Sunday, April 1, 2012

ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ምንጭ

‹የዓለም የሥልጣኔ ምንጭ ኢትዮጵያ ናት›፤ ማንስ ነው አይደለችም የሚል?

26 Mar 2012       በካሳሁን ዓለሙ
እንዳውም ‹ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ› ብላችሁ ካልተሳለቃችሁብኝ የዓለም ሥልጣኔ ምንጩ ኢትዮጵያ ናት የሚል አስተሳሰብ ከሰረፀብኝ ውሎ አድሯል፡፡ ምን ላድርግ የግብፅን የጥንት ሥልጣኔ ያጠኑ የግብፅ ጥናት ሊቆች(Egyptologists)  ‹የጥንቱ የዓለም ሥልጣኔ ከግብፅ ተነሥቶ እንደተስፋፋ ሞገቱኝ!› ተስማማሁ፡፡ ስስማማላቸው ነው መሰል ‹ግብፅ የተመሠረተችው እኮ በጥንት ኢትዮጵያውያን ነው› ብለው ማስረጃ አቀረቡ፡፡ አረ ተው ብላቸው ‹የጥንቱን ከአሁኑ ጋር እያነጻጸሩ እመን አሉኝ› እስቲ ቆይ ላስብበት ብዬ የሀገር ውስጡን ትውፊቱን፣ ተረቱንና ባህሉንና መልካችንን ‹የጥንት ግብፅ ሥልጣኔ ነው› ከተባለው ጋር ሳነጻጽር ቁርጥ የራሳችን ሆኖ አገኘሁት፡፡ ከዚያም ባሰብከው መሠረት ‹ውሳኔህ ከምን?› አሉኝ ‹አመንኩ ተጠመቅኩ› አልኳቸው፡፡ እናንተ ጥርጣሬ ይዟችሁ ‹የውሳኔ እጅህ ከምን? አስረዳ!› ብላችሁ ከላዬ ላይ አልወርድ ካለችሁ ‹ግራ ቀኙን ተመልክቼ የውሳኔዬን ማብራሪያ ላቀርብ ነው›!
መቼም እንዳልኳችሁ ዋና የማስረጃ ምንጮቻችን የጥንት ታሪክ ሊቆች ናቸው፡፡ እናንተም በእነዚህ ሊቃውንት ዘገባና ማስረጃ እንደምትስማሙ እገምታለሁ፡፡ ከዚያ ውጭ አምጣ ካችሁኝ ግን ‹እንዴት ብዬ?› ነው መልሴ፡፡ በዚህም ቢሆን መጀመሪያ ልትጠይቁ የምትችሉት ‹ለመሆኑ ዓለም አንድ የጋራ የሥልጣኔ ምጭ አላት ወይ?› የሚል ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ ልገምት የቻልኩትም ሊቃውንቱም ይህንን ጥያቄ ስለሚያነሱት ነው፡፡ ሆኖም እነሱ በመጨረሻ የደረሱበት መደምደሚያ ‹የዓለማችን ሥልጣኔ ከአንድ የጋራ መነሻ ፈልቆ ወደ ተለያየ አቅጣጫ ፈሷል› የሚል ነው፡፡ እዚህ መደምደሚያ ላይ ለመድረስም ያስቻሏቸውን የተለያዩ ማስረጃዎችም አስቀምጠዋል፡፡ ከእነዚህ ማሰረጃዎች መካከልም የሥልጣኔ ቅሪቶች፣ የሥነ ተረት ማሳያዎችና የታሪክ ፍሰቶች ወደ አንድ አቅጣጫ በመምራት ቅድሚያውን ይይዛሉ፡፡
በሥነ ምድር ጥናት የዓለማችን ሥልጣኔ ከአንድ ከተወሰነ አካባቢ ከሚኖሩ ማኅበረሰቦች መነሣቱን ማረጋግጥ የሚያስችሉ ብዙ ማስረጃዎች ማግኘት ተችሏል፡፡ በዚህም የጥንት ዘመን ሥልጣኔ ማሳያዎች የሆኑት የሐውልት አሠራር፣ የግብርና አጀማመር፣ የአምልኮ ሥርዓት፣ የጊዜ አቆጣጠር፣ የባህል ውርርስ፣ የልምድ ድርጊት … ተመሳሳይነት የሥልጣኔ መነሻ አንድ ስለመሆኑ መስካሪዎች ሆነው ተገኝተዋል፡፡

Thursday, March 29, 2012

«ክብሩን እንመልስ፤ እጃችንንም እንታጠብ!»

«ክብሬን ለሌላ አልሰጥም»
(by dejebirhan)        to read in PDF   (Click here)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ አላት። በቀደሙት ዘመናት ውስጥ ሃይማኖታዊ መንግሥት የሀገሪቱ አስተዳደር ሥርዓት ስለነበረ ቦታዋና ወሳኝነቷ አሌ ሊባል የማይችል እውነት ነው። ቤተክርስቲያኒቱ ያልፈቀደችው ሰው ዙፋን ላይ ሊወጣ አይታሰብም ነበር። በጉልበትም ይሁን በዘዴ አንዱ አንዱን አጥፍቶ ሥልጣን ላይ ቢወጣ እንኳን የቤተክርስቲያኒቱን እውቅና ለመጠየቅ መገደዱ አይቀርም። የንጉሠ ነገሥትነቱ ክብር እሷ ካላጸደቀችው የጸና ስለማይሆን ይህንኑ ለመስጠትና ለመፍቀድ ድርሻዋ ትልቅ ነው። በእርግጥም «እምነ መንግሥት የዐቢ ክህነት» እንደሚለው ቃሉ ቢያንሳት እንጂ ይህ ድርሻዋ የሚበዛባት አይደለም። ከተወሰነኑ ወቅቶች ማለትም ከወለተ ጌዴዎን ዮዲት 40 ዘመንና ከኢብን ኢብራሂም አልጋዚ (ግራኝ) 15 ዓመታት ወረራ ጊዜያት በስተቀር የቤተክርስቲያኒቱ ሥፍራ ላለፉት 1600 ዓመታት ከቤተመንግሥቱ የራቀ አልነበረም። በዚህም የተነሳ ቤተክህነቱ ከቤተመንግሥቱ አልራቀም ወይም ቤተመንግሥቱ ከቤተክህነቱ አልወጣም ማለት ይቻላል።
በነዚህ ዘመናት ሀገርን በማስከበር፣ በተለይም ዛሬ ኢትዮጵያ የምንላትን ሀገር ከመገንባትና ከመጠበቅ አንጻር፣ ፊደላትንና ስነ ጽሁፋትን በማስፋት፣ ቅርስን እንዲሁም ትውልዱን ከታሪክ፣ ታሪኩን ከሀገር ጋር በማስተሳሰር ረገድም ሚናዋ የጎላ ነው። ብዙ ብዙ ሊባልላት እንደሚቻል የሚታወቅ እውነታ ነው።
ከዚሁ ጋር በተነጻጻሪ ነገሥታቱ በዘመናቸው በሰሯቸው መልካምም ይሁን መጥፎ ስራቸው ድርሻዋ አብሮ የሚታይ መሆኑንም መካድ አይገባንም። ለምሳሌ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ደቂቀ እስጢፋኖስ የተባሉ ክፍሎችን አንድ በአንድ እየለቀሙ ጆሮ እየቆረጡና አፍንጫ እየፎነኑ ሲያሰቃይዋቸው መናፍቃንንና ጸረ ማርያሞችን ማስወገድ ነው በማለት ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትብብሯን አሳይታለች። እነዚህን መናፍቃን አሰቃይቶ መግደል ተገቢ እንደነበር በማመንና በማሳመን በየተአምራት መጻሕፍቱና በየታሪክ ድርሳናቱ ጽፋ አቆይታለች። ዛሬም በነዚሁ ታሪክ የጸሎት ቡራኬ ይደርስባቸዋል።
ጉዳዩን አስቸጋሪ የሚያደርገው መናፍቃንንና ጸረ ማርያም የተባሉትን (ለዚያውም ሆነው ከተገኙ) እየለቀማችሁ አጥፏቸው የሚል አስተምህሮ አለ ወይ ብለን ብንጠይቅ የእውነቱን ጽዋ ለመጠጣት ካላስቸገረን በስተቀር በወንጌል አለሁ የሚል ማንም ቢኖር ይህንን በፍጹም ሊቀበል የሚችለው አይደለም።
«እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና» ማቴ 544
ብላ የምታስተምር ቤተክርስቲያን የነገሥታቱን የግድያ ተግባር ደግፋ ብቻ ሳይሆን አሞካሽታ ስታበቃ ግድያቸውን የጽድቅ ተግባር አድርጋ መጻፏ ወንጌል አልተሰበከም ወይም ሃይማኖቱ የቆመው ሠይፍ በታጠቀው ንጉሠ ነገሥት ብርታት ነው ለማለት እንደፍራለን።
መቼም እንደዚህ ዓይነት ጠጠር ያለ ግን እውነተኛ ጽሁፍ በአክራሪዎች የሚታየው ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት እንደሚነገር እንጂ በሰራነው መልካም ነገር መሞገስን እንደምንሻው ሁሉ ባጠፋው ነገር ደግሞ ልናዝን እንደሚገባን ለማሰብ በማይችሉ ሰዎች ዘንድ ይሆናል። «በሽታችንን ደብቀን መድኃኒት እናገኛለን ማለት ዘበት ነው»
ምንም ይሁን ምንም ነገሥታቱ በፈጸሙት ግድያና ትውልድን ለቅሞ የማጥፋት ዘመቻ አብራ በተሰለፈችው ቤተክርስቲያናችን ላይ አመልከዋለሁ የምትለው ኢየሱስ ክርስቶስ «እሰይ አበጀሽ፣ ለእኔ ስትይ ልቅምቅም አድርገሽ ስለፈጀሻቸው ደስ ብሎኛል» የሚል የምስራች ይነገራታል የሚል ቢኖር እሱ ክርስቶስን የማያውቅ ሰው መሆን አለበት ብለን እውነቱን አስረግጠን እንናገራለን።
ምክንያቱም ለሰቀሉት ይቅርታ የጠየቀ፣ ለሚገድሉ ክብርንና ጸጋን ይሰጣል ተብሎ አይጠበቅምና ነው።
«ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት» ሉቃ 2334
ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመልካምነትዋና በጥሩ ስራዋ በሀገራችን ታሪክ ከፍ አድርገን እንደምናያት ሁሉ በመጥፎ ነገሯና ይህንን መጥፎ ነገሯንም እንደጀብድ የምትቆርበትን የሚያሳዝን ተአምራዊ ድርሰቷን አንብበን ልናፍርብ ይገባል። ወደድንም ጠላንም የእነዚያን የእግዚአብሔር ፍጡራን ደም ከሰማይ ይጮሃል! እግዚአብሔርም ደማቸውን ከእጃችን ይፈልጋል።
እስኪ ከእነ አባ እስጢፋኖስ ፍጅት በኋላ የሆንነው እንይ!

Wednesday, March 28, 2012

ፍጹም ከቅጣቱ!


ማን ይገኝ ነበረ?


(By dejebirhan)     to read in PDF (click here)
በከንቱ አትጥራኝ፤ ስሜን ባንተ ይክበር
ኢታምልክን ጠብቅ፣ ምልክት አታስቀር
ባልንጀራን ውደድ፤በሀሰት አትመስክር
እድሜህ እንዲረዝም፤ ወላጅህን አክብር
ገላህንም ቀድስ፣ክልክል ነው ማመንዘር
አድርግና ጠብቅ፣ የቆመውን አጥር
ያልሰማ ማን አለ? ኦሪት ስትናገር?
በከንቱ የጠራው በደለኛ ይሆናል፤ (ዘጸ ፳፣፯)
ከአምላኩ መጽሐፍ፤ ከርስቱ ይፋቃል፤ (ዘጸ ፴፪፣፴፫)
ቢሰግድና ቢወድቅ ለቀረጸው ምስል
ቢያሸው፤ ቢዳብሰው ሥሩ ቢንከባለል
የአምላኩ መልክ ሆኖ ከፊቱ ቢተከል፣
ኢታምልክን ሽሯል ትለዋለች ኦሪት
ሕጓን ትጠቅስና፣ ታወርዳለች ቅጣት
...................ከቶ ያየኝ የለም፤
አይቶኝም የሚቆም፣ (ዘጸ ፴፫፣፳)
ምስሌ ምንድነው፣ ከማን ጋር ልተያይ? (ኢሳ ፵፮፣፭)
ከቶ ማን አይቶኛል? ከደመናት በላይ፣ (ዘዳ ፴፫፣፳፮)
በምድር የተካኝ ፣እኔነቴን ወካይ፣
ከወዴት ተገኘ፣ሴትና ወንድ መሳይ? (ዘዳ ፬፣፲፮)