Sunday, April 26, 2015

ኢትዮጵያ ውስጥ የተዳፈነ አክራሪነት አለ!

ወደድንም ጠላንም ኢትዮጵያ ውስጥ በእምነት ተከባብሮ የመኖር የቆየውን ልምድ በተቃራኒው የሚፈታና የሚመለከት የፍጅት፤ የእልቂት፤ የሁከትና ኢስላማዊ መንግሥት የማቋቋም የተዳፈነ አክራሪ ኃይል አለ። ይህንን ጉዳይ ጠበቅ አድርገን መናገራችን እርስ በእርስ አለመተማመንን እንዲኖር ሳይሆን በመሬት ያለውን እውነታ ደብቀን «የኢስላሚክ ስቴት ሽብርተኛ ቡድን እኛን አይወክለንም» የሚለው ወቅታዊ መፈክር የችግሩን አደገኛነት ስለማይለገልጽ ላይ ላዩን ማውራቱ ለአብሪነት በቂ መልስ መሆን ስለማይችል ብቻ ነው። በተለይ መንግሥት ከቀበሌ አንስቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሕዝቡን እያወያየ ያለውን የአክራሪ ኃይል በተለይም ወጣቱን በማሳተፍ ስር ነቀል መፍትሄ ካልሰጠበት ውሎ አድሮ አደጋውን መቀልበስ ከማይቻልበት መድረሱ አይቀርም። ይህንን ሐቅ ከሚያረጋግጡልን ማስረጃዎች አንዱ «ጀማል ሀሰን አሊ ይመር» የተባለ ከሙስሊም ቤተሰብ የተገኘ ኦርቶዶክሳዊ፤ በሙስሊም ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ መካከል ያለውን ችግር ከተወለደበት መንደር ባሻገር እየተከሰተ ያለውን የአክራሪነት አደጋ በዓይን ምስክርነት እንዲህ ያወጋናል።

ሦስት መልዕክቶች አሉኝ!
መልዕክቶቹም ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ኅብረተሰብ እና መንግሥትን ይመለከታሉ፡፡

መልዕክት አንድ-ለሙስሊም ወገኖቻችን፡-በፎቶው ላይ በቀኝ በኩል ያለው የሥጋ ወንድሜ "አህመድ ሀሰን" ሲሆን በግራ በኩል ያለሁት ደግሞ እኔ ጀማል ሀሰን ነኝ፡፡ ነገር ግን ስመ ጥምቀቴ ገብረ ሥላሴ ነው፡፡ ሁለቱ ሴቶች ደግሞ ወላጅ እናቴና አኅቴ ሲሆኑ ከእኔ ጋር በልጅነት የተነሳው ነው፡፡ ሙስሊም የሆነው የሥጋ ወንድሜ አህመድ ከደቡብ ወሎ ወደ አዲስ አበባ እኔን ክርስቲያን ወንድሙን ሊጠይቀኝ መጥቶ 3 ሳምንት እኔ ጋር ከርሞ ከሄደ ዛሬ ገና 8ኛ ቀኑ ነው፡፡
ጁምዓ ጁምዓ አህመድን አንዋር መስጊጂድ አድርሼው እኔ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን እገባ ነበር፡፡ የሙስሊም ሥጋ ቤት ሄደን ገዝተን እቤት ሄደን እኔው ራሴ ሠርቼ አህመድ ሲመገብ ነው የቆየው፡፡ እኔ ደግሞ አባቴን ሀሰን ዓሊንና ሌላውንም ሙስሊም ቤተሰቤን ልጠይቅ ወሎ ስሄድ ለብቻዬ በግ ያርዱልኛል፡፡ በአጠቃላይ ከእኔም ቤተሰብ አልፎ ወሎ ስሄድ የማየው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና ተቻችሎ መኖር እንዴት ያስቀናል መሰላችሁ!!! ቤተ ክርስቲያን ሲሠራ ሙስሊሞቹ በገንዘብም በጉልበትም ሲረዱ በዓይኔ ተመልክቻለሁ፡፡ መስጂድም ሲሠራ ሕዝበ ክርስቲያኑ አብሮ ከሙስሊሞች ጋር ሠርቷል፡፡
ነገር ግን ይህ እጅግ ያስቀና የነበረው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና መተሳሰብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየደበዘዘና መጥፎ ጥላ እያጠላበት መጥቷል፡፡

ባለፈው መስከረም ወር ላይ ግሸን ማርያም ደርሼ በዚያው ቤተሰቦቼን ጠይቄ እስከ ቦረና አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫና አባ ጽጌ ድንግል ገዳማት ድረስ በእግሬ ለ7 ሰዓት ተጉዤ ሄጄ ነበር፡፡ አጎቴ ሼህ እንድሪስ ምን አሉኝ መሰላችሁ? "እናንተ ከከተማ የምትመጡ ልጆቻችንኮ ልታስቀምጡን አልቻላችሁም" አሉኝ፡፡ ሼኹን ለምን እንዲህ እንዳሉ ስጠይቃቸው ወደ ዐረብ ሀገራት ሄደው የተመለሱ የሙስሊም ወንዶች ልጆቻቸው ጉዳይ በጣም እንዳሳሰባቸው ነገሩኝ፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ከዐረብ ሀገራት የተመለሱት ልጆቻቸው በዚያ በሰፈራቸው ክርስቲያኖች መኖር የለባቸውም የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎችንና ሼኾችን "እናንተ ሙስሊም አይደላችሁም" ይሏቸዋል፡፡ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም ካላራመዱ ማለትም ከክርስቲያኖች ጋር ቡና ከጠጡና በችግርና በደስታ ከተረዳዱ ሙስሊም እንዳልሆኑ ይነግሯቸዋል፡፡ ወጣቶችን እየሰበሰቡ ጥላቻን ይሰብኳቸዋል፡፡ ሲመክሩ ውለው የሚያድሩት እስልምናን በኃይል ስለማስፋፋትና ክርስቲያኖችን ስለማጥፋት ነው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎቹና ሼኾቹ ደግሞ በዚህ ፈጽሞ አይስማሙም፡፡ "እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እንኖራለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ አጠቃላይ የወጣቶቹ ሙስሊሞች ሁኔታቸው ሼህ እንድሪስንም ሆነ ሌሎቹን ታላላቅ ሽማግሌዎች በጣም አሳስቧቸዋል፡፡ እነሱ ካለፉ በኃላ ተረካቢውና መጪው ትውልድ ያስፈራቸዋል፡፡

ሼኹ እውነታቸውን ነው፡፡ እኔም በዘዴ ቀርቤ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም የሚያራምዱ ሙስሊም ወጣቶችን ሳናግራቸው የሰጡኝ መልስ እውነትም አስፈሪ ነው፡፡ "ክርስቲያኖችን እናጠፋለን ኢትዮጵያንም እንገዛለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸዉ፡፡ እኔ በዚያው ቦረና ወግዲ አባ ጽጌ ድንግል ገዳም ስሄድ ያየሁትን ልንገራችሁ፡፡ መነኮሳቱ ከገዳሙ ወጥተው ገበያ እንኳን መሄድ አይችሉም፡፡ ሲሄዱ ጠብቀው መንገድ ላይ በድንጋይ ይመቷቸዋል፡፡ ሴቶቹ መነኮሳት ብቻቸውን ወደ ወንዝ ወርደው ውኃ መቅዳት አይችሉም ምክንያቱም የመደፈር አደጋ ላይ ይወድቃሉ፡፡

ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን፡- ሰሞኑን የISIS ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪ በክርስቲያኖች ላይ የፈጸመውን እጅግ ዘግናኝ ድርጊት ከልብ አውግዛችሁ ቂርቆስ ሰፈር የታረዱት ሰማዕታት ቤተሰቦች ዘንድ መጥታችሁ አብራችሁን ስታለቅሱ አይቻለሁ፡፡ ምስጋናዬንና አድናቆቴን ሳልገልጽ አላልፍም፡፡ ግን በተቃራኒው ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ ልጆቻችሁ በዘመናዊው መገናኛዎች አማካኝነት "እሰይ ታረዱ" ሲሉ እያየናቸውና እየሰማናቸው ነው፡፡ በየፌስቡኩ አስተያየታቸው ላይ አንድ ሙስሊም እንኳን "አላህ ነፍሳቸውን ይማር" ብሎ ምኞቱን የገለጸ የለም፡፡ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ባገኘነው መረጃ መሠረት "ሀዘናችንን በጋራ እንግለጽ ድርጊቱንም በጋራ እናውግዝ" ተብሎ ለሁለቱም እምነቶች በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ ሙስሊም ተማሪዎች አልተገኙም፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ እኔ ግን የድርጊቱ ደጋፊዎች መሆናቸውን ነው የምረዳው፡፡ በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ ሙስሊሙና ክርስቲያኑ ተማሪ በጠላትነት ነው የሚተያየው፡፡ ይህንንም ከዩኒቨርሲዎች የወጣን ሁላችን በተግባር አይተነዋል፡፡ በአንድ ትልቅ የመንግሥት መ/ቤት ውስጥ አብሮኝ የሚሠራ ሙስሊም ጓደኛዬም ከዚህ በፊት እነ አልቃይዳ እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነርሱ መሆናቸውን ሽንጡን ገትሮ ሲከራከረኝ ነበር፡፡

ወደ መፍትሄው እንምጣ........
ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን! እንደቀድሞው እንዳማረብን እንዴት ተከባብረንና ተዋደን እንኑር??? መፍትሄው ቀላል ነው፡፡ ይሄኛው መልዕክት መንግሥትም ይመለከታልና ባለሥልናት ሁላችሁ ስሙ፡፡ መንግሥት እንኳን ለህልውናህ ስትል ሳትወድም ቢሆን በግድ ትሰማለህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ግን የድሮውን መዋደድና መተሳሳብ ብሎም መቻቻል እንዳለ ይዘን መቀጠል ከተፈለገ ለጉዳዩ አጽንኦት በመስጠት ችግሩን በግልጽ መነጋገር አለብን፡፡
የችግሩ የመጀመሪያው መፍትሔ ችግሩ መኖሩን አምነን እንቀበል! የአጎቴ የሼህ እንድሪስ ሀሳብ በጣም ትክክል ነው፡፡ ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ "አዳዲስ ዘመነኛ ሙስሊሞች" የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች ናቸው፡፡ እኔ በዚህ 101% እርግጠኛ ነኝ! በየመስጂዱ ውስጥ ለወጣቶቹ ሙስሊሞች ምን ዓይነት ሥልጠናና ትምህርት እንደሚሰጥ እኔው ራሴ እምነቱ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት ያየሁትንና የተማርኩትን ነው እየመሰከርኩ ያለሁት፡፡ መንግሥት ሆይ! ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ሆይ! ችግሩን በየሚዲያው በቀን ሺህ ጊዜ "ISIS እስልምናን አይወክልም" በሚል ፉከራና ሽለላ ችግሩን መቅረፍ እንደማይቻል እመኑ፡፡ ጥቂት የማይባሉ የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች በሀገራችን ሞልተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ የሩቁን ትተን በቅርቡ በጂማ፣ በስልጤ፣ በኢሉባቡርና በሌሎቹም ክልሎች ጽንፈኛና አክራሪ ሙስሊሞች ቤተ ክርስትያን ውስጥ እየገቡ በጸሎት ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች በገጀራ ሲቆራርጧቸው ያኔ isis አይታወቅም ነበርኮ! "isis የትኛውንም ሃይማኖት አይወክልም" የሚል ባዶ ፉከራ እያሰማችሁ የምታጃጅሉን ለምንድነው? ክርስቲያኖችን በገጀራ እየቆራረጠ ቤ/ክንን ሲያቃጥል ደነበረው ያ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ከነ ገጀራው ማንን ነበር የሚወክለው? የዛኔ የትኛው ሙስሊም ነው በአደባባይ ወጥቶ እኛን አይወክልም ያለው? የisis ዘግናኝ ድርጊት እኛ ሀገር ከተጀመረ ቀየኮ!
isis ዛሬ የፈጸመው አረመኒያዊና እጅግ ዘግናኝ ተግባር በዓይነቱም ሆነ በይዘቱም ከዚ በፊት በሀገራችን ከተፈጸመው ጋር ምንም ልዩነት የለውም። "እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነ አልቃይዳ ናቸው" ያለኝ ያ የመንግሥት መ/ቤት ጓደኛዬ ሁኔታዎች ቢመቻቹለትና አጋጣሚውን ቢያገኝ እኔንም አጋድሞ እንደሚያርደኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ በየገጠሩ ያሉ ጽንፈኛ አክራሪዎች ሁኔታዎች በተመቻቹላቸው ጊዜ ምን እንዳደረጉ አይተናል፡፡
ኢትዮጵያው ውስጥ የሚገኙ ሙስሊም መምህራን በተለያየ ጊዜ የአመጽ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የተቀረጸውን ቪዲዮ ማየት እንችላለን፡- "በዚህ ማንም ክርስቲያን አንገቱን ቀና አድርጎ አይሄድም፡ በሜንጫ ነው አንገታቸውን የምንላቸው" "ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክንን እናቃጥላታለን..." ሲሉ የነበሩ አመጸኛ አክራሪዎች አጋጣሚውን ቢያገኙና ሁኔታዎች ቢመቻቹላቸው የተናገሩትን ተግባራዊ ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ ደግሞም ተግባራዊ አድርገውት አሳይተውናል፡፡

እውነታውን አንሸፋፍን! የመጀመሪያው መፍትሔ ይሄ ነው፡፡ ጉዳዩ የማይመለከታችሁ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችንና መንግሥት ችግሩን አምናችሁ ተቀበሉና ወደ መፍትሔው በጋራ እንምጣ፡፡ ዝም ብሎ በአፍዓ ብቻ አክራሪነትን እንቃወም ማለት ብቻ ሳይሆን በሀገራችን ያሉ አክራሪዎቻችንን በተግባርም እንቃወማቸው፡፡ የጽንፈኛዎቹን እንቅስቃሴዎቻቸውን ተከታትሎ ለሕዝብ ይፋ ማድረግና ግለሰቦቹንም ለይቶ መረጃ አጠናክሮ ለሕግ ማቅረብ ቀጣዩ ተግባር ይሁን፡፡ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ይህን ማድረግ ስትችሉ ነው isis እንደማይወክላችሁ የምናውቀው፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪዎቹ "ክርስቶስን ክዳችሁ አላህን ብቻ አምልኩ..." እያሉ ነው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ያረዱብን፡፡ ሰያፊዎቹ ቢያንስ እነሱ ለራሳቸው ሙስሊሞች ናቸው እናንተ በግድ "ሙስሊም አይደላችሁም እስልምናንም አትወክሉም" ልትሏቸው አትችሉም፡፡ እነሱ ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ነው እየገደሉና እያረዱ ያሉት፡፡

ስለዚህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ፖለቲካኛውን አስተሳሰብና አነጋገር ተውትና በጎረቤትኛና በዘመድኛ አስተሳሰብ እንተሳሰብ፡፡ በፍቅርና በመውደድኛ ቋንቋ እንነጋገር፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽንፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ የድርጊቱ ፈጻሚዎች ተጸየፏቸውና ተቃውሞአችሁን አብራችሁን ሆናችሁ በተግባር አሳዩን፡፡ አቤት ያኔ ፍቅራችን ሲደረጅ........

መልዕክት ሁለት-ለክርስቲያን እኅት ወንድሞቼ፡- ከዚህ ከሊቢያው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ምን ተማርን??? የትኛውም ሐዋርያ በክብር ዐረፈ የሚል ገድል የለውም፡፡ ሁሉም ሐዋርያት "ተዘቅዝቆ ተሰቀለ፡ አንገቱን በሰይፍ ተቆረጠ፡ በእሳት ተቃጠለ፡ ቆዳው ተገፈፈ..." የሚል ገድል ነው ያላቸው፡፡ ሰማዕታት ሁሉ በሐዋርያት መንገድ ተጉዘው ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ በስንክሳሩ መጽሐፍ ላይ ስናነበው የኖርነውን የሐዋርያትንና የሰማዕታትን ታሪክ ወንድሞቻችን ዛሬ በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመንም በተግባር አሳዩን፡፡ ወንጌልን በተግባር ሰበኩልን፡፡ ክርስቶስን ክደው የአንገታቸውን ክር በጥሰው ቢሆን ኖሮ ማንም አይነካቸውም ነበር፡፡ ሦስት ቀን ሙሉ በረኀብ አሠቃይተዋቸው እስከ መጨረሻው ድረስ በጽናት ቆይተው አንገታቸውን በጸጋ ለሰይፍ ሲሰጡ ስናይ ከጥልቅ ሀዘን ባለፈ ምን ተሰማን በእውነት!?
እኛስ በቃል ሰይፍ ብቻ ታርደን የክብር ባለቤት መድኀኔዓለም ክርስቶስን የካድን ስንቶቻችን እንሆን?
አንድ ዐይን ያለው ሰው በአፈር አይጫወትም፡፡ ሐዋርያው "ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠች አንዲት ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ" ያለው ለዚህ ነው፡፡ ይሁ 1፡3፡፡ ሞት እንደሆነ ሰው በዝሙት ይሞታል፡ በመኪና አደጋ ይሞታል፡ በትንታ ወይም የሚበላው እህል አንቆትም ይሞታል፡፡ ምን!... በኃጢአት ላይ ኃጢአት ለመጨመርና እህል ለማመላለስ ተኖረ አልተኖረ!....፡፡ ክርስቶን እንዲህ ሞቱን በሚመስል ሞት አክብሮ ሰማዕት ሆኖ መሞት ምንኛ መታደል ነው!!! ሰማዕታት ወንድሞቻችን ዛሬ ክርስቶስን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ተባብረውት በእቅፉ ውስጥ ናቸው፡፡ ክርስቶስን በሞታቸው ያከበሩት የሰማዕታቶቻችን በረከታቸው ይደርብን በእውነት!!! አባቶችን በገዳም ሰማዕታትን በደም ያጸና አምላክ እኛንም በሃይማኖት በምግባር ያጽናን!

ታስታውሳላችሁ አይደል አሁን በወጣቱ ዘንድ ያለውን የክርስትናውን መነቃቃት የተፈጠረው በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በተሰየፋ ክርስቲያኖች አማካኝነት ነው፡፡ ዛሬም እነዚህ 30 የሊቢያ ሰማዕታት ወንድሞቻችን የለኮሱት የእምነት ችቦ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ እየተቀጣጠለ ክርስትናችንን በዓለም ዙሪያ አጠንክሮ እንደሚያስፋፋው ሳይታለም የተፈታ ነው!!! ነገር ግን አካሄዳችን ሁሉ በፍጹም ፍቅርና በትዕግስት ይሁን፡፡ ለሙስሊም ወገኖቻችን ፍቅር እንስጥ፡፡ እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እኑር፡፡ በፍቅር የሚሞትለት አንጂ በጥላቻ የሚገደልለት አምላክ እንደሌለን ፍቅር ሰጥተን እናሳያቸው፡፡ በቀል የእኔ ነው ያለ አምላካችን ለእኛ ግን "ጠላቶቻችሁን ውደዱ" የሚል መመሪያ ነው የሰጠን!!!

መልዕክት ሦስት-ለቤተ ክህነትና ለቤተ መንግሥት፡- እግዚአብሔር አምላክ ከሁለቱም ወገን በአንድ ጊዜ ቀንድ ቀንዱን ነቅሎ ሲወስድ አይታችሁ ያልተማራችሁ አሁን ሰው ነግሯችሁ ልትሰሙ ስለማትችሉ ምንም አልልም! ዝምምምም.....

ohhh ሙስሊሞች አንድ የረሳኃት መልዕክት ትዝ አለችኝ! ጀማል የሚባል ልጅ አብሮ ተሰይፏል እያላችሁ ነው መረጃ ግን አልተገኘም፡፡ እስቲ ቤተሰቦቹን ጠቁሙንና አብረን ሄደን እናስተዛዝን??? እስካሁን ጀማል የሚባል የተሰየፈ ከሌለ ግን ምናልባት ወደፊት እኔ ተሰይፌ ያኔ "ካፊሩ ጀማል ተሰየፈ" የምትሉበት ጊዜ ከመጣ እሰየው ነው!