Thursday, May 10, 2012

የሰናዖር ማበር



በትልቅ ቸርነት ሌሊቱን አንግቶ
በጽልመቱ ቦታ ፀሐይን አብርቶ
ጨለማን በብርሃን ለለወጠ ጌታ
ምስጋና ሊያቀርቡ፤ ሊያደርሱ ሰላምታ
ወፎች እንኳን አውቀው ሲያሰሙ እልልታ
ክፉ ማኅበር ክፉ  ያነሰ ከእንስሳ
ጠዋት ከመኝታው ከእንቅልፉ ሲነሳ
በስመ አብ ብሎ ማመስገን ሲገባው
መርዝ ሃሳብ ያወጣል ጠማማ ልቡናው
ከደካሞች ጋራ እንዳይኖር ተስማምቶ
ተንኰል የሚዘራ ከመካከል ገብቶ

Tuesday, May 8, 2012

«የሁለቱ ማቆች የታክሲ ውስጥ ወግ »

                                 ምንጭ፦ደጀ ሰላዓም ብሎግ
ሁለቱ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት በትላንትናው ዕለት ሰኞ ከምሽቱ 3፡20 ሰዓት ላይ ከአራት ኪሎ ወደ ቤላ በሚሄደው ታክሲ ጋቢና ውስጥ ጎን ለጎን ተቀምጠው ወጋቸውን ይጠርቃሉ፡፡ በእነርሱ ቤት በታክሲዋ ከተሳፈሩት ሰዎች ውስጥ ከእነርሱ በስተቀር ስለቤተክርስቲያን ሚስጥርና ወቅታዊ ሁኔታ የሚያውቅ ማንም የለም፡፡ ይሁን እንጂ፣ ያላዩት አንድ የቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆነና እነርሱን በደንብ የሚያውቅ ዘጋቢያችን ከጀርባቸው ልጥፍ ብሎ የሚነጋገሩትን በጥንቃቄ ያዳምጥ ነበር፡፡
ሰዎቹ ማንያዘዋልና ዘማሪ ኤፍሬም ነበሩ፡፡ ማንያዘዋል ትውልዱ ከወደ ደብረብርሃን ሲሆን፣ የዘርዓ ያዕቆብ ዘር ነኝ በሚል እየተመፃደቀ ዘወትር ነጭ በነጭ ለብሶ በመንሸራሸር ባህርይው ሰው ሁሉ ሊለየው ይችላል፡፡ ከዚህም በላይ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት የልማትና ተራድዖ ክፍል ውስጥ ሲሠራ በፈጸመው የሙስና ተግባር ከሥራው መባረሩ ይታወቃል፡፡ ከዚያ ደግሞ "ማኅበረ ቅዱሳን" በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አካባቢ የቲዎሎጂ ምሩቃን ማኅበር ተጠሪ እንዲሆን አስመድባው እዚያ ላይ ሆኖ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ ኤፍሬም የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባል ከመሆኑ በስተቀር ይህን ያህል የሚታወቅበት የጎላ ገጽታ የለውም፡፡

አባትነት በገንዘብና በፖለቲካ ሲፈተን



                              የጽሁፉ  ምንጭ፦አውደ ምህረት
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምእመናን ተለምኖ በተገኘ ገንዘብ የተገዛውን የዲ.. እና አካባቢው መንበረ ጵጵስና /ቤት እንዲያስረክቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወሰነ። ማኅበረ ቅዱሳን እያለ ራሱን በሚጠራው ድርጅት አቀንቃኝነታቸው የሚታወቁት ወጣቱ ጳጳስ አቡነ አብርሃም በአሜሪካ በተለያየ ስቴቶች በተካሄዱ ጉባዔያት አማካይነት ከምእመናን በተሰበሰበ የአሜሪካ ዶላር 265 000.00 የተገዛው መንበረ ጵጵስና በራሳቸው እና በወሮ. ሀረገወይን ስም ለምን ለማዛወር እንደፈለጉ ባይታወቅም መንበረ ጵጵስናው የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ንብረት መሆኑ እየታወቀ አላስረክብም ማለታቸው በዘመናዊ አነጋገርየመርካቶ ቁጩዐይነት ቢሆንም የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግሥታት እንዲያውቁት ተደርጎ በአስቸኳይ እንዲያስረክቡ ከዚህ በታች አባሪ በሆነው ደብዳቤ መታዘዛቸውን ቤተ ክርስቲያን ገለጸች።
 ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ(ጽሁፉን አሳድገው ያንብቡ)

መቼም መስከረም ሳይጠባእንደሚባለው የዋሽንግተንና አካባቢዋ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል መንበረ ጵጵስናውን በሥርዐት እንዲያስረክቡ በተደጋጋሚ ቢጽፍላቸውም አሻፈረኝ ብለው መንበረ ጵጵስናውን ለማኅበረ ቅዱሳን /ቤት (ደጀ ሰላምና አሃቲ ተዋህዶ ብሎግ ማዘጋጃ) አከራይተው እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ታውቁዋል። እኒህ ጳጳስ እንደሚታወቀው ቀደም ሲል ከመርካቶው ራጉኤል ቤተ ክርሰቲያን ባካበቱት (በዘረፉት ቢባልም ሥራቸው ነውና ራሳቸው ይፈሩ!) ገንዘብ .ኤም.. አጠገብ ፎቅ ቤታቸውን ሠርተው ሳያፍሩ ያስመረቁ ሲሆን፣ በቅርቡም በባንክ ሂሣብ የተጠራቀመውን ከዲ. ከወሰዱት የሀገረ ስብከቱ ገንዘብ እና አቶ አሥራት የሚባል (የጎጃሙ ባለአውሊያ) የቸራቸውን ብር 400 000.00 በመጨመር ሁለት ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ገንዘብ ልዩ ላንድ ክሩዘር ገዝተው -መንፈሳዊ የሆኑ ተግባራትን እያከናወኑበት ይገኛሉ።