Wednesday, January 23, 2013

"ከፍሬአቸው ታውቁአቸዋላችሁ"

(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበና ከድረ ገጹ የተወሰደ)
ምሁር ነኝ የሚሉ አረጋዊ ከሰዎች ጋር ሲነጋገሩ፥የእኛን ሃይማኖት የሚያህል ፈጽሞ የለምብለው የማውራት ልምድ ተጠናውቷቸዋል፡፡ እንዲህም ሲናገሩ ስመ ሃይማኖታቸውን እየጠሩ ነው፡፡ ቅያሬ የሌለውና የተጋነነው ከቃል ንግግር በቀር የሕይወት ምስክርነት ያልነበረው ወሬአቸው ወዳጆቻቸውንና ቤተ ሰባቸውን ጭምር አሰልችቷቸው ኖሮአል፡፡
አንድ ቀን ከአንድ ወዳጃቸው ጋር ይጨዋወቱ ነበር፡፡ እንደ ተለመደውየእኛን ሃይማኖት የሚያህል የለም፤ ብቻ ምን ያደርጋልሲሉ፤ በተከታዮች ብዛት ከሆነ እምነት ተከታዮች ይባልጣሉኮ! አለና መለሰላቸው፡፡ ትልቋ ልጃቸው ግንአባባ የእኛ ሃይማኖት ካለማመን የሚለይበትን አንድ ነጥብ ቢነግሩኝብትላቸው ምን ለማለት እንደ ፈለገች አልተረዱላትም፡፡ ልጅቷ የመደነጋገር ምልክት በአባቷ ፊት ላይ እንዳየች በሌላ የአገላለጽ ዘዬ ልታስረዳቸው ሞከረች፡፡ አባቷም ሲረዱ በጣም ተቈጡ፡፡
የአረጋዊው ምሁር አስተሳሰብ እምነታችን ጥሩ ነው፤ የእምነታችን ፍሬ ግን መራራ ነው፤ ወይም እምነታችን ፍሬ አልባ (መካን) ነው እንደ ማለት ነው፡፡ ሊሆን ግን አይችልም፡፡ አንድ ሰው ወይም ቡድን የተቀበለውና የሚመራበት የክርስትና እምነት ሕያው ከሆነ የቃል ምስክር ሳያስፈልገው ጣፋጭ ፍሬ አንዠርግጎ ይታያል፡፡

Saturday, January 19, 2013

እንኳን ለ1975ኛው ዓመት በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!




ውሃ ለሥጋችን ሕይወት ነው። ከዚያም በላይ የፍሳችንን መዳኛ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስን ሞት የምናዘክርበት ትልቅ ተስፋችን ነው። ውሃ በዘመነ ኖኅ የኃጢአት በትር ሆኖ የሰው ልጆችን የቀጣ ቢሆንም ነገሮችን አዲስ ማድረግ የባህሪው የሆነው እግዚአብሔር ውሃን በልጁ  ሞት ሞተን ፤ በኃይል ስለመነሳታችን  የምስክርነት ተስፋ አድርጎ ሰጥቶናል።
ውሃ የሞት መሣሪያ በሆነበት ዘመን «ለቀደመውም ዓለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን አድኖ በኃጢአተኞች ዓለም ላይ የጥፋትን ውኃ ካወረደ» 2ኛ ጴጥ 2፤5  ካጠፋቸው በኋላ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የትንሣዔው ኅብረት ምልክት ሆኖ፤«በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ» ቆላ 2፤12 በማለት  በትንሣዔው  ያለንን አንድነት ነግሮናል።
እንደዚሁ ሁሉ በክርስቶስ ያመኑቱ ሁሉ ሊያደርጉት የሚገባና የሕያውነት ምስክርነታቸውን የሚሰጡበት የጥምቀት ዝክረ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከከተራው ጀምሮ የጌታ ጥምቀት ተፈጽሞበታል ተብሎ እስከሚታሰበው እለት ድረስ ብዙ ሺህ ሕዝብ በተገኘበት፤ የውጪ ቱሪስቶች ለጉብኝት በሚገኙበት ሥርዓት ጥር 11/2005 ዓ/ም በጃንሜዳና በየአድባራቱ ተከብሮ እንደሚውል ይታወቃል።  በአዲስ አበባ ጃንሜዳ የተከናውነውን ሥነ ሥርዓት  ከፊል ምሥል አቅርበናል።

Friday, January 18, 2013

የአሜሪካው ሲኖዶስ መግለጫ አወጣ!


በ4ኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የሚመራው የአሜሪካው ሲኖዶስ ጠንከር ያለና መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦችን የሚያመላክት መግለጫ አውጥቷል። የሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ሕጋዊ እንዳልሆነና ሕጋዊ ሊባል የሚቻለው በአቡነ መርቆሬዎስ የሚመራው ሲኖዶስ እንደሆነ ሕገ ቤተክርስቲያንን አጣቅሶ ያቀረበ ሲሆን ከመንበር ላይ በመሰደድ ቅዱስነታቸው በቤተክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እንዳልሆኑ በማመልከት ሁሉም ስደቶች የአባቶች ጥንካሬና የምእመናን ብርታት አሰዳጆችን እምቢ በማለት አንድነትና ኅብረትን ያሳየ ሆኖ ከማለፉ በስተቀር ለመኳንንቱ ፍላጎት ይሁንታን በመስጠት ኅብረታቸውን በታትነው እንደዚህ እንደዛሬው አለመታየታቸውን በመግለጽ  መግለጫው ሰፊ ሀተታ አቅርቧል።
ወደ 6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ ለመግባት ጥቂት የሥልጣን ጥመኞች ጳጳሳት መንግሥትን ተገን አድርገው ያቀናበሩት እንደሆኑ በማመልከት በቤተክርስቲያናችን ታሪክ  ሌላኛውን ስህተት ለመፈጸም በመቋመጥ  ወደምርጫ የመሄድ አድራጎቱን በውግዘት ኮንኖታል።
 ከአባ ሰላማ ብሎግ ላይ ያገኘነውን ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ( Click here )