Wednesday, November 30, 2011

ሰዶምና ገሞራ ወደኢትዮጵያ?


ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል ፈጽመው ይገደሉ ደማቸው በላያቸው ነው» ዘሌ 20፣13
በኢትዮጵያ የአራቱም ሃይማኖቶች መሪዎች በአዲስ አበባ በቅርቡ በሚካሄደው 16ኛው የአይካሳ ጉባዔን አስታክኮ በአገሪቱ ጸያፍ፣ ከሥነ ምግባር ውጭና ባህልን የሚያንቋሽሽ አጀንዳ ለማስፈጸም ተነሣሥቷል ያሉትን የአንድ ቡድን እንቅስቃሴን በመቃወም ትናንት ሊሰጡት የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ፡፡
የሪፖርተር ፎቶግራፍ ጋዜጠኛ መሪዎቹ መግለጫ ለመስጠት እንደተዘጋጁ ያነሳውም ፎቶግራፎች እንዲጠፉ ተደረገ፡፡

መሪዎቹን በመወከል መግለጫው ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቄስ ኢተፋ ጎበና ሲሆኑ፣ የጋዜጠኛው ፎቶ ግራፎች እንዲጠፉ ያደረገውም በሥፍራው የነበረ አንድ የደኅንነት አባል ነው፡፡

መግለጫው የሚሰጥበት ትክክለኛው ቀን መቼ ነው ተብሎ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹ከጉባዔው በፊትም ሆነ በኋላ ሊሆን ይቻላል፡፡ ከዚህ ውጭ ትክክለኛው ቀን ይህ ነው ብዬ ለመናገር ያስቸግረኛል፤›› ሲሉ ቄስ ኢተፋ መልሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መሪዎች በተወካያቸው አማካይነት መግለጫው ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አጽሃኖም በተገኙበት የዝግ ስብሰባ አድርገው በጉዳዩ ላይ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው፡፡

ጉልበተኛው ረባሽ!!




ቦረና ሀገረ ስብከት በክብረ መንግሥት ከተማ በጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን እስከ ህዳር 19 ቀን 2004 ዓ.ም ላለው ጊዜ የተዘረጋው የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ጉባዔ መቋረጡን በዚያው ያሉ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተደጋጋሚ እንደሚደረገው የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ቡችሎች በለኮሱት ሁከት ጉባዔው መቋረጡ ታውቋል፡፡ በተለይም የግጭቱ አስተባባሪ በመሆን ቀዳሚውን ድርሻ የወሰደው ያሬድ ውብሸት የተባለ የማኅበሩ አባል ሲሆን፣ ይኸው ግለሰብ ለማኅበሩ መረጃ በማቀበልና በመሰለል ወንድሞችን ለአደጋ የሚጥል መሆኑ ጭምር ተገልጿል፡፡ በዚሁ ጉባዔ ላይ፣ ለጊዜው ስሙና ማንነቱ ካልተገለጸ ሌላ ግለሰብ ጋር በመሆን ጠቡን እንዳስነሱት የታወቀ ሲሆን፣ ይኸው ግብረ አበር ሰዎችን ከደበደበ በኋላ ጌታዋን እንደተማመነች በግ ከተማዋ ውስጥ በነፃነት ሲንሸራሸር፣ የወንጌል መምህር የሆኑትን ቀሲስ ተስፋዬ መቆያን ለእሥራት እንዳበቋቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

የክብረ መንግሥት ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን፣ ቀሲስ ተስፋዬ መቆያ ከፊደል ቆጠራ እስከ ዲቁና ከዚያም እስከ ቅስና ያገለገሉባት፣ ጥርስ ነቅለው ያደጉባት እናት ቤተክርስቲያናቸው ስትሆን፣ የከተማዋ ምዕመናን የወንጌሉ የምሥራች ቃል እንዲሰበክላቸውና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲጎለብቱ፣ የዘማሪያንንና የሰባክያንን ወጪዎች በመሸፈን ጭምር በተደጋጋሚ የወንጌል ጉባዔ ያዘጋጁ ቅን የቤተክርስቲያን አገልጋይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Sunday, November 27, 2011

ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?




ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?to read in PDF

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዲያቆን ዓባይነህ ካሴ የተሰጠውና ስለጽላት የአዲስ ኪዳን ዘመን አስፈላጊነት ስብከቱ የተነሳ ነው። አባይነህ ካሴ ያልገለጻቸው፣ ያልመለሳቸውና ያላብራራቸው፣ ነገር ግን በምንም መልኩ ሊታለፉ የማይገባቸው ነጥቦች ስላሉ በዚህ ጽሁፍ ይዳሰሳሉ። ምክንያቱም ለክርስቲያኖች ከየትኛውም መረጃ በላይ የእምነታቸው መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን እሱም ሳይሸፋፍን ለብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ይሁን ለአዲስ ኪዳኑ ዘመን እምነት መመሪያን፣ትእዛዛቱንና መንገዶቹን በግልጽ አስቀምጦት ስለሚገኝ ነው።
ዓባይነህ ካሴ ስሜቶቹን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እያዛመደ በዚህ የጽላት ዓለም እምነት ላሉ፣ በዚያው እንዲጸኑ፣ ይህንን ለማይቀበሉት ደግሞ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ በመስጠት የሁለት ወገን ስራውን ለመስራት ሞክሯል። ይሁን እንጂ መረጃውን በማብራሪያ ለማጠናከር ከመሞከር ባለፈ በተጨበጠ ማስረጃ ማስደገፍ ባለመቻሉ ግልጽ እውነቶችን እያነሳንሥነ አመክንዮ «Give reasons or cite evidence in support of an idea, action, or theory, typically with the aim of persuading others to share one's view» እንሰጥበታለን።
ታቦት ለእስራኤል ዘሥጋ ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት
ነብዩ ሙሴ ከእግዚአብሔር ቃል እየተቀበለ ለሕዝቡ መልእክቱን ያደርስ ነበር።
ዘጸ 3፣15 እግዚአብሔርም ደግሞ ሙሴን አለው። ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ላከኝ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው።