Monday, August 20, 2012

ሰበርዜና፡-በማኅበረ ቅዱሳን እየተዘወረ ያለውና መሪውን ያጣው ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስን ከአመራር ሰጪነት ለማውረድና ዐቃቤ መንበር በአፋጣኝ ለመሰየም ለነገ ቀጠሮ ይዟል

 የደርግ  ርዝራዥ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን፤ ደርግ ሲያስተጋባ እንደነበረውና « ተፈጥሮን ሁሉ በቁጥጥራችን ስር እናደርጋለን» ሲል እንደነበረው ሁሉ ብላቴ ጦር ካምፕ ላይ ከውትድርና ወደ ስመ ቅድስና ሺፍት በማድረግ ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ስሩን የዘረጋው ማኅበር፤ የቅዱስ የፓትርያርኩ ሞት ሳይታሰብ እንደተገኘ ሎተሪ በመቁጠር የራሱን ንጉሥ ቀኑ ሳይመሽ ለማሾም የሞት ሽረት ትግሉን እያደረገ «ቤተክርስቲያንን በቁጥጥራችን ስር እናደርጋለን» በሚል መንፈስ እንደአባቱ ደርግ እየሰራ ይገኛል። ቁጭ ብለው የሰቀሉት፤ ቆሞ ማውረድ እስኪቸግር ድረስ ይህ ማኅበር ጳጳሳቱን እያስፈራራና በገመናቸው ሳቢያ እያሸማቀቀ ተሰብሰቡ ሲላቸው፤ የሚሰበሰቡ፤ ተበተኑ ሲላቸው የሚበተኑ የምስኪናን ጉባዔ ሆነዋል። የቅዱስ ፓትርያርኩ ሥርዓተ ቀብር ከተፈጸመ በኋላ ዐቃቤ መንበር እንዲሾም፤ እስከዚያው ድረስ በዋና ሥራ አስኪያጁ አቡነ ፊልጶስና ቋሚ ሲኖዶስ እንዲመራ የተወሰነ መሆኑ ቢታወቅም የዚህንን ቆይታ ጊዜ በማስላት ተጠቃሚ ሊሆን እንደማይችል ያረጋገጠው ክፉው ማኅበር፤ ሲኖዶሱ በአስቸኳይ ተሰብስቦ አስተላልፎ የነበረውን ውሳኔ እንዲሽርና አቡነ ናትናኤልን ዐቃቤ መንበር አድርጎ እንዲያስቀምጥለት ባስተላለፈው ትእዛዝ መሠረት አቤት፤ ወዴት እያሉ ለመሰብሰብ ፈቃደኛ ሆነውለታል።  እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ የሚባለው ዛሬ ነው። አስተዳዳሪዎች፤ ካህናትና፤ዲያቆናት፤ አበው መነኮሳት ዛሬ ያልተናገራችሁ ነገ መራራ ዘመናችሁ ከደጃችሁ ቆሟል።
የዓውደ ምሕረትን ዘገባ ከታች አቅርበንላችኋል። መልካም ንባብ!

ማኅበረ ቅዱሳን አቡነ ናትናኤል ይሁኑልኝ ብሏል።

(ዐውደ ምሕረት፤ ነሐሴ 13 2004 ዓ.ም. / www.awdemihret.blogspot.com //www.awdemihret.wordpress.com) የአቃቤ መንበሩን ምርጫ ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ሥርዓተ ቀብር በኋላ ይፈጸማል ብሎ የነበረው ቅዱስ ሲኖዶስ የአቡነ ፊሊጶስ የሰሞኑ አካሄድ በማኅበረ ቅዱሳን በኩል ስላልተወደደ የአቃቤ መንበሩን ምርጫ በነገው ዕለት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን ወስኗል ተባለ።
     ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በሕይወት እያሉ መልካም ሥራዎቻቸውን እያኮሰሱና እንከን እየፈለጉባቸው ክፉኛ ሲያብጠለጥሏቸውና ሲያሳዝኗቸው የነበሩ ብዙዎች፣ ቅዱስነታቸው ካንቀላፉ በኋላ የእርሳቸው መልካም ስራዎችና ተሸክመው የነበሩት ትልቅ ሀላፊነት ከባድ መሆኑንና ብዙ ኅልፈታቸው እንዳጎደለ ለመረዳት ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ በመሆኑም ያለማንም አስገዳጅነት የቅዱስነታቸውን መልካምነት በመመስከር ሥራ ተጠምደዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ይጠቀሳሉ፡፡
   በማኅበረ ቅዱሳን ወዳጅነታቸው የሚታወቁትና ማህበሩ አውጆት በየአዳራሹ ሲያካሂድ ለነበረው የተሀድሶ ግንዛቤ ማስጨበጫና ገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ባራኪ የነበሩት ብፁዕነታቸው አሁን የቅዱስነታቸውን በአይን የሚታይ በእጅ የሚዳሰስ መልካም ገጽታቸውን መገንባታቸው በማኅበረ ቅዱሳን ዘንድ አልተወደደም፡፡ ስለዚህ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስን ከዚህ ወሳኝ ጨዋታ ውጪ ለማድረግ ሲባል፣ ከቅዱስነታቸው ስርአተ ቀብር በኋላ ሊከናወን ቀጠሮ የተያዘለት የዐቃቤ መንበር ምርጫ በነገው ዕለት እንዲካሄድ በማኅበረ ቅዱሳን እየተዘወረ የሚገኘውና ሁነኛ መሪውን ያጣው ሲኖዶስ መወሰኑን ውስጥ አዋቂዎች ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
     ቅዱስ ሲኖዶሱ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላ ባደረገው የመጀመሪያ ስብሰባው ብጹዕ አቡነ ፊልጶስ እስከ ሥርዓተ ቀብር ድረስ በሲኖዶስ ሰብሳቢነት እንዲቆዩ ወስኖ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን ግን በፓትርያርኩ ድንገተኛ ሞት የተነሳ ቤተክርስቲያኒቱ ወደ አለመረጋጋት እንዳትሔድ ብጹዕ አቡነ ፊልጶስና መሰሎቻቸው በሚያደርጉት አዎንታዊ እንቅስቃሴ ለማህበረ ቅዱሳን ፍላጎቶች በበቂ ሁኔታ ተገዢ ባለመሆናቸው እና ማኅበርዋ ባቀደችው መሰረት ነገሮች ሊሄዱላት ስላልቻሉ፣ በሰብሳቢነት እንዲቆዩ ከተወሰነ ከሁለት ቀን በኋላ የዐቃቤ መንበሩ ምርጫ በነገው ዕለት እንዲደረግ ተወስኗል።
     ቅዳሜ ዕለት የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው የቅዱስነታቸው ቀብር በስራ ቀን ስለተደረገ ወደቅዳሜ ይዘዋወርልን የሚል ጥያቄ ሲያቀርብ “አንዴ ለሚዲያ የተናገርነውን ነገር አንሽርም ህጻናት አይደለንም።” በማለት ውድቅ ያደረጉት ጳጳሳት አሁን ግን የማኅበረ ቅዱሳንን ፍላጎት ለመፈጸም ሲሉ የአቃቤ መንበሩን ሹመት ከቅዱስነታቸው ቀብር በኋላ ይፈጸማል በማለት ለሚዲያ የተናገሩትን ቃላቸውን ሽረው በእነሱው አነጋገር “የሕጻን ስራ” ሰርተዋል።
     ማኅበሩ መንግስትን በጣልቃ ገብነት እየከሰሰና ስሙን እያጠፋ ራሱ ግን ይህን ዕድል ተጠቅሞ የራሱን ሰው ለማስመረጥ መንገድ ጠራጊ የሚሆኑለትን በዐቃቤ መንበርነት ለማስመረጥ ተግቶ እየሰራ ሲሆን፣ ስውሩም ግልጹም አመራር በከፍተኛ ስብሰባ ተጠምደዋል፡፡ አንዳንዶቹ ሥራቸውን ሁሉ ትተው በጉዳዩ ላይ ተግተው እየሰሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡
   ከቀድሞ ጀምሮ በጳጳሳቱ በኩል ያለውን ስራ በማከናወን የሚታወቀውና አቡነ ጳውሎስን አምርሮ የሚጠላው ማንያዘዋልም ጳጳሳቱን የማግባባት ስራውን እየተወጣ ሲሆን፣ ማኅበረ ቅዱሳንም ያመነበትን ሰው ለማስቀመጥ ከዚህ የተሻለ ጊዜ እንደሌለው አውቆ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በነገው ዕለት ሊደረግ ለተወሰነው የአቃቤ መንበር ምርጫ ሊመረጡ የሚገባቸው አቡነ ናትናኤል መሆናቸውን ዛሬ ማምሻውን እየዞሩ ጳጳሳቱን በማግባባት ስራ ተጠምደው ያሉት አቡነ ህዝቅኤል እና በማኅበረ ቅዱሳን በኩል ለፓትርያርክነት ተስፈኛ የተደረጉት አቡነ ሉቃስ መሆናቸው ታውቋል።
   አቡነ ናትናኤል ከእርጅና ብዛት ሽንታቸውን እንኳ መቆጣጠር የማይችሉ አባት ሲሆኑ ስብሰባ የመምራትም ሆነ ተናግሮ የማሳመን ብቃት የሌላቸው ሰው መሆናቸው ይታወቃል። በእሳቸው በኩል ያሉት ጉድለቶች እና የጤና እክላቸው የታወቀ ቢሆንም የማኅበረ ቅዱሳንን አላማ በማስፈጸም ረገድ የተሻሉ ሰው በመሆናቸው እንዲመረጡ የማግባባት ስራው ተጀምሯል። የማኅበሩ አላማ እሳቸውን ዝም ብሎ አስቀምጦ በ2001 ዓ.ም. ቅዱስ ፓትርያርኩን ከስልጣን ለማውረድ ተቋቁሞ የነበረው አቡነ ጢሞቴዎስ፣ አቡነ ሳሙኤል አቡነ እስጢፋኖስ እና አቡነ ሉቃስ የሚገኙበት የማኅበረ ቅዱሳን ታማኝ የሆኑ ጳጳሳት ኮሚቴ እንዲመራው ለማድረግ ነው።

Sunday, August 19, 2012

ፓትርያሪክ መርቆሪዮስ ወደ መንበራቸው ይመለሱ!



ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል 
የፓትርያሪክ ጳውሎስ ሞት ከአወዛጋቢነት አልፎ አስደንጋጭ ዜና እየተሰሙ ነው። ፓትሪያሪኩ ህይወታቸው ለህልፈት እስከተዳረገች ዕለት ድረስ በተለይ የዕለቱ ውሎአቸው እስከ ሥርዓተ ቁርባን ድረስ ምንም ዓይነት ችግርና እንዲሁም የድካም መንፈስ ያልታየባቸውና ያልተስተዋለባቸው ሲሆኑ ቅዱስቁርባኑን ከወሰዱበት ቅጽበት ጀምሮ ግን በሰውነታቸውን ላይ የመዛል፣ በሚታይ የሰውነት ክፍላቸውም በላብ የመጠመቅ ዓይነት ምልክት እንደታየባቸው በትናት ዕለት ካነጋገርቸው በዕለቱ አብሮአቸው ቤተ- መቅደስ ውስጥ ነበሩ ከተባሉ ካህናት ተጨባጭ ምስክርነት ለማግኘት ተችለዋል።
በሁኔታው ግራ የተጋቡ የዓይን ምስክሮች ጨምረው እንዳወሱልኝም ከሥርዓተ ቁርባኑም ሆነ ከዚያ በፊት የነብሩ ቀናት ፓትሪያሪኩ እንደ ወትሮ የዕለተ ዕለት ግዴታዎቻቸውን በሚገባ ሲያከናውኑ እንደሰነበቱና ምንም ዓይነት ለሞት ሊዳርግ የሚያስችል ዓይነት ሕመም እንዳልነበራቸውም ለማወቅ ተችለዋል። ታድያ ገዳያቸው ማን ሊሆን ይችላል? ቤተ- ክርስቲያን እነሆ ደመ ክርስቶስ ብላ ለስዎች ልጆች ሕብረት በምታቀርበው በጽዋ ላይ ገዳይ መርዝ ጨምሮ ጭቃኔ በተሞላበት አረመንያዊ ድርጊት የሰው ነፍስ ለህልፈት ዳርጎ ሲያበቃ ተጠቃሚ የሚሆነው ማን ሊሆን ይችላል? የቤተ- ክርስቲያኒቱ አባቶችና ሊቃውንት መምህራን በመግደልስ የጥቅም መርበቡን በቤተ- ክርስቲያን ላይ የመዘርጋትና እውን የማድረግ ዓላማ አነግቦ የተነሳ ነፍሰ ገዳይ ማን ይሆን? ለሚሉና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎች በሰፊውና በተጠናከረ መልኩ ሳምንት እመለስበታለሁ።
በዛሬው ዕለት ግን ህልፈተ ሥጋ ፓትርያሪክ ጳውሎስ ተከትሎ በብዙሐን ዘንድ አነጋጋሪ ከሆኑት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል በቀዳሚነት እያነጋገረ የሚገኘውን የፕትርክና መንበሩ/መቀመጫው ማን ይተካው? የሚለው ጥያቄ ዙሪያ ላይ አጭር መልስ/መፍትሔ ለመጠቆም ነው። ስህትት በስህተት ለማረም ወይንም ደግሞ ለማስተካከል እንደማይቻል ከሌላው በተሻለ ኢትዮጵያውያን ብዙ ማለት እንደምንችል አመናለሁ። ይኸውም ስህተትን በስህተት ለማስተካከበል በሞከርናቸው ዘመናት ሁሉ እርምጃዎቻችን ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው አመዝኖ ዛሬ ምድራችንም ሆነ ሕዝባችን የሚገኝበት አሳፋሪ ገጽታና የተመሰቃቀለ ህይወት ማየቱ በቂ ማስረጃ ነው ብዬ አምናለሁ።
እዚህ ላይ አጽንዖት ሰጥቼ ለማስተላለፍ የምወደው መልዕክት ቢኖር ቤተ- ክርስቲያን በተለይ በሀገር ውስጥ የሚገኘውን ሲኖዶስ ከቀድሞ ስህተት ይልቅ የባሰ ስህተት እንዳይሰራ ከወዲሁ እርምጃዎችን ይመረምር ዘንድ ነው የሚጠየቀው። ፓትሪያሪክ ጳውሎስ አልፈዋልና አዲስ መሾም ያስፈልጋል በማለት በጥድፍያ የሚሆን ነገር እንደሌለ በመገንዘብ በተለይ በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች መካከል የተጀመረውን የዕርቀ ሰላም አጀንዳ በሁለቱም አካላት በጎ ተነሻሽነት በአስቸይ ፋይሉን በመክፈት ቤተ -ክርስቲያኒቱ አንድ የምትሆበትና ወደ ቀድሞ አንድነትዋ የምትመለስበት እንዲሁም የቀድሞ ፓትሪያሪክ ወደ መንበራቸው የሚመለሱበት መንገድ በርትቶና ተግቶ መስራት እንደሚጠበቅበት ነው የማምነው። ይህን አይነቱ እርምጃ ደግሞ ከየትኛውም አቅጣጫ ለማየት ቢሞከር ሀገራዊም ሆነ መንፈሳዊ ጠቀሜታውም የጎላ ነው
በተጨማሪም የመንፈሳዊያን መሪዎችም ሆነ የቤተ- ክርስቲያን አጀንዳ ሰላምና ሰላም እስከሆነ ድረስ ለዓመታት የዘለቀውን ቀውስና ትርምስ መግታትና ማስቆም የሚቻለው መንበሩ ከፖትሪያርክ መርቆርዮስ አልፎ ለማንም ሊሆን እንደማይችልና እንደማይገባ በማመን ፓትሪያሪክ መርቆሪያስ ወደ ቀድሞ መቀመጫቸው ለመመልስ በሚሳየው በጎ ተነሳሽነት ነው። ይህም የምለው ያለ ምክንያት አይደለም። በቤተ- ክርስቲያኒቱ ጉዳይ ላይ የሚመለከተውም የማይመለከተውም አፉን በከፈተ ቁጥር ለዚህ ሁሉ ዕንቅፋትና መሰናክል መዋቹ ፓትሪያሪክ ጳውሎስ ብቸኛ ተጠያቂ ያደርግ እንደነበረ ማናችንም አንስተውም። ታድያ አሁን ማንን ተጠያቂ ልናደርግ ነው? በህይወት ባሉ ፓትሪያሪክ ላይ ፓትሪያሪክ ለመሾም አይደለም ሊሞከር ፈጽሞ ሊታሰብም አይገባውም። ፓትርያሪክ መርቆሪዮስ ወደ መንበራቸው ይመለሱ!
መቀመጫው አሜሪካ ላያደረገ የአበው ጉባኤ (ሲኖዶስ):
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሆይ! ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕ 12 :17 በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ። ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ ሲል እንደ ጻፈላቸው ዛሬ ደግሞ እኛ ባለተራዎች በእኩል ኃይል ሥልጣንና መንፈስ ቃሉ ከፍ ባለ ድምጽ ሰላምን እናወርድ ዘንድ አፍ አውጥቶ እየጮኸ ይገኛል። ሳሙኤል ገና ብላቴና በነበረበት ዘመን እግዚአብሔር በስሙ ይጠራው ነበር። ሳሙኤልም ገና የእግዚአብሔር ድምጽ ለይቶ ካለማወቁ የተነሳ እግዚአብሔር በጠራው ቁጥር ብድግ እያለ ወደ ኤሊ በመሄድ እነሆ የጠራኸኝይለው ነበር። ታድያ ከዕለታት አንድ ቀን ነገሩ የገባው ሊቀ ካህን ሳሙኤልን ሄደህ ተኛ ቢጠራህም አቤቱ ባሪያህ ይሰማልና ተናገር በለው በማለት አሰናብቶታል። 

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ጽ/ቤት የተሰጠ የኃዘን መግለጫ



ነሐሴ 11/2004 /     /Aug 17/2012
ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር” (መዝ 1156)
የአምስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ  የብፁዕ ወቅዱስ / አቡነ ጳውሎስን ዕረፍት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  የሰላምና አንድነት ጉባኤ /ቤት የተሰጠ የኃዘን መግለጫ።
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
እንዲሁም በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያና በመላው ዓለም ለሚኖሩ የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን በሙሉ።

        በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ በአምስተኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ / አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፤ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንትና የዓለም የሰላም አምባሳደር ድንገተኛ ዕረፍት ምክንያት የተሰማውን ከፍተኛና ትልቅ ኃዘን ይገልጻል። እንደሚታወቀው ቅዱስነታቸው   ለቤተ ክርስቲያናችን ዕድገትና መሻሻል፣ መጠናከርና መስፋፋት የሚጠቅሙ በርካታ መንፈሳዊ ተግባራትን ያከናወኑ  ታላቅ የቤተ ክርስቲያናችን አባትና  የሥራ ሰው ነበሩ። በመሆኑም ቅዱስነታቸው በአገልግሎት ዘመናቸው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከናወኗቸው ዘርፈ ብዙ ሐዋርያዊ ተግባራት ምን ጊዜም ሕያውነታቸውን ሲያስታውሱ ይኖራሉ። ቅዱስነታቸው ብሔራዊውን የአብነት ትምህርትና ዘመናዊውን ዕውቀት አገናዝበው የተማሩ ታላቅ ሊቅ ስለነበሩ ለቤተ ክርስቲያን እጅግ አስፈላጊ ቅዱስ አባት ነበሩ፤ ይልቁንም ባለንበት ዘመን ቤተ ክርስቲያናችንን በዓለም መድረክ ወክለው ያከናወኗቸው ብዙ ሥራዎች ዘወትር ሲታሰቡ ይኖራሉ። ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን እኒህን ታላቅ አባት በድንገት በማጣቷ ልባዊ ኃዘናችንን በድጋሚ እንገልጻለን። በእውነቱ የቅዱስነታቸው  ድንገተኛ ዜና ዕረፍት ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ  ኃዘን ነው።
          ይልቁንም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ በቅዱስነታቸው አባታዊ ቡራኬና በቅዱስነታቸው በሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መልካም ፈቃድ ሦስተኛውን ዙር የሰላምና አንድነት ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ሳለ ይህንን ቤተ ክርስቲያንን አንድ የሚያደርግ ታሪካዊ ሒደት ለፍጻሜ ሳይበቃ የቅዱስነታቸው ዜና ዕረፍት መስማቱ ጉባኤውን በእጅጉ አሳዝኖታል፤ ሊያስከትል የሚችለው ውጣ ውረድም ከወዲሁ አሳስቦታል። ቅዱስነታቸው የጀመሩትን የቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት ጥረት የመጨረሻ ፍሬ ሳያዩ በድንገት በማለፋቸው ኃዘናችን ወሰን የለውም። የሰላምና አንድነት ጉባኤው በቅዱስነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው የጉባኤውን የኃዘን መግለጫ የሚያደርሱ ልዑካንን  ሰይሞ ለመላክ በአንድነት ወስኗል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ቤተ ክርስቲያንን አሁን ካለችበት አሳሳቢ የልዩነት ፈተና ይበልጥ ወደ ባሰና ወደ ከፋ ችግር እንዳትሄድ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ተቀዳሚ ሥራው በማድረግ ለዘመናት በአንድነቷ ጽንታ የኖረችውን ቤተ ክርስቲያን የቀድሞ ታሪኳን ለመመለስና ለማደስ ተገቢውን ሥራ በአንድነት እንዲሠራና እስካሁን ድረስ የቆየው የልዩነት ምዕራፍ እንዲዘጋ፣ በቅዱስነታቸውና በቅዱስ ሲኖዶስ በጎ ፈቃድ የተጀመረውን የሰላምና አንድነት ሒደትም ለፍሬ ያበቃው ዘንድ ጉባኤው ከታላቅ አደራ ጋር ይማጸናል።
በመሆኑም የሰላምና አንድነት ጉባኤው ለቅዱስ ሲኖዶስና ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መላው ካህናትና ምእመናን ወምእመናት ከዚህ የሚከተለውን መልእክት ያስተላልፋል።
1/ በቅዱስነታቸው ድንገተኛ ዕረፍት ምክንያት የተሰማንን ጽኑ ኃዘን እየገለጽን ከምንም በላይ በቅዱስ ሲኖዶስ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ዋነኛውና አንገብጋቢው ጉዳይ ቤተ ክርስቲያንን አንድ ማድረግ መሆኑን በአጽንኦት እንገልጻለን፤  እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ባለፈው ሐምሌ ወር ሦስተኛውን ጉባኤ አበው ለማካሄድ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነበር። ይሁን እንጂ በግንቦቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የላክነው ደብዳቤና ባለ ሰባት ነጥብ የመፍትሔ ሐሳቦች በአገር ውስጥና በውጭው ዓለም የሚገኙት አባቶቻችን በዕርቀ ሰላም ውይይቱ ላይ ለመገኘት ሙሉ ፈቃዳቸው መሆኑን ገልጸውልን ነበር። በዚህ መካከል ግን በአዲስ አበባ በኩል በሰላምና አንድነት ጉባኤው የቀረቡትን ሰባቱን የመፍትሔ ሐሳቦች አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በወርኃ ሐምሌ መግቢያ ላይ ተነገጋሮባቸው በአፋጣኝ መልስ እንደሚሰጠን በደብዳቤ ተገልጦልን ነበር።