Thursday, August 9, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን ምንቸት ግባ፤ ማኅበረ ቅዱሳንን የምትቃወም ምንቸት ውጣ!!!



ብጹእ አቡነ ገብርኤልን ከአስመራ ሊቀጵጵስና ዘመናቸው ጀምሮ ስለእሳቸው በሲኖዶሱ አካባቢ የተባለውን ነገር ብዙ ብዙ ሰምተናል። ከዓመታትም በኋላ ምድረ አሜሪካ ከኮበለሉ በኋላም  ቢሆን ወያኔ ወይም ሞት ብለው ከተቃውሞ ጎራ መሰለፋቸውን በተለያዩ ሚዲያዎች አይተናል። አቡነ ጳውሎስን ቤተክርስቲያን እንደገባች እንትን…….  ሙልጭ አድርገው ሲያክፋፉ ተመልክተን፤ እንዴት ተደርገው ቢበደሉ ይሆን? ሊቀ ጵጵስናቸውን ግምት ውስጥ እስኪያገባ ድረስ ለዚህ ዓይነት አንደበት የበቁት ብለን ታዝበንም ነበር። በእርግጥ ይህ ተቃውሞ ሰልፍ በአሜሪካ ውስጥ እንደፖለቲካ ስደተኝነት የመኖሪያ ፈቃድ ለማስገኘት የሚያስችል የመረጃ ማጠናከሪያ መንገድ በመሆኑ ጥሩ ጥበብነቱን አድንቀን ተቀብለንላቸዋል።
የመኖሪያ ፈቃድ ማግኘት ከተቻለና የግል የገቢ ካፒታልን ማሳደግ የሚያስችል የቤተክርስቲያን ምስረታ ከተጠናቀቀ በኋላ ያገኙትን ገንዘብና ዝና ከጥሩ ነፋሻ አየር ጋር በነጻነት ለመተንፈስ ደግሞ በትውልድ ሀገር ኢትዮጵያ ውስጥ እንደመኖር ተመራጭና ለሚዛን የሚደፋ ሌላ ስፍራ ባለመኖሩ ብጹእ አባታችን አውጥተው፤ አውርደው ሁኔታዎችን ሲጠብቁ  የአሜሪካው ሲኖዶስ የጳጳሳት ሹመት የሚሰጥበትን ጥሩ አጋጣሚ ተጠቅመው ወደ ውጤት በመቀየር፤ ሲኖዶስ ማለት በአቡነ ጳውሎስ የሚመራው ነው በሚል የተለመደ የተቃውሞ ጥበባቸው ከፓትርያርኩ ጋር የመደራደሪያ ሰነድ ለመጨበጥ ችለዋል።  በተቃዋሚነት ሰልፍ በመውጣት የመኖሪያ ፈቃድ ማግኘት እንደቻሉት ሁሉ፤ የአሜሪካውን ሲኖዶስም በመቃወም፤ ሲዘልፏቸው የነበሩትን የአባ ጳውሎስን ፓትርያርክነት 3600/ሶስት መቶ ስልሳ ዲግሪ/ ተገልብጠው ከእሳቸው ወዲያ ማንም የለም በማለታቸው ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ አዲስ የመኖሪያ ፈቃድ አግኝተው ሀገር ቤት መመለሳቸውን አይተናል። ባንድ ጊዜ ሁለት መኖሪያ ፈቃድ ማግኘት ብልጠትንና የታክቲክ ስፖርትን ማወቅ ይጠይቃል።
ስለእሳቸው ባህርይ መምህር ጽጌ ስጦታው «ይነጋል» በሚለው መጽሐፉ «ዘክልዔ ልብ» ሲል በደንብ አድርጎ የገለጸበት ነገር በእውነትም አንድ ቦታ የማይረጉ እንደዓሳ ጎበዝ ዋናተኛ መሆናቸውን ነው ።
አባ ገብርኤል ምንም እንኳን በክብር ደረጃቸው ጳጳስ ቢሆኑ ስህተት የማይጎበኛቸው ፍጹምና ቅዱስ መልአክ እንዳይደሉ ስለምናምን፤ በተሳሳቱት ነገር ተጸጽተው ለደረጃቸው የሚመጥንና ሌሎችም እሳቸው መልካም ነገር እንዳላቸው በማመን ሊማርና ሊመሰክርላቸው እንዲችል ቢያደርጉ የሚጠላ ማንም ባለመኖሩ አየር ጠባዩ ሲደብር ወደ አሜሪካ መሄዳቸውና አየር ጠባዩ ደግሞ ሲስማማቸው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን በራሱ እንደስህተት አይቆጠርም።
ይሁን እንጂ አባ ገብርኤል ሀገር ቤት ከተመለሱና ወደ ሀዋሳ ከዘለቁ በኋላ ግን እየሆነ ያለውና የሚታየው ነገር ጥሩ እንዳልሆነ መታየት ከጀመረ ሰንብቷል። አባ ገብርኤል የሃዋሳ ሕዝብ ሊቀ ጳጳስ እንጂ የማኅበረ ቅዱሳን ሊቀ ጳጳስ  እንዳልሆኑ እየታወቀ፤  የሥራቸው መጀመሪያ አድርገው የፈጸሙት ነገር አስገራሚ ነበር።  «ማኅበረ ቅዱሳንን የምትቃወም ምንቸት ውጣ፤ የማኅበረ ቅዱሳን ምንቸት በኔ ሀገረ ስብከት ግባ» የሚል ቡራኬ ለመስጠት ጊዜ አልፈጀባቸውም። ሸምቆ ወጊው ማኅበር በዚህ ቡራኬ ያገኘውን ፈቃድ አሜን ብሎ በመቀበል፤ እነ እገሌን ምቱልኝ፤ እገሌንም ውጉልኝ ለማለት ጊዜ አልፈጀበትም። ይህ ነጋዴ፤ ከፋፋይ፤ መሰሪ፤ ሸቃጭና አስመሳይ ማኅበር እንደ ባህር ዓሳው/ Octopus/ ሰላሳ የመርዝ ጭራውን እያወራጨ፤ የቤተክርስቲያን ልጆችን ከመድረክ አስወገደ። ከሥራ አባረረ። ሺዎች እስከዛሬ ድረስ ከቤተክርስቲያን ተሰደው በየቤታቸው ተቀምጠዋል። ለጸሎትና ለጋራ የመማማር መድረክ እንኳን የግልና የህዝብ አዳራሾችን ለመጠቀም ተገደው ይገኛሉ። አባ ገብርኤል ስለነዚህ ተሰዳጆች ሲጠየቁ ምን የሚሉ ይመስሏችኋል? ጥቂት አፈንጋጮች!!!!!!!!!!
እውን እዚህ ፎቶ ላይ በአንድ ወቅት የተሰበሰቡትና በማኅበረ ቅዱሳን መሪነት አባ ገብርኤል ያባረሯቸው ምእመናን ጥቂቶች ናቸው?
የፎቶ ምንጭ፤dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com

Sunday, August 5, 2012

ማሕበረ ቅዱሳን( ማኅበረ ሰይጣን) ጉባኤ አርድዕት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ከማንም በላይ ስጋት ላይ ጥሎኛል በማለት ለጳጳሳቱ 2.5 ሚሊዮን ብር በመበጀት የእግድ ደብዳቤ እንዲዘጋጅ አስደርጓል ተባለ።


ሐምሌ 30 2004 .. ዐውደ ምሕረት/ www.awdemihret.blogspot.com / www.awdemihret.wordpress.com) የቅርብ ምንጮቻችን እንደገለጡትጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተሰኘው በአገር ውስጥና በውጭ አገር ባጭር ጊዜ በርካታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን እየማረከና እያስከተለ የመጣውን ጉባኤ ለማሳገድ ማኅበረ ቅዱሳን ለጳጳሳቱ ጉርሻ የሚሆን 2.5 ሚሊየን ብር በጀት መደበ፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የገንዘብ ምንጩ ከምን እንደሆነ እንዳይታወቅ እና ኦዲት እንዳይደረግ የሚታገለው ገንዘቡን እንዲህ ላለው ሕገ ወጥ ተግባር በስፋት ስለሚጠቀምበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ የቤተክርስቲያኒቱ ከፍተኛ የአመራር አካላትና ከፍተኛ ሊቃውንትን ማዕከል ያደረገው ጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ በከፍተኛ ደረጃ እያካሄደው ባለው ቅዱስ ተግባር ምክንያት የማሕበሩ ደጋፊ የሆኑት ጳጳሳት ካህናት ሰባክያንና ምእመናንን ቀልብ እየሳበ በመምጣቱ ማኅበረ ቅዱሳንን የተለመደውን ድጋፍ እንዳያገኝ  እያደረገው መምጣቱ ታውቋል።
ከዚህ በፊት ሁሉንም የቤተክርስቲያኒቱ አካላት በተለያየ መንገድ እየከፋፈለ ቤተክርስቲያኒቱን ለውድቀት እያፋጠነ የቆየውና ያለው ማሕበረ ቅዱሳን በተለይ በአሁኑ ሰዓት ከአክራሪዎችና ከፖለቲከኞች ጋር ግንባር በመፍጠር እያካሄደ ያለውን እኩይ ተግባር እየተጋለጠበት በመምጣቱና በአገር ውስጥና በውጭ አገርም ከፍተኛ ኪሳራ እየደረሰበት በመምጣቱ ከዚህ ያድኑኛል ያላቸውን አቶ እስክንድር ገብረክርስቶስንና አቶ ተስፋዬ ውብሸትን(የጠቅላይ ቤተክህነት /ሥራ አስኪያጅ) በመደበው በጅት በመደለል  በዋና ሥራ አስኪያጁ በአቡነ ፊልጶስ እና በቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ አቡነ ሕዝቅኤል አማካኝነትጉባኤ አርድእትንአናውቀውም ይታገድልን የሚል ደብዳቤ እንደሚያጽፉ የውስጥ ምንጮቻችን ገልጸዋል።

 ከዚህ በፊት እንደገለጽነው አቶ እስክንድር  ከመንግሥት ሥራ ከተባረረ በኋላ ሙሰኞች ወደ የማይባረሩባት ቤተክህነት በመግባት ከግብረ አበሩ ጋር በመሆን ከፍተኛ ምዝበራ እየፈጸመ ያለ ግለሰብ ሲሆን በተለያየ ጊዜ ከማሕበረ ቅዱሳን የአመራር አካላት ጋር ባደረገው ስብሰባ ጳጳሳቱ የግል ቤት በመገንባትና በተለያየ ሥራ የተጠመዱ በመሆናቸው ገንዘብ ስለሚያስፈልጋቸው ለሁሉም የሚከፋፈል 2.5. ሚሊዮን  ብር ከመደባችሁ የእግድ ደብዳቤ ማጻፍ ይቻላል በማለት የማኅበረ ቅዱሳንን ሰዎች  ያሳመነ ሲሆን ጉባኤ አርድእትንም የሚመለከተውን የእግድ ደብዳቤ ለማጻፍ ቅድመ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ ታውቋል። ገንዘቡን ለማግኘት  እነ አቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስና አቶ ተስፋዪ ውብሸት  የተጠቀሙበት ዘዴ አሁን ማሕበሩ  ይህንን ካላደረገ  ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት ጉባኤው የጉባኤ አርድእትን መተዳደሪያ ደንብ ያጸድቅለታል። የሚል ሲሆን ይህም ከጉባኤ አርድእት ዓላማ ውጭ እንደሆነ ታውቋል። ምክንያቱም በጉባኤ አርድእት መመስረቻ ጽሑፍ እንደተገለጸው ጉባኤ አርድእት ጉባኤና የቤተክርስቲያኒቱ አካል በመሆኑ በአሏት ሕገ ደንቦች የሚመራ እንጂ  ማሕበር ስለአይደለ የሚጸድቅም ሆነ የሚታገድ መተዳደሪያ ደንብ ስለሌለው ነው፡፡
በመሆኑም  ሐሳብንም ሆነ መንፈስን ሊያግድ የሚችል አካል ስለሌለ ጉባኤው ሊታገድ የሚችል ነገር የለውም። የጉባኤ አርድእትን ራእይ ተልእኮና ዓላማ አግዳለሁ የሚል ካለ በአጠቃላይ የቤተክርስቲያኒቱን ሊቃውንትን ካህናትን ሰባክያንንና ዲያቆናትንን ከቤተክርስቲያኒቱ አስወግዳለሁ ብሎ እንደ መነሳት ነው።

Saturday, August 4, 2012

በድንግል ማርያም ትንሣዔና እርገት ታሪክ ላይ ችግር አለ!


ቅዱሳንን ስለማክበር ምንም ጥያቄ የለንም። መታሰቢያ ማድረግም የነገሮችን ሁሉ ባለቤት እስካልተካ ድረስ የሚደገፍ ነው። ነገር ግን  «ጥቂት አሻሮ ይዞ፤ ዱቄት ወዳለው መጠጋት» የሚለውን ብሂል ለመተግበር መሞከር ግን ተቀባይነት አይኖረውም። በተለይም በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ወቅት ወንጌል እንደዚህ ስለሚል፤ እኔም እንደዚህ ብል ችግር የለውም የሚለውን ራስን መሸሸጊያ ምክንያት በማቅረብ ለመከለል መሞከር አያዋጣም። ብዙ ጥያቄዎችን የሚያስነሱትና እነዚህ የመሳሰሉ የስህተት ችካሎች አልነቀል ያሉት በምክንያት ስር በመወሸቃቸው ነው። ራሱን የማርያምን እረፍትና ትንሣዔ ሳይሆን በማርያም እረፍት፤ ቀብር፤ ትንሣዔና እርገት ላይ ያሉ አስተምህሮዎችን ለመቃኘት እንሞክራለን።
ስለማርያም እረፍት፤ ትንሣዔና እርገት አብያተ ክርስቲያናት አንድ ዓይነት የእምነት አቋም የላቸውም። እንዲያውም ስለማርያም ሞትና የእርገት ዕለት በግልጽ የሚታወቅ ማስረጃ እንደሌለ በ5ኛው ክ/ዘመን  የኖረው የሳላሚሱ ኤጴፋንዮስ   ተናግሯል። [ 1 ] ዕረፍቷና እርገቷ በኢየሩሳሌም እንደሆነ  የሚናገሩ ቢኖሩም  ይህንን አባባል የማይቀበሉ አብያተ ክርስቲያናትና የቴኦሎጂ ምሁራን ሞልተዋል። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚለውን አባባል የማይቀበሉበትን ማስረጃ ሲያቀርቡም ዮሐንስ በወንጌሉ ላይ እንደተናገረው «እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት»  ዮሐ19፤27 ባለው መሠረት ማርያም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ድረስ ከዮሐንስ ጋር ስለኖረችና ወንጌላዊው ዮሐንስም ከጌታ ሞት በኋላ በኢየሩሳሌም  ጥቂት ዓመታትን ከቆየ በኋላ በ37 ዓ/ም ገደማ ወደ ቤዛንታይን ከተማ ኤፌሶን ሄዶ ወገኖቹን ወንጌል እያስተማረ መቆየቱንና  ማርያም በሞት እስከተለየችው ድረስ  ከ48-52 ዓ/ም እዚያው እንደነበር ብዙ ተጽፏል። ከማርያም ክፍል ትይዩ ያለው የዮሐንስ መኖሪያ ቤት ፎቶ፤

 በኋላም  በቅርብ ርቀት ባለችው ደሴተ ፍጥሞም  በግዞት መኖሩ ይነገራል ።  አንዳንዶች ከዶሚኒሽን አገዛዝ ቀደም ብሎ የራእይ መጽሐፉን  ከ55-65 ዓም ገደማ እንደጻፈም  ይናገራሉ።
ዋናው ነገር  ማርያም በኤፌሶን ከዮሐንስ ጋር ኖራለች  ወይስ አልኖረችም ነው ጥያቄው።  በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚሉ ሰዎች አንድም ጊዜ ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን ኖራለች ሲሉ አይደመጥም። ለምን?  ዮሐንስ ማርያምን እንደእናት ሊይዛት አደራ ተሰጥቶታል የሚባል ከሆነ ከዮሐንስ ጋር ኤፌሶን ስለመቀመጧ የማይነገረው ለምንድነው?  ዮሐንስ እስከ 96 ዓመቱ ድረስ ከኤፌሶንና ከደሴተ ፍጥሞ ውጪ ስለመኖሩ የተነገረ ነገር የለም። ማርያም ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን አልኖረችም ብሎ በመከራከርና በኢየሩሳሌም ኖራ፤ እዚያው ማረፏን በግልጽ በመናገር  መካከል ልዩነት አለ።  «እነኋት እናትህ» ባለው መሰረት አብረው ኤፌሶን ኖረው እዚያው ማረፏን የማይቀበሉና  ኢየሩሳሌም ኖራ አርፋለች የሚሉ ሰዎች እንደልጅና እናት አብረው የመኖራቸውን የወንጌል ቃል መካድ ሊሆንባቸው የግድ ነው። ያ ደግሞ እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ በኢየሩሳሌም ኖራ እረፍቷም፤ ቀብሯና እርገቷ ሆነ ከሚለው አስተምህሮአቸው ጋር «እነኋት እናትህ» የሚለው  የወንጌል ቃል ስለሚጋጭባቸው ለዚህ ዓይነት ያፈጠጠ እውነት ምን እንደሚሉ አይታወቅም። ወይ ደግሞ ኤፌሶን ላይ እድሜውን ሙሉ የኖረው ዮሐንስና ኢየሩሳሌም ማርያምን ይዞ የኖረው ዮሐንስ የተለያዩ ናቸው ሊሉ ይገባል።
ሮበርት ክሬው የተባለ የነገረ መለኮትና የታሪክ ጸሐፊ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዘመኑን ሁሉ በኖረበት ከኤፌሶን ከተማ 8 ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ ባለች ኰረብታ ላይ በተሰራ ቤት ውስጥ እንደኖረና ማርያምም እዚያ ማረፏን ጽፏል።  ይህንን በኤፌሶን ያለውን የማርያምን መቃብር የዓለም ክርስቲያኖች እንዲሆም ሙስሊሞች ሳይቀሩ ይጎበኙታል፤ ይሳለሙታል።  በቱርክ ግዛት ያለው ይህ ስፍራ በቱርካውያን ሙስሊሞች ዘንድ «ሜሪዬማና» ተብሎ ይጠራል።  ይህ ስዕል የሚያመለክተው ያንን ስፍራ ነው።

ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም የተለየችው መቼ ነው? ለሚለው ጥያቄ ጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት የምሥራቁና የምዕራቡ ጎራዎች የተለያየ አመለካከት አላቸው።
 በተወለደች በ58 ዓመቷ ዐርፋለች የሚሉ አሉ። በ72 እና 63 እድሜዋም አርፋለች የሚሉ መረጃዎች አሉ። እንደ ግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ግን የሚታመነው በ64 ዓመት እድሜዋ ማረፏ ነው።  ኖረችበት ተብሎ ከሚገመተውና አርፋለች ከሚባለው ቦታ ያለው ልዩነት እንዳለሆኖ በጥር ወር ከዚህ ዓለም ተለይታ በ40ኛው ቀን ማረጓን የሚናገሩ አሉ። በነሐሴ ወር አርፋ ከተቀበረች በኋላ ትንሣዔዋን ሳያዩ መቃብሯ ባዶ ሆኖ ስላገኙት ሐዋርያት ሱባዔ ይዘውበሦስተኛው ቀን ተገለጸችላቸው የሚሉም አሉ። እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ደግሞ በጥር ሞታ፤ በነሀሴ ተቀበረች የሚል ትምህርት አለ። በጥር ወር አርፋ፤ በነሀሴ ተቀብራለች የሚሉ ሰዎች ሥጋዋ በገነት ዛፍ ስር ለስምንት ወራት መቀመጡንና በሱባዔ ጸሎት በተደረገው ልመና የተነሳ ለመቀበር መቻሏን አስፋፍተው ይነግሩናል።