Tuesday, July 17, 2012

የዳላሱ አቡነ አረጋዊ የማቅ ወኪል ቄስ፤ ከግንድ ላይ ተገንጥሎ በኪራይ ቤት ውስጥ ተተከለ!

የዳላስ ደ/ፀሐይ አቡነ አረጋዊ ወተ/ሃይማኖት ቤተክርስቲያን የፊት ገጽታ

በመሠረቱ ቤተክርስቲያንን ለመንፈሳዊ አገልግሎት ማቋቋም ቀና ሃሳብ መሆኑ አይካድም። ጥፋት የሚሆነው አንዲቱን ቤተክርስቲያን ለማዳከምና ምእመናን በቡድን ለመከፋፈል ሲባል ከሆነ የመንፈሳዊ ተግባርን እሳቤ በማደብዘዝ ስውር ዓላማን ለመፈጸም መንፈሳዊ ካባን የደረቡ ወረበሎች የሚጠቀሙበት ስልት መሆኑ እየታየ ነው። እናም ቄስ መሥፍን ማሞ የተባለው የዳላስ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል የነበረው ግለሰብእ የተሰጠውን የማቅን ተልእኰ አንግቦ በኅቡእ የቆየ ቢሆንም ሰዓቱ ሲደርስ ከዛሬ ጀምሮ ተገንጥያለሁ ማለቱ ተሰምቷል።
በኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ  ያለ ዋና ሲኖዶስ ፤ በስደት ያለ ዋና ሲኖዶስ እና  አሁን ደግሞ በፓትርያርክ ማኅበረ ቅዱሳን የሚመራ አዲስ ሲኖዶስ በምድረ አሜሪካ እየተገነጠለና ራሱን እያራባ ወደ ሦስትነት እያደገ ይገኛል።
በዳላስ አቡነ አረጋዊ ወተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል የሆነው የማኅበረ ቅዱሳኑ ታማኝ ሎሌ ለመገንጠልና በይፋ አውጆ በ5000 ዶላር ቤት ተከራይቶ የወጣ ሲሆን  መነሻ ምክንያት  የሆነው ነገር ሲቃኝ እንዲህ መሆኑን ምንጮቻን አረጋግጠዋል።
በታህሳስ ወር ገደማ በአዝማሪ መዘምራን ሴቶች የታጀበና በገበሬ አስደንግጥ ስብከቱ ስሙዓ ዜና  በሆነው ዳንኤል ክብረት የተመራው ከፍተኛ የማኅበረ ቅዱሳን የልዑካን ቡድን ጥቂት መርዝ ነስንሶ፤ ብዙ ምርት ማፈስ በሚል መርህ በሄዱበት የ3 ቀናት ዘመቻ ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ወቅት ከዳህጸ ልሳን በዘለለ የተነገረው ዲስኩር ለችግሩ መነሻ ምክንያት ሆኗል። ይኼው ቄስ መሥፍን የተባለው የማኅበረ ቅዱሳን አባል የደብሩ ስብከተ ወንጌል ኃላፊ እንደመሆኑ መጠን አዝማሪ መዘምራኖቹና ገበሬ አስደንግጥ ሰባኪያኑ ከደብሩ እንዲገኙ ሁኔታዎቹን በማመቻቸት ግንባር ቀደሙ ሰው ነበር።
በስብከቱ መድረክ ራሱን የሰየመው ዳንኤል ክብረት ወንጌልን እንዳያስተምር ያልዋለበት በመሆኑ በወግ ጥረቃና በምሳሌያዊ ተረት ዘመኑን የጨረሰ በመሆኑ የሚናገረው  ቢጠፋበት የተቆጣጠረውን መድረክ በመጠቀም  ሀገር ቤት አፍኖ የቆየውን የፖለቲካ  ትኩሳት አሜሪካ ሲደርስ እስኪበቃው ድረስ ሲተነፍስበት መታየቱ በምእመናኑና በደብሩ ካህናት በኩል ተቀባይነት ሳያስገኝለት  ከመቅረቱም በላይ የስብከት መድረክ የእግዚአብሔር መንግሥት የሚነገርበት እንጂ የግል ስውር ዓላማንና የፖለቲካን ትኩሳት ማስተላለፊያ መንገድ እንዳልሆነ በደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ታደሰ አርአያ በሀዘኔታ መገለጹን ተሰምቷል። 
ዳንኤል ክብረት በወቅቱ ወዴት እንሂድ? ኢትዮጵያ ውስጥ ታፍነን ተሰቃየን እኰ? ዝምታው እስከመቼ ነው? ወዘተ የሚሉ ቅስቀሳዎችን ሲያስተላልፍ የደብሩ አስተዳዳሪም የዳንኤልን  «ሁሉም ነገር ወደጦር ግንባር» ዓይነት ስብከቱን በመቃወም አሁን ይሄ ስብከት ነው? በባእድ ሀገር ለሚገኝ ምእመንና ምእመናት ከአንድ ሰባኪ የሚሰጥ የሕይወት   ቃል ይሄ ነው? ዓላማን ለይቶ ወደ ፖለቲካው መግባት አለበለዚያም ምእመናንን የሚያጽናና ትምህርት መስጠት ሲገባ ይህን ሁሉ ሀገር አቋርጣችሁ ከመጣችሁ በኋላ ህዝብን መቀስቀስ ተገቢ አይደለም ሲሉ ሀዘኔታቸውን ገልጸዋል።  ቤተክርስቲያን የሚመጣ ደጋፊም፤ ተቃዋሚም እንደመሆኑ መጠን ቤተክርስቲያን ማስተማር የሚገባት ሁሉንም የሚያንጽ እንጂ የአንድ አቅጣጫን ዓላማ ማስተጋቢያ መሆን የለበትም የተባለ ሲሆን የገበሬ አስደንግጡ ስብከት ውድቅ ተደርጓል። ማቅና ገበሬ አስደንግጥ ሰባኪያኑ ዳግመኛ እንዳይመጡ በመነገሩ ይህ ለማቅ ትልቅ ኪሳራ ሆኖ  ነበር።
የማቅ ታማኝ አገልጋያቸው የደብሩ ስብከተ ወንጌል ቄስ መስፍን ገበሬ አስደንግጦችን በማሰባሰብና በማስጮህ ብዙ የለፋበት የማቅ አገልግሎት ዋጋ በማጣቱና ተቀባይነት ባለማግኘቱ ውስጥ ውስጡን ሲቆስል ቆይቶ ከነፍስ አባቱ ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ከመከረ በኋላ የደብሩን አስተዳዳሪ፤ ካህናትንና ማኅበረ ምእመናንን ቆይ ሳንሰራላችሁ ብንቀር በሚል ብቀላ አዲስ ቤት በአምስት ሺህ ዶላር ገደማ ተከራይተው እዚያው በቅርብ ርቀት የተተከለ ሲሆን ይህም በፓትርያርክ ማኅበረ ቅዱሳን የሚመራው ሦስተኛው ሲኖዶስ መሆኑ ነው።
ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ ሀገረ ስብከቱ በአቡነ ፋኑኤል የሚመራ መሆኑ እየታወቀ የሀገር ቤቱን ሲኖዶስ ከድተው ማኅበረ ቅዱሳን ቤት ተከራይቶ ሲያትል በሚያኖራቸው የሶስተኛው ሲኖዶስ ቋሚ አባል በሆኑት በአቡነ ኤዎስጣቴዎስ በኩል የቄስ መሥፍን ቤት ተመርቆ መከፈቱ ነገሩን አስገራሚ ያደርገዋል። በእርግጥ ሦስተኛውን ሲኖዶስ በምድረ አሜሪካ ቤቶችን በመክፈት ላይ የተጠመደው ማቅ ምንም ሀገረ ስብከት የሌላቸውን አቡነ ኤዎስጣቴዎስን ቤት ተከራይቶ ማስቀመጡ ምናልባት የአሜሪካ ፓትርያርክ አደርግዎታለሁ የሚል ተስፋ ሰጥቷቸው ይሆናል። በዚያ ላይም ለማቅ  አልገዛም፤ አልታዘዝም ያሉትን አቡነ ፋኑኤልን ለማናደድ ጭምር የተጠቀመበት የግንጠላ ስልት ሲሆን  ካከራየበት ቤት ጎትቶ በማምጣት ጳጳሱ ታዛዥነታቸውን ማሳየታቸው  ነገሩን አስገራሚ ያደርገዋል። አቡነ ኤዎስጣቴዎስም የጵጵስና ማእረግ ወንድማቸውን ለማቅ ደስታ ሲሉ መጥላታቸውና ሕገ ቤተክርስቲያንን ማፍረሳቸውን ስንመለከት እንዲህ ብለንለመጠየቅ እንገደዳለን።  እሳቸው ከጣሱት የትኛውን ህገ ቤተክርስቲያን  ተግባራዊ ለማድረግ ነው የጰጰሱት እንላቸዋለን?
አንዳንድ የማቅ ደጋፊዎች አቡነ ፋኑኤልም  በአቡነ አብርሃም ላይ እንደዚሁ ሰርተዋል በማለት ሊሞግቱ ይፈልጉ ይሆናል።
ያለፈ ጥፋት  ካለ፣ ላሁኑ ጥፋት እንደትክክለኛ መከራከሪያ ሆኖ ሊቀርብ አይችልም።
 ጎረምሳው ቡድን የራሱ ዓላማ ያለው ሲሆን ጳጳሱ ደግሞ  የራሳቸውን የሲኖዶስ ዓላማ ጥለው ለማቅ ዓላማ ስኬት መዞራቸው ያሳዝናል። ዘወትር የአቡነ ፋኑኤልን ስም በየድረ ገጾቹ  እያነሳ የሚያጨልማቸው አልበቃ ብሎት፤ አቡነ ኤዎስጣቴዎስን ወስዶ በአቡነ ፋኑኤል ሀገረ ስብከት ላይ ቤት እንዲመርቁ ያደረገው እርር ድብን ላድርጋቸው ብሎ እንጂ  ሕገ ቤተክርስቲያን ያንን እንዲያደርግ የሚፈቅድ ሆኖ አልበረም። ነገሩ ባልበላውም ልድፋው ነው! 

Monday, July 16, 2012

በመልካም መበደል



                       የጽሁፍ ምንጭ፤ ቤተፍቅር/www.betefikir.blogspot.com/
 

         ከምድራችን ጩኸት አንዱ የመልካም ያለህ የሚለው ነው፡፡ በጎውን ማድረግ ሰው የተፈጠረበት ዓላማ ሆኖ ሳለ ዛሬ አንድ መልካም ማግኘት የአንድ በዓልን ያህል የሚያስቦርቅ ሆኖአል፡፡ በእርግጥም በክፉ በተያዘው ዓለም ክፉዎች አይደንቁንም፡፡ ጥሩ ነገር ከሰዎች ልቦና በተንጠፋጠፈበት፣ ለዓመጽ የተዘረጉ፤ ለመታደግ የታጠፉ እጆች በበረከቱበት፣ ለመርዶ የሚፋጠኑ፤ ለምስራች ሽባ የሆኑ እግሮች በሚስተዋሉበት፣ አደበት ሁሉ ስንፍናን አብዝቶ በሚያወራበት ዓለም መልካምነት ጌጡ የሆነ ሰው ሲገኝ ከዚህም በላይ ያስደስታል፡፡ ልብ ብለነው ከሆነ ግን መልካም መሆን፤ በጎ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በዚያ መልካም ላለመበደል፣ በዚያ በጎ ላለመሳት መጠንቀቅም እንደ እግዚአብሔር አሳብ ሊኖሩ ለሚፈልጉና ከሕሊና ውቅሻ ማምለጥ ለሚሹ ሁሉ የተገባ ነው፡፡
        አብዛኛውን ጊዜ በውጪው ዓለም ላይ በሥራ የሚሰማሩ ወገኖቻችን የኑሮአቸውን ያህል የሚኖሩት ለቤተሰብና ለዘመዶቻቸው ጭምር ነው፡፡ አንዳንዴም የራሳቸውን እስኪረሱ ለቤተሰብ የሚኖሩ፣ የሚለፉ ሰዎችን አስተውለናል፡፡ አገር ቤት ያለውን ነገር ስንመለከተው ደግሞ በእህትና ዘመድ ልፋት ሳይማሩ፣ ሳይሠሩ፣ ሳይጥሩ የሰው ወዝ ባመጣው የሚኖሩ ወጣቶችንና ወላጆችን ታዝበናል፡፡ ነገር ግን ረጂዎቹ አስተውለውት ከሆነ በመልካምነት እየበደሉ ነው፡፡ መስጠት ስላለብን እንጂ ብር ስላለን ብቻ አንሰጥም፡፡ መርዳት ስላለብን እንጂ መርዳት ስለቻልን ብቻ አንረዳም፡፡ ምናልባት ይህንን ከመንፈሳዊው ጎን ተመልክታችሁ ልክ ያልሆነ አባባል እንደሆነ ሊሰማችሁ ይችል ይሆናል፡፡ ዳሩ ግን መንፈስ ሁሉን ይመረምራል፡፡ የእግዚአብሔር አሳብም ሞኝነትን አያበረታታም፡፡ ሁሉን ለማነጽ እንድናደርገው ታዘናል፡፡

Saturday, July 14, 2012

ማኅበራት የክፍፍል መድረኮችና የሁከት ምንጮች ሆነው እያስቸገሩ ነው!



ከወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አካባቢ ሰሞኑን «ጉባዔ አርድእት» የሚባል ጊዜያዊ ማኅበር ይቋቋማልን እንደማንኛውም ሰው ሰምተናል። እኛን ግራ የገባን ይህ «ጉባዔ አርድእት« የተባለው መቋቋሙ ሳይሆን ከተቋቋመ 20 ዓመቴን ሞልቻለሁ የሚለው ጎረምሳው ማኅበር ማቅ ግን ሽብር የገባበት ምክንያት አስገራሚ መሆኑ ነው። 

ሁለት ነገር እንድናነሳ ተገደድን። አንደኛ ማኅበሩ ከእኔ ወዲያ ሌላ ማኅበር አያስፈግም  የሚል የጽንፈኝነት ጥግን የታጠቀና በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በእኔ በኩል ያላለፈ መንፈስ ቅዱስ እንዴት እዚያ ይደርሳል? ስለዚህ እፍ! ያላልኩበት  ማኅበር ሊኖር አይችልም የሚል ስግብግብነት የሞላው ጠባብ አስተሳሰቡ ነው።

በአንድ በኩል የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና የቅድስት ሥላሴ ኰሌጅ ደቀመዛሙርት ማኅበራት መኖራቸውን እደግፋለሁ ሲል እየተደመጠ በሌላ በኩል ደግሞ የቤተክርስቲያኒቱ ሊቃውንትና አመራር ላይ ያሉ ሰዎች ስብስብ እንደሆነ የሚነገርለት «ጉባዔ አርድእት» መቋቋምን  ስመለከት ዓይኔ ደም ይለብሳል  ዓይነት ቅናት ከሰይጣን እንጂ ከመንፈስ ቅዱስ ሊሆን አይችልም።
ይህ ይቋቋማል የሚባለው የጉባዔ አርድእት ማኅበር አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ  በሥራ ላይ ያሉ የቤተክርስቲያኒቱ ሰዎች እስከሆኑ ድረስ ማኅበረ ቅዱሳንን ይህን ያህል ያስጨነቀው ለምንድነው?   ቤተክርስቲያኒቱን  ይጥቀምም፤ አይጥቀምም ራሱ ማቅ እንደ ማኅበር የተቋቋመበትን መንገድ ሌሎች የዚሁ መብት ተጠቃሚ የመሆን  መብት እንዳይኖራቸው መጮሁስ ምን ይባላል?

ማንም የሾመው ባይኖርም« ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው እንዲሉ» ራሱን በራሱ ሾሞ  ከጉባዔ አርድእት አባላት መካከል  አንዳንዶቹን በተሐድሶነት ይወነጅላል።  በተለመደ የድራማው ትወና  አፈኞቹን ጉዳይ ፈጻሚዎቹን በደንብ ጭኖና አስፈራርቶ እነዚያ የሚወነጅላቸውን ሰዎች በቀጣይ ጉባዔ እስኪያስወግዝ ድረስ የቤተክርስቲያኒቱ አባላት መሆናቸውን አምኖ መቀበል የግድ ይሆናል። ስለዚህ ጉዳይ ፈጻሚ  አባቶቹ የማኅበሩን ተልእኰ ተቀብለው ውግዘት  እስኪያወርዱ ድረስ በሥራ ላይ ያሉ ሰዎች የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ናቸውና ማቅ ማኅበር ሆኖ እንደሚንቀሳቀሰው ሰዎቹንም ማኅበር እንዳያቋቁሙ የሚከለክላቸው ምንም አሳማኝ ነገር የለም።
ይልቁንም  ማኅበርሩን እንደዚህ ሽብር ውስጥ የከተተውን ነገር ከማኅበሩ ግልጽና  ስውር ዓላማ አንጻር ከታች የተመለከቱትን ነጥቦች ማንሳት እንችላለን።

1/ ጉባዔ አርድእት በቤተክርስቲያን ሙያ የበለጸጉ ምሁራንና በዘመናዊውም የበሰሉ ሰዎች ስብስብ እንጂ እንደ ማቅ አባላት የክብር ቅስና ያልተሸከሙና  የንግድ ግዛት /ኢምፓየር/ ያላቋቋሙ በመሆናቸው፤

2/ የጉባዔ አርድእት አባላት ናቸው ተብለው የሚነገርላቸው ሰዎች አብዛኛዎቹ በቤተክርስቲያኒቱ ከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ የሚገኙና  በሰንበት /ቤት ሽፋን አንድ እግራቸውን እንደማቅ ውጪ ያላደረጉ ስለሆነ፤

3/ በዚሁ በአዲሱ ማኅበር ውስጥ ይካተታሉ የሚባሉት ሰዎች አብዛኛዎቹን ማቅ ሲወጋቸውና ሲያደማቸው የቆዩ በመሆናቸው ውሎ አድሮ የእጄ ይከፈለኛል የሚል ፍርሃት ማቅን ስለሚያስጨንቀው፤

4/ በማኅበረ ካህናቱ ዘንድ «ማቅ፤ ጢም የሌለው አልቃኢዳ» እየተባለ መጠራቱ የሚታወቅ ሲሆን ጉባዔ አርድእት ህልው ሆኖ ከተቋቋመ በአባልነት ይሁን በተሳታፊነት ማኅበረ ካህናቱን ሁሉ ስለሚጠቀልል  መንቀሳቀሻ ስፍራ ያሳጡኛል የሚል ስጋት፤

5/ በሕዝብና በመንግሥት ዘንድ አስቸጋሪነቴ ግልጽ ይወጣል ከሚል ፍርሃት፣

 6/ ተሐድሶ ወይም ጴንጤ እያልኩ የዓይኑ ቀለም ያላማረውንና ለእኔ ያልተንበረከከውን ሁሉ ለማድቀቅ ይቸግረኛል ከሚል እሳቤ የተነሳ፤
7/ የታዛዦቼን ሊቃነ ጳጳሳት ቅስም በመስበርና በማስፈራራት ለአቡነ ጳውሎስ እንዲገዙ በማድረግ የሲኖዶስ ላይ ስውር ድምጼ ይታፈናል፤ አባ ጳውሎስም  ጉባዔ አርድእትን እንደአንድ ኃይል ሊጠቀሙት ይችላሉ ብሎ በመስጋት፤

8/ አሁን ያለኝ እንቅስቃሴ ከጫፍ እጫፍ መድረሱ እክል ሊገጥመው ይችላል ብሎ ለእጀ ረጅምነቱ ከመጨነቅ አንጻር ሲሆን

ከብዙ በአጭሩ ሊነሳ የሚችል ውጥረቶቹ እንደሆኑ እነዚህን ልንገምት እንችላለን። እንዲያውም ከግምት በዘለለ የማኅበሩ አፈቀላጤ የሆነው «ደጀ ሰላም» ማቅ ይደርስብኛል ብሎ ከሚያስበው አንዱን ስጋት እንዲህ ሲል ተናግሯል።

«የአባ ጳውሎስን ዐምባገነንት ለማጠናከር፣ መንፈሳውያን ማኅበራትን ለማፈራረስ፣ የግል እና የቡድን ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ….» በማለት በግልጽ አስቀምጧል።