Tuesday, July 24, 2012

አቢሲኒያ የሚለውን ስም ከእኛ ይልቅ ነጮቹ ይጠቀሙበታል!


የዛሬዋ ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ታላቅ ሀገር እንደነበረች ታሪክ ይናገራል።  በግዛት ስፋት፤ በጦር ኃይል ብዛት፤ በሥነ ሕንጻና በሥነ ጽሁፍ ገናና ሆና መቆየቷን የሚናገሩ ብዙ የታሪክ ድርሳናት አሉ። በእርግጥ ብዙዎቹም ድርሳናት የተጻፉትና በሰነድነትም የሚገኙት በውጪው ዓለም ነው። አቢሲኒያ የሚለው ስም የትመጣነት ለታሪክ ሀተታ ይቆየንና ኢትዮጵያ የሚለው / ጥቁር መልክ/ ስያሜ ከመሰጠቱ በፊት አቢሲኒያ የምትባለው ሀገራችንን ታሪክ አብዛኛው የምናውቀው « የኢትዮጵያ የቀድሞ ስም» የሚለውን ጥሪ ብቻ ነው። ግፋ ቢልም «አቢሲኒያ ባንክን» !!!
ታሪካዊነቱን የሚገልጽ መታሰቢያ ዩኒቨርሲቲ፤ የጎዳና ስም፤ ሆስፒታል ወይም ሌላ ተመሳሳይ መጠሪያ እስከምናውቀው ድረስ የለንም። ምናልባት ያልሰማነው ካለ ይታረማል። ታሪክና ቅርስ ለአንድ ሀገር ሕዝብ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ማንነት ወሳኝ ነው።  በዘመናት ያለፈባቸውን የጥንካሬና የድክመት ጉዞዎቹን ይቃኝበታል። መጻዒውንም ያማትርበታል።
እስራኤሎች ታሪካቸውን እየጻፉ ለመጪው ትውልድ የሚያኖሩላቸው ጸሐፊያን በየዘመኑ ነበራቸው። በሕይወታቸው ያለፈውን፤ ያደረጉትንና የተደረገላቸውን እየከተቡ ያኖሩ ነበር።
1ኛ ነገ 43
«ጸሐፊዎቹም የሴባ ልጆች ኤልያፍና አኪያ፥ ታሪክ ጸሐፊም የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ»
የእያንዳንዱ ነጋሲ ታሪክና ሥራ እየተጻፈም ይቀመጥ ነበር። ይህም ለልጅ ልጆች የሚቀመጥ ውርስ ነበርና ነው።
1ኛ ነገ 1532
በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን?
እኛ ለዚህ አልታደልንም።

 እንኳን እንደዚህ ዓይነት ታሪክ ጽፈን ለማቆየት ይቅርና በዘልማድ  ስለምናውቀው «አቢሲኒያ» ስለሚለው የሀገራችን ስም መታሰቢያ የሚሆን ነገር የለንም። ይሁን እንጂ ፈረንጆቹ በመጽሐፍ ቅዱስ «ኩሽ» በታሪክ አቢሲኒያ፤ በመጠሪያ ደግሞ ዛሬ ኢትዮጵያ ስለምትባለው ሀገራችን የእምነት፤ የጀግንነት፤የታሪክ፤ የቅርስና የመልክዓ ምድር ወዘተ ሰፊ ጥናት አድርገዋል። መጻሕፍትንም ጽፈዋል።
ፈረንሳዊው የታሪክ ጸሐፊ  ጂን ክሪስቶፍ ሩፊን/Jean-Christophe Rufin/ ዘ አቢሲኒያን፤ ሳሙኤል ጆንሰን፤ ጀምስ ብሩስ፤ሪቻርድ በርተን፤ ኢቭሊን  ዎግ፣ ዴርቭላ መርፊ፤ ሲልቪያ ፓንክረስት፤ ኸርበት ቪቪያን፤  ሮማን ፕሮቼስካ ፤ ጆንስ እና ኤልሳቤጥ/ መጽሐፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ /  ወዘተ እና ሌሎች ብዙዎች ጸሐፊያን ስለአቢሲኒያ ጽፈዋል።

 ይህንኑ ገናናውን የአቢሲኒያን ታሪክ ተከትሎና ከጥቁር ምድር ቀዳሚ የክርስትና ሀገር ኢትዮጵያ በመሆኗም ጭምር አሜሪካውን ጥቁሮች ቤተክርስቲያኖቻቸውን ጭምር በምድረ አሜሪካ ውስጥ በአቢሲኒያ ስያሜ ይጠሩ ነበር።  ኮሎራዶ በ516ኛው ክሬስትሞር ጎዳና ላይ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን ክርስቲያኖች ቤተክርስቲያን፤  ኒውዮርክ በምእራብ 138ኛው ጎዳና ላይ በ1808 የታነጸው የአቢሲኒያውያን መጥምቅ ቤተክርስቲያን፤ 1828 ዓ/ም በ75 ኒው በሪ ጎዳና የተመሰረተው የፖርት ላንድ አቢሲኒያውያን ቤተክርስቲያን፤ እዚው ፖርት ላንድ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን የመሰብሰቢያ አዳራሽ፤  ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ በኢትዮጵያ የቀድሞ ስም በአቢሲኒያ ስም የተጠሩ የአሜሪካ ጥቁሮች የታሪክና እምነት ስያሜ መጠሪያዎች ነበሩ። ዛሬም በዚሁ ስም እየተጠሩበት ይገኛሉ። ብዙዎቹም እናት ምድራችን በሚሏት አቢሲኒያ /ኢትዮጵያ/ ተገኝተው ታሪኳን ቅርሷን፤ ክብሯን ሁሉ በአካል ለማየት ችለዋል። ያ ሁሉ ዝናና ታሪክ ተንኮታኩቶ የድሆች መናኸሪያ፤ የስደተኞች መፍለቂያ መሆኗን ሲያዩ ምን ብለው ይሆን?
አብያተ ክርስቲያኖቻቸውን በአቢሲኒያ ስም ከመጥራት ባሻገር አቢሲኒያን በተለያየ ዘመናት የረገጡ ነጮች ከምድረ አቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ፤ ድብ፤ አሳማ፣ እጽዋት በመውሰድ በሀገራቸው አራብተዋል፤ አዳቅለዋል።  
ዛሬ በአሜሪካ የአቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ ወዘተ በስም ተለይቶና ተመርጦ የሚገዛበት ትልቅ  ስም ነው። እንዲያውም ተፈላጊ መለያ ነው።
የአበሻ ውሾች ቁጡዎችና ኃይለኞች፤ ድመቶቹ አይጥ አዳኞች፤ ፈረሶቹ የጦር ሜዳ ዘመቻ ጋላቢዎች ስለነበሩ እየወሰዱ ተዳቅለዋል። ሳንዲያጎ በሚገኘው ግዙፉ የእንስሳት ፓርክ ውስጥ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ አእዋፍና አሞራዎች አሉ። የአቢሲኒያ ድመቶች ማደቀያ ማኅበር ራሱን ችሎ በአሜሪካና በእንግሊዝ የተቋቋመ ነው።  እንስሳዎቹም በአቢሲኒያ ስም እስከዛሬ ይጠራሉ።
ከታች የሚታዩት ስእሎች በ«አቢሲኒያ» ስም ከሚጠሩ መካከል ጥቂቶቹ  ናቸው።

Sunday, July 22, 2012

ለማኅበረ ቅዱሳን ፍርሀት የሆነው ጉባኤ አርድዕት በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ።


ብዙ ጊዜ ስለማኅበረ ቅዱሳን በሚቀርቡ ጽሁፎች ላይ አስተያየት የሚሰጡ የማኅበሩ አቀንቃኞች የሚያዩን  ስለማኅበሩ ጭፍን አመለካከት እንዳለንና ሥራውን ሁሉ እንደምናቃወም አድርገውን ነው። ይሁን እንጂ ማኅበሩ እንደማኅበር የሰዎች እንጂ የቅዱሳን መላእክት ስብስብ ባለመሆኑ በጉዞው ውስጥ መልካምም ይሁን መጥፎ ሰውኛ ድክመቶች የሚገለጽበት መሆኑን ሁሉም አምኖ እንዲቀበልና ጥንካሬው ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ እንደሚሆን ሁሉ ድክመቱም አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያመጣ በመገንዘብ ራሱን እንዲያይ፤ እኛም ማን መሆኑን በማወቅ የተሻለ ግንዛቤ ይዘን እንደባህሪው  የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ ነው። ለስህተት ትምህርቶችን የአዞ እንባ አፍሳሽነት፤ የሁሉን አውቃለሁና ጠበቃ ነኝ ባይነት መጥፎ ዐመል፤ የእኔ ላቡካው፤ እኔው ልጋግረው ግብዝነት፤ ከቤተክርስቲያኗ ኪስ ወደራስ ጓዳ የመሰብሰብ አባዜ፤ የሰላይ፤ የመቺ፤ የአሳዳጅና የፈራጅ ቡድን የማዋቀር ሲሲሊያዊ አካሄዱን ነቅሰን በማውጣት ይህን፤ ይህን ስትሰራ ቆይተሃል፤ ይህን ይህንንም እየሰራህ ትገኛለህ፤ መረጃዎቻችንም እነዚህ ናቸውና ከተነቃብህ እራስህን አርም፤ አስተካክል ወይም ቢያንስ ራስህን እስኪ  ጠይቅና ከሚወራው ውስጥ የትኛው እውነትና የትኛውስ ስም ማጥፋት ነው ብለህ ፈትሽ በማለት ለማሳሰብ ነው።  እኔ ቅዱስ እንጂ ስህተት የማይጎበኘኝ ነኝ ማለት ሲያበዛ ደግሞ አንተ ፈሪሳዊ ሆነህ ሳለ መጸብሐዊው አይጸድቅም የምትል ግብዝ ነህና መንገዳችንን አትዝጋ፤ የናቡከደነጾር የህልም ሀውልት ስለሆንክ ከተራራው የሚወርደው ዐለት ይፈጭሃልና ግዙፍነትህን አይተህ አትመካ እንለዋለን። ሌላውም  እንዲያይ የእስከዛሬ ማንነቱን ገልጠን ለሌሎች እናሳያለን። በዚህም ሥራችን ብዙዎች ራሳቸውን እንዲጠይቁ፤ የሚባለውን እውነትነት እንዲመረምሩ አድርገናል። በዚህም የመረጃ ስርጭትና ማንነቱን የመግለጽ ሥራችን ግምገማቸውን ወስደው ራሳቸውን ከማኅበሩ ክፉ ስራ ያገለሉ ብዙዎች ናቸው። ተሸፍኖ የነበረባቸውን የማኅበሩን ማደንዘዢያ መርፌ ነቅለው ከድንዛዜ ወጥተው፤ እስከዛሬ የት ነበርኩ? ያሉና ራሳቸውን የጠየቁ ብዙዎች ናቸው። ከዚህ በታች ያለውም የማኅበረ ቅዱሳን አቀንቃኝ ብሎጎች ማጭበርበርና የነፍስ ውጪ፤ ነፍስ ግቢ ውሸት ማሳያ ቀርቧልና  ሄዳችሁ ብሎጎቹን አንብባችሁ ከታች በቀረበው መረጃዎች ላይ ተመርኩዛችሁ ማቅ ማን መሆኑን ተመልከቱ! ሁሌም ውሸት! ውሸት! ውሸት! አቤት ማቅ?
ምንጫችን፤ ዓውደ ምሕረት ብሎግ፤

  •     ሊቀ ሥዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ መኪና አልተቀማም
  •     ጉባኤ አርድእት ስብሰባ እንዳይሰበሰብ አልታገደም
  •     መንግስት ለማኅበረ ቅዱሳን የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ማንም አልሰማም በማለት ወደ ጉባኤ አርድዕት ለማዞር ሞክረዋል
የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በተለመደው ዋሾ ባህሪያቸው ያልሆነውን ሆነ እያሉ መዘገብን ቀጥለውበታል፡፡ ስለጉባኤ አርድዕት በመፈራረቅ በሰሩት ዜናም ገና በመደራጀት ላይ ያለውን ጉባኤ ተፈረካከሰ ተልፈሰፈሰ ሄደ ተመለሰ እያሉ የጅል ምኞታቸውን ይነግሩን ይዘዋል፡፡ ሊቀ ሥዩማን ኃይለጊዮርጊስም በጠቅላይ ቤተክህነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ፊርማ መኪናው ስለተበላሸ ቅያሪ መኪና እንዲሰጠው የትብብር ደብዳቤ እንደተፃፈለት እያወቁ  ደብዳቤውን ከኛ በቀር ማንም አያገኘውም በማለት ተበላሽቶ ወደ ጋራዥ የገባውን መኪና ተቀማ በማለት ዘግበዋል፡፡
እነዚህ የማኅበሩ የውሸት ቃል አቀባይ የሆኑ ደጀ ሰላምና አንድ አድርገን የተባሉት ብሎጎች በጉዳዩ ላይ እርስ በእርሳቸው እንኳ መስማማት አቅቷቸዋል። ዋሽቶ ስምምነት የት አለና? ደጀ ሰላም ኃይለጊዮርጊስ መኪና የተቀማው በአቡነ ጳውሎስ ትዕዛዝ ነው ብላ ጀምራ ወደ ታች ወደ ወረድ ሲባል ደግሞ በምክትል ስራ አስኪያጁ በተስፋዬ ነው በማለት ራስዋን ተጣልታ ዘግባለች። አንድ አድርገን ደግሞ በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ነው ትላለች።
እውነታው ግን ሌላ ነው በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ፊርማ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው የኃይለጊዮርጊስ መኪና በብልሽት መቆምዋን እና እንዲያውም ተለዋጭ መኪና እንዲፈለግለት ልማትና ክርስቲያናዊ መምሪያን የሚጠይቅ ነው።
 ደብዳቤውን ለማንበብ ( እዚህ ይጫኑ )

Friday, July 20, 2012

የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን በስራዬ ጣልቃ እየገባ ስላስቸገረ አደብ ይያዝልኝ አለ

(ሐምሌ 13 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)ማኅበረ ቅዱሳን በማን አለብኝነት ወዋቅራዊ አሰራርን በመጣስ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሥራ ላይ ጣልቃ በመግባት በስሩ የሚገኙ ገዳማትንና አድባራትን ሰበካ ጉባኤ ስብሰባ እየጠራ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን ከሶስተኛ ወገን የሚገናኝበትን መመሪያ እየጣሰ ይገኛል ሲል የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አስታወቀ፡፡ ለተጻፈው ደብዳቤ ( እዚህ ይጫኑ )
ይህ የመዋቅር ጥሰት አግባብ ያልሆነ ስለሆነ ሃገረ ስብከቱ “…ማኅበሩ በሃገረ ስብከታችን ጣልቃ እየገባ የሚያስተላልፋቸውን ጥሪዎችና የመዋቅር ጥሰቶች እንዲያቆም…”የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አካሄዱን የሚያተካክልበት መመሪያ እንዲሰጥልን እናሳስባለን ብሏል፡፡
ከፅንሰቱ ጀምሮ አመጽ በቀል የሆነው ማኅበር እኔ ያልጣድኩት ድስት አያስፈልግም እያለ በተለያየ ሥራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ለቤተክርስቲን የሚጠቅም ሥራ ከመስራት ይልቅ የማኅበሩን ገጽታ በመገንባት ሥራ ላይ ተጠምዶ ይገኛል፡፡  ህዝብ ወደ እግዚአብሔር እውነት የሚደርስበትን መንገድ ከማመቻቸት ይልቅ ቤተክርስቲያን ያለህዝብም ቢሆን በማኅበሩ ቁጥጥር ሥር የምትውልበትን ስራ በመስራት ላይ ያለው ማኅበር ባልተፈቀደለት የስራ መስኮች እየገባ በማን አለብኝነት እየበጠበጠ ነው፡፡
ደፋሩ ማኅበር ለመምሪያዎች ከተለያዩ አካለት የሚመጡ በየስልጠና ጥሪዎችን መምሪያዎች ውስጥ ባሉ ሰዎቹ አማካኝነት ደብዳቤ እያስከፈተ መምሪያው ሳያውቅ በመምሪው ስም ስልጠናዎችን የማኅበሩ ሰዎች እንዲወስዱ እያስደረገ መሆኑ ሲታወቅ ከዚህ በፊት እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲከሰት ከማዘን ያለፈ ተቃውሞ ሳይሰማ ቀርቶ ነበር፡፡ ይህም የልብ ልብ እየሰጠው በሃገረ ስብከቶችና በአጠቃላይ በቤተክኅነቱ ስራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ማኅበረ ቅዱሳን ወይም ሞት ፉከራን እያሰማ ይገኛል፡፡
እንደ አንድ አለሌ ሽፍታ የተወሰኑ እበላ ባይ ጳጳሳትን ማስገበሩ የልብ ልብ እየተሰማው ምንስ ባደርግ ምን እሆናለሁ ያሻኝን ሰርቼ ወጥቼ እገባለሁ እያለ በአንድ መጠምሻ ጎረምሳ ስሜት የሚንቀሳቀስ ማኅበር መሆኑ ለቤተክርሰቲኒቱ አደጋ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል፡፡
የቤተክርሰቲያንን ክፍተት ለመሙላትና አደጋዋን ለመቅረፍ በሚል አባባይ ቃል የታገዘው የማኅበሩ አካሄድ ግቡ ቤተክርስቲኒቱን በማኅበሩ መተዳደሪ ደንብ እንድትመራ ማድረግ ሲሆን ዶግማዋም ቀኖናዋም ማኅበሩ እንዲሆን የሚያስገድድ አካሄድ እየተከተለ መሆኑ የአደባባይ ሚሥጢር ሆኗል፡፡
የአንድ ተቋም ትክክለኛነት ከሚለካበት መንገድ አንዱ ህጋዊ መዋቅሮችን አክብሮ መንቀሳቀስ መቻሉ ነው፡፡ ያለ ሕጋዊ መዋቅር ህግ እና እውነት የበላይነት ይዘው መቀጠል የማይችሉ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግን ህግ የት እንዳለ የሚያስታውሰው ሌሎችን ለመምቻ የሚጠቅመው ከሆነ ብቻ ነው፡፡ የማኅበሩን ፍላጎት ለማስጠበቅ  ግን እስካዋጣው ድረስ በህጋዊ አሰራር እሱም ካላዋጣ የወንጀል ድርጊቶችን ጨምሮ የትኛውንም ህገ ወጥ አካሄድ ለመጠቀም ወደ ኋላ የማይል ድርጅት መሆኑን እስካሁን ያሉት ተሞክሮዎቹ ያስረዳሉ፡፡