቸዋል፡፡  ሕዝቡም  ያምናሉ፡፡
ከነርሱም  በኋላ  የመጡት  እነርሱ  ሳይመረምሩ  የተቀበሏትን  የአባቶቻቸውን  እምነት  አልመረመሩም፡፡  ከዚያ  ይልቅ  ለእውነትና ለሃይማኖታቸው  ማስረጃ  ታሪክን፣ ምልክቶችን ፣ ተዓምራትን  እየጨመሩ እውነት  አስመስለው  አጸኑት፡፡  በነገሩ ሁሉ እግዚአብሔርን  ስም ጨመሩ።  እግዚአብሔርንም የሐሰኞች ተካፋይና  የሐሰት  ምስክር  አደረጉት፡፡

  ጥልቅ   ምርመራ  ስለ  ሙሴና  መሐመድ  ሕግጋት

 ለሚመረምር  ግን  እውነት  ቶሎ  ይገለፃል፡፡  ፈጣሪ  በሰው  ልብ  ያስገባውን  ንጹህ  ልቦና  የፍጥረት  ሕግጋትና  ስርዓትን  ተመልክቶ የሚመረምር  እርሱ  እውነትን  ያገኛል፡፡ ሙሴ  ፈቃዱንና  ሕጉን  ልነግራችሁ  ከእግዚአብሔር  ዘንድ  ተልኬ  መጣሁ  ይላል፡፡ ከሆነ ታዲያ «ሴት በወር አበባ ወቅት የረከሰች ናት» ለምን ይላል? የሙሴ  መጽሐፍ  ከፍጥረት  ሕግ  ሥርዓትና  ከፈጣሪ  ጥበብ  ጋር  አይስማማም፡፡  ከውስጡ  የተሳሳተ  ጥበብ  ይገኛል፡፡ ለሚመረምር  ግን  እውነት  አይመስለውም፡፡  በፈጣሪ  ፈቃድና  በፍጥረት  ህግ  የሰው  ልጅ  እንዳይጠፋ  ልጆችን  ለመውለድ  ወንድና  ሴት  በፍትወተ  ሥጋ  እንዲገናኙ  ታዟል፡፡  ይህም  ግንኙነት  እግዚአብሔር  ለሰው  በሕገ  ተፈጥሮ  የሰጠው  ነው፡፡ እግዚአብሔርም  የእጁን  ሥራ  አያረክስም፡፡ እግዚአብሔር  ዘንድ  እርኩሰት  ሊገኝ  አይችልም፡፡  ፈጣሪ የፈጠረውን መልሶ አያረክሰውም እላለሁ። 

  እንደገናም  የክርስቲያን  ሕግ  ለማስረጃዋ  ተአምራቶች ተገኝተዋልና  ከእግዚአብሔር  ናት  ይላሉ፡፡  ነገር  ግን  የወሲብ  ሥርዓት  የተፈጥሮ  ሥርዓት  እንደሆነ  ምንኩስና  ግን  ልጆች ከመውለድ  ከልክሎ  የሰውን  ፍጥረት  አጥፍቶ  የፈጣሪን  ጥበብ  የሚያጠፋ  እነደሆነ  ልቦናችን  ይነግረናልና  ያስረዳናል፡፡ የክርስቲያን  ሕግ  ምንኩስና  ከወሲብ  ይበልጣል  ብትል  ሐሰት  ትናገራለችና  ከእግዚአብሔር  አይደለችም፡፡  የፈጣሪን  ሕግ  የሚያፈርስ  እንዴት  ከጥበብ በለጠ ?  ወይስ  የእግዚአብሔርን  ስራ  የሰው  ምስክር ሊያስተካክለው ይቻለዋልን ? ሰዎች ግን ሳይመረምሩ ምንኩስና ከጋብቻ ትበልጣለች ይላሉ። ዘርን የሰጠ ፈጣሪ ዘር አያስፈልግም አይልም። ቀጣፊዎች በእግዚአብሔር ስም  እውነት አስመሰሉት እንጂ።

እንዲሁም  መሐመድ  የማዛችሁ  ከእግዚአብሔር  የተቀበልኩትን  ነው  ይላል፡፡  መሐመድን  መቀበል  የሚያስረዱ  የተዓምራት  ፀሐፊዎች  አልጠፉምና  ከሱም  አመኑ፡፡ እኛ  ግን  የመሐመድ  ትምህርት  ከእግዚአብሔር  ሊሆን  እንደማይችል  እናውቃለን፡፡ የሚወለዱ  ሰዎች  ወንድና  ሴት  ቁጥራቸው  ትክክል  ነው፡፡ በአንድ  ሰፊ  ቦታ  የሚኖሩ  ወንድ  ሴት ብንቆጥር  ለእያንዳንዱ  ወንድ አንዲት  ሴት  ትገኛለች  እንጂ  ለአንድ  ወንድ  ስምንት  ወይም  ዐሥር  ሴቶች  አይገኙም፡፡ የተፈጥሮ  ህግም  አንዱ  ከአንዲት  ጋር እንዲጋቡ  አዟል፡፡ አንድ  ወንድ  ዐሥር  ሴት  ቢያገባ  ግን  ዘጠኝ  ወንዶች  ሴት  የሌላቸው  ይቀራሉ፡፡ ይህም  የፈጣሪን  ስርዓትና  ሕገ ተፈጥሮን  የጋብቻንም  ጥቅም  ያጠፋል፡፡ አንድ  ወንድ ብዙ ሴቶች ሊያገባ  ይገባዋል  ብሎ  በእግዚአብሔር  ስም  ያስተማረ  መሐመድ  ግን  ትክክል  ነው አልልም፡፡ ከእግዚአብሔር  ዘንድ  አልተላከም፡፡  ጥቂት  ስለጋብቻ  ሕግ  መረመርኩ  ፡፡ ከመጀመሪያም  ለአዳም አንድ ሴት ከመፍጠር ይልቅ ዐሥር ሴት ያልፈጠረለት ለምንድነው? ይህን የፈጣሪ ሕግ  ሳይመረምሩ የመሐመድን  ሕግ መቀበል ስህተት ነው። ከእግዚአብሔር እንደተገኘ  ብመረምርም  በህገ  ኦሪትና  በክርስትናና  በእስልምና  ሕግ  ፈጣሪ  በልቦናችን  ከሚገልጽልን  እውነት  እና  እምነት ጋር የማይስማማ ብዙ ነገር አለ  አልኩ።

    ፈጣሪ  ለሰው  ልጅ  ክፉና  መልካም  የሚለይበት  ልቦና  ሰጥቶታል፡፡  «በብርሃንህ  ብርሃንን  እናያለን»  እንደተባለውም  የሚገባውን  የማይገባውን  ሊያውቅ፣  እውነትን  ከሐሰት እንዲለይ ነው፡፡ ስለዚህ የልቦናችን  ብርሃን  እንደሚገባ  በእርሱ  ብናይበት  ሊታይልን አይችልም፡፡ ፈጣሪያችን ይሄን ብርሃን  የሰጠን  በርሱ  እንድንድን  ነው እንጂ  እንድንጠፋ  አይደለም። የልቦናችን  ብርሃን  የሚያሳየን  ሁሉም  ከእውነት  ምንጭ  ነው፡፡ ሰዎች  ከሐሰት  ምንጭ  ነው  ቢሉን ግን  ሁሉን  የሰራ  ፈጣሪ  ቅን እንደሆነ  ልቦናችን  ያስረዳናል፡፡ ፈጣሪ  በመልካም ጥበቡ  ከሴት  ልጅ  ማህጸን  በየወሩ  ደም  እንዲፈስ አዟል፡፡  ሙሴና  ክርስቲያኖች  ግን  ይህን የፈጣሪ  ጥበብ  እርኩስ  አደረጉት፡፡
እንደገና  ሙሴ  እንዲህ  ያለችው  ሴት ከተቀመጠችበት የተቀመጠውንም፤ የተገናኛትንም  ያረክሳል፡፡  ይህም  የሙሴ  ህግ  የሴትን  ኑሮ  በሙሉና  ጋብቻዋን  ከባድ አድርጎታል፡፡ የመራባትንም  ህግ  አጥፍቷል፡፡ ልጆችንም  ከማሳደግ  ከልክሎ  ፍቅርንም  ያፈርሳል፡፡ ስለዚህ ይህ  የሙሴ  ሕግ  ሴትን  ከፈጠረ  ሊሆን  አይችልም  እላለሁ፡፡ «ሞተውን ሰው በድን የነካ ሁለመናውን ባያጠራ የእግዚአብሔርን ማደሪያ ያረክሳል ያ ሰው ከእስራኤል ዘንድ ተለይቶ ይጠፋል » የምትለው የሙሴ ሕግ ሞትን ከፈጠረ ከእግዚአብሔር አይደለችም። እንደገናም  የሞቱትን  ወንድሞቻችንን  ልንቀብራቸው  ተገቢ መሆኑን ልቦናችን  ይነግረናል፡፡ በድኖቻቸውም  በሙሴ  ጥበብ  ካልሆነ  በስተቀር  ከመሬት  የተፈጠርንበት  ወደ መሬትም  ልንገባበት  በፈጣሪያችን  ጥበብ  እርኩሳን  አይደሉም፡፡ ነገር  ግን  ለፍጥረት  ሁሉ  እንደሚገባ  በትልቅ  ጥበብ  የሰራ  እግዚአብሔር ሥርዓቱን  አያረክሳውም፡፡ ሰው  ግን  የሐሰትን  ቃል  እንዲያከብር  ብሎ  ሊያረክሰው ይፈልጋል፡፡

  እንደዚሁም  እግዚአብሔር  የከንቱ  ነገር  አያዝም፡፡  «ጥረህ ግረህ በላብህ ወዝ ብላ» ያለው አምላክ ይህን  ብላ፣ ይህን  አትብላ፣ ዛሬ ብላ፣ ነገ  አትብላ  አይልም፡፡ ለክርስቲያኖች  እንደሚመስላቸውና  የጾም  ሕግጋት  እንደሚጠብቁ  ሥጋን  ዛሬ  ብላ፤  ነገ  አትብላ  አይልም፡፡  ለክርስቲያኖች እንደሚመስላቸውና  የጾም  ሕግጋት  እንደሚጠብቁ  ሥጋን  ዛሬ ብላ ነገ ግን  አትብላ  አይልም፡፡  እስላሞችንም  እግዚአብሔር  ለሊት  ብሉ  ቀን  አትብሉ  ብሎ  ይሄንና  የመሳሰሉትን  አይላቸውም፡፡ የፍጥረታችንን  ጤና  የማያውክ ነገር ሁሉ  ልንበላ  እንደሰለጠንን  ልቦናችን  ያስተምረናል።  አንድ  የመብል ቀን፤ አንድ  የጾም  ቀን ግን  ጤናን  ያውካል፡፡ የጾም ህግ መብላትን  ለሰው  ሕይወት  ከፈጠረና  ልንበላቸው  ከፈቀደ  ፈጣሪ የወጣ  አይደለም፡፡ በልተን ልናመሰግነው  እንጂ  በረከቱን  ልናርም አይገባንም፡፡ ሕገ  ፆም  የሥጋን  ፍትወት ለመግደል  የተሰራ  ነው  የሚሉም  ቢኖሩ  ፍትወተ  ሥጋ  ወንድ  ወደ ሴት  ሊሳብ  ሴትም ወደ  ወንድ  ልትሳብ  የፈጣሪ ጥበብ  ነውና  እርሱ  ፈጣሪ  በሰራው  በታወቀ  ማጥፋት  አይገባም  እላለሁ፡፡  ፈጣሪያችን  ይህን ፍትወት ለሰው፤  ለእንስሳት  ሁሉ  በከንቱ  አልሰጠም፡፡ ነገር ግን  ለዚህ  ዓለም  ሕይወትና  ለፍጥረት  የተሰራለት  መንገድ  ሁሉ  መሠረቱ  ሆኖ እንዲቆይ  ይህ  ፍትወት  ለሰው  ልጅ  ተሰጠ፡፡ አስፈላጊያችንን ልንበላ  ይገባናል፡፡ በእሁድ  ቀንና  በበዓል  ቀናት  በአስፈላጊው  ልክ  የበላ  እንዳልበደለ  እንዲሁ  በአርብ  ቀንና  ከፋሲካ  በፊት  ባሉት  ቀናት  ለክቶ  የሚበላ  አልበደለም፡፡  እግዚአብሔር  ሰውን  በሁሉ  ቀንና  በሁሉ  ወራት  ካስፈላጊ  ምግብ  ጋር  አስተካክሎ  ፈጥሮታል፡፡  አይሁድ፣  ክርስቲያንና  እስላም  ግን  የፆምን  ሕግ  ባወጡ  ጊዜ ይህን  የእግዚአብሔር  ሥራ  ልብ  አላሉም፡፡ እግዚአብሔር  ፆምን  ሰራልን፤  እንዳንበላም  ከለከለን  እያሉ ይዋሻሉ፡፡ እግዚአብሔር ፈጣሪያችን  ነው፡፡ ግን  የምንበላውን  ምግባችንን   እንድንመገበው ሰጠን  እንጂ  እርሱን  ልናርም  አይደለም፡፡  በሚያስተውል ልቡናችን  ለክተን  መኖር የኛ ፈንታ ነው።

 ስለ  ሃይማኖቶች    መለያየት

 ሌላ ትልቅ  ምርመራ  አለ፡፡ ሰዎች  ሁሉ  በእግዚአብሔር  ዘንድ  ትክክል  ናቸው፡፡ እርሱም  አንድ  ሕዝብ ለሕይወት፤  አንድ  ሕዝብ ለሞት፤  አንድም  ለምህረት፤  አንድም  ለኩነኔ  አልፈጠረም፡፡  ይህም  አድሎ  በስራው  ሁሉ  ጻድቅ  በሆነ  በእግዚአብሔር  ዘንድ እንደማይገኝ  ልቦናችን  ያስተምረናል፡፡ ሙሴ  ግን  አይሁድን  ለብቻቸው  እንዲያስተምራቸው  ተላከ፡፡ ለሌሎች  ሕዝቦች  ፍርዱ አልተነገረም፡፡  እግዚአብሔር  ስለምን  ለአንድ  ሕዝብ  ፍርድ  ሲነግር  ለሌላው  አልነገረም፡፡  በዚህም  ጊዜ  ክርስቲያኖች  የእግዚአብሔር  ትምህርት  ከኛ  ጋር  ካልሆነ  በስተቀር  አይገኝም  ይላሉ፡፡ አይሁድና  እስላም  የህንድ  ሰዎችም  ሌሎችም  ሁሉ እንደነሱ  ይላሉ፡፡ እንዲሁ  ደግሞ  ክርስቲያኖች  እርስ  በርሳቸው  አይስማሙም፡፡ ካቶሊኮች  እግዚአብሔር  ከኛ  ጋር  ነው  ያለው እንጂ ከናንተ  ጋር አይደለም  ይሉናል፡፡ እኛም  እንዲሁ  እንላቸዋለን፡፡ ሰዎች  እንደምንሰማቸው  ግን  የእግዚአብሔር  ትምህርት  እጅግ  ጥቂቶች  ወደ ሆኑት  እንጂ  ለብዙዎቹ  አልደረሰም፡፡  ከእነዚህ  ሁሉ  ደግሞ  ወደ  ማን  እንደደረሰ  አናውቅም፡፡ እግዚአብሔር  ከፈቀደ ቃሉን  በሰው  ዘንድ  ማጽናት ተስኖት  ነውን?  ሆኖም  ግን  የእግዚአብሔር  ጥበብ  በመልካም  ምክር  ይህ  ነገር  እውነት እንዳይመስላቸው  ሰዎች  በሐሰት  ሊስማሙ  አልተወም፡፡ ሰዎች  ሁሉ  በአንድ  ነገር  በተስማሙ  ጊዜ  ይህ  ነገር እውነት ይመስላል፡፡ ሰዎች  ሁሉ  በሃይማኖታቸው  ምንም  እንደማይስማሙ  በሃሳብም  ሊስማሙ  አይችሉም፡፡
    እስኪ  እናስብ  ሰዎች  ሁሉ  ሁሉን  የፈጠረ  እግዚአብሔር  አለ  በማለታቸው  ስለምን  ይስማማሉ?  ፍጡር  ያለ  ፈጣሪ  ሊገኝ  እንደማይችል፤ ስለዚህም  ፈጣሪ  እንዳለ እውነት  ነውና  ነው፡፡ ይህ  የምናየው  ሁሉ  ፍጡር  እንደሆነ  የሰው  ሁሉ   ልቦና  ያውቃል ፡፡ ሰዎች ሁሉ በዚህ  ይስማማሉ፡፡  ነገር  ግን  ሰዎች  ያስተማሩትን  ሃይማኖት  በመረመርን  ጊዜ  በውስጡ  ሐሰት  ከእውነት  ጋር  ተቀላቅሎበታል፡፡  ስለዚህ  እርስ  በርሱ አይስማማም፡፡ ሰዎች  እርስ በርሳቸው  አንዱ  ይህ  እውነት  ነው ሲል፤ ሁለተኛው  አይደለም፤  ሐሰት  ነው  ሲል  ይጣላሉ፡፡ ሁሉም  የእግዚአብሔርን  ቃል  የሰው  ቃል  እያደረጉ  ይዋሻሉ፡፡  እንደገናም  የሰው  ሃይማኖት  ከእግዚአብሔር  ብትሆን  ክፉዎችን   ክፉ  እንዲያደርጉ  እያስፈራራች  መልካም  እንዳያደርጉ ትፈቅድላቸው  ነበር፡፡ ደጎችንም በትዕግስታቸው ታጸናቸው ነበር፡፡

  ለኔም እንዲህ ያለው  ሃይማኖት  ባሏ  ሳያውቅ  በምንዝርና  የወለደች ሴትን ትመስለኛለች፡፡ ባሏ ግን  ስለመሰለው  በሕፃኑ  ይደሰታል፡፡ እናቲቱንም ይወዳታል፡፡ በዝሙት  እንደወለደችው  ባወቀ  ጊዜ  ግን  ያዝናል፡፡ ሚስቱንም  ልጅዋንም  ያባርራል፡፡ እንዲሁም  እኔም  ሀይማኖቴን አመንዝራና  ዋሾ  መሆኑዋን  ካወኩ  በኋላ  ስለርሷ  በዝሙት  ስለተወለዱ   ልጆቿ አዘንኩ ፡፡ እነሱ  በጠብ፣ በማሳደድ፣ በመማታት፣ በማሰር፣ በመግደል  ወደዚህ  ዋሻ  ያባረሩኝ  ናቸው፡፡  ከውሸታቸው ጋር ስላልተባበርኩ ጠሉኝ። ነገር  ግን  የክርስቲያን  ሃይማኖት  ሀሰት  ናት እንዳልል  በዘመነ  ወንጌል  እንደተሰራ  ክፉ  አልሆነችም፡፡  የምህረትን  ሥራ  በሙሉ  እርስ   በርስ መፋቀርን ታዛለች፡፡  እነሱ ግን ፍቅርን ፈጽሞ አያውቋትም። በዚህ ዘመን  ግን  የሀገራችን  ሰዎች  የወንጌልን  ፍቅር  ወደ ጠብና  ኃይል  ወደ  ምድራዊ  መርዝ  ለወጡት፡፡  ሃይማኖታቸውን  ከመሰረቱ  ዐመጻ  እየሰሩ  ከንቱ  ያስተምራሉ፡፡  በሐሰትም  ክርስቲያኖች ይባላሉ፡፡

Wednesday, July 30, 2014

ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብ

 ዘርዓ ያዕቆብ ፈላስፋ (ክፍል አንድ)

እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሁሉ ለነፍስ ያደረጋችሁትን መናገር እጀምራለሁና ኑ ስሙኝ፡ ሁሉን በፈጠረ መጀመሪያና መጨረሻ በሆነ ሁሉን በያዘና የሕይወትና የጥበብ ሁሉ ምንጭ በሆነ እግዚአብሔር በሰጠኝ ረዥም እድሜየ ትንሽ እጽፋለሁ፡፡ ነፍሴ በእግዚአብሔር ዘንድ የተከበረች ትሁን ጆሮዎችም ሰምተው ይደሰቱ፡፡ እኔ እግዚአብሔርን ፈለኩት መለሰልኝ፡፡ አሁንም እናንተ ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፤ ፊታችሁንም አያሳፍርም፡፡ እግዚአብሔርን ከኔ ጋር ከፍ ከፍ አድርጉት አብረን ስሙን እናንሳ፡፡

  እኔ የተወለድኩት በአክሱም በካህናት ሀገር ነው፡፡ ነገር ግን እኔ በአክሱም አውራጃ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት በ1592 ዓ/ም ከ አንድ ገበሬ ቤተሰብ ተወለድሁ፡፡ በክርስትና ጥምቀት ዘርዓ ያዕቆብ ተብየ ተሰየምኩ፡፡ ሰዎች ግን ወርቄ ይሉኛል፡፡ ካደኩ በኋላ ትምህርት እንድማር አባቴ ወደ ትምህርት ቤት ላከኝ፡፡ ዳዊትም ከደገምኩ በኋላ መምህሬ አባቴን ይህ ህፃን ልጅህ ልቦናው የበራ በትምህርት ታጋሽ ነውና ወደ ትምህርት ቤት ብትልከው ሊቅና መምህር ይሆናል አለው፡፡ አባቴም ይህን ሰምቶ ዜማ እንድማር ላከኝ፡፡ ሆኖም ድምጼ ሸካራ ሆኖ አላምር አለኝ፡፡ በዚህ ምክንያት ጓደኞቼ መሳቂያና መዘባበቻ አደረጉኝ፡፡ እዚያም ሦስት ወር ያህል ቆየሁ፡፡ ስላልተሳካልኝ ከልቤ አዘንኩ፡፡ ተነስቼ ሰዋስውና ቅኔ ለመማር ወደ ሌላ አስተማሪ ሄድኩ፡፡ ከጓደኞቼ ፈጥኜ እንድማርም እግዚአብሔር ጥበቡን ሰጠኝ፡፡ ይህም የመጀመሪያ ሃዘኔን አስረሳኝ ፡፡ በጣም ተደሰትኩ፡፡ እዛም አራት አመት ቆየሁ፡፡ በነዚያ ቀኖች እግዚአብሔር ከሞት አዳነኝ፡፡ ከጓደኞቼ ጋር ስጫወት ወደገደል ወደቅሁ፡፡ እግዚአብሔር በታምራቱ አዳነኝ እንጅ ፈጽሞ ልድን አልችልም ነበር፡፡ ከዳንኩ በኋላ ገደሉን በረዥም ገመድ ለካሁት፡፡ ዐሥራ ሦስት ሜትር ሆኖ ተገኝ፡፡ እኔም ድኜ ያዳነኝን እግዚአብሔርን እያመሰገንኩ ወደ መምህሬ ቤት ሄድኩ፡፡ ከዚያም ተነስቼ የቅዱሳት መጻሕፍትን ትርጓሜ ለመማር ሄድኩ፡፡

 በዚያም ዐሥር ዓመት ቆየሁ፡፡ መጻሕፍትን ፈረንጆች እንዴት እንደሚተረጉሟቸው፤ የኛም ምሁራን እንዴት እንደሚተረጉሟቸው ተማረኩ፡፡ ትርጓሜያቸው ግን ከኔ ልቡና ጋር የሚስማማ አልነበረም፡፡ ሆኖም ይህን ስሜቴን፤ ሃሳቤን ለማንም ሳልገልጽ በልቤ ይዠው ቆየሁ፡፡ ከዚያም ወደሃገሬ ወደ አክሱም ተመለስኩ፡፡ በአክሱም ለአራት አመት መጽሐፍ አስተማረኩ፡፡
ይህ ዘመን ክፉ ዘመን ሆነ፡፡ አፄ ሱስንዮስ በነገሠ በ 19ኛው ዓመት የፈረንጆች ተወላጅ አቡነ አልፎንዝ መጣ፡፡ ከ2 ዓመት በኋላም ንጉሡ የፈረንጆቹን ሃይማኖት ስለተቀበለ በኢትዮጵያ ትልቅ ስደት ሆነ፡፡ ይህን ሃይማኖት ያልተቀበለ በሙሉ ግን እጣው ስደት ሆነ፡፡

 አፄ ሱስንዮስ፣ አልፎንዝና ጠላቴ ወልደ ዮሐንስ

እኔ በሃገሬ መጻሕፍት ሳስተምር ብዙዎቹ ጓደኞቼ ጠሉኝ፡፡ በዚህ ዘመን የባልንጀራ ፍቅር ጠፍቶ ነበርና ቅናት ያዛቸው፡፡ በትምህርትና ጓደኛን በመውደድ ከነርሱ እበልጣለሁ፡፡ ከሁሉ ሰው፤ ከፈረንጆቹና ከግብጻውያን ጋር እስማማለሁ፡፡
መጻሕፍትን ሳስተምርና ስተረጉም እንዲህ እንዲህ ይላሉ፤ ግብጻዊያኖች ደግሞ (ኦርቶዶክሶች) እንዲህ እንዲህ ይላሉ እላለሁ፡፡ እኛም ብንመረምር ይህን ሁሉ እናውቃለን እላለሁ እንጅ ይህ መልካም ነው፤ ይህ ደግሞ ክፉ ነው አልልም፡፡ ግብጾቹ የፈረንጅ፣ ፈረንጆቹ ደግሞ የግብጻውያኖቹ እመስላቸዋለሁ፡፡ ስለዚህ ሁሉም ጠሉኝ፡፡ ብዙ ጊዜም ወደንጉሡ ከሰሱኝ፡፡ እግዚአብሔር ግን አዳነኝ፡፡ ከዚህም በኋላ ከአክሱም ካህናት አንድ ወልደ ዮሐንስ የተባለ ጠላቴ፤ የንጉሥ ወዳጅ ስለነበረ፣ የነገሥታት ፍቅር በሽንገላ ምላስ ስለሚያገኝ ወደ ንጉሡ ሄደ፡፡ ወደ ንጉሡም ገብቶ እንደዚህ አለው ፡፡
“ይህ ሰው ህዝብን ያሳስታል፡፡ ስለሃይማኖታችን እንነሳና ንጉሡን እንግደለው፣ ፈረንጆቹንም እናባራቸው ይላል” እያለ ይሄንና ይሄን በመሰለ ውሸት ከሰሰኝ፡፡ እኔም ይህን አውቄ ገና ለገና ይገድለኛል ብዬ ፈርቼ የነበረኝን ሶስት ወቄት ወርቅና የምጸልይበትን መዝሙረ ዳዊት ይዠ በሌሊት ሸሸሁ፡፡ ወዴት እንደምሄድ ለማንም አልተናገርኩም፡፡ ወደተከዜ በረሀ ገባሁ፡፡ በነጋታውም ራበኝ፡፡

  ከሀብታሞች ገበሬዎች እንጀራ ለመለመን እየፈራሁ ወጣሁ፡፡ ሰጡኝና በልቼ እየሮጥኩ ሄድኩ፡፡ እንዲህ እያልኩ ብዙ ቀን ቆየሁ፣ በኋላ ወደ ሽዋ ግድም ስሄድ ሰው የሌለበት በርሃ አገኘሁ፡፡ ከገደሉ በታች መልካም ዋሻ ነበርና ሰው ሳያየኝ በዚህ ዋሻ እኖራለሁ ብየ ወሰንኩ፡፡ ሱስንዮስ እስኪሞትም ድረስ በዚያ 2 ዓመት ቆየሁ፡፡ አንዳንዴ ወደገበያ እየወጣሁ ወይም ወደ አምሐራ ሀገር እሄድ ነበር፡፡ ለአምሐራ ሰዎች የምበላው እንዲሰጡኝ የምለምን ባህታዊ መነኩሴ እመስላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ሰዎች ከየት እንደምወጣና ወዴት እንደምገባ አያውቁም፡፡ ከዋሻየ ለብቻየ በሆንኩ ጊዜም በመንግሥተ ሰማያት የምኖር መሰለኝ፡፡ ቁጥር የሌለው ክፋታቸውን አውቄ ከሰዎች ጋር መኖር ጠላሁ፡፡ ሌሊት መጥተው የበርሃ አራዊት እንዳይበሉኝም በድንጋይና በአሽዋ አጥር ዋሻየን አጠርኩ፡፡
እሚፈልጉኝ ሰዎች ወደኔ ቢመጡ የማመልጥበት መውጫም አዘጋጀሁ፡፡ እዚያ በሰላም ኖርኩ፡፡ በሚሰማኝ በእግዚአብሔር ተስፋ አድርጌ በሙሉ ልቤ በመዝሙረ ዳዊት ጸለይኩ፡፡

ስለአምላክ መኖርና የሐይማኖት መለያየት

ከጸሎት በኋላም ስራ ስለሌለኝ ሁልጊዜ ስለሰዎች ክፋትና ሰዎች በእርሱ ስም ሲበድሉ፣ ወንድሞቻቸውን ጓደኞቻቸውን ሲያባርሩ እና ሲገድሉ ዝም በማለቱ ስለፈጣሪ ጥበብ አስብ ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ ፈረንጆቹ አየሉ፡፡ ነገር ግን ያገሩ ሰዎችም ከነሱ የባሰ ክፋት ሰሩ እንጅ ፈረንጆቹ ብቻቸውን አልነበረም የከፉት፡፡ የካቶሊክ ሃይማኖት የተቀበሉት፤ ኦርቶዶክሶች የመንበረ ጴጥሮስን እውነተኛዋን ሃይማኖት ክደዋልና የእግዚአብሔር ጠላቶች ናቸው አሉ፡፡ ስለዚህም አሳደዱአቸው፡፡
ኦርቶዶክሶችም ለሃይማኖታቸው እንዲሁ አደረጉ፡፡ እግዚአብሔር የሰዎች ጠባቂ ከሆነ ለምን ፍጥረታቸው እንዲህ ከፋ ብየ አሰብኩ፡፡ በአርያም የሚያውቅ አለን ? ኧረ እግዚአብሔርስ ያውቃልን ? በቅዱስ ስሙ ሲበድሉና ሲረክሱ የሚያውቅ ከሆነ እንዴት የሰዎችን ክፋት ዝም ይላል? አልኩ፡፡
ምንም ልብ አላደረኩም ብዙ አሰብኩ፡፡ የፈጠርከኝ ፈጣሪየ ሆይ አዋቂ አድርገኝ፤ የተደበቀውን ጥበብህን ንገረኝ ብየ ጸለይኩ፡፡ ለሞት እንዳይተኙ አይኖችህን አብራቸው፤ እጆችህ አደረጉኝና ሰሩኝ፡፡ ትዕዛዝህን እንድማር ልብ ስጠኝ፡፡ ለኔ ግን እግሮቼ በተፍገመገሙ፤ ተረከዞቼም በተንሸራተቱ ነበር ፡፡ ይህም በፊቴ ስላለው ድካም ነው፡፡ ይህንን እና ይህን የመሰለ ፀሎት አደርግ ነበር፡፡
 አንድ ቀን እኔ ወደ ማን ነው የምፀልየው? አልኩ፡፡ በእውነት የሚሰማኝ እግዚአብሔር አለን? በዚህም አሳብ በጣም አዝኜ እንዲህ አልኩ፡፡ዳዊት እንዳለ እንዴት ምንኛ ልቤን አጸደኳት፡፡ ኋላም አሰብኩ።ይህ ዳዊት እንዲህ የሚለው «ጆሮን የተከለ አይሰማምን ?»  በእውነት እንድሰማበት ጆሮ የሰጠኝ ማነው? አዋቂስ አድርጎ የፈጠረኝ ማነው? በዚህስ ዓለም እኔ እንደምን መጣሁ? ከዓለም በፊት ብኖር የሕይወቴ መጀመሪያና የእውቀቴ መጀመሪያን ባወቅሁ፡፡ እኔ በገዛ እጄ ተፈጠርኩን ? ነገር ግን እኔ በተፈጠርኩ ጊዜ አልኖርኩም፡፡ አባት እናቴ ፈጠሩኝ ብልም እንደገና ወላጆችና የወላጆችን ወላጅ፣ወላጅ የሌላቸው በሌላ መንገድ ወደዚህ ዓለም የመጡትን እንደኛ ያልተወለዱትን የፊተኞቹ ድረስ ፈጣሪያቸውን እፈልጋለሁ፡፡ እነርሱም ቢወለዱ የፈጠራቸው አንድ ህላዌ አለ ከማለት በቀር የጥንት መወለጃቸውን አላውቅም፡፡ ያለና በሁሉም የሚኖር የሁሉ ጌታ ሁሉን የያዘ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው ዓመቱ እማይቆጠር እማይለወጥ ያልተፈጠረ ፈጣሪ አለ አልኩ፡፡ ፈጣሪስ አለ፡፡ ፈጣሪ ባይኖር ፍጥረት ባልተገኘ አልኩ፡፡ እኛ ብንኖር ፍጡራን እንጅ ፈጣሪዎች አይደለንም፡፡ የፈጠረ ፈጣሪ አለ እንል ዘንድ ይገባናል፡፡ ይህም የፈጠረን ፈጣሪ አዋቂና ተናጋሪ ካልሆነ በቀር ከዕውቀቱ በተረፈ አዋቆዎችና ተናጋሪዎች አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ ሁሉን ፈጥሯል ሁሉን ይይዛልና እርሱ ሁሉን ያውቃል፡፡ ፈጣሪየ ወደ እርሱ ስጸልይ ይሰማኛል ብየ ሳስብ ትልቅ ደስታ ተደሰትኩ፡፡ በትልቅ ተስፋም እየጸለይኩ ፈጣሪየን በሙሉ ልቤ ወደድኩት፡፡ ጌታየ ሆይ፤ አንተ ሃሳቤን ሁሉ ከሩቅ ታውቃለህ አልኩት፡፡ አንተ የመጀመሪያየ ነህ፡፡ የመጨረሻየን ሁሉን አወቅህ፡፡ መንገዴንም ሁሉ አንተ አስቀድመህ አወቅህ፡፡ ስለዚህም ከሩቅ ታውቃለህ ይሉሃል፡፡ እኔ ሳልፈጠር ሀሳቤን ያውቃልና ፈጣሪየ ሆይ እውቀትን ስጠኝ አልኩ፡፡

ስለ ሃይማኖት ምርመራና ፀሎት

በኋላም ይህ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ እውነት ይሆን? ብየ አሰብኩ፡፡ በጣም አላወቅሁምና የተማሩና ተመራማሪ ሰዎች እውነቱን እንዲነግሩኝ ሄጄ ልጠይቃቸው ብዬ ብዙ አሰብኩ፣ እንደገናም ሰዎች በየልባቸው ያለውን ካልሆነ በቀር ሌላ ምን ይመልሱልኛል ብየ አሰብኩ፡፡ ሰው ሁሉ የኔ ሃይማኖት እውነተኛ ናት ይላል፡፡ በሌላ ሃይማኖት የሚያምኑ ሐሰተኞች
የእግዚአብሔር ጠላቶች ናቸው፡፡ ዛሬም ቢሆን ፈረንጆች ሃይማኖታችን መልካም ናት፣ ሃይማኖታችሁ ግን መጥፎ ናት ይሉናል፡፡ እኛም መልሰን እንዲዚህ አይደለም፤ የናንተ ሃይማኖት መጥፎ፤ የኛ ሃይማኖት ግን መልካም ናት እንላቸዋለን፡፡
እንደገናም የእስልምና፣ የአይሁድ አማኞችን ብንጠይቃቸው እንዲሁ ይሉናል፡፡ በዚህም ክርክር ፈራጅ ማን ይሆናል? ሰዎች ሁሉ እርስ በእርሳቸው ወቃሾችና ተወቃሾች ሆነዋል፡፡ አንድ እንኳን ከሰው ልጅ የሚፈርድ አይገኝም፡፡ እኔ መጀመሪያ ስለብዙ ሃይማኖቶች ጉዳይ አንድ የፈረንጅ መምህር ጠየኩ፡፡ እሱ ግን ሁሉን እንደራሱ ሃይማኖት አድርጎ ፈታው፡፡ ኋላም አንድ ትልቅ የኢትዮጵያ መምህር ጠየቅሁ ፡፡ እርሱም ሁሉን እንደ ሃይማኖቱ አድርጎ ተረጎመው፡፡ እስልምና እና አይሁድንም ብንጠይቅ እንዲሁ እንደ ሃይማኖታቸው ይተረጉማሉ፡፡ ታዲያ እውነት የሚፈርድ የት አገኛለሁ? የኔ ሃይማኖት ለኔ ትክክል እንደሚመስለኝ እንዲሁ ለሌላውም ሃይማኖቱ እውነት ይመስለዋል፡፡ ነገር ግን ጽድቅ አንዲት ብቻ ናት፡፡

 እንደዚህ እያልኩ አሰብኩ፡፡ ጠቢብና የእውነተኞችም እውነተኛ እኔን የፈጠርክ ሆይ አዋቂ አድርገህ የፈጠርከኝ ሆይ፤ ዳዊት ሰው ሁሉ ዋሾ ነው ካለው በስተቀር በሰው ዘንድ ጥበብና እውነት አይገኝምና አንተ አዋቂ አድርገኝ ብዬ ጸለይኩ፡፡ ሰዎች በዚህ ትልቅ ነገር ነፍሳቸውን ለማጥፋት ስለምን ይዋሻሉ? ብየ አሰብኩ፡፡ የሚዋሹም መሰለኝ፡፡ የሚያወቁ እየመሰላቸው ምንም አያውቁምና የሚያውቁ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ እውነትን ለማግኝት ብለው አይመረምሩም፡፡ ዳዊት እንዳለው ልባችን እንደወተት ረካ፡፡ ከአባቶቻቸው በሰሙት ልባቸው ረክቷል፡፡ እውነት ወይም ሀሰት ሊሆን ይችላል ብለው አልመረመሩም፡፡ እኔም ጌታ ሆይ ፍርድህን እንዳውቅ ያሳመንከኝ ይገባኛል አልኩ፡፡
አንተ በእውነት ቅጣኝ፣ በምህረትህም ገስጸኝ፡፡ አንተ አዋቂ አድርገህ የፈጠርከኝ ጥበበኛ አድርገኝ እንጅ የዋሾ መምህራንና የኃጢአት ቅባት እራሴን አልቀባም፡፡
እኔ አዋቂ ብሆን ምን አውቃለሁ ብየ አሰብኩ፡፡ ከፍጥረት ሁሉ የሚልቅ ፈጣሪ እንዳለ አውቃለሁ፡፡ ከታላቅነቱ የተረፈ ታላላቅን ፈጥሯልና፡፡ ሁሉንም የሚያውቅ ነውና፡፡ ከአዋቂነቱ በተረፈ አዋቂዎች አድርጎ ፈጥሮናልና፡፡ ለርሱ ልንሰግድለት ይገባል፡፡ እርሱ የሁሉ ጌታና ሁሉንም የያዘ ነውና ወደርሱ በጸለይን ጊዜ ይሰማናል፡፡ እግዚአብሔር አዋቂ አድርጎ የፈጠረኝ በከንቱ አይደለም፡፡ እንዲህ አድርጎ የፈጠረኝ እንድፈልገውና እርሱ በጥበቡ በፈጠረኝ መንገድ እንዳውቀው እስካለሁም ድረስ እንዳመሰግነው ነው ብየ አሰብኩ፡፡ ሰዎች ሁሉ ሀሰት ካልሆነ በስተቀር ስለምን እውነት አይናገሩም ብየ አሰብኩ፡፡

Saturday, July 26, 2014

መጠጥና ዘፈን ጨለማን ተገን አድርገው መልካም ስብከት ሲሆኑ ልብ በሉ !

(ከአሌክስ አብረሃም  ጽሁፍ) በመካነ ጦማሩ ተሻሽሎ የቀረበ

ወገኖቸ እሰብካችኋለሁ !! በደሌ ቢራ አትጠጡ እንደተባለ ሰምታችኋል...... እኔ ግን እላችኋለሁ ባጠቃላይ አልኮል መጠጥ አትጠጡ ! ለጤና ጠንቅ ነውና !! መጠሃፉ ‹‹ደሃ ድህነቱን እንዲረሳ የወይን ጠጅ ስጠው ›› ቢልም እኛ ኢትዮጲያዊያን <አስራ አንድ> በመቶ እያደግን ያለን ሃብታም ህዝቦች ነንና እኛን አይመለከትም !
አዎ ! መጠጥ አገር እያጠፋ ነው ትዳር እየበጠበጠ ነው።  ይሄ ሁሉ ያማረበት ጠጭ ብርጭቆውን በቄንጥ ይዞ ውሰኪውን የሚከነብል ይሄን ሆንኩ ሳይል ወጋኝ ፈለጠኝ ሳይል ድንገት የሚከነበለው ለምን ይመስላችኋል ......መጠጥ .....መጠጥ ነው ወገኖቸ !! ህዝቤ ቁሞ ይንከላወሳል እንጅ ጉበቱ እኮ የለም .....ሳንባውኮ በጥቃርሻ ተዥጎርጉሮ የሚያፈስ ኮርኒስ መስሏል። ......ነብሱ አድፏል ! ይሄ ሁሉ የሆነው በምንድን ነው በመጠጥ !! መጠጥ እንዝህላል ያደርጋል፤ ግዴለሽ ያደርጋል፤ ዋጋ ቢስ ያደር .... ጋል ወገኖቸ .....
ዛሬ እኮ ምፅአት ቀርባለችና ንስሃ ግቡ ሲባል ‹ሎ...ል› የሚል ወጣት ነው እያፈራን ያለነው .... ትውልዱ በቀቢፀ ተስፋ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጥቷል ቤተስኪያኖቻችን  ርግብና ዋነስ  ሰፍሮባቸው  ካለሰው  እየዋሉ  ቡና ቤቱ  በሰው ተጨናንቋል ..... ጭፈራ ቤቱ ካፍ እስከገደፉ ሞልቷል ..... ጥርሱ በጫት ያለቀ፤ በሺሻና በሀሺሽ የናወዘ ትውልድ መቅኖ የለውም። ፈጣሪውንም አያውቅም።
ስለሳምሶን ታሪክ ሰምታችኋል (ለነገሩ መቸ መጠሃፉን ታነቡና ፌስ ቡክ ላይ አፍጥጣችሁ እየዋላችሁ ) ሳምሶን ታላቅ የህዝብ ነፃአውጭ ነውና ሲረገዝ እናቱ የአልኮል መጠጥ በአፏ እንዳይዞር እግዜር አዟት ነበር ! ለትውልድ የምታስብ ሴት እንዲያ በክብርና በቅድስና ትኖር ዘንድ መፅሃፉ ያዛል !
ዛሬ ግን ሴቶቻችን በየመሸታው አኮሌ ሙሉ መጠጥ ሲገለብጡና ሲያሽካኩ ያመሻሉ ያድራሉ የረከሰ ትውልድ ከሰካራም  እናት ይወለድ ዘንድ ስምንተኛው ሽ ቀርቧል ! ወንዱ መቸስ አንዴውኑ ጠጥቸ ልሙት ብሏል ! ደግሞኮ የድሮ መጠጥ  ሲያሰክር  ጀግና ያደርጋል የልብን ያናግራል። ጀምበሯ ዘቅዘቅ ማለት ስትጀምር ትውልዱ መጠጥ የሚሉትን የመርዝ ብርጭቆ አፉ ላይ ለግዶ ሞት ይጨልጣል።
.....የለም ! ወንዱ ሰክሮም ፈሪ ባይሰክርም ፈሪ ነው ! ቤቱ ገብቶ ሚስቱና ቤተሰቡ ላይ ነው የሚደነፋው ! ወገኖቸ ስካር ድሮ ቀረ !! ስለዚህ አልኮል መጠጥ አትጠጡ ! እንደአሸን የሚፈላው  የቢራ ፋብሪካና  መጠጥ ቤት የዝሙት ቤት ድራሹ  ይጥፋ ለአንድ ሽ ሰው የስራ እድል ፈጠረ የምንለው የመጠጥ ስራ ሚሊየኖችን ከሰውነት ክብር ካወረደ አትጠጡ !!
ይሄ  ውስጡ ኑሮ የሚጮህበት ህዝብ  ጩኸቱን  በጩኸት ለማጨናበር ዲጀ ማንትስ እከሊት  ጭፈራ ቤት እያለ ሲያላዝን ያመሻል። የውስጥን ጩኸት በውጭ ጩኸት  ለጊዜው  ነው ማጥፋት  የሚቻለው .....እናም  እላለሁ መጠጥ አትጠጡ !! አልኮል በደረሰበት አትድረሱ ! አልፎ አልፎ  ምናለበት ለምትሉ ለእናንተ  እላለሁ!  መጠጥ ሞት አለበት፤ መርከስ፤ ውርደት፤ ክስረት፤ ጩኸት፤ጥልና ክርክር፤ግድያም ሳይቀር አለበት !!
 ወገኖቸ የቴዲ አፍሮን ዘፈን አታዳምጡ እንደተባለ ሰምታችኋል ..... እኔ ግን እላችኋለሁ ባጠቃላይ ዘፈን አታዳምጡ .....መጠሃፉ ዘፋኝነት ዝሙት ሴሰኝነት ሰውን መግደል ..... እኩል  ሃጢያት ናቸው ብሏልና  ትውልዱን  እያዘናጉ ሲያስጨፍሩትና ሲያዘልሉት የሚኖሩትን  ስለምን  ትከተላላችሁ .....ዘፈን  የዝሙት  ቀኝ  እጅ  ነው ! ጥበብ ነው እያሉ ሌላ ነገር እንዳታስቡ የሚያጠቧችሁ ጠላቶቻችሁ ዘፋኞች ናቸው ! ብሶታችሁን  ከመናገር ይልቅ ከበሯቸውን  እየደለቁ  ሴት አሰልፈው  ሲያደንዟችሁ  የሚውሉት  እነሱ አይደሉምን? ጭንሽንና ዳሌሽን የሚል ዘፋኝ የዝሙት ሰባኪ አይደለምን? ፈራሽና በስባሽ ገላን እየጠራ፤ ልብህን ወደዚያ ከሚጎትት ዘፋኝ ወዲያ ዘመናዊ ጠላት ከወዴት ይገኛል? በመጠጥ ያሰክሩሃል፤ በዘፈን ወደዝሙት ይጠሩሃል።
ደግሞስ ጠጪና ዘፋኝ ትውልድ ሀገራዊ ርእይ፤ መንፈሳዊ ህልም እንዴት ይኖረዋል? ትልቁ ሀብቱ የደነዘ አእምሮና የፈጠራ ወሬ ብቻ ነው።
ሰለጠኑ ወይም ሰየጠኑ በሚባሉት ሀገሮች መጠጥ ቤት ተሰልፎ ከጠርሙስ አንገት ስር የሚገኘው ቦርኮ፤ ህልምና ርእዩን የገደለ፤ በሸሺሽ የደነዘዘ፤ በመንግሥት ድጎማ የሚኖር ተስፋ የለሽ እንጂ ጤናማ ሰው አይደለም። በሀገራችን ግን ብርጭቆ ጨብጦ በየሆቴሉ፤ በየድራፍት ቤቱና በየበረንዳው ሲጠጣ አምሽቶ ሲጠጣ የሚያድረው ከላይ እስከታች ከሊቅ እስከደቂቅ መሆኑያሳፍራል፤ ያሳዝናል።  መጠጥና ዘፈን ሁለት የሀገር ጠላቶች ናቸው። በመንፈሳዊው ዓለም ኃጢአቶች ናቸው፤ በሥጋዊውም ዓለም ቢሆን ከመጠጥ ሻጩና ከዘፋኙ በስተቀር ዘፈን እያዳመጠ፤ ሲጠጣ ካደረ ትውልድ ማንም ያተረፈ የለም።  ኪሳራ፤ ኪሳራ፤ ኪሳራ ብቻ!
እናም እላችኋለሁ፤ እባካችሁ መጠጥ አትጠጡ! መጠጥ ቤቶች የበዙት የሚያከስሩትንና የሚገድሉትን ትውልድ ለማብዛት እንጂ አእምሮውንና ኪሱን ለመገንባት አይደለም። ዝሙት ለማስፋፋት፤ ተላላፊ በሽታን ለማዛመት በህጋዊ ፈቃድ ከለላ ስውር ወንጀል የሚፈጽሙ የጥፋት ስፍራዎች ናቸውና መጠጥ ቤቶችን አጥብቃችሁ ሽሹ! ሁለት ሞት ትሞታላችሁ፤ በስጋም በነፍስም!

«ዋይታ ለማን ነው? ኀዘን ለማን ነው? ጠብ ለማን ነው? ጩኸት ለማን ነው? ያለ ምክንያት መቍሰል ለማን ነው? የዓይን ቅላት ለማን ነው? የወይን ጠጅ በመጠጣት ለሚዘገዩ አይደለምን? የተደባለቀ የወይንን ጠጅ ይፈትኑ ዘንድ ለሚከተሉ አይደለምን?
ወደ ወይን ጠጅ አትመልከት በቀላ ጊዜ፥ መልኩም በብርሌ ባንጸባረቀ ጊዜ፥ እየጣፈጠም በገባ ጊዜ። በኋላ እንደ እባብ ይነድፋል፥ እንደ እፉኝትም መርዙን ያፈስሳል። ዓይኖችህ ጋለሞታዎችን ያያሉ፥ ልብህም ጠማማ ነገርን ይናገራል። በባሕር ውስጥ እንደ ተኛ ትሆናለህ፥ በደቀልም ላይ እንደ ተኛ። መቱኝ፥ ያውም አልተሰማኝም ጐሰሙኝ፥ አላወቅሁምም። መቼ እነሣለሁ? ደግሞ ጨምሬ እሻታለሁ ትላለህ»  ምሳሌ 23፤29-35


ጆሮ ያለው ይስማ! ልብ ያለው ያስተውል!

Wednesday, July 23, 2014

ተአምረ ማርያም የተባለው መጽሐፍ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን እናት የቅ/ማርያምን የቅድስና ባህርይ አይወክልም!

(እዝራ ስነጽሁፍ፤ ዘላለም መንግሥቱ)
የመጨረሻ ክፍል

የተአምረ  ማርያም  ጸሐፊዎች  ሰዎችን  በማስፈራራትና  በማስደንገጥ የማይመረምሩትና  ከገዢው  ቃል  ጋር  የማያስተያዩት  ሃይማኖት  ግዞተኛ አድርገው  ለማኖር  የፈጠሩት  ፈጠራ  ከተፈጥሮና  ከስነ  ፍጥረትም ከአእምሮም  ጋር  የሚጋጭ  ነው።  እነዚህ  ናሙና  ከስነ  ፍጥረት  ሕግ  ጋር የሚጋጩ ያፈነገጡ ታሪኮች ናቸው።

ጥቂት ተጨማሪ ናሙና ግጭቶች

መጽሐፍ  ቅዱስ  የሚናገረው  መደመጥና  መከበር  እንዳለበት  ሁሉ  ዝም ባለበት  ጉዳይ  ሁሉ  ዝምታውም  መከበር  አለበት  እንጂ  በራሳችን  ምናብ የተፈተሉ  ነገሮችን  እየፈጠርን  ያላለውን  ማስባል  የለብንም።  የኢየሱስ የልጅነቱ  ዘመናት  ታሪኮች  በወንጌላት  ውስጥ  አልተጻፉም።  ያልተጻፉት አስፈላጊ  ስላልሆኑ  ነው።  ቢሆኑ  ኖሮ፥  እኔ  ደግሞ  ስለ  ተማርኸው  ቃል እርግጡን  እንድታውቅ  በጥንቃቄ  ሁሉን  ከመጀመሪያው  ተከትዬ በየተራው  ልጽፍልህ  መልካም  ሆኖ  ታየኝ    ያለውና  ከወንጌላቱ  ሁሉ በዝርዝር የዘገበው ሉቃስ ይህን አይጽፍም ኖሮአል?

   ስሟስ? የማርያምን  የስሟን ትርጉም በመቅድሙ  ላይ  “መንግሥተ  ሰማይ መርታ  የምታገባ”  ማለት  ነው  ሲል  ይተረጉማል።  በሌሎችም  ቦታዎች፥ ለምሳሌ፥  ምዕ.  12፥  74፥  98  ወዘተ፥  በዕብራይስጥ  ማሪሃም  የተባለች እያለ ተመሳሳይ ስምና ትርጉም ያቀርባል። እንዴት ፈጥረው ቢተረጉሙት ነው  ባለ  አራት  ፊደል  ስም  ይህ  ሁሉ  ቃል  ያለበት  ትርጉም  የሚሰጠው?
መምራት፥  ማስገባት፥  እና  መንግሥተ  ሰማያት  የሚባሉት  ቃላት  ማርያም ወይም  ሚርያም  በሚባለው  ስም  ውስጥ  ከቶም  የሉም።  በመጀመሪያ በዕብራይስጥ  ማሪሃም  አትባልም፤  ሚርያም  ናት።  ማርያም  በምንም ቋንቋ፥  በዐረብኛም  እንኳ  ማሪሃም  አልተባለችም።  ደግሞም  የስሟ ትርጉም  የተለያዩ  አገባብ  ትርጉሞችም  እንኳ  ተጨምረው  ዓመጽ፥ እንቢተኝነት፥ መራራ፥ መራራ ባሕር ማለት ነው እንጂ መንግሥተ ሰማይ መርታ  የምታገባ  ማለት  አይደለም።  ይህ  አልዋጥ  ካለንም  በግድ እንዋጠው፤ ዕብራይስጥ ብለን ከጠቀስን ትርጉሙ ይኸው ነው። በተአምር  21  ኢየሱስና  ማርያም  ለሐዋርያት  ተገልጠው  ጌታ  ለሐዋርያት በእርሱና  በእናቱ  ስም  በ4ቱ  ማዕዘናት  አብያተ  ክርስቲያናት  ይሠሩ  ብሎ አዘዘ።  በስሟ  ቤተ  ክርስቲያን  ማነጽ  ቀርቶ  ሐዋርያት  ስሟን  ጠርተው ሰብከው  ያውቃሉ?  በምዕ. 7  ደግሞ  ዕርገቷን  በ4ቱ  ማዕዘን  እንዲያውጁ አዘዛቸው  ይላል።  ሐዋርያት  እንዲህ  ተብለው  ይህን  አለመጻፋቸው ይደንቃል!  የታዘዙትን  ቤተ  ክርስቲያን  አለመሥራታቸውም  ዕርገቷን
አለማወጃቸውም  ያስጠይቃቸዋል።  አንዱን  ቤተ  ክርስቲያን  ጴጥሮስ እዚያው  ማነጹ  ተጽፎአል።  በአዲስ  ኪዳንና  በመጀመሪያዎቹ  የቤተ ክርስቲያን  ታሪክ  ዘመናት  ውስጥ  ክርስቲያኖች  ምእመናንን ሲያንጹ እንጂ ሕንጻ  ሲሠሩ  አይታወቅም።  ያመልኩ  የነበረውም  በምኩራቦችና  በቤት ውስጥ  እንጂ  ሕንጻስ  አላነጹም።  ማርያም  ለመጨረሻ  ጊዜ  በመጽሐፍ ቅዱስ  ውስጥ  የተጠቀችውም  ይኖሩበት  በነበረው  በተባለው  ሰገነት ውስጥ  ከጌታ  ሐዋርያት፥  ከደቀ  መዛሙርትና  ከወንድሞቹ  ጋር  በጸሎት ስትተጋ  ነው  የታየችው  እንጂ  ሰዎች  ወደ  እርሷና  ወደ  ስዕሏ  ሲጸልዩ አትታይም፤  ሐዋ. 1፥14  እነዚህ ሁሉ  ከሴቶችና  ከኢየሱስ  እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር ይላልና።

     ይኼ ሁሉ  የተደረተባት  ድሪቶ  ማርያምን  እንደሚያሳዝናት  የታወቀ  ነው። በእውነቱ  የተአምረ  ማርያሟ  ማርያም  ደራሲዎቹ  በመልካቸው እንደምሳሌያቸው  የፈጠሯት  እንጂ  የመጽሐፍ  ቅዱሷ  ማርያም  ከቶም አይደለችም።  እምነታችንንም  ራስና  ፈጻሚውን  ኢየሱስን  ተመልክተን ከተባለለት  ከኢየሱስ  ሰዎች  ዓይናቸውን  እንዲያነሡ፥  እንዲያውም ከቶውኑ  እንዳያዩት ተብሎ  የተፈጠረችና ማርያም  ተብላ  የተሰየመች  ሴት ናት  እንጂ  የመጽሐፍ  ቅዱሷ  ማርያም  ዛሬም  ብትጠየቅ  ያኔ  እንዳለችው፥ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ የምትል ናት።
በተአምር  4  ላይ  ማርያምን  ለመገነዝ  ሲሄዱ  ታውፋንያ  የተባለ  አይሁድ አልጋዋን  ስለያዘ  እጁ  በመልአክ  ተቆርጦ  አልጋው  ላይ  ቀረ።  ይህ  ሰው ሐዋርያትን  ይቅርታ  ጠየቀ፤  ክርስቶስንም  ይቅር  እንዲለው  ለመነ። ሐዋርያት  ግን  ወደ  እመቤታችን  ለምን  አሉት።  ማርያም  ቀድሞውኑ ከሞት  ተነሥታ  ነበርና  ለመናት።  ማርያምም  ጴጥሮስን  እንዲቀጥልለት ነገረችው። ጴጥሮስም በክርስቶስ ስምና በማርያም ስም እጁን መለሰለት። ይህ  ጴጥሮስ  ሐዋርያው  ጴጥሮስ  ከሆነ  መቸም  ይደንቃል።  ይህ  ጴጥሮስ በሐዋ.  3፥6  ብርና  ወርቅ  የለኝም፤  ይህን  ያለኝን  ግን  እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው ያለውና በኋላ በዚህ ስም ላይ ሌላ የለጠፈበት ነው? ይህ ጴጥሮስ በሐዋ. 4፥12 መዳንም በሌላ  በማንም  የለም፤  እንድንበት  ዘንድ  የሚገባን  ለሰዎች  የተሰጠ  ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና  ያለው ነው? እንዴት ያለ ቁልጭ  ያለ ግጭት ነው?  ይህ  የተከሰተው  ከሐዋ. 3  እና  4  በኋላ  ነው  ቢባል  ጴጥሮስ  ብዙ ቆይቶ  በጻፈው  በመልእክቱ  ምነው  የማርያምን  ስም  እንዲያው  አንዴ እንኳ  ያላስገባው?  ይህ  በኢየሱስና  በማርያም  ስም  ብሎ  እንደተናገረ የተጻፈለት  ጴጥሮስ  በመልእክቱ  ውስጥ  በ1ጴጥ. 4፥14  ስለ  ክርስቶስ  ስም ብትነቀፉ የክብር መንፈስ የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ላይ ያርፋልና ብፁዓን  ናችሁ  ያለውና  የክርስቶስን  ስም  ብቻ  ያጎላውና  የእርሱን  ብቻ ማንነት  አጉልቶ  የገለጠው  ነው?  ነው  ቢባል  እንኳ  የቱን  እንቀበል?  መጽሐፍ ቅዱስን ወይስ መጽሐፍ ቅዱስን የሚጻረረውን ሌላ መጽሐፍ? በተአምር  3  ማርያምን  ለመቅበር  ሲሄዱ  ሐዋርያት  ሁሉ  ጥለዋት  ተበተኑ ከዮሐንስ  በቀር  ይላል።  ልክ  ጌታ  ሲያዝ  እርቃኑን  በነጠላ  ከሸፈነው ዮሐንስ  በቀር  ሁሉ  እንደሸሹ  ይህንንም  የጻፈው  ይህ  ደቀ  መዝሙር መሆኑ  እንደተጻፈ  እዚህም  የፍልሰቱን  መጽሐፍ  የጻፈ  እርሱ  መሆኑ
ተጽፎአል።  የዚህ  ምዕራፍ  ግጭት  ከምዕ.  6  ጋር  ነው።  በተአምር  3  ጥለዋት  ተበተኑ  ሲል  በተአምር  6  ፈጽሞ እንዳልጣሏት፣  ግን  ገንዘው፥ ታቅፈው፥  ተሸክመው  እጅ  ነስተው  በጌቴሴማኒ  ቀበሯት  እንጂ አልጣሏትም ይላል። የቱ ነው ትክክል? ምዕ. 3 ወይስ 6? ለነገሩ የተለያዩ ሰዎች  ያዋጡት  መጽሐፍ  ስለሆነ  እንዲህ  እርስ  በርሱ  ቢጋጭ አያስገርምም።
በምዕ. 10  ኢየሱስ  በዋሻ  ውስጥ  መወለዱና  በጨርቅ  መጠቅለሉ  ሳይሆን የበለስ ቅጠል መልበሱ፥ በምዕ. 11 ደግሞ በጨርቅ መጠቅለሉ ተጽፎአል። በመንገድ  መካከል  ተወለደም  ይላል።  ይህ  የራስ  ከራስ  ግጭት  ነው።
መልአክ  ሄዶ  ለሰብዓ  ሰገል  እንደነገራቸው፥  ሰብዓ  ሰገል  ደግሞ  ሽቱም አምጥተውለት  እንደነበር  ተጽፎአል።  እነዚህ  ሁሉ  የተጻፈ  ታሪክን የሚያፋልሱ ናቸው።

    ከንጉሥ  ልጇ  ደም  በፈሰሰ  ደሟ  እኛን  ንጹሐን  አድርጋ  . . .  ይላል  ምዕ. 12፥54።  የማን  ደም  ነው  የፈሰሰ?  የማን  ደም  ነው  ያዳነ?  የማርያም  ደም ያዳነ በሆነማ  ኖሮ  ክርስቶስ ምነው  በመስቀል መዋሉ? ቃሉ በኤፌ. 2፥13  የሚለው አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ  በክርስቶስ  ደም  ቀርባችኋል  ነው  እንጂ  ከልጇ  በፈሰሰው በማርያም ደም  ቀርባችኋል  አይልም።  ጳውሎስ  ኤፌሶንን  ሲጽፍ ማርያም ሞታ  ወይም  ተአምረ  ማርያም  እንደሚለው  አርጋ  ስለነበረ  ጳውሎስ ይህንን  ማወቅ  ነበረበት።  ቆላ.  1፥19  በመስቀሉ  ደም  ሰላም  ማድረጉን ይናገራል፤  ሌላ  ደም  አይናገርም።  ዕብ.  9  በሙሉው  ይህንን  ደም ይናገራል  እንጂ  የማርያም  ደም  አይልም።  1ጴጥ. 1  የተዋጀንበትን  ክቡር ደም የክርስቶስ ደም ይለዋል እንጂ የማርያም አይለውም።
በምዕ.  7  በፍልሰቷ  ቀን  (ለነገሩ  ቀኖቹ  ሁሉ  በኛ  አቆጣጠር  ነው የተጻፉትና  በግብጽ  ወይም  በአይሁድ  ቆጠራ  ተጽፈው  መመንዘራቸው አልተነገረም)  በነሐሴ  16  ተዝካሯን  ለዘከረ  ኃጢአቱ  እንደሚሰረይ  ጌታ እንደሰጠ  ይናገራል።  በጣም  ትልቅ  ግጭት!  ኃጢአት  የሚደመሰሰው በነሐሴ  16  ተዝካር  ማድረግ  ከሆነ  መጽሐፍ  ቅዱስ  ከሚለው  ጋር  ፈጽሞ ይጣላል።  በክርስቶስ  በማመን  በጸጋ  ድኖ  በመስቀል  ላይ  በፈሰሰ  ደሙ የኃጢአት  ማግኘት  ወይስ  ደግሶ  አብልቶ  መዳን?  ወይስ  ከሁለቱ  ደስ ያለንን መርጠን መውሰድ?
በተአምር  32  ስለ  አንዲት  ዘማዊት  ይናገራል።  እንደ  ሙሴ  ሕግ እንድትወገር  እንደተፈረደ  ይናገራል  ደግሞም  ቤተ  መቅደስ  ውስጥ  ገብታ ይላልና  ደግሞም  በአዲስ  ኪዳን  ኃጢአተኛን  በድንጋይ  መውገር  የለምና ይህ  የብሉይ  ኪዳን  ዘመን  ይመስላል።  እንዳይባል  ደግሞ  ዘማዊቷ የማርያምን  ስዕል  አግኝታ  ለመነች  ይላል።  መልእክቱ  ወደ  ስዕል  ለምኖ መፍትሔ  ማግኘት  ቢሆንም  በመቅደስ  ውስጥ  የማርያም  ስዕል  ሊኖር አይችልም።  የቤተ  ክርስቲያን  መቅደስ  ነው  ከተባለ  ደግሞ  በቤተ ክርስቲያን  ወይም  በክርስትና  ዘመን  ኃጢአተኛን  መውገር  ከየት  የመጣ ፍርድ ነው? እርስ በራሱ የተማታ ታሪክ ነው።
ሰይጣን  መንፈስ  ነው  እንጂ  ስጋዊ  አካል  አይደለም።  በምዕራፍ  34  ሰይጣንን ማርያም በጥፊ አጩላው ልቡናውን ሲስት ይታያል። በምዕራፍ 51  ደግሞ  የመነኮሳትን  ምድጃ  ስላፈረሰ  አንድ  ሰይጣን  ተጽፎአል። መነኮሳቱ  ወደ  ማርያም  ጮኹና  ለ12  ዓመታት  ባሪያ  ሆኖ እንዲያገለግላቸው  ምድጃቸውን  ያፈረሰውን  ያንኑ ሰይጣን ሸለመቻቸው።
እነዚህ  መነኮሳት  ሰይጣንን  ተቃወሙት  የሚለውን  ቃል  አይታዘዙም ማለት  ነው።  ወይም  ቃሉን  ጨርሶውኑ  አያውቁም  ማለት  ነው።  ሳያውቁ ግን  መነኩሴዎች  ናቸው።  ማዕድ  ቤት  አስገብተው  እየፈጨ፥  እያቦካ፥ እየጋገረ ዓሳ ነባሪ እያጠመደ ከመርከብ ጋር እየተሸከመ አምጥቶ መርከቡ ውስጥ  የነበሩትን  ሰዎች  የሚያስመነኩስ  ይህ  አገልግሎት  ከማዕድ  ቤት ሥራ ያለፈ ነው!
    በምዕራፍ  37  ማርያም  ቴክላ  ወደተባለች  ሴት  ሄዳ  ስታስተዛዝናት፥ ልጇን  30 ዓመት በሆነው  ጊዜ  ከእርሷ ቀምተው  በእንጨት  ላይ ሰቅለው እንደ  ገደሉት  ነገረቻት። ጌታ ከማርያም  ተቀምቶ  ተገደለ  ወይስ ቀድሞም ሊሞት  ነው  የመጣው?  ደግሞስ  በ30  ዓመቱ  ነው  የተገደለው?  ሉቃ.  3፥23  በሠላሳ  ዓመቱ  አገልግሎቱን  መጀመሩን  ነው  የጻፈው።  ሳያገለግል ነው የተሰቀለው ማለት ነው? ተአምረ ማርያም ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ገድሎች ጋርም ይጋጫል፤  ይጣላል።  አንድ  ብቻ  ምሳሌ  ለመውሰድ፥  በገድለ  ተክለ ሃይማኖት  በመግቢያው  ምዕራፍ  ቁ.  40-46  እና  80-81  “.  .  .  አባቴ የሚለው  ግን  ዝክሩን  የሚዘክር  ስሙን  የሚጠራ  ከሱ  ጋራ  የዘላለም ሕይወት  ያገኛል  ዝክሩን  ያልዘከረ  ቃሉን  ያልጠበቀ  ከርስቱ  ከመንግሥተ ሰማያት  የተለየ  ይሆናል  የሞቱ  ሰዎችን  ነፍስ  ሁሉ  ክርስቲያን  የሚባሉ ጻድቅም  ኃጥእም  ቢሆን  የሞቱትን  ከክቡር  አባታችን  ከተክለ  ሃይማኖት ዘንድ  ሳያደርሱ  አይወስዳቸውምና  . . .  ለሥጋችሁ  መጠበቂያ  ለነፍሳችሁ መዳኛ  ነውና፤  ኃጢአታችሁን  የሚያነጻ  .  .  .”  ይላል።  እዚህ  ተክለ ሃይማኖት  የመንግሥተ  ሰማያት  መንገድ፥  የነፍስ  መዳኛና  የኃጢአት ስርየት  ሆኖ  ተገልጦአል። 16
   ማርያም  ወደ  መንግሥተ  ሰማይ  መርታ የምታስገባ  ተብላለች  ተክለ ሃይማኖትም በሩ  ከሆነ  የመዳን መንገዱ ብዙ ነው ማለት ነዋ! የማርያም ዝክር ነው መዳኛው ወይስ የተክለ ሃይማኖት?
በምዕ.  98  ስለ  ይሁዳ  እግረ  መንገድም  ቢሆን  የተነገረው  ጌታን  ሽጦ እናቱን  አግብቶ  አባቱን  መግደሉ  ተጽፎአል።  ቅደም  ተከተሉ  እንደዚያ ከሆነ  እናቱን  አግብቶ  አባቱን  የገደለው  ጌታን  ከሸጠ  በኋላ  ነው  ማለት ነው።  በትክክል  የሞተው  መቼ  እንደሆነ  ባይታወቅም  ተጸጽቶ  ወዲያው ሄዶ  ነው  ታንቆ  የሞተውና  (ማቴ.  27፥1-10)  ጋብቻውም  ግድያውም በሰዓቶች  ውስጥ  ምናልባት  በደቂቃዎች  መሆን  አለበት።  ያለዚያ  እናቱን አግብቶ  አባቱን  የገደለውንና  የአይሁድ  ሕግ ዝም  ያለውን  ሰው  ነው  ጌታ ከሐዋርያቱ ክልል ያስገባው።
     በምዕ. 121  ኢየሱስን  በ8  ዓመቱ  በጎች  እንዲጠብቅ  ላከችው  ይልና  ወደ ደብረ ዘይት መጥቶ በጎቹን አሰማራ ይላል። ለማያውቅ ሰው ልክ  እሰፈር ዳርቻ  በጎቹን  ወስዶ  የመሰገ  ይመስላል።  የሚኖሩት  ናዝሬት  በጎች የሚጠብቀው  ደግሞ  ደብረ  ዘይት  መሆኑን  እንደገና  እናስተውል።  ደብረ ዘይት እኮ ከናዝሬት የ105 ኪሎ ሜትር ሩቅ አገር ነው። በኛ አገር ከአዲስ አበባ  ናዝሬት  ማለት  ነው።  መልክዓ  ምድሩን  ለማያውቁና  ለማይጠይቁ ወይም  የተባለውን  ሁሉ  እውነት  ነው  ብለው  ለሚቀበሉ  አድማጮች የተጻፈ  በመሆኑ  ደራሲዎቹ  ይህን  እና  ይህን  የመሰሉትን  ግጭቶች ለመመርመር ሙከራ አላደረጉም።
በምዕ.  120  ኢየሱስን  በ5  ዓመቱ  የሚያስተምረው  አስተማሪ፥  “ይህ የመበለት  ልጅ”  ይለዋል።  ማርያም  መበለት  ሆነችሳ!  ዮሴፍ  ሞተ  ይሆን?
መቼም  የኢየሱስ  አስተማሪ  ተአምረ  ማርያም  እንደሚለው  ዮሴፍ “ጠባቂዋ”  መሆኑን  አያውቅም።  በምዕ. 121  ደግሞ  በ8  ዓመቱ  አሳዳጊው ዮሴፍ  ተጠቅሶአል።  በወንጌሉ  ውስጥ  ደግሞ  በ12  ዓመቱም  በሕይወት መኖሩ  ተዘግቦአል።  በተአምረ  ማርያም  ዮሴፍ  የማርያም  እጮኛ  እንኳ ሆኖ  አልቀረበም።
ሲደመደም፥  ተአምረ  ማርያም  ለሥጋዊ  አኗኗርና  ለኃጢአተኛ  ተፈጥሮ የሚስማማ  መጽሐፍ  ነው።  መጽሐፍ  ቅዱሳዊ  የቅድስና  አመላለስ፥ ክርስቶስን  መምሰል፥  ዋጋ  መክፈል፥  ለእውነት  መሰደድ  በውስጡ የሉበትም።  ክርስቶስን  አዳኝ  አድርጎ  መቀበልና  የሕይወት  ጌታ  አድርጎ እርሱን  መከተል  የሉበትም።  በምንም  ኃጢአት  ውስጥ  ተኑሮ  ለስዕል አቤት  ከተባለ፥  ዝክር  ከተዘከረ፥  በማርያም  ስም  አንዳች  ከተደረገ መንግሥተ  ሰማያት  የመግባት  ተስፋ  አለ።  ስለዚህ  እንደፈለጉ  ኖሮ ማርያምን  ጠርቶ  መናገርና  እርሷ  ደግሞ  ለልጇ  ተናግራ  የሚሹትን  ሁሉ ማድረግ ስለምትችል መልካሙን ገድል መጋደል አይታወቅም። ተአምረ  ማርያምን  ማሔስን  ካላቆሙት  በቀር  መቆም  አይችልም።
ምክንያቱም  እያንዳንዱ  ምዕራፍ  ከራሱ  ከመጽሐፉ  ሌላ  ምዕራፍ፥ ከታሪክና  ከእውነት፥  ከአእምሮና  ከተፈጥሮ፥  በተለይም  ከመጽሐፍ  ቅዱስ ጋር  በምሬት  የሚጣላ  መጽሐፍ  ነው።  በአጭር  ቃል  ተአምረ  ማርያም ጠላት ከዘራቸው ብዙ እንክርዳዶች አንዱ ነው።
ጌታ ከአርያም ይባርካችሁ።
ዘላለም መንግሥቱ  © 2012 (፪ሺህ፬) ዕዝራ ስነ ጽሑፍ አገልግሎት
1 ሰውና እግዚአብሔር በኃጢአት ምክንያት ተለያዩ
3. ሰው በራሱ ጥረት ወደ እግዚአብሔር መድረስ አይችልም።
በመጣጥፉ ውስጥ የተጠቀሱ መጻሕፍት፤
በአባቶቻችን  አፈርን፥  ባዩ  ታደሰ  እርዳቸው  (መምህር)፥
[ማተሚያ ቤት አልተጠቀሰም] አዲስ አበባ፥ ፪ሺህ፫ ዓ. ም.።
ይነጋል፥  ጽጌ  ስጦታው  (ዲያቆን)፥  አፍሪካ  ማተሚያ፥  አዲስ
አበባ፥ Ŧ ŹƃƂƋ ዓመተ ምሕረት።
ገድለ  አቡነ  እስጢፋኖስ  ዘጉንዳጉንዶ፥ 1997   ዓ.  ም.  አሳታሚ፥
መምህር ወማኅበር ዘጉንዳጉንዶ ደብረ ገሪዛን።
ለእውነት እንቁም፥ ስሜ ታደሰ፥ SIM Publishing፥ አዲስ አበባ፥
፪ሺህ ፬ ዓ. ም.።
ገድለ ተክለ ሃይማኖት፥ [አሳታሚና ማተሚያ ቤት አልተጠቀሰም]
አዲስ አበባ፥ 1989 ዓ. ም. ።
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በአስተዋጽዖ፥ መሠረት ስብሐት
ለአብ፥  አሳታሚ  ፍኖተ  ሕይወት  ማኅበረ  መነኮሳት፥  የኅትመት
ዘመን አይታወቅም፥ አዲስ አበባ።
ገድለ  ክርስቶስ  ሠምራ፥  ትንሣኤ  ዘጉባኤ  ማተሚያ  ቤት፥  አዲስ
አበባ፥  1992ዓ. ም. ።
Schaff, Philip,  History of the Christian Church,  Nicene
and Post Nicene Christianity,  T & T Clark, Edinburgh,
1884.
Tamrat, Tadesse,  Church  and State in Ethiopia  1270-1527, Oxford University Press, London, 1972.

Friday, July 18, 2014

በኢየሩሳሌም ገዳም መነኮሳትና በሊቀ ጳጳሱ መካከል የተከሰተውን አለመግባባት ለመመልከት የተሰየመው አጣሪ ጉዳዩን ለማየት መጓዙ ታወቀ።




በኢየሩሳሌም ገዳም መነኮሳትና በገዳሙ ሊቀጳጳስ በአባ ዳንኤል መካከል በተከሰተው አለመግባባት ያለውን ችግር ለመፍታት ቋሚ ሲኖዶስ እንዲጣራ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። ከዚህ በፊት እንደዘገብነው የገዳሙ ሊቀጳጳስ በመነኮሳቱ በኩል በረሃብ እየተቀጣሁ ነው ያለሁት ያሉትን ስሞታና መነኮሳቱ ደግሞ ውሸት ነው በማለት የሰጡትን ማስተባበያ ለአንባብያን መግለጻችንም አይዘነጋም። አሁን ዘግይቶ በደረሰን መረጃ ደግሞ ቋሚ ሲኖዶስ አሳልፎት በነበረው ውሳኔ መሠረት ግራ ቀኝ የተሰሙትን ክሶች ለማጣራት እንዲቻል አጣሪዎቹን ወደ ኢየሩሳሌም እንደላካቸውና ከስፍራው መድረሳቸውን የቤተ ክህነት ዘጋቢያችን ያደረሰን ዜና ያስረዳል።

ዘጋቢያችን የአጣሪዎቹን ማንነት ለማወቅ ጥረት እያደረገ ሲሆን የተላኩት የሲኖዶስ መልእክተኞች ወደእስራኤል መጓዛቸውን ግን ከተጨባጭ ምንጮች የተገኘው ዘገባ አመልክቷል።
ማጣራቱ የሚደረገው የገዳሙ መነኮሳቱ በሊቀ ጳጳሱ በኩል ተፈጽሟል የሚሉትን ክሶች መመርመርና ሊቀ ጳጳሱ ደግሞ በመነኮሳቱ በኩል ተፈጽሞብኛል የሚሉትን በደልና ግፍ አንድ በአንድ መርምሮ ለቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ማቅረብ እንደሆነ ይታወቃል።
የአጣሪዎቹን ማንነት፤ የተደረገውን የማጣራት ሂደትና የተገኘውን አጠቃላይ ውጤት የተመለከተ የመረጃ ዘገባ ተከታትለን ለማቅረብ እንሞክራለን።

Sunday, July 13, 2014

ተአምረ ማርያም የተባለው መጽሐፍ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን እናት የቅ/ማርያምን የቅድስና ባህርይ አይወክልም!



( እዝራ ስነ ጽሁፍ፤ ዘላለም መንግሥቱ)
ክፍል አምስት

6.  የተጣረሰ  ደኅንነትና  የተቃወሰ  ክርስትና።

 በተአምረ  ማርያም  ውስጥ ተዝካር  ያድናል፤  ማርያምን  ማመን  ያድናል፤  ተዝካሯን  መደገስ  ያድናል። በምዕ. 67  እረኞች  ያጠመቁት  አይሁድ  ውኃ  በቋጫ  ስለረጩበት  ብቻ ክርስቲያን  ሆነ፤  በ94  በንጹህ  እጅ  መቁረብ  መንግሥተ  ሰማያት ያስገባል።  78  ሰዎች  ቆርጥሞ  በልቶ  በማርያም  ስም  ጥርኝ  ውኃ  ከተሰጠ  ያ  ሚዛኑን  ደፍቶ  ከገሃነም  ፍርድ  ነጻ  ያወጣል።  ምጽዋት  መስጠት መንግሥተ  ሰማያት  ያስገባል፤  ምዕ.  44፤  ወዘተ።  ክርስትና  በተአምረ ማርያም  መመነን፥  መመንኮስ፥  ያለማግባት  ወይም  ጋብቻን  መጠየፍ፥ ከተጋቡም  በኋላ  አብሮ  ከመተኛት  ያለመገናኘት፥  ወደ  ስዕል  መጸለይና  መስገድ፥ ወዘተ፥ ናቸው። በመጽሐፍ  ቅዱስ  ውስጥ  ግን  ደህንነትና  የክርስትና  ኑሮ  በቃልና  በሥራ ክርስቶስን  እየመሰሉ፥  እየተከተሉ  የመኖር፥  መስቀሉን  የመሸከም  የደቀ መዝሙርነት  ኑሮ  ነው።  በመጽሐፍ  ቅዱስ  መዳን  በሌላ  በማንም እንደሌለ፥  እንድንበት  ዘንድ  የተሰጠ  የኢየሱስ  ስም  ብቻ  መሆኑ፥ ክርስቶስን  የተቀበሉ  ሁሉ  የእግዚአብሔር  ልጆች  መሆናቸው፥  ለመዳን ማመን  ብቻ  እንጂ  ልፋት  እንደማያስፈልግ፥  ያመነ  የተጠመቀ እንደሚድን፥  መዳን  ደግሞ  የሚታወቅና  የሚረጋገጥ  እንደሆነ  በግልጽ  ቋንቋ  ተጽፎአል።  በተአምረ  ማርያም  ግን  ይህ  አዳኝ  እና  የማዳኑ  ደስታ  ሲሸፈንና  እንዳይታይ  ሲደበቅ  ይስተዋላል። በምዕ.  41፥13  “በእግዚአብሔር  አምነው፥  በወለደችውም  በእመቤታችን አምነው  ከቤተ  ክርስቲያን  ወጡ”  ይላል።  ቁ.  25  እምነቱን  በናቱና  በእግዚአብሔር  ላይ  ያደረገ  ሁሉ  አያፍርምና  ይላል።  53፥55  ላይ  እግዚአብሔርን  አመሰገኑ  እመቤታችንንም  አመሰገንዋት  ይላል።  እምነት ክርስቶስ  ሲደመር  ሌላ  ነገር  ሆነ  ማለት ነው! በምዕ. 56  ማርያም  አንዱን መነኩሴ፥ “ከሚያልፈው ዓለም እስክወስድህ  ድረስ  ልጄ  ካንተ  አይለይም”  አለችው። ወሳጇ  እርሷ ስትሆን እስክትወስደው  ከመነኩሴው  የማይለየው  ልጇ  ነው።  ልክ  እንደ  አገልጋይ  ማለት  ነው።  በመጽሐፉ  ማርያም  ብቻ “ከልጇ  ጎን  በፈሰሰው  ደሟ”  አዳኝ  ሆና  ቀርባለች።  ታዲያ  ይህ የሰሚዎችን  ጆሮ  እያደነቆረ  የጠፉቱ  የምሥራቹን  ወንጌሉን  እንዴት ይስሙ?

7.  የተላቀቀ  መልክዓ  ምድር።

 በተአምረ ማርያም  ውስጥ  የተናጋ  መልክዓ  ምድርም  ይታያል።  ኢየሱስ  በዋሻ  ውስጥ  ተወለደ  ይላል፤  ለምሳሌ፥  ምዕ. 10።  ግርግምና  ዋሻ  እንደምን  አንድ  ሆኑ?  በ106  በኢያሪኮ  ባህር  ዳርቻ  ገዳም  ያለባት  ደሴት  መኖሯን  ይናገራል።  ደሴት  በባህር  ውስጥ  እንጂ  በባህር  ዳርቻ  አይኖርም።  ይሁን  እዳሩጋ  ጠጋ  ብሎ  ነው  ይባል።  ግን ኢያሪኮ  እኮ  ከተማ  እንጂ  ባህር  አይደለችም።  ኢያሪኮ  የሚባል  ባህር ኖሮም  አያውቅም።  በኢያሪኮ  አቅራቢያ  የዮርዳኖስ  ወንዝ  ነው  ያለው፤ ያም ቢሆን ገዳም የተገደመበት ደሴት የለበትም። ምዕ. 9  እና  ምዕ. 118  ከእስራኤል  ወደ  ግብጽ  ወይም  ከግብጽ  እስራኤል ሲሄዱ  ባህር  ሲሻገሩ  ይታያሉ።  በሁለቱ  አገሮች  መካከል  የየብስ  መንገድ ሳለ  በባህር  የሚያስዞር  ምክንያት  የለም።  ምናልባት  ከእስራኤል  ባህረ  ኤርትራን  መሻገር  ጋር  ለማቆራኘት  ይሆናል።  ወይም  ምናልባት  ከክብረ ነገሥት  ታሪክ  ጋር  ለማመሳሰል  የተደረገ  ሙከራ  ነው።  በጉዞውም  ተጋንነው  የተጻፉት  ነገሮች  ከክብረ  ነገሥት  ጋር  መመሳሰል  ስላላቸው  ከዚያ  የተኮረጀ  ይመስላል።
በምዕ. 72  ከሄሮድስ  ሸሽታ  ወደ  ዮሳፍጥ  ሸለቆ  ሄዳ  መሸሸጓ  ተጽፏል። ሊያያት  የመጣው  ገዢ  ከሄሮድስ  ሌላ  ሲሆን  ይህ  ሰው  ከሄሮድስ  ጋር ሊዋጋ  ዘምቶ  በማርያም  አማላጅነት  ተመለሰ።  እንደ  ፀሐይ  የሚያበራ ግርማ  ኖሯት  መሸሿ ወደ  ጎን ይቅርና፥ ጫካውም  ጫካ  ሆኖ ገዳም  መሆኑ ወይም  መባሉም  ይቅርና  በዮሳፍጥ  ሸለቆ  መደበቋና  ሁለቱ  ኃያላን  ሊዋጉ  መሰላለፋቸው  ሁለት  አገሮች  ብቻ  ሳይሆኑ  የሩቅ  አገሮችም  ያስመስላቸዋል።  ግን  የዮሳፍጥ  ሸለቆ  ከኢየሩሳሌም  በ20  ኪሎ  ሜትር ርቀት  የሚገኝ  ስፍራ  ነው።  በዚህ  አጭር  ርቀት  በሄሮድስ  ግዛት  ውስጥ ሌላ ገዥ ያውም  ከሄሮድስ  ሊዋጋ  የቃጣ  አልኖረም።

8.  የተዋረደ  ጋብቻ። 

መጽሐፍ  ቅዱስ  ጋብቻ  ክቡር  መኝታውም  በሁሉ  ቅዱስ  መሆኑን  ያስተምራል።  ጋብቻ  በማኅበራዊ  ረገድ፥  ለቤተ  ሰብ  ጤናማነት፥  በቅድስና  ለመኖር፥  ዘርን  ለመጠበቅ  በሙሉ  መልኩ፥ የተከበረ  ተቋም  ነው።  በተአምረ  ማርያም  ውስጥ  የሚታየው  ግን  የዚህ ተቃራኒ  ነው።  ጋብቻ  የተናቀ  ነው።  ያላገቡ  ሰዎች  በተአምረ  ማርያሟ ; ማርያም  እንዳያገቡ  ይመከራሉ።  የተጋቡም  ሳይቀሩ  ትዳራቸው  ፈርሶ  እንዲመንኑ  ይደፋፈራሉ።  ምዕ.  65፥  66፥  68፥  75፥  86፥  92፥  100 እንዳያገቡ  የተከለከሉ  ሰዎች  ታሪኮች ይነበባሉ።
በምዕ. 30  ካህን  ዘራፊዎችን  ግደሉ  አባለ  ዘራቸውንም  ስለቧቸው  ብሎ  ሲያዝ  ይታያል።  ለነገሩ  ከተገደሉ  በኋላ  ብልት  ዋጋ  የለውም፤  ግን የተደረገው  ሁሉ  ተደርጎ  ይህ  ሁሉ  በማርያም  አማላጅነት  ተደረገ  ብሎ ይደመድማል።  የተአምረ  ማርያሟ  ማርያም  አባለ  ዝርም  እንዲሰለብ  ታደርጋለች።  በምዕ. 85  ከገዛ  ሚስቱ  ጋር  መተኛቱ  እንደ  ኃጢአት  ሆኖበት  አባለ  ዘሩን  የቆረጠ  ሰው  ይገኛል።  ይህ  ሰው  ከደም  ፍሰት  የተነሣ  ሞቶ  መንግሥተ  ሰማያት  ሄዶ  በማርያም  ትእዛዝ ነፍሱ  ወደ  ሥጋዋ  ተመለሰችና  በሕይወት ኖረ።  መንግሥተ  ሰማያት  ከገባ  በኋላ  ነፍሱን  ብትመልስም  ቅሉ  ብልቱን ግን  አልቀጠለችለትም።  የሽንት  መሽኛ  ቀዳዳ  ብቻ  ተደርጎለት  መንኩሶ ኖረ።  በተአምረ  ማርያም  ትዳር  የቀለለ  ብቻ  ሳይሆን  የረከሰ  ነገር  ነው።
ከመነኮሰች  በኋላ  በፈቃደ  ሥጋ  ተሸንፋ  ከገዳም  የወጣችና  ያገባች  ሴት በመካንነት  ተቀጥታ  ወደ  ገዳሟ  ተመለሰች።  ሌሎችም  ይህም  የመሰሉ ታሪኮች ታጭቀውበታል።

9.  ያፈነገጠ  ተፈጥሮ።

 በተአምረ  ማርያም  ውስጥ  የበዙ  ከተፈጥሮ ሥርዓት  ጋር  የማይስማሙና  የሚቃረኑ  ነገሮች  ይነበባሉ።  በምዕ.  70  አንድ  ሰው  ሥጋ  ወደሙን  ከወሰደ  በኋላ  አውጥቶ  በንብ  ቀፎው  ውስጥ አደረገው።  በኋላ  ሥጋ  ወደሙ  ወደ  ብርሃንና  የማርያም  ስዕልነት  ተለወጠ።  በእጅግ  ብዙ  ቦታዎች  የማርያም  ስዕል  ከስዕል  ተፈጥሮ  ውጪ  ድምጽ ሲወጣው፥  ሲደማ፥  ወዝ  ሲወጣውና  ሰዎች  ያንን  እየተቀቡ  ሲፈወሱ ይታያል።  እጅ  ዘርግቶ  ከተንቀሳቀሰ  ወይም  ሌላ  ስዕል  ከሰጠ፥  የቆሰለበት  ስፍራ  ጠባሳ  ከኖረው፥  ስዕል  ሲወጉት  ከደማ  (ለምሳሌ፥  ምዕ. 31)  ስዕሉ  ሕይወት  አለው  ማለት  ነው።  ምክንያቱም  መጽሐፍ  ቅዱስ  ሕይወት በደም  ውስጥ  መኖሩን  ይመሰክራል።  ከላይ  እንደተጠቀሰው  ስዕል  በራሱ  የተፈጠረ  ካልሆነ  ስዕል  እየሠሩ፥  እየሸጡ  የሚተዳደሩ  ሰዎች  አሉና  ስዕሎቹ  በሰው  የተሠሩ  ለመሆናቸው  ጥርጥር  የለበትም።  የስዕል  አምልኮ  በመጽሐፍ  ቅዱስ  የተወገዘ  መሆኑ  እንዳለ  ሆኖ  ስዕሎቹ  ተአምራት ካደረጉ፥  ሲወጉአቸው  ከደሙ  ሕይወት  አላቸውና  ሠሪዎቹ  ምን  ሊባሉ ነው?  ፈጣሪ?  አምላክ?  በተአምረ  ማርያም  ስዕል  ብቻ  ሳይሆን  ዳቦም ሲቆርሱት ደምቷል። በተአምረ  ማርያም  ወደ  ዓሳነት  ሳይለወጡ  በባህር  ውስጥ  ሆኖ  መተንፈስም፥  መጸለይም፥  እንዲያውም  መውለድም  ይቻላል።  በተአምር 97  አንድ  መነኩሴ  የውኃ  ሙላት  አማታውና  ሰይጣን  ወስዶ  እባህር ከተተው። እዚያ ሳለ ማርያምን  ጠርቶ ሲጸልይ ማርያም  መጥታ  ሰይጣንን  ገሰጸችለት።  እሱም  ውዳሴውን  ቀጠለ፤  የሚጸልይበትን  ቦታ  አሳየችውና በዚያ  ሲጸልይ  አደረ።  ዋናተኞች  ለፍለጋ  ሲጠልቁ  ውዳሴዋን  ሲደግም  አግኝተው  አወጡት።  እዚያ  ለመቆየት  ሲል  ባትመጡብኝ  ይሻለኝ  ነበር አላቸው።  በተአምር  88  ደግሞ  አንዲት  ነፍሰ  ጡር  ከመስጠም  መዳኗ  ብቻ ሳይሆን  በባሕር  ውስጥ  ሳለች  በቤት  ውስጥ  እንዳለች  ሆና  በማርያም  ተሸፍና  ወልዳለች።  ያውም  ያለምጥ  ነው  የወለደችው።  ከተአምረ  ማርያሟ  ማርያም  ሌላ  ያለምጥ  የወለደች  ሴት  ናት  ይህች  ሴት።  በ375  ዓመቷ  የሞተችው  ክርስቶስ  ሠምራ  በጣና  ባህር  ውስጥ  ሰውነቷ  ተበጣጥሶ  ዓሳዎች  በውስጧ  እየሾለኩ  12  ዓመት  ጸልያ  ወጣች  እንደሚባለው  የመሰለ  ታሪክ  ነው። 15 በምዕ. 59  አንድ  የቤተ  ክርስቲያን  ጠባቂ  አንድ  ቀን  ከራት  በኋላ  የሥጋ ድቀት  አግኝቶት  ዝሙት  ፈጸመ።  በመልአክ  ተነክቶ  የሴት  መርገም ደረሰበትና  ከዚያ  በኋላ  ማርያም  ያደረገችበትን  ይህን  ነገር  አገር  ላገር  እየተናገረ  በመዞር  ኖረ።  መልአክ  ቢነካውም  ይህን  ያደረገችው  ማርያም  ናት።  ይህች  የዚህ  መጽሐፍ  ማርያም  ምንም  ነገር  ማድረግ  ትችላለች።

ሰብዓዊ  ተፈጥሮንም  ትቀይራለች።  የወር  አበባ  ካየ  ማኅጸን  ተሠራለት ማለት  ነው።  ማመንዘሩ  ኃጢአት  ሳለ  ቅጣቱ  ሴት  መደረግ  ወይም  እንደ ሴት  መደረግ  ከሆነ  ይህች  ማርያም  ሴትነቷንም  ትጠላዋለች  ማለት ይሆን? በምዕ.  107  ብዙ  ኃጢአት  ፈጽማ  ተስፋ  የቆረጠች  ተቅበዝባዥ  የሆነች ሴት  ታሪክ  ይገኛል።  ይህች  ሴት  ወደ  በረሃ  ሂዳ  ጊንጥ  አገኘችና ዋጠችው።  መርዙ  በሰውነቷ  ተሰራጭቶ  ስትሰቃይ  የማርያም  ስዕል  መጥቶላት  በዚያ  ሆዷን  እያሸች  ማርያምን  ለመነች።  ማርያም  ወደ  ቄስ ልካት  ለዚያ  ቄስ  ተናዝዛ  አምጣ  ወለደች።  የወለደችው  ሕጻንን  ሳይሆን 40  ትልልቅና  ትንንሽ  ጊንጦችን  ነው።  ወደ  አፍ  የገባ  ወደ  እዳሪ እንደሚወጣ  ጌታ  የተናገረው  ስሕተት  ተደርጎ  ወደ  ማሕጸን  ገብቶ  በ40  ተባዝቶ ወጣ!  እንደዚህ  ትምህርት  ከሆነ  ሴቶች ላም  እንወልዳለን  ብለው  በመፍራት  ወተት  መጠጣት  ማቆም  አለባቸው።  ወይም  አስር  ዶሮ  እንወልዳለን  ብለው  እንቁላል  መብላት  መተው  ይኖርባቸዋል።  ደግሞ  ሁሉም  እንደየወገኑ  እንዲዋለድ  በፍጥረት  መጀመሪያ  የተነገረውም  ተሰረዘና  ሴት  ጊንጥ  ወለደች።  ለተአምሩ  ትክክልነት  ሲባል  መጽሐፍ ቅዱስ  መስተካከል  አለበት።
ጊንጥ ብቻ  ሳይሆን  ሌላም  የከፋ  ወሊድ ታሪክ  አለ። በምዕ. 55 የሌላ  ሴት  ባል  የቀማች  አንዲት  ሴትና  ሌላኛዋ  ሴት  በማርያም  ታቦት  ፊት  እውነተኞች  መሆናቸውን  ይማማላሉ።  የቀማችው  ሴት  ኃጢአተኛ  ኖራለችና  እርጉዝም  ነበረችና  ቆይታ  ወለደች። የወለደችው  ሕጻን  ሳይሆን  በትል  የተሞሉ  ሁለት  የላም፥  ሁለት  የበግ  ቀንዶችን  ነው።  ይህች  ሴት እብድ  ሆና  እየዞረች  ይህንኑም  ያደረገችው  ማርያም  መሆኗን  እየተናገረች  ቆይታ  ሞተች። ቀንዶቹ  ደግሞ  ከማኅጸን  እንደወጡ  እንኳ  አልተቀበሩም።
በማርያም  ቤተ  ክርስቲያን  መስኮቶች  ተሰክተው  ይኖራሉ።  የትኛዋ  ቤተ ክርስቲያን  እንደሆነች  እንኳ  ቢናገሩ  ጉዱ  ይታይ  ነበር።  አገሩ  ብሔረ አግዓዚ  ከመባሉ  ሌላ  አይታወቅም።  በቀጣዩ  ምዕራፍ  (ምዕ. 56)  የያሬድ ቅኔ  ማኅሌት  እውስጡ  ስለተጠቀሰ  ብሔረ  አግዓዚ  የኛው  አገር  መሆኑን  እንረዳለን።  ቀድሞውኑም  የሌለ  ነገር  ስለሆነና  እንዲጠየቅና  እንዲመረመርም  ስለማይፈለግ  ስፍራው  አይገለጥም።  ወይስ  ዛሬም  ቀንዶቹ  ከአገራችን  ቤተ  ክርስቲያኖች  ባንዷ  መስኮቶች  እንደተሰኩ  ይሆኑ?