Sunday, July 1, 2012

አፄ ዓምደ ጽዮንና የኢትዮጵያ አንድነት

ፀሐፊ፤ ሔኖክ ጌትነት

አፄ ዓምደ ጽዮን ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ

ግዛት      ከ1314-1344 ፤  ቀዳሚ ንጉሥ  አፄ ውድም አርእድ(አባት)
ተከታይ ንጉሥ፤  አፄ ነዋየ ክርስቶስ/ ሰይፈ አርእድ ልጅ/
ባለቤት ብሌን  ሳባ/ የባሕረ ነጋሲ ንግሥት/
ሙሉ ስም፤  ገብረ መስቀል
ሥርወ-መንግሥት፤   ሰሎሞናዊ
አባት ፤     ውድም አርእድ
ሀይማኖት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና
ቀዳማዊ አጼ ዐምደ፡ጽዮን (የዙፋን ስም ገብረ መስቀል) ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. የነገሡ ሲሆን በጥንቱ ዘመን ከተነሱ ነገሥታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ሰፋ ያለ አሻራ ትተው ካለፉት (ለምሳሌ፦ ዘርአ ያዕቆብ ) ጎን ወይም በላይ ስማቸው ይጠቀሳል። አጼ ዐምደ ጽዮን የአጼ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅና የአጼ ውድም አርእድ ልጅ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ይኩኖ አምላክ አዲሱን የሰሎሞን ስርወ መንግስት ቢመሰርቱም፣ በልጅ ልጆቻቸው የነበረው ፉክክርና አዲስ ከሚስፋፋው የእስልምና ሃይማኖት የሚሰነዘረው ጥቃት ስርዓቱን ስጋት ላይ የጣለ ነበር። አጼ አምደ ጽዮን ይህን ፉክክር በማስቆምና በዘመናት በማይደበዝዘው ጀግንነታቸው የኢትዮጵያን ድንበር ከሞላ ጎደል አሁን በሚታወቀው መልኩ በማስቀመጥ፣ የአዲሱን ስርወ መንግስት መሰረት በማጽናት እንዲሁም በማረጋጋት ዝናቸው በጥንቱ አለም ክአፍሪቃ ቀንድ እስከ አውሮጳ የተንሰራፋ ነበር።
1/ የአጼ ዐምደ ጽዮን ዘመንና ዘመቻዎች
ዘመቻ ወደ ደቡብ ምዕራብና ሰሜን ኢትዮጵያ
ዓምደ ጽዮን በእንዴት መንገድ ወደ ስልጣን እንደመጡ መረጃ የለም፣ ስለሆነም ታሪክ አጥኝው ታደሰ ታምራት ንጉሱ ከአባታቸው ጋር ትግል ገጥመው ዘውድ ላይ እንደወጡ መላ ምት ያቀርባል ። ንጉሱ በመንግስታቸው መጀመሪያ (፲፫፻፲፮ ዓ.ም. ) የተሳካላቸው ዘመቻዎች በጎጃም፣ ዳሞትና ሐድያ በማድረግ እኒህ አካባቢወች እንዲገብሩ ሆነ[5]። ሆኖም በኒህ ዘመቻወች ትኩረታቸው ስለተሳበ በተገኘው ክፍተት የእንደርታ ገዢ የነበረው ይብቃ እግዚ የአምባ ሰናይት፣ ብልሃትንና ተምቤን ሰራዊትን በማደራጀት በንጉሱ ላይ ተነሳ ። በ1320ዓ.ም ንጉሱ የይብቃ እግዚን አመጽ ከደመሰሱ በኋላ በአምባ ሰናይት የጦር ዕዝ አቋቋመው ወደ ስሜን በመዝመት እስከ ቀይ ባህር ድረስ ያለውን ክፍል ለመቆጣጠር ቻሉ። በዚህ ወቅት እንደርታን እንድታስተዳድር የተሰየመችው የትግሬ ተወላጅ የነበረችው የንጉሱ ሚስት ንግስት ብሌን ሳባ ነበረች። ስልጣኗም ባልታ ብሃት በመባል ይታወቅ ነበር። ቆይቶ እንደርታን እንዲያስተዳድር የተደረገው የንጉሱ ሦሥተኛ ልጅ ባህር አሰገድ በማዕከለ ባህር ማእረግ ነበር፣ ግዛቱም እስከ ቀይ ባህር ወደብ ድረስ የተንሰራፋ ነበር ።

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን፤ ተመራቂ ተማሪዎችን ማደሪያ ከለከሉ!

             
   የጽሑፍ ምንጭ፤ ዓውደ ምሕረት

በቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን ከመመደባቸው በፊት ተማሪዎች ግቢውን መልቀቅ የለባቸውም የሚለውን መመሪያ ጥሰው ተማሪዎቹን ከግቢ አስወጡ፡፡ መነኮሳትን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ማደሪያ አጥተው እየተንከራተቱ ይገኛሉ፡፡ እስከአሁን ደረስ ባለው ሕግ መሰረት ተመራቂ ተማሪዎች ምደባ እስኪደረግላቸው ድረስ በኮሌጁ ውስጥ ማደር መብታቸው ነበር።ተማሪዎቹ ችግራቸውን ለቅዱስ ፓትርያርኩ ያስረዱ መሆናቸው ሲታወቅ እሳቸውም የኮሌጁ የበላይ ጠባቂ እንደመሆናቸው በቤታችሁ ማደር መብታችሁ ነው፡፡ መመሪያውን ማፍረስም አይቻልም ስለዚህ ሂዱ እቤታችሁ እደሩ ብለው ቢያዙም የኮሌጁ ዲን ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡
   በርካታ መነኮሳት ያሉበት ተማሪች ማደሪያ አጥተው እየተንገላቱ መሆኑ የኮሌጁን ማህበረሰብ ጨምሮ በርካቶችን ያሳዘነ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ባለፈው ሐሙስ ምደባ እንደሚደረግ ተነግሮ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች ምደባው ለማክሰኞ መዞሩ በጠቅላይ ቤተክህንት ምክትል ሥራ አስኪያጅ በኩል ተነግሮዋቸዋል፡፡
ነገሩ ግራ የገባቸው ተማሪዎች መብታችን ተነክቷል በማለት ለፖሊስ ጣቢያ ያመለከቱ ሲሆን ፖሊሶች ችግሩን መፍታት ከተቻለ ብለው አቡነ ጢሞቲዎስን ለማነጋገር ቢሞክሩም አቡኑ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡
የኮሌጁ የአስተዳደር ዲን / አባ ሃይለ ማርያምን ችግሩ መፍትሔ ሊያገኝ የሚችልበትን መንገድ ካለ እንዲፈልጉ እንደ አስተዳደር ዲንነታቸውም አንድ ነገር ማድረግ የሚችሉ እንደሆነ ተጠይቀው የነበረ ሲሆን እሳቸውም ከአባ ጢሞቲዎስ ያልተሻለ ምላሽ ሰጥተዋል።መምህራንና  ሌሎች የኮሌጁ ሰራተኞች ከተማሪዎች ጎን ቢቆሙም አቡነ ጢሞቴውና አባ ሃይለማርያም ስላልተስማሙ ግን ተማሪዎቹ ማደሪያ በማጣት በመንገላታት ላይ ይገኛሉ።
ምክንያቱ ይህ ነው ብለው ባልጸገለጹበት ሁኔታ መመሪያንን ሸሮ ቤተክርስቲያን ባሳደገቻቸው ልጆችዋ ላይ ይህን ያህል መጨከንዋ አሳዛኝ መሆኑን ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡

Friday, June 29, 2012

የፍቅር ለይኩን አላማ ማኅበረ ቅዱሳንን መታደግ ወይስ እውነትን መዋጋት?

                               ምንጭ፤ ዓውደ ምሕረት
ፍቅር ለይኩንን በግሌ በጣም አደንቀዋለሁ። በማንኛውም ርዕስ ጽሁፍ ሲጽፍ ነገሮችን በሚያይበት ዕይታ በእጅጉ እመሰጣለሁ። አገር ውስጥ ያሉ መጽሔቶች ለምን አምድ እንደማይሰጡት ሁሌም ግራ ይገባኛል። አገሩን እና ቤተክርስቲያንን የሚወድበትን ፍቅር ያንንም የሚገልጽበትን መንገድም አደንቃለሁ። ነገር ግን ማኅበረ ቅዱሳን ጋር ሲደርስ ሚዛናዊነቱን ሚዛን ያሳጠበት ምክንያት እየደነቀኝ ግን መልስ ልሰጠው ተገድጃለሁ። በመጀመሪያ አባ ሰላማ ላይ በጻፈው ጽኁፍ ካለኝ ከበሬታ አንጻር በዝምታ ላልፈው ብፈልግም ለደጀ ብርሃን የሰጠው የመልስ መልስ ግን ያለመናገር መብቴን ስለገፈፈው በጽኁፉ ላይ ያሉትን ሚዛን ያጣባቸውን ነገሮች ለመተቸት ተገድጃለሁ።
ላለፉት ስድስት አመታት አቡነ ጳውሎስ በዘረኝበት በሌብነት በተሃድሶነት ተጠርጥረው ሲሰደቡ አቡነ ገሪማ አቡነ ፋኑኤል አቡነ ሳዊሮስ ያለስማቸው ስም እየተሰጣቸው ሲሰደቡ ዲያቆን አሰግድ በሀሰት በከፍተኛ ደረጃ ስሙ ሲጠፋ ወንጌል ሰበክ ተብሎ ፓስተር ሲባል መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ለምን እውነትን አገለገልክ ተብሎ በከፍተኛ ደረጃ የስነ ምግባር ጉድለት በተቀነባበረ ካሴት ካደ ሲባል አባ ሰረቀብርሃን በህጋዊ መንገድ ሂዱ ባሉ በጠላትነት ተፈርጀው ሲብጠለጠሉ እነ አእመረ፣ ሀይለጊዮርጊስ፣ ኑብረዕድ ኤልያስ፣ ዲያቆን ትዝታው፣ መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል፣ በሪሁን፣ ተረፈ፣ ያሬድ፣ ታሪኩ……በተለያዩ የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በከፍተኛ ደረጃ ሲብጠለጠሉ እንደ ተራራ የተቆለለው ትዕግስትህ ምነው አውደ ምህረትና አባ ሰላማ በጻፉት ጽሁፍ ጊዜ እንደ ገለባ ክምር ተበታተነ?

በመጀመሪያ አባ ሰላማ ላይ ላወጣኸው ጽኁፍ ለተሠጡህ ጠንካራ አስታየቶች በሰጠኸው ምላሽ እንጀምር “…የመጻፋችን ዓላማ እርስ በርስ ለመተናነጽና ለመማማር እስከሆነ ድረስ መልካም ነው እላለሁ፡፡” በማለት ጀምረሀል ፍቅር እስኪ እንደገና አባ ሰላማ ላይ ያወጣኸውን ጽሁፍ ተመልከተው በርግጥ እሱ ጽሁፍ የመመካከርና የመማማር ለዛ ነበረው? ስድብ ያልከውን ነገር በስድብ ከማወራረድ በቀር ምን አይነት ምክር ጠቅሰሃል? የጻፍከው መቅሰፍት አዘል ማስፈራሪያ መሆኑንስ ትስተዋለህ?  ጽሁፍህ ላይ “…እየተገለጸ ያለው ገመና ጆሮን ጭው የሚያደርግ ነው።…” በማለትህ ግን ሳናመሰግንህ አናልፍህም። አንተም ቢሆን ያልሆኑትን ተባሉ አላልክምና እና ነው። በበኩላችን በጻፍነው ነገር አናፍርም ሀሰትን ላለመጸፍ እንጠነቀቃለን።
ለገመናቸው ሲሉ ግን የቤተክርስቲያን ልጆችን ለማጥቃትና ቤተክርስቲያንን ለማፍረስ የሚተጉትን አባቶችንና የማኅበረ ቅዱሳን አባላትን ብሎጎቻቸው ሊገነቡላቸው የሚፈልጉትን የሐሰት ገጽታ ከመናድና ትክክለኛ ማንነታቸውን ከመግለጽ ግን ወደ ኃላ እንልም። እነዚህ ሰዎች ስለ ራሳቸው ኃጢአት እየተጸጸቱ ንስሀ ከመግባት ባለፈ ንጹሀንን እያሳደዱ ሊገነቡ የሚፈልጉትን ከንቱ ዝና የመግለጽና መንፈሳዊ ሰው መስለው ሌሎችን ለመቃወም የሞራል ብቃቱና መንፈሳዊነቱ እንደሌላቸው እውነትን ለሚፈልጉ አንባቢዎቻችን የማሳየት ግዴታ አለብን።
በአስተያየትህ ላይ “እንግዲህ እግዚአብሔር ያሳያችሁ እኔ የማንንም ግለሰብም ሆነ ብሎግ ስም አልጠቀስኩም፡፡” ብለህ መጻፍህ በጉዳዩ ላይ ሚዛናዊነት እንደጎደልህ ያሳያል። ሌላ አስተያየት ሰጪ በምላሽህ አዝኖ “ሁሉንም ብሎጎች ሳይሆን የጠቀስከው አባ ሰላማን እና አውደ ምህረትን ብቻ ነው። ምሳሌዎችህን በጥንቃቄ ተመልከታቸው። ቀውስ ጦስ ማን ላይ የወጣ ጽሁፍ ነው? የጉድ ሙዳይ ማን ላይ የወጣ ጽሁፍ ነው? ሁሉንም ለመውቀስ ብትፈልግ ሳይሳደቡ ውለው ከማያድሩት ከደጀ ሰላምና ከአንድ አድርገን የሚጠቀስ ምሳሌ አጣህ? ቢያንስ እንድንረዳህ ስህተትህን እመን።” ያለውን ሀሳብ አኔም እጋራለሁ። በኛ በኩል አቡነ አብርሃምን የጉድ ሙዳይ ማለታችንን አናፍርበትም ስለ እሳቸው ጉድ አይደለም ሙሉ ታሪኩን ገና መቅድሙንም አልጻፍነው። ሲጀመር መቼ የተዋህዶ ልጅ ሆኑና ነው። ለእሳቸው እኮ የቤተክርስቲያን ልጆች መወገዝ በጣም ተራ ነገር ነው። የሚመኙት ጠቅላላ ቤተክርስቲያኒቱን ማውገዝ ነው። ሲቀጥል እንዲህ እና እንዲያ ተብለው የሚጠቀሱ እንኳን ከጳጳስ ከአንድ ምዕመንም የማይጠበቁ በርካታ ጉዶች አሉባቸው። በቤተ ክህነት አካባቢ እሳቸው ሲገቡ ጳጳሳቱ  ቀስ እያሉ “ሙዳየ መና ዘጉድ ሙዳየ መና” እያሉ የሚዘምሩላቸው ማንነታቸውን በሚገቡ ስለተገነዘቡ ይመስለኛል።
 ስለአባ ሳሙኤል ስለጻፍነው ጽኁፍ ስትጽፍም እንዲህ ብለሀል “…አባ ሳሙኤልና ሚጡ ተለዋውጠውታል የተባለው ለጆሮ የሚቀፍ ንግግርን በዝርዝር መዘገብ በምን መልኩ መንፈሳዊ ለዛ ያለው ለቤተ ክርስቲያን ህልውና የቆመ ጹሑፍ ሊሆን እንደሚችል አንባቢ ይፍረደው…” ፍቅር እንዴት አድርገህ እንዳነበብከው አናውቅም እንጂ እኛ ግን ሚጡ የተናገረችውን ጸያፍ ንግግር … አድርገን ነው ያለፍነው ለምን አልገለጻችሁትም ከሆነ እና ምን እንዳለች ማወቅ ከፈለክ ግን ሁሌም በጽሁፍ ስር በምትገልጸው ኢሜልህ እንልክልሀን። ነገሩን ከ10 በላይ ምስክሮች እንዳዩት ስለምናውቅና የማኅበረ ቅዱሳን መሳሪያ የሆኑበት ኢየሱስ ክርስቶስ ዋናችን ነው ያለን ሰው ከእነርሱ በቀር ማንም የሚያውቀው በሌለ ፍጹም ስህተት በሆነ ልዩ የውግዘት ሀሳብ ለማውገዝ የደፈሩ ሰው መንፈሳዊነቱ ቢጎል ሰብዓዊነቱ እንኳ ያጡበት ምክንያት ምን እንደሆነ ማሳየት ተገቢ ነው፡፡ ደግሞ ጥፊው ለሳቸውም ለአይዞህ ባያቸው ማኅበር ማኅበረ ቅዱሳንም የእግዚአብሔር ፍርድ መሆኑን እናምናለን፡፡
አስተውለኸው ከሆነ አባ ሰላማ ላይ ከቀረቡት ጽሁፍ ሁሉ በሬሽዎ ሲሰላ ያንተን ጽኁፍ ያህል ብዙ ተቃማዊ ያስተናገደ ጸሀፊ የለም ለምን ይመስልሀል? ምክንያቱም በከፍተኛ ደረጃ ሚዛናዊነት ስላጣህ ነው።
የጳጳሳትን ገመና የምንከድነው እኛ አይደለንም። ወይም እያስፈራራ ያልኩዋችሁን ፈጽሙ አሊያ…የሚለው ማኅበረ ቅዱሳንን አይደለም። እነርሱን ገመና የሚከድነው እውነተኛ ንስሀና ለእውነተኛው የእግዚአብሔር ክብር መኖር ነው። እስከመውለድ ድረስ የገለጡትን ገመና እንዴት አርገን ነው የምንሸፍነው? ልጁን ለካደ ጳጳስ ጌታውን እንደማይክድ ምን ዋስትና አለን? እያደረጉት ያለውንስ ይሄንን አይደለምን?
ፍቅር አንተ ተንጠራርተህ መንካት የፈለከው የማኅበረ ቅዱሳን ተቃዋሚ ብሎጎችን ብቻ ነው። አይንህን ጨፍነህ እንኳን ብታይ በጭላንጭል ውስጥ ከቶውን ልታጣቸው የማትችላቸውንና አንተም ብትሆን  ውሸትነታቸውን ልትመሰክርላቸው የምትችላቸውን በርካታ የስም ማጥፋት ዘገባዎችን የሚያወጡ የማቅ ብሎጎችን በዝምታ አልፈህ የእነርሱን ተቃማዊሞች ግን እወቁልኝ በሚል መንፈስ ስማቸውን ተራ በተራ እየዘረዘርክ ማሻቀልህ አሳዝኖናል። ጽኁፍህ ሰው ምንም ሚዛናዊ ቢሆን ሁሌም በቀላሉ የሚነካ ስስ ብልት እንዳለው  ያሳየ ጽኁፍ ነው።