ሰላም ለእናንተ ይሁን
በብሉይ ዘመንና በአዲስ ኪዳን ዘመን ስላሉት ነብያት ልዩነት ላኩልኝ በአዲስ ኪዳን ያሉት ነብያት በበለጠ አገልግሎታቸው እንዴት መሆኑን እንዳለበት ላኩልኝ ተባረኩ! (ስሙን ያልገለጸ ጠያቂ)
ከደጀብርሃን መልስ፣
በአዲስ ኪዳን ውስጥ ነቢይነት ጨርሶ የሚረሳና የማይሰራ ጸጋ ነው እንዴ?
ስለ
ነብይ ምንነት፣ማንነትና አገልግሎት በዚህ በአዲስ ኪዳን ዘመን ብዙ እያከራከረ ይገኛል። አንዳንዶች አብያተ ክርስቲያናት እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ያሉት በአዲስ ኪዳን ስላለ ነብይነት ምንም ሲናገሩ አይሰማም። አዲስ ኪዳን ግን ብዙ ቦታ ላይ ከጸጋ ስጦታዎች አንዱ የነብይነት አገልግሎት እንደሆነ ጽፎ ይገኛል። ስለየትኛውና ስለምን ነብይነት አዲስ ኪዳን እየተናገረ እንደሆነ አንድም ሰው ትንፍሽ ሲል አይሰማም። ለምን? የተጻፈውን መተንተን ወይም መካድ ወይም መናገር እየተገባ ዝምታ ለምን? ኢየሱስ ነብይ ነው ከሚል ጥቅል ሃሳብ ውጪ ስለጸጋ ስጦታው ምንነት ግን ምንም አለመባሉ ያሳዝናል። ሌሎች ደግሞ እኛ ለነብይነት የተላኩና የተመረጡ ሰዎች ያሉባቸው አብያተክርስቲያናት ነን ይላሉ። እንዴትና ለምን? ብለን እነዚህኞቹንም ብንጠይቅ አጥጋቢ መልስ ከሚሰጡን ይልቅ ለራሳቸው እንደሚመቻቸው አድርገው ይተነትናሉ። ስለአዲስ ኪዳኑ ነብይነት ጨርሶ የረሱና እንደራሳቸው ምርጫ የሚጠቀሙበት ክፍሎች ቢኖሩም ስለብሉይ ኪዳን ዘመን
ነብይነት ግን ሁሉም ብዙ አይከራከሩም። አለመከራከራቸውም የሚገለጸው ሁሉንም የብሉይ ኪዳን ነብያት በጋራ ይቀበሏቸዋልና ነው። በሁሉም ዘንድ ማለት በሚቻልበት ደረጃ ሃሳቡና ትርጉሙ የጋራ ተቀባይነት አለው።
ከሥነ መለኰት ምሁራንና ሚዛናዊ አስተምህሮ ካላቸው ሊቃውንት ያገኘነውን ትምህርትና መረጃ መሠረት አድርገን ስለነብይነትና የነቢያት እንዴትነት ጥቂት ለማለት እንፈልጋለን።
ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው?
የግሪኩ «ፕሮፌሚ» ቃል ሲሆን ትርጉሙም «አስቀድሞ መናገር» ማለት ነው። ይህም ትንቢቱ ከመፈጸሙ በፊት ትንቢቱ ለተነገረለት ሕዝብ የትንቢቱን ምንነትና የፍጻሜ ሂደት አስቀድሞ ማሳወቅ ወይም ማስተላለፍ ነው።
ብሉይ ኪዳን፣
ነብይነት ለምን አስፈለገ?
የነብይነት አገልግሎት የተፈለገው የመጀመሪያው ሰው አዳም ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት ከተቋረጠ በኋላ ነው። እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት የተቋረጠ ስለነበር እግዚአብሔር መልእክቱን «አስቀድሞ መናገር» ፕሮፌማ ሰው ስለፈለገ ለዚህ አገልግሎት ከሰው መካከል በመምረጥ ነው ነብይነት የተፈገለው።
መልእክቱ የሚተላለፍበት መንገድ፣
በራእይ፣ በህልም፤ በድምጽና በምልክት ሊሆን ይችላል።
«እርሱም፦ ቃሌን ስሙ በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ፥ ወይም በሕልም እናገረዋለሁ» ዘኁ 12፤6
«እግዚአብሔር ሳሙኤልን ጠራው እርሱም፦ እነሆኝ አለ»1ኛ ሳሙ3፣4
«እርሱም፦ በአንተ ዘንድ ሞገስ ካገኘሁ፥ የምትናገረኝም አንተ እንደ ሆንህ ምልክት አሳየኝ»መሳ 6፣17
ኢሳይያስ ራእይ አይቶ፣ ኤርምያስ ቃል ሰምቶ፣ሕዝቅኤልም ዳንኤልም ራእይ አይተው ነብይነታቸውን ፈጽመዋል። ሌሎቹም እንዲሁ!
እንግዲህ የብሉይ ኪዳን ነብያት ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ሸክም ወደሕዝቡ በማድረስና የሕዝቡንም ጩኸት ወደእግዚአብሔር በማድረስ የነብይነት አገልግሎታቸውን መካከለኛ ሆነው ፈጽመዋል።
አዲስ ኪዳን፣
ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው?
የግሪኩ «ፕሮፌሚ» ቃል ሲሆን ትርጉሙም «አስቀድሞ መናገር» ማለት ነው። ይህም ትንቢቱ ከመፈጸሙ በፊት ትንቢቱ ለተነገረለት ሕዝብ የትንቢቱን ምንነትና የፍጻሜ ሂደት አስቀድሞ ማሳወቅ ወይም ማስተላለፍ ነው።
ብሉይ ኪዳን፣
ነብይነት ለምን አስፈለገ?
የነብይነት አገልግሎት የተፈለገው የመጀመሪያው ሰው አዳም ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት ከተቋረጠ በኋላ ነው። እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት የተቋረጠ ስለነበር እግዚአብሔር መልእክቱን «አስቀድሞ መናገር» ፕሮፌማ ሰው ስለፈለገ ለዚህ አገልግሎት ከሰው መካከል በመምረጥ ነው ነብይነት የተፈገለው።
መልእክቱ የሚተላለፍበት መንገድ፣
በራእይ፣ በህልም፤ በድምጽና በምልክት ሊሆን ይችላል።
«እርሱም፦ ቃሌን ስሙ በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ፥ ወይም በሕልም እናገረዋለሁ» ዘኁ 12፤6
«እግዚአብሔር ሳሙኤልን ጠራው እርሱም፦ እነሆኝ አለ»1ኛ ሳሙ3፣4
«እርሱም፦ በአንተ ዘንድ ሞገስ ካገኘሁ፥ የምትናገረኝም አንተ እንደ ሆንህ ምልክት አሳየኝ»መሳ 6፣17
ኢሳይያስ ራእይ አይቶ፣ ኤርምያስ ቃል ሰምቶ፣ሕዝቅኤልም ዳንኤልም ራእይ አይተው ነብይነታቸውን ፈጽመዋል። ሌሎቹም እንዲሁ!
እንግዲህ የብሉይ ኪዳን ነብያት ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ሸክም ወደሕዝቡ በማድረስና የሕዝቡንም ጩኸት ወደእግዚአብሔር በማድረስ የነብይነት አገልግሎታቸውን መካከለኛ ሆነው ፈጽመዋል።
አዲስ ኪዳን፣