Friday, August 31, 2012

በአሜሪካ ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ለአቡነ ጳውሎስ የሀዘን መግለጫ አወጣ!


ቤተክርስቲያን ለሁለት የመከፈሏ ምክንያት የሥርዓት ለውጥ መከሰቱ እንደሆነ ይታወቃል። ከጊዜው ንፋስ ወዲህና ወዲያ የሚነፍሱ ወገኖች አንደኛውን ወገን የዚያ ሥርዓት ጥገኛ ሲል አንደኛውን ደግሞ የዚህ ቡድን ደጋፊ እያለ የገመድ ጉተታ ዓይነት ሃሳብ በመዘፈቁ የቤተክርስቲያን እርቅና ሰላም በሰመመን ውስጥ ሰጥሟል። አንዳንዶች ደግሞ ፓትርያርክ መርቆሬዎስ ማናቸው? የት ናቸው? በማለት ከ21 ዓመት በኋላ ጥያቄ የሚያቀርብ ጽሁፎቻቸውን በየድረ ገጾቻቸው ላይ ለጥፈዋል። ድምጽዎትን እንስማ፤ እዚህ ቦታ አለሁ በሉን! የሚለው ጥያቄ የፍቅር ከሆነ ይህንን ጥያቄ ለማቅረብ ዛሬ ምን ተገኘ? እንድልንል ያደርገናል። እንዲያውም ወደመንበራቸው ይመለሱ! የሚባሉት እርስዎ ማነዎት? የሚለው ፌዝ መሰል ጥያቄ ግልጽነትና ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ የቤተክርስቲያንን እርቅ ገና ብዙ ፈተና እንደሚጠብቀው ያመላክታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካው ሲኖዶስ በሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ፓትርያርክ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። ለቤተክርስቲያን አንድነትና ሰላም በጋራ እንስራ! የሚል መልእክቱንም አስተላልፏል።
ከቤተ ጳውሎስ ድረ ገጽ ላይ ያገኘነውን መረጃ አካፍለናችኋልና ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን እንዲያነቡ ተጋብዘዋል።


( መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Wednesday, August 29, 2012

የደም ምስል ጨርቁ!


ሰልሞንና ካሌብ ሊሰልሉ ወጥተው
ከዔናቆች መንደር አጥር ከከበው፤
ኢያሪኰ ገቡ ዮርዳኖስን አልፈው።
ግዙፋን አህዛብ ጥብቅ ሆኖ በራቸው ፤
ጥንካራ የነበር መግቢያና መውጪያቸው።
                     መሹለኪያ በሌለው  መዝጊያ ገረገራ፤
                      ሰርጎ ይገባ ዘንድ ፤እስራኤል አመራ፤
                        ጸጉረ ልውጥ ሰው ቢታይ በመንደሯ
                       ከበባ ታወጀ ከዔናቆች ጭፍራ።
                         ሰልሞንና ካሌብ በነፍስ አድን ሩጫ
                          መሸሸጊያ ሲሹ ከገዳይ ማመለጫ
                           ፈጣሪ አዘጋጀ፤ የከተማ ዋሻ
                           ከዔናቅ ሰራዊት መዳኛ መሸሻ
አንድ ሴት ነበረች ዘማነቷን ፈታ
ባል አልቦ የሆነች፤ በሕይወት ከርታታ
ብለው የሚጠሯት ረዓብ ጋለሞታ።
ሰዎቹን ሸሸገች ከቤቷ ውስጥ ጓዳ፤
በተልባ እግር ሽፋን፤ አድርጋ መከዳ።

                           ገዳይ ወገኖቿ አልፈው እንደሄዱ
                          ካሌብ፤ ሰልሞንም  ውለታ እንዳይክዱ
                          ቃል ታስገባ ጀመር፤ ሀገሯን ሲንዱ።
                          ሰባ ነገሥታትን ከፊት ያደቀቀ
                          ዮርዳኖስን ከፍሎ  በየብስ ያደረቀ
                         ሕዝቡን እየመራ ለድል የጠበቀ
                        ነውና አምላካችሁ ክንዱ የታወቀ
                        ኢያሪኰን መጣል እንደሚችል አየሁ፤
                       ኃጢአት የከበዳት፤ ረዓብ እባላለሁ፤
                       እባካችሁ ያኔ፤ ታደጉኝ እኔን፤
                       አብሬ አልጥፋ፤ ምሕረት አርጉልኝ
                        ብላ ብታነባ፤ ሰባብራ ልቧን
                      ገረመው ካሌብን፤ ደነቀው ሰልሞንን
                        ከሴት አመንዝራ፤ ድንገት ማግኘቱን
                        የእስራኤልን አምላክ፤ የሚያውቅ አምላኩን

Tuesday, August 28, 2012

ሚዲያ ጥሩና ሌላ ዐቃቤ መንበር ሹሙ! ብጹእ አቡነ ናትናኤል

   ድግሷ እንዳማረላት የሴት ወይዘሮ የቤተክህነቱን ወጥ የሚወጠውጠው ማኅበረ ቅዱሳን ነገሮች ሁሉ እንዳሰበው  ሊሄዱለት እንዳልቻሉ ሁኔታዎች እያመላከቱ  ናቸው። መንፈስ ቅዱስን በስም እንጂ በእምነት የማያውቀው ማኅበር ሲኖዶሱ በመንፈስ ቅዱስ ይመራናል እያለ፤ የራሱን ዓላማና ግብ ለማስፈጸም ባሰባሰበው የሰሞኑ ሲኖዶስ ጉባዔ ላይ  ፍትጊያውና ሩጫው ያላማራቸው ዐቃቤ መንበር አቡነ ናትናኤል ፤ እኔ በስተርጅና ስምና ክብሬን አዋርጄ፤ ቤተክርስቲያንንም ለማንም መጫወቻ እንድትሆን አሳልፌ ሰጥቼ ታሪኬን አላበላሽም፤ ነገረ ሥራችሁም ደስ አላለኝም በማለት ዐቃቤ መንበርነቱን ተረከቡኝ ብለው ጉባዔውን ትተው መውጣት ከጀመሩ በኋላ በእድሜ የገፉ አባቶች ባቀረቡላቸው ልመናና ተማጽኖ ለመመለስ ችለዋል። 

ወጣቶቹ ጳጳሳት 7ቱ ኮሚቴዎች የምንመራበት የራሳችንን አዲስ ሕግ እናውጣ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ካህናትንም ለስብሰባ እንጥራ በማለት ማስቸገራቸው የተሰማ ሲሆን በብጹእ አቡነ እስጢፋኖስ በኩል ተሰጣቸው የተባለው መልስ እንደሚያስረዳው ሕግን በተመለከተ ከሲኖዶስ ሕግ ውጪ ዛሬ የምናወጣው ሕግ አይኖርም፤ አዲስ አበባ ሀ/ስብከትም  የራሱ ሊቀጳጳስ እያለው ጣልቃ በመግባት የካህናት ስብሰባ እኛ ማድረግ አንችልም በማለታቸው  የእነ አቡነ ነደ እሳት ጥያቄ ተቀባይነት ሳይኖረው ቀርቷል። በእድሜ የገፉትን እኒህን አባት ዐቃቤ መንበር ማድረግ ያስፈለገው እንዳሻን እንነዳቸዋለን፤ እየጠመዘዝን እንሰራለን ከሚል የሥጋዊ አእምሮ ስሌት የነበረ ቢሆንም ለጊዜው አቡነ ናትናኤል አይተው የማያውቁት ሩጫና ግርግር አስደንግጧቸዋል።  ደጀ ብርሃን ብሎግ  «የፓርትርያርክ የምርጫ ግርግር ለማኅበረ ቅዱሳንና ለወዳጅ ጳጳሳት ጥቅም እንዳይውል ያስፈራል!» በሚል ርእስ ያወጣችው ጽሁፍ በተግባር እየታየ መሆኑን አመላካች ነው።  በሌላ መልኩም አቡነ መልከ ጼዴቅ ከወደ አሜሪካ በአቡነ ጳውሎስ እረፍት ላይ ውግዘታቸው ሳይነሳ የሞቱ መሆናቸውን በመናገራቸው  መሳሳብ ማስከተሉ ተነግሯል። ሁለቱም ወገን መወጋገዛቸው አይካድም። የውስጥና የውጪው ሲኖዶስ የተወጋገዙት ቃል ሳይፈታ አቡነ ጳውሎስ ማረፋቸውም እውነት ነው። እንደእኛ እምነት አሁንም ቢሆን ለእርቁ መንገድ እንዲሆንና እንደተወጋገዙ ሌሎች አባቶችም በመሐል በሞት እንዳይለዩ ከሁሉም ቅድሚያ ውግዘቱን ማንሳት አለባቸው እንላለን። ወንጌሉም የሚለው ይህንኑ ነው። ሉቃ 1126 እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።
ከዚህ አንጻር የአቡነ መልከ ጼዴቅ ተወጋግዘን በሞት ተለያየን የሚለው ቃል ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ እንጂ እንደስህተት ቃል ማስተባበያ የሚያስፈልገው አይደለም። እንደተወጋገዙ በሞት መለያየት ጥሩ ነው የሚል ይኖር ይሆን?
ለቀሪ መረጃ የዓውደ ምሕረትን ዘገባ እነሆ ብለናልና መልካም ንባብ ይሁንላችሁ።

 awdemihret.blogspot.com// awdemihret.wordpress.com)
ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የቅዱስነታቸው የቀብር ሥነ ስርዓት ከተፈጸመ በኋላ በነጋታው ሲኖዶሱ ወደ መደበኛ ሥራው ተመልሷል። ከተመለከታቸው ጉዳዩች አንዱም የእርቁ ሁኔታ ነበር። የቅዱስነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ቀን ማታ አቡነ መልከ ጼዴቅ ቅዱስነታቸው ተወግዘው ነው የሞቱት ብለው መናገራቸው የእርቁን ሀሳብ አደጋ ላይ ጥሎታል።
አርብ ዕለት በነበረው ስብሰባ የእርቁ ሀሳብ ሲነሳ በርካታ ጳጳሳት የአቡነ መልከጻዲቅን ንግግር ማዘናቸውን ገልጸዋል። በተለይም የአቡነ እስጢፋኖስ አቋም ጠንካራ እና የሁሉንም ልብ ማሸነፍ የቻለ ነበር። ብጹዕነታቸው ሲናገሩቀብቶ የሾመን ተወግዞ ሞተ ከተባለ እኛም የተወገዝን ነን ማለት ነው። ስለዚህ የምን እርቅ ነው የሚደረገው? እኛ የእርቅን ሀሳብ መነጋገር ከጀመርን ጀምሮ ከቅዱስነታቸው ጀምሮ ሁላችንም ስለ እነርሱ መወገዝ አንስተን አናውቅም። ምክንያቱም እርቅ የሚመጣው ያሉበትን አቋም ትቶ ነው እንጂ የወሰድኩት አቋም አይለወጥም ብሎ አይደለም። ስለዚህ ቅዱስነታቸው ሲያርፉ መነሳት የሌለበትን ርዕስ አቡነ መልከጻዲቅ ሰላነሱ በአደባባይ የተናገሩትን ንግግራቸውን በአደባባይ እስካላስተባበሉ ድረስ የእርቅ ሀሳብ አይኖርምበማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ይህንንም ሀሳብ አብዛኛዎቹ ጳጳሳት ተቀብለውታል።