Tuesday, February 3, 2015

የፓስተር ተከስተ ጌትነት የወሲብ ቅሌት በቪኦኤ

የዝሙትና የአፍቅሮ ንዋይ አንበሳ ያልሰበረውን መንፈሳዊ ሰው ማግኘት ከባድ እየሆነ ነው። በመጨረሻው ዘመን ላይ ሰይጣን እንደሚያገሳ አንበሳ እየዞረ ሰዎችን የሚሰብርበት ትልቁ መንጋጋው ትዕቢት፤ ዝሙትና ገንዘብን መውደድ ናቸው።
በየቤተ እምነቶቹ ትላልቅ የሚባሉት ሁሉ መንፈሳዊ አከርካሪያቸው የተሰበረው በነዚህ ወጥመዶች ነው። ጳውሎስም አለ፤ «ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤
እንደ ገና ስመጣ በእናንተ ዘንድ አምላኬ እንዲያዋርደኝ፥ አስቀድመውም ኃጢአት ከሠሩትና ስላደረጉት ርኵሰትና ዝሙት መዳራትም ንስሐ ካልገቡት ወገን ስለ ብዙዎች ምናልባት አዝናለሁ ብዬ እፈራለሁ»
2ኛ ቆሮ 12፤20-21

Thursday, January 29, 2015

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የካይሮ ጉብኝት በከፊል


የኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የሆኑት አቡነ ታዋድሮስ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ባደረጉላቸው ጥሪ ይፋዊ ጉብኝት አድርገው መመለሳቸው ይታወሳል። ፓትርያርክ ማትያስ በቆይታቸውም ከግብጽ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው በብዙ ጉዳዮች ላይ የተነጋገሩ ሲሆን የኮፕቲክ ገዳማትንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ከጎበኝታቸው በኋላ በግብጽ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር በሆኑትና ምድረ ግብጽን እስኪለቁ ከጎናቸው ባልተለዩት በአቶ ሙሐመድ ድሪር ቱርጁማንነት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በከፊል የተወሰደው ይህ ትዕይንተ ምስል የተገኘው ከራዲዮ ምስር 88.7 FM ነው።