Wednesday, June 6, 2012

ጥያቄ፤ ገነት እና መንግሥተ ሰማያት ልዩነት አላቸውን?


 by Mihretu
ገነት ወይም Garden ቦታ ሲሆን መንግሥተ ሰማያት/Kingdom of God/  ማለት ግን የእግዚአብሔር አገዛዝ ማለት ነው። የሰማያት ወይም የሰማይ መንግሥት ማለት ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ማለት ነው፡፡

በአብዛኛው በማርቆስ ወንጌል "የእግዚአብሔር መንግሥት" የሚለው ቃል ነው በማቴዎስ ወንጌል "መንግሥተ ሰማያት" የተባለው። ትርጉሙም የሰማይ መንግሥት ወይም የእግዚአብሔር መንግሥት ማለት ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ አዋቂዎች እንደሚናገሩት፤ ማቴዎስ "የእግዚአብሔር መንግሥት" ከማለት ይልቅ "የሰማይ መንግሥት" ወይም በግዕዙ "መንግሥተ ሰማያት" ብሎ የጻፈበት ምክንያት የማቴዎስ ወንጌል የተጻፈው ለአይሁዶች ስለነበርና አይሁዶች ደግሞ "እግዚአብሔር" የሚለውን ስም ደጋግመው መጥራት ያስቀስፋል ብለው ስለሚያምኑ እንደነበር ይናገራሉ (ምክንያቱም በህግ የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ ይላልና)
ጥቅስ፤
የማርቆስ ወንጌል114-15 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።

የማቴዎስ ወንጌል 417 የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ። ከዚያ ዘመን ጀምሮ ኢየሱስ፦ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ እያለ ይሰብክ ጀመር።

የእግዚአብሔር መንግሥት ደግሞ  በደረጃ የምትቀመጥ ቦታ አይደለችም። ነገር ግን የእግዚአብሔር አገዛዝና ፈቃድ የሚፈጸምበት ማለት ነው። ለዚህ ነው በአባታችን ሆይ ጸሎት  "መንግስትህ ትምጣ" ካለ በኋላ ወዲያው "ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን" የሚለው።

Monday, June 4, 2012

ማኅበረ ቅዱሳን እንዲህም ነበር! በቀሲስ መልአኩ


 ካለፈው የቀጠለ.................ክፍል 3

ፕሮቴስታንቶች አንዳችም ሊያደርጉት ያልተቻላቸውንና በሌሎች ሃይማኖት በተከበበች ምድር አስደናቂ እንቅስቃሴ ያደርግ የነበረውን የሰንበት ትምህርት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ በድርጅታዊ ፍቅር ታውሮ የበታተነው ማኅበረ ቅዱሳን በሚል ስም የተቋቋምው ድርጅት ነበር ማኅበረ ቅዱሳን ሐረር ላይ ያለውን የሰንበት ትማህርት ቤቶች እንቅስቃሴ በክፉ ዓይን ማየት የጀመረው  ዓለማያ ግብርና ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ገና እግሩን በተከለበት ወቅት ነው በዚህ ወቅት ማኅበረ ቅዱሳን የሚባል ማኅበር በሐረር ስሙም  የማይታወቅ ስለነበረ በሐረር ያሉ ካህናትም ሆኑ ምእመናን ቦታ አልሰጡትም ነበርነገር ግን ጥቂት ቆይቶ ማኅበረ ቅዱሳን ለጠቅላይ ቤተ ክህነትና ለሐረርጌ ሀገረ ስብከት አቤቱታ አስገባ አቤቱታውም ሐረር ውስጥ ያሉት ሰንበት ትማህርት ቤቶች በሙሉ ተሐድሶ ናቸው የሚል ነበር።  ለጊዜው የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት የማኅበሩን ክስ አጥብቆ ተቃወመ የሐረር ሕዝበ ክርስቲያንም ሁኔታውን ሲስማ አጥብቆ ተቃወመ።
ማኅበረ ቅዱሳንን ሐረር ምድር ላይ ላለማስገባት ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ ተጀመረ።  ሁኔታው ያላመረው ማኅበረ ቅዱሳን የሐረር ሕዝበ ክርስቲያንን የሚከፋፈልብትን አንድ ረቂቅ ተንኮል አርቅቆ አወጣ።  ያም በሐረር የሚገኙ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን የተሐድሶ አባላት የሚያሳይ የሐሰት ሰነድ ነበር።  ሰነዱ በቃለ ጉባኤ መልክ የተዘጋጀ ሲሆን የተሐድሶ አባላት የሆኑ ከመላው ኢትዮጵያ ተሰብሰበው ለሐረር እንቅስቃሴ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚሰጡ ለሐረርም መሪዎችን እንደሾሙ የሚናገርና ስሞችንም የሚዘረዝር ነበር።

በዚህ የሐሰት ሰነድ ላይ መልአከ  ሰላም ጴጥሮስ አዘነን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅ፤ የሀገረ ስብከቱን የመዝገቡ ቤት ኃላፊ፤ ሌሎች ካህናትና ታዋቂ ምእመናን የያዘ ነበር።  በሰነዱ ላይ የተዘረዘሩት ቀንደኛ የሆኑ ማኅበር ቅዱሳንን አላፈናፍንም ያሉ ሰዎች ነበሩ።  በወቅቱ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሆነው የተሾሙት መምህር ብርሃነ ህይወት (አባ ዜና ማርቆስ የተባሉት በስሜን አሜሪካ ባሉት ታላቅ አባት ምትክ የተሾሙት ) በደስታ ቸኩለው ተሐድሶዎች ቤተክርስቲያኔን ወረዋል በማለት በሸኚ ደብዳቤ የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅ፤ ካህናቱን፤ የደብር አስተዳዳሪውን ታላቁን ሊቅ መልአከ ሰላም ጴጥሮስ ከስራና ከደሞዝ አገዱአቸው።

መምህር ዘበነ ለማ መመሪያ አክብሮ እንዲሠራ ደብዳቤ ተጻፈለት !

                       ምንጭ፦ ዓውደ ምሕረት ብሎግ
የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነውንና ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የተሰጠውን መመሪያ ጥሰዋል ያለፈቃድም ሰብከዋል በሚል ለመምህር ዘበነ ለማ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተጻፈ። ደብዳቤውን የጻፈው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሲሆን፣ ዘበነ መኖሪያውን በአሜሪካ ቢያደርግም በእናት ቤተክርስቲያን ውስጥ እያገለገለ ለመሆኑ የሚያስረዳ ደብዳቤ በአሜሪካ ከሚገኘው ሀገረ ስብከት ይዞ መምጣት ሲገባው እርሱ ግን ያለ ፈቃድ እየተዘዋወረ በመስበክ የስብከተ ወንጌል መምሪያ ውሳኔዎቹን ለማስፈጸም በሚያደርገው ጥረት ላይ አፍራሽ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ደብዳቤው ገልጾ፣ ከዚህ በኋላ ከሚኖርበት ሀገረ ስብከት በእናት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግል መሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ ካላመጣና እንደለመደው እሰብካለሁ ቢል ለሚመለከተው አካል ሪፖርት በማድረግ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾአል።