Thursday, July 26, 2012

ማህበረ ቅዱሳን እና የወደፊት እቅዱ!

ሐምሌ 19 2004 .. ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com) (ይህን ጽሁፍ ያገኘነው ፌስቡክ ላይ ነው። ጸሀፊው ራሱንማህበሩ ውስጥ ሆነን የማህበሩን አደጋ ገልጠን የጠቆምን የቁርጥ ቀን የቤተክርስቲያን ልጆችሲል ይገልጻል። ጸሃፊው አለኝ በሚላቸው መረጃዎች መሰረት ጽሁፉን አዘጋጅቷል። የማኅበሩን የኑፋቄ ትምህርት ጨምሮ ጊዜ የምጠብቅላቸው ሌሎች መረጃዎች አሉኝ የሚለው ጸሐፊ እንደ ውስጥ አዋቂ የማኅበሩ እቅዶች እነዚህ ናቸው ሲል ይነግረናል። እንደ ጸሐፊው እምነት ማኅበሩ ከቤተክርስቲያን ተገንጥሎ እስከ መውጣት የጨከነራዕይያለው ነው። ለዚህም የሚረዳውን ጥናት የጨረሰ ሲሆን ተጨማሪ ጥናቶችን ለማድረግ ግብጽ ድረስ ሰው ልኳል ይለናል። በብሎጋችን እንዲወጡላችሁ የምትፈልጉዋቸው ጽሁፎች ካሉዋችሁ awdemihret@live.com ብላችሁ ብትልኩልን ይደርሰናል።  መልካም ንባብ)

ማህበረ ቅዱሳን ሁለት አይነት እቅድ አለው። አንደኛው ቤተክርስቲያኒቱን መቆጣጠር ሲሆን አሱ ካልተሳካ ደግሞ ሁለተኛውን ማለትም ሂደቶችን አይቶ በቂ የሚለውን አቅም ከገነባ በኃላ ወደፊት ተገንጥሎ የመውጣት ድብቅ ራዕይ አለው፡፡ ሁለተኛው አላማውም በቤተክርስቲያን ላይ አደጋ ለመፍጠርና አባላቱን ይዞ የራሱን ቤተ እምነት መመስረት ሲሆን ጉዞውን 40 በመቶ አድርሷል፡፡ ይህን እቅዱን ለማሳካት የተጠና እስትራቴጂ አዘጋጅቶ ተግባር ላይ አውሏል፡፡

 ከእቅዶቹ ዋና ዋናዎቹ እንደሚከተሉት ይቀርባሉ
1- ወደፊት ማህበሩ ቤተክርሰቲያኒቱን ከተቆጣጣረ ወይም ደግሞ ከተገነጠለ የራሱ አገልጋዮችን ብቻ መጠቀም ስለሚፈልግ ለሚገነጥለው ቤተ እምነት አገልጋይ እንዲሆኑ ካህናትንና መነኮሳትን በገዳማትና በአብነት /ቤቶች በጥንቃቄ ማሰልጠን እንዲቻል ከፍተኛ በጀት መድቧል፡፡ ይህን ስውር ተልእኮ ሊቃነ ጳጳሳቱ ነቅተው እንዳያስቆሙት በዘዴና በጥንቃቄ መያዝ
2- ጵጵስና ለቀሳውስት እንዲሰጥ በቅ/ሲኖዶስ ግፊት እንዲያደርጉ የማህበሩ አባላት የሆኑ ጥቂት ጳጳሳትን ማሳመን በዚህ ጉዳይ ጥናት እንዲሰሩ ስንታየሁ የተባሉ አንድ ቄስ ግብጽ ሃገር ተልከዋል፡፡
3- በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ የማህበሩን አላማ በስውር የሚያስፈጽሙ ጳጳሳት እንዲሾሙ ማህበሩ መነኮሳትን መልምሎ በምርጫው ግዜ አባቶች ድምጽ እንዲሰጣቸው በየቤታቸው እየዞሩ የማግባባት ስራ መስራት፡፡ ማግባባቱ ለሃገረስብከታቸው እስከ ሁለት መቶ ብር በጀት ድጎማ ማድረግን፣ በግል እጅ መንሻ ማዘጋጀትን በአንዳንድ በልማት እቅዶቻቸው ውስጥ የማማከር ድጋፍ ማድረግን ይጨምራል፡፡ ለቤተክርስቲያን ቢጠቅሙም ለማህበሩ አካሄድ ግን አደገኛ ናቸው ያሏቸው አባቶች እንዳይሾሙ አባላት በሆኑ ጥቂት አባቶች በኩል መታገልና በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ወቅት በእያንዳንዱ ሊቃነ ጳጳሳት ማረፊያ ተሰሚ የሆኑ አባላትንና አንዳንድ ባለጸጎችን በመላክ የማሳመን ስራን መስራት፡፡ እንቢ ያሉትን ማስፈራራት
4- የማህበሩን አካሄድ ትክክል አይደለም መታየት አለበት የሚሉ ጳጳሳትን ሰባኪያንን የአስተዳደር ሰዎችንና የመንግስት አካላትን ህዝቡ እንዲጠላቸው መናፍቃን ሆነዋል ተወግዘዋል ሌላ ተልእኮ አላቸው ወዘተ የመሳሰሉትን ቀለሞች በመቀባት ሃይላቸውን ለማድክም መሞከር፡፡ ይህን በአሜሪካና በአውሮጳ በገንዘብ የሚደግፍ ኮሚቴ በነያሬድ /መድህን በነዳንኤል ክብረት በነህብረት የሺጥላ በነፋንቱ ወልዴ በነዶ/ መስፍን የተቋቋመ ሲሆን ኮሚቴው የማህሩን የጥፋት አላማ የሚያደናቅፉትን ሁሉ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው በፋይናንስ መደጎም ሲሆን በስውር ሲዲ እያዘጋጁ መበተን፣ ስብሰባ እያዘጋጁ ባለጠጎችን ቤተክርስቲያን ልትፈርስ ስለሆነ እንድረስላት ገንዘባችሁን ስጡን በማለት የማህበሩን አቅም ማደራጀት፣
5- ለጥምቀት ምንጣፍ የሚያነጥፉ የዋህ ወጣቶችን ቀስ ብሎ ወደ ማህበሩ በማስገባት ቤተክርስቲያን አደጋ ላይ ነች ድረሱላት በማለት የአመጽ ትምህርታቸውን አስተምሮ ወደ ነውጥ እንቅስቃሴ እንዲገቡ በማድረግ ተጨማሪ ሃይል እንዲሆኑ ማሰልጠን፣
6- በአዲስ አበባ እና በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የሰንበት /ቤቶች ሰርጎ መግባትና የማህበሩን መሰረት ማስፋት ካልተቻለ በየአጥቢአው ቢሮ በመክፈት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን መበጥበጥ እና ማፈራረስ
7- በመንግስት ፖለቲካ ውስጥ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነት በተጠና ሁኔታ ማጠናከር ይህም በሃገር ውስጥ ያሉ አባላት መንግስት እንዳይመታቸው የቤተክርስቲያኑን ጉዳይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ በውጭ ያሉት ግን የተለያዩ ሚዲያዎችን እየተጠቀሙ መንግስትን እንዲቃወሙ ተደርጎ እስትራቴጂው ተቀርጿል፡፡ ደጀ ሰላም፣ አንድ አድርገን፣ደቂቀ ናቡቴ፣ savewaldeba, ecadforum … የተባሉትን ድረ ገጾች በመጠቀም ጸረ ሰላም ቅስቀሳዎችን ማጠናከር ፡፡
8- ማህበረ ቅዱሳንን ራሱን ችሎ እንዲወጣ የገንዘብ አቅሙን ቋሚ በሆነ ሁኔታ ማጠናከር ይህም የማህበሩን ህንጻ መገንባት፣የቤተክርስቲያን ልጆች በተለይ መንግስት ሰራተኞች ለቤተክርስቲያናቸው ሳይሆን ለማህበሩ አስራት አንዲከፍሉ ማድረግ፣ በተለያዩ ቦታዎች የንግድ ተቋማትን መመስረት፣ አንድ ባንክ በአባላቱ አክስዮን (እንቅስቃሴው ተጀምሯል።) መክፈት ወዘተ
9- በቤተክርስቲያን መድረኮችና በግል ሚዲያዎች ላይ የህዝብን ሰላም የሚያውክ የጽንፈኝነት ቅስቀሳ ማጠናከር፡፡ ይህን እንዲመሩ የተወሰኑ መምህራንን መድቦ ጽንፈኝነትን በሃይማኖት ቤተሰቦች ላይ ሽብርን እና ቅራኔን በሃማኖቶች መካከል የማስፋት ስራን አጠናክሮ መቀጠል፣ እንዲሁም በአንዳንድ የአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ አርባ ምንጭ፣ደሴ፣ በአውሮፓ አሜሪካ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባሉ ትላልቅ አብያተክርስቲያናት ያሉ መምህራንን በጥቅም በመደለል በቤተክርስቲያን መድረክ ማህበሩን ማስተዋወቅ ችግር ተፈጥሯል፣ ቤተክርስቲያን መሪ የላትም ሲኖዶሱ የሞተ ነው መንግስት ቤተክርስቲያንን እየገደለ ነው እያሉ ሁከት በመፍጠር ህዝቡ እንዲታወክ ቤተክቲያንን እንዲሰለችና እረኞቹን ከበጎቹ ነጥለው ወደ አዲሱ ቤተእምነታቸው እንዲቀላቀሉ መሳብ

10- ቤተክርስቲያን በራሷ እንዳትተማመን በስነ ልቦና ጦርነት ማሽመድመድ ይህም ጠንከረው የሚሰሩ ሰባኪዎቿንና ሰራተኞቿን በሃይማኖት ስም ከስሶ በማዳከም ፈሪ እንድትሆን ማድረግ ዝም ማሰኘት፡፡ ልጆቿን በየአሉበት ፈልጋ እንዳታስተምር ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ ሰብካ ወደ በረቷ መስብሰብ እንዳትችልማከላከል የንስሃ አባቶች እንኳ ልጆቻቸውን በየቤታው ሄደው እንዳያስተምሩ፣ በቤተክርስቲያን ግቢ የሚደረጉ ጉባኤዎችን የመናፍቃን እጅ አሉባቸውና ምእመናን እንዳይሄዱ ቅስቀሳ ማድረግ፣ማህበረ ቅዱሳን ከጠራው ጉባኤ ውጭ ሌሎቹ የተሳሳቱ አድርጎ ማቅረብ፣ መዝሙር እንዳይዘመር፣ ሰባኪዎችን ሁሉ ሰው እንዲፈራቸው፣ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ቤተክርስቲያን ዝም እንድትል እና ሌሎች እንዲቀድሟት ለማድረግ አባቶችንም ስርአት ተጣሰ ህግ ፈረሰ ብለው በማደናገር ለክፉ ተልኮአቸው ተባባሪ እንዲሆኑ ማድረግ።

Tuesday, July 24, 2012

አቢሲኒያ የሚለውን ስም ከእኛ ይልቅ ነጮቹ ይጠቀሙበታል!


የዛሬዋ ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ታላቅ ሀገር እንደነበረች ታሪክ ይናገራል።  በግዛት ስፋት፤ በጦር ኃይል ብዛት፤ በሥነ ሕንጻና በሥነ ጽሁፍ ገናና ሆና መቆየቷን የሚናገሩ ብዙ የታሪክ ድርሳናት አሉ። በእርግጥ ብዙዎቹም ድርሳናት የተጻፉትና በሰነድነትም የሚገኙት በውጪው ዓለም ነው። አቢሲኒያ የሚለው ስም የትመጣነት ለታሪክ ሀተታ ይቆየንና ኢትዮጵያ የሚለው / ጥቁር መልክ/ ስያሜ ከመሰጠቱ በፊት አቢሲኒያ የምትባለው ሀገራችንን ታሪክ አብዛኛው የምናውቀው « የኢትዮጵያ የቀድሞ ስም» የሚለውን ጥሪ ብቻ ነው። ግፋ ቢልም «አቢሲኒያ ባንክን» !!!
ታሪካዊነቱን የሚገልጽ መታሰቢያ ዩኒቨርሲቲ፤ የጎዳና ስም፤ ሆስፒታል ወይም ሌላ ተመሳሳይ መጠሪያ እስከምናውቀው ድረስ የለንም። ምናልባት ያልሰማነው ካለ ይታረማል። ታሪክና ቅርስ ለአንድ ሀገር ሕዝብ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ማንነት ወሳኝ ነው።  በዘመናት ያለፈባቸውን የጥንካሬና የድክመት ጉዞዎቹን ይቃኝበታል። መጻዒውንም ያማትርበታል።
እስራኤሎች ታሪካቸውን እየጻፉ ለመጪው ትውልድ የሚያኖሩላቸው ጸሐፊያን በየዘመኑ ነበራቸው። በሕይወታቸው ያለፈውን፤ ያደረጉትንና የተደረገላቸውን እየከተቡ ያኖሩ ነበር።
1ኛ ነገ 43
«ጸሐፊዎቹም የሴባ ልጆች ኤልያፍና አኪያ፥ ታሪክ ጸሐፊም የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ»
የእያንዳንዱ ነጋሲ ታሪክና ሥራ እየተጻፈም ይቀመጥ ነበር። ይህም ለልጅ ልጆች የሚቀመጥ ውርስ ነበርና ነው።
1ኛ ነገ 1532
በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን?
እኛ ለዚህ አልታደልንም።

 እንኳን እንደዚህ ዓይነት ታሪክ ጽፈን ለማቆየት ይቅርና በዘልማድ  ስለምናውቀው «አቢሲኒያ» ስለሚለው የሀገራችን ስም መታሰቢያ የሚሆን ነገር የለንም። ይሁን እንጂ ፈረንጆቹ በመጽሐፍ ቅዱስ «ኩሽ» በታሪክ አቢሲኒያ፤ በመጠሪያ ደግሞ ዛሬ ኢትዮጵያ ስለምትባለው ሀገራችን የእምነት፤ የጀግንነት፤የታሪክ፤ የቅርስና የመልክዓ ምድር ወዘተ ሰፊ ጥናት አድርገዋል። መጻሕፍትንም ጽፈዋል።
ፈረንሳዊው የታሪክ ጸሐፊ  ጂን ክሪስቶፍ ሩፊን/Jean-Christophe Rufin/ ዘ አቢሲኒያን፤ ሳሙኤል ጆንሰን፤ ጀምስ ብሩስ፤ሪቻርድ በርተን፤ ኢቭሊን  ዎግ፣ ዴርቭላ መርፊ፤ ሲልቪያ ፓንክረስት፤ ኸርበት ቪቪያን፤  ሮማን ፕሮቼስካ ፤ ጆንስ እና ኤልሳቤጥ/ መጽሐፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ /  ወዘተ እና ሌሎች ብዙዎች ጸሐፊያን ስለአቢሲኒያ ጽፈዋል።

 ይህንኑ ገናናውን የአቢሲኒያን ታሪክ ተከትሎና ከጥቁር ምድር ቀዳሚ የክርስትና ሀገር ኢትዮጵያ በመሆኗም ጭምር አሜሪካውን ጥቁሮች ቤተክርስቲያኖቻቸውን ጭምር በምድረ አሜሪካ ውስጥ በአቢሲኒያ ስያሜ ይጠሩ ነበር።  ኮሎራዶ በ516ኛው ክሬስትሞር ጎዳና ላይ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን ክርስቲያኖች ቤተክርስቲያን፤  ኒውዮርክ በምእራብ 138ኛው ጎዳና ላይ በ1808 የታነጸው የአቢሲኒያውያን መጥምቅ ቤተክርስቲያን፤ 1828 ዓ/ም በ75 ኒው በሪ ጎዳና የተመሰረተው የፖርት ላንድ አቢሲኒያውያን ቤተክርስቲያን፤ እዚው ፖርት ላንድ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን የመሰብሰቢያ አዳራሽ፤  ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ በኢትዮጵያ የቀድሞ ስም በአቢሲኒያ ስም የተጠሩ የአሜሪካ ጥቁሮች የታሪክና እምነት ስያሜ መጠሪያዎች ነበሩ። ዛሬም በዚሁ ስም እየተጠሩበት ይገኛሉ። ብዙዎቹም እናት ምድራችን በሚሏት አቢሲኒያ /ኢትዮጵያ/ ተገኝተው ታሪኳን ቅርሷን፤ ክብሯን ሁሉ በአካል ለማየት ችለዋል። ያ ሁሉ ዝናና ታሪክ ተንኮታኩቶ የድሆች መናኸሪያ፤ የስደተኞች መፍለቂያ መሆኗን ሲያዩ ምን ብለው ይሆን?
አብያተ ክርስቲያኖቻቸውን በአቢሲኒያ ስም ከመጥራት ባሻገር አቢሲኒያን በተለያየ ዘመናት የረገጡ ነጮች ከምድረ አቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ፤ ድብ፤ አሳማ፣ እጽዋት በመውሰድ በሀገራቸው አራብተዋል፤ አዳቅለዋል።  
ዛሬ በአሜሪካ የአቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ ወዘተ በስም ተለይቶና ተመርጦ የሚገዛበት ትልቅ  ስም ነው። እንዲያውም ተፈላጊ መለያ ነው።
የአበሻ ውሾች ቁጡዎችና ኃይለኞች፤ ድመቶቹ አይጥ አዳኞች፤ ፈረሶቹ የጦር ሜዳ ዘመቻ ጋላቢዎች ስለነበሩ እየወሰዱ ተዳቅለዋል። ሳንዲያጎ በሚገኘው ግዙፉ የእንስሳት ፓርክ ውስጥ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ አእዋፍና አሞራዎች አሉ። የአቢሲኒያ ድመቶች ማደቀያ ማኅበር ራሱን ችሎ በአሜሪካና በእንግሊዝ የተቋቋመ ነው።  እንስሳዎቹም በአቢሲኒያ ስም እስከዛሬ ይጠራሉ።
ከታች የሚታዩት ስእሎች በ«አቢሲኒያ» ስም ከሚጠሩ መካከል ጥቂቶቹ  ናቸው።

Sunday, July 22, 2012

ለማኅበረ ቅዱሳን ፍርሀት የሆነው ጉባኤ አርድዕት በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ።


ብዙ ጊዜ ስለማኅበረ ቅዱሳን በሚቀርቡ ጽሁፎች ላይ አስተያየት የሚሰጡ የማኅበሩ አቀንቃኞች የሚያዩን  ስለማኅበሩ ጭፍን አመለካከት እንዳለንና ሥራውን ሁሉ እንደምናቃወም አድርገውን ነው። ይሁን እንጂ ማኅበሩ እንደማኅበር የሰዎች እንጂ የቅዱሳን መላእክት ስብስብ ባለመሆኑ በጉዞው ውስጥ መልካምም ይሁን መጥፎ ሰውኛ ድክመቶች የሚገለጽበት መሆኑን ሁሉም አምኖ እንዲቀበልና ጥንካሬው ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ እንደሚሆን ሁሉ ድክመቱም አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያመጣ በመገንዘብ ራሱን እንዲያይ፤ እኛም ማን መሆኑን በማወቅ የተሻለ ግንዛቤ ይዘን እንደባህሪው  የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ ነው። ለስህተት ትምህርቶችን የአዞ እንባ አፍሳሽነት፤ የሁሉን አውቃለሁና ጠበቃ ነኝ ባይነት መጥፎ ዐመል፤ የእኔ ላቡካው፤ እኔው ልጋግረው ግብዝነት፤ ከቤተክርስቲያኗ ኪስ ወደራስ ጓዳ የመሰብሰብ አባዜ፤ የሰላይ፤ የመቺ፤ የአሳዳጅና የፈራጅ ቡድን የማዋቀር ሲሲሊያዊ አካሄዱን ነቅሰን በማውጣት ይህን፤ ይህን ስትሰራ ቆይተሃል፤ ይህን ይህንንም እየሰራህ ትገኛለህ፤ መረጃዎቻችንም እነዚህ ናቸውና ከተነቃብህ እራስህን አርም፤ አስተካክል ወይም ቢያንስ ራስህን እስኪ  ጠይቅና ከሚወራው ውስጥ የትኛው እውነትና የትኛውስ ስም ማጥፋት ነው ብለህ ፈትሽ በማለት ለማሳሰብ ነው።  እኔ ቅዱስ እንጂ ስህተት የማይጎበኘኝ ነኝ ማለት ሲያበዛ ደግሞ አንተ ፈሪሳዊ ሆነህ ሳለ መጸብሐዊው አይጸድቅም የምትል ግብዝ ነህና መንገዳችንን አትዝጋ፤ የናቡከደነጾር የህልም ሀውልት ስለሆንክ ከተራራው የሚወርደው ዐለት ይፈጭሃልና ግዙፍነትህን አይተህ አትመካ እንለዋለን። ሌላውም  እንዲያይ የእስከዛሬ ማንነቱን ገልጠን ለሌሎች እናሳያለን። በዚህም ሥራችን ብዙዎች ራሳቸውን እንዲጠይቁ፤ የሚባለውን እውነትነት እንዲመረምሩ አድርገናል። በዚህም የመረጃ ስርጭትና ማንነቱን የመግለጽ ሥራችን ግምገማቸውን ወስደው ራሳቸውን ከማኅበሩ ክፉ ስራ ያገለሉ ብዙዎች ናቸው። ተሸፍኖ የነበረባቸውን የማኅበሩን ማደንዘዢያ መርፌ ነቅለው ከድንዛዜ ወጥተው፤ እስከዛሬ የት ነበርኩ? ያሉና ራሳቸውን የጠየቁ ብዙዎች ናቸው። ከዚህ በታች ያለውም የማኅበረ ቅዱሳን አቀንቃኝ ብሎጎች ማጭበርበርና የነፍስ ውጪ፤ ነፍስ ግቢ ውሸት ማሳያ ቀርቧልና  ሄዳችሁ ብሎጎቹን አንብባችሁ ከታች በቀረበው መረጃዎች ላይ ተመርኩዛችሁ ማቅ ማን መሆኑን ተመልከቱ! ሁሌም ውሸት! ውሸት! ውሸት! አቤት ማቅ?
ምንጫችን፤ ዓውደ ምሕረት ብሎግ፤

  •     ሊቀ ሥዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ መኪና አልተቀማም
  •     ጉባኤ አርድእት ስብሰባ እንዳይሰበሰብ አልታገደም
  •     መንግስት ለማኅበረ ቅዱሳን የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ማንም አልሰማም በማለት ወደ ጉባኤ አርድዕት ለማዞር ሞክረዋል
የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በተለመደው ዋሾ ባህሪያቸው ያልሆነውን ሆነ እያሉ መዘገብን ቀጥለውበታል፡፡ ስለጉባኤ አርድዕት በመፈራረቅ በሰሩት ዜናም ገና በመደራጀት ላይ ያለውን ጉባኤ ተፈረካከሰ ተልፈሰፈሰ ሄደ ተመለሰ እያሉ የጅል ምኞታቸውን ይነግሩን ይዘዋል፡፡ ሊቀ ሥዩማን ኃይለጊዮርጊስም በጠቅላይ ቤተክህነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ፊርማ መኪናው ስለተበላሸ ቅያሪ መኪና እንዲሰጠው የትብብር ደብዳቤ እንደተፃፈለት እያወቁ  ደብዳቤውን ከኛ በቀር ማንም አያገኘውም በማለት ተበላሽቶ ወደ ጋራዥ የገባውን መኪና ተቀማ በማለት ዘግበዋል፡፡
እነዚህ የማኅበሩ የውሸት ቃል አቀባይ የሆኑ ደጀ ሰላምና አንድ አድርገን የተባሉት ብሎጎች በጉዳዩ ላይ እርስ በእርሳቸው እንኳ መስማማት አቅቷቸዋል። ዋሽቶ ስምምነት የት አለና? ደጀ ሰላም ኃይለጊዮርጊስ መኪና የተቀማው በአቡነ ጳውሎስ ትዕዛዝ ነው ብላ ጀምራ ወደ ታች ወደ ወረድ ሲባል ደግሞ በምክትል ስራ አስኪያጁ በተስፋዬ ነው በማለት ራስዋን ተጣልታ ዘግባለች። አንድ አድርገን ደግሞ በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ነው ትላለች።
እውነታው ግን ሌላ ነው በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ፊርማ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው የኃይለጊዮርጊስ መኪና በብልሽት መቆምዋን እና እንዲያውም ተለዋጭ መኪና እንዲፈለግለት ልማትና ክርስቲያናዊ መምሪያን የሚጠይቅ ነው።
 ደብዳቤውን ለማንበብ ( እዚህ ይጫኑ )