Friday, July 20, 2012

የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን በስራዬ ጣልቃ እየገባ ስላስቸገረ አደብ ይያዝልኝ አለ

(ሐምሌ 13 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)ማኅበረ ቅዱሳን በማን አለብኝነት ወዋቅራዊ አሰራርን በመጣስ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሥራ ላይ ጣልቃ በመግባት በስሩ የሚገኙ ገዳማትንና አድባራትን ሰበካ ጉባኤ ስብሰባ እየጠራ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን ከሶስተኛ ወገን የሚገናኝበትን መመሪያ እየጣሰ ይገኛል ሲል የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አስታወቀ፡፡ ለተጻፈው ደብዳቤ ( እዚህ ይጫኑ )
ይህ የመዋቅር ጥሰት አግባብ ያልሆነ ስለሆነ ሃገረ ስብከቱ “…ማኅበሩ በሃገረ ስብከታችን ጣልቃ እየገባ የሚያስተላልፋቸውን ጥሪዎችና የመዋቅር ጥሰቶች እንዲያቆም…”የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አካሄዱን የሚያተካክልበት መመሪያ እንዲሰጥልን እናሳስባለን ብሏል፡፡
ከፅንሰቱ ጀምሮ አመጽ በቀል የሆነው ማኅበር እኔ ያልጣድኩት ድስት አያስፈልግም እያለ በተለያየ ሥራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ለቤተክርስቲን የሚጠቅም ሥራ ከመስራት ይልቅ የማኅበሩን ገጽታ በመገንባት ሥራ ላይ ተጠምዶ ይገኛል፡፡  ህዝብ ወደ እግዚአብሔር እውነት የሚደርስበትን መንገድ ከማመቻቸት ይልቅ ቤተክርስቲያን ያለህዝብም ቢሆን በማኅበሩ ቁጥጥር ሥር የምትውልበትን ስራ በመስራት ላይ ያለው ማኅበር ባልተፈቀደለት የስራ መስኮች እየገባ በማን አለብኝነት እየበጠበጠ ነው፡፡
ደፋሩ ማኅበር ለመምሪያዎች ከተለያዩ አካለት የሚመጡ በየስልጠና ጥሪዎችን መምሪያዎች ውስጥ ባሉ ሰዎቹ አማካኝነት ደብዳቤ እያስከፈተ መምሪያው ሳያውቅ በመምሪው ስም ስልጠናዎችን የማኅበሩ ሰዎች እንዲወስዱ እያስደረገ መሆኑ ሲታወቅ ከዚህ በፊት እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲከሰት ከማዘን ያለፈ ተቃውሞ ሳይሰማ ቀርቶ ነበር፡፡ ይህም የልብ ልብ እየሰጠው በሃገረ ስብከቶችና በአጠቃላይ በቤተክኅነቱ ስራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ማኅበረ ቅዱሳን ወይም ሞት ፉከራን እያሰማ ይገኛል፡፡
እንደ አንድ አለሌ ሽፍታ የተወሰኑ እበላ ባይ ጳጳሳትን ማስገበሩ የልብ ልብ እየተሰማው ምንስ ባደርግ ምን እሆናለሁ ያሻኝን ሰርቼ ወጥቼ እገባለሁ እያለ በአንድ መጠምሻ ጎረምሳ ስሜት የሚንቀሳቀስ ማኅበር መሆኑ ለቤተክርሰቲኒቱ አደጋ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል፡፡
የቤተክርሰቲያንን ክፍተት ለመሙላትና አደጋዋን ለመቅረፍ በሚል አባባይ ቃል የታገዘው የማኅበሩ አካሄድ ግቡ ቤተክርስቲኒቱን በማኅበሩ መተዳደሪ ደንብ እንድትመራ ማድረግ ሲሆን ዶግማዋም ቀኖናዋም ማኅበሩ እንዲሆን የሚያስገድድ አካሄድ እየተከተለ መሆኑ የአደባባይ ሚሥጢር ሆኗል፡፡
የአንድ ተቋም ትክክለኛነት ከሚለካበት መንገድ አንዱ ህጋዊ መዋቅሮችን አክብሮ መንቀሳቀስ መቻሉ ነው፡፡ ያለ ሕጋዊ መዋቅር ህግ እና እውነት የበላይነት ይዘው መቀጠል የማይችሉ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግን ህግ የት እንዳለ የሚያስታውሰው ሌሎችን ለመምቻ የሚጠቅመው ከሆነ ብቻ ነው፡፡ የማኅበሩን ፍላጎት ለማስጠበቅ  ግን እስካዋጣው ድረስ በህጋዊ አሰራር እሱም ካላዋጣ የወንጀል ድርጊቶችን ጨምሮ የትኛውንም ህገ ወጥ አካሄድ ለመጠቀም ወደ ኋላ የማይል ድርጅት መሆኑን እስካሁን ያሉት ተሞክሮዎቹ ያስረዳሉ፡፡ 

ለሁሉም ነገር መልካም ጤንነት ይሁንልዎ!


መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው። ሰሞኑም መታመማቸውን ከሰማን ጊዜ ጀምሮ ሞታቸው እንዲቃረብ ከሚጸልዩት ጀምሮ ፤ በሀገሪቱ ውስጥ እየታየ ባለው የልማት እንቅስቃሴ ላይ አንድ ምዕራፍ ላይ ሳያደርሱ በሞት እንዳይሉ እስከሚማጸኑት ድረስ አይተናል። ከዚህ በተለየም  በሦስተኛው ረድፍ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሞት የማይመኙ ነገር ግን በሀገሪቱ ውስጥ ብዙ በደል ስላደረሱ፤ ከህመም ኃያልነት የተነሳ ጠላቶቼ ከሚሏቸው ወይም ከሚጠሏቸው ጋር እርቅን የሚፈጽሙበት ጊዜ  እንዲሆንላቸው የሚመኙትንም  ተመልክተናል።
እንደሚታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ መሪ ናቸው። መሪነትና የፖለቲካ ስልት እንደማይነጣጠሉ ሁሉ ከፖለቲካ አስተሳሰብ በሚመነጭ አመራር ሀገሪቱን እየመሩ 21 ዓመታትን አሳልፈዋል። በዚህ የአመራር ዘመን ያልተደሰቱ እንዳሉ ሁሉ በእሳቸው አመራር የሚመኩ መኖራቸው አይካድም። የዚህ ጽሁፍ ዓላማ የተደሰቱባቸውና ያዘኑባቸውን ሰዎች ማንነትና የፖለቲካ ልዩነት፤ ምንነቱንና አፈታቱን ለማብራራት ስላልሆነ ያንን ለሚተነትኑ ሰዎች ትተን በጤናቸው ዙሪያ ማለት በሚገባን ላይ ለማተኰር ነው።
እንደእኛ እምነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህመም  ወይም በሌላ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩ የኢትዮጵያ ችግር ሁሉ አብሯቸው ይወገዳል ብለን አናስብም። የጠቅላይ ሚኒስትሩም በህይወት ረጅም ዘመን መኖርም እንደዚሁ የሀገሪቱ የተጠራቀመ የዘመናት ችግርና ውስብስብ የፖለቲካ ባህል ባንድ ጊዜ ያበቃለታል ብለን አንጠብቅም።
ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያን ሁኔታ ከእሳቸው መኖርና መሞት ጋር በሚያዛምዱ ሰዎች ዘንድ ያለን ልዩነት ከነባራዊ ሁኔታ የሚነሳ ስለሆነ የጠቅላይ ሚኒስትሩን መታመም እንደ መልካም አጋጣሚ በመመልከት ሞታቸውን በሚጠባበቁ ሰዎች በጣም እናዝናለን።  ስለሞቱ ማንም ምስጥ ሆኖ አይበላቸውም። በሕይወት ቢኖሩም ማንም  ቤተመንግሥት ገብቶ በምኞት ወንበሩን አይረከብም።
ለሁሉም ጊዜ አለው እንዳለው ሰሎሞን!
የሚወዳቸውም ቢኖር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ጥላቻ ላላቸው ሰዎች ማማካሻ መስጠት ስለማይችል፤ ለጥላቻችንም ሆነ ለፍቅራችን እንደሰብአዊ ፍጡር ዳርቻ ቢኖረው  ጥሩ ነው። ሚዛናዊ ሰዎች ብንሆን እግዚአብሔር በዚህ አመለካከት ይደሰታል እንጂ ቅር አይሰኝም።
 አንዳንድ ጊዜ በአጭሩ የምንመኘው ነገር ረጅም ጠባሳ ሊያደርስ ይችላል። ለምሳሌ ያህል የኢራቁ መሪ ሳዳም ሁሴን ግንድ ላይ በስቅላት በመቀጣቱ ተበድናል ያሉቱ ተደስተው ነበር። የሚወዱት ደግሞ በሞቱ እጅጉን አዝነው እንደነበር አይዘነጋም። ሳዳም ያልፈጠራቸውን ሰዎች እየገደለ ነፍስና ሥጋቸውን በመለየቱና ለዚህ ድርጊቱ እሱም የእጁን ማግኘት አለበት በማለት  በተመሳሳይ መንገድ ያልፈጠሩት ሰዎች የሳዳምን ነፍስና ሥጋ   ግንድ ላይ በሞት ለይተዋል።  ሳዳም  ያልፈጠራቸውን ሰዎች ገደለ፤ ሳዳምንም ያልፈጠሩት ሰዎች ገደሉት። ሁለቱም  ያልፈጠሩትን ሰው በመግደል አንድ ናቸው።
እንደዚሁ ሁሉ ለአቶ መለስ ስህተቶች፤  ሞታቸው  ለእኛ ማካካሻ ይሆናል ማለት የደካማ አስተሳሰብ ውጤት  ነው። ምክንያቱም  በሳዳም ሞት ምክንያት ያልፍልናል የሚል አስተሳሰብ የነበራቸው ኢራቃውያን  እንኳን ሳይቀሩ  117,000  ሞተዋል። 4 ሚሊዮን ኢራቅን ጥለው ተሰደዋል። ሳዳም ከበደላቸው ይልቅ የሳዳም ድንገተኛ ስቅላት የፈጠረው የኢራቅ ቀውስ ከባድ ነው። ዛሬም አላባራም። በሀገራችንም አፄውን ሌባ ሌባ ያሉና በሞታቸው እልል ያለ ሁሉ በቀይ ሽብር ወዮ! ወዮ! ለማለት ዓመት አልፈጀባቸውም። ስለዚህ አሁን ይሆን ዘንድ የምንመኘውን ነገር ቆይቶ ምን ይከተለዋል ማለቱ ጠቃሚ ነው።
 እንደዚሁ ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንደህልም አላሚዎቹ በድንገት ቢሞቱ፤ በሚፈጠረው ክፍተት ሀገሪቱ ችግር ላይ አትወድቅም ብሎ ማሰብ የዋህነት ይሆናል። ሥልጣናቸውን የሚመኝ ማንም ስለተመኘ አያገኝም። በድንገተኛ ሞት ምክንያት በሚፈጠር ቀውስ ሥልጣን ወደ ደም ማፋሰስ ሊያመራ፤ ሕዝቡንም ሊያቃውስ ይችላል። ቢያንስ ቢያንስ፤ የመተካካት ሁኔታ እስኪኖር የሃሳብና የአመለካከት ሽኩቻ መኖሩን የማይጠረጥር ቢኖር እሱ የዋህ ነው። ለሀገርና ለሕዝብ የሚያስብ ሰው በአቶ መለስ ሞት ሳይሆን ሥልጣን በሕጋዊ መንገድ በሕይወት ሳሉ እንዲሸጋገር መመኘት የተሻለ መሆኑን ማሰብ እንጂ ህመማቸው አጣድፎ ሞታቸውን እንዲያቃርብ ማለም ከጤነኛ አእምሮ የሚመነጭ አይደለም።
ሥልጣን ምን ጊዜም  በሕዝብ ፍላጎትና ምርጫ በሰላማዊ መንገድ ሽግግር እስካልተደረገበት ድረስ ቀውስና ብጥብጥ  ሊከተለው ይችላል። ስለዚህ እንደ ደጀ ብርሃን ብሎግ እምነት፤
1/ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንደ ማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር ከደረሱበት ህመም ድነው ፈውስና ጤንነት እንዲጎበኛቸው እንጸልያለን። ለታሰሩ፤ ለተሰደዱና በሀገሪቱ ውስጥ በሰላም መኖር ለሚፈልጉ ሁሉ መንግሥት አባት ነውና ይቅር እንዲሉም እንመኛለን።
2/  አንዳንዴ ከዚህ ዓለም ገዢ የፖለቲካ መንፈስ ወጣ ብለው፤ ከሞት በኋላ ስለሚኖረው ህይወት በማሰብ  ቢያሳልፉ ይጠቀማሉ እንጂ አይጎዱም እንላቸዋለን። በጤንነት ዘመን መሪነት እንዳለ ሁሉ በጤንነት መጣት አልጋ ላይ መዋል፤ ሞትና ከሞት በኋላ  ስላለው ነገር ማሰቡን ባይረሱ ምክራችን ነው።
3/  ለመሥራትም፤ ለመስማማትም፤ ይቅርም ለማለትና ከፖለቲካው መንፈስ ለመውጣትም ቢሆን የእርስዎ ጤና መሆን አስፈላጊ ነውና እግዚአብሔር ጤናውን እንዲያድልዎ ጸሎታችን ነው።
 ለሁሉም ነገር መልካም ጤንነትና የቀና ሃሳብ መጻዒ ጊዜ ይሁንልዎ!

Thursday, July 19, 2012

«ደጀሰላም» ብሎግ እንዴት እንደሚያጭበረብር ተመልከቱ!


 የማቅ አፈቀላጤ ስለሆነውና ከዳላሱ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ራሱን ስለገነጠለው ቄስ መሥፍን ማሞ አዲስ የሥራ ፈጠራ ጉዳይ በ10/11/2004 ወይም በ(17/7/2012) ዓ/ም  ዝርዝር ሀተታ ደጀብርሃን ብሎግ ማስነበቧ ይታወሳል። ከዚያም  ስለ ላስቬጋስ ኪዳነ ምሕረት ጢም አልባው መነኩሴ ጥቂት ዳሰሳ አድርገን ወደምእራቡ ክፍለ አሜሪካ ተጉዘን፤ በመምህር ወ/ሰማዕት ስለሚመራው ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን የማቅ ሰርጎ ገቦች እያደረሱ ስላለው የህውከት አገልግሎትና የረጋውን ወተት የመበጥበጥ ተልእኰ ከጠቃቀስን በኋላ የካሊፎርኒያና የዲሲ አካባቢ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ አባታዊ ጉብኝት ለማድረግ ወደ ሲያትል ደ/ም  ቅ/ አማኑኤል ቤተክርስቲያን  እንደሚያመሩ ዘግበን እንደነበር ይታወሳል።
አስቀድመን እንደዘገብነው የማቅ ሰርጎ ገብ በጥባጮች፤ በሀገር ቤቱ እንቅስቃሴ እየተዳከሙ ሲመጡ የውጪውን ሀገረ ስብከት የመጠብጠጥ እቅድ ነድፈው፤ የቆየ  ዐመላቸውን እየተገበሩ ይገኛሉ። በቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ጉብኝት ያደርጋሉን የሰማው መምህረ ህውከት ማቅ አንድም ቀን ተኝቶላቸው እንደማያውቀው ሁሉ አስቀድሞ ጆሮውን አቅንቶ የብጥብጥ አጁን በመዘርጋት እንቅፋት መፍጠሩን ቅንጣት ሳያፍር «ደጀ ሰላም» የተባለው የማቅ ማእከላዊ ኰሚቴ ቃል አቀባይ ብሎግ  ዘግቦ አስነብቦናል።  ወደ ህውከትና ዐመጻ እንዲገቡ የሚቀሰቅሳቸውና የስህተት መንገድን አሰማምሮ ስለቅድስና እንደመታገል አድርጎ በኅሊናቸው በመሳል የሚያነሳሳቸው ከሌለ በስተቀር ምእመናን የዋሃን ናቸው። ገንዘባቸውን፤ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለአገልግሎት የሚያበረክቱትን እነዚህን የዋሃን የእግዚአብሔር ቤተሰቦችን ማቅ እንዴት መጠምዘዝና ለተፈለገው ዓላማ ማዋል እንደሚቻል ብዙ የሥራ ልምድ ስላለው ይህንኑ ጥበበ ዐመፃውን በሲያትል አማኑኤል ቤተክርስቲያን  ተግባራዊ አድርጎ ብጹእ አቡነ ፋኑኤልን የመቃወም ህውከት ለመፍጠር ሞክሯል። እንኳን እምነት፤ ኅሊና ያለው ማንም ሰው የሚፈርደውና ጥያቄ ሊያነሳበት የሚገባው ነገር፤  ብጹእ  አቡነ ፋኑኤል በሀገረ ስብከታቸው ባሉ አድባራት ተዘዋውረው እንዳያስተምሩ የሚከለክላቸው ምንድነው? ቅዳሴ ቀድሰው፤ ቡራኬ ሰጥተው ከመመለስ በስተቀር በደብሩ የውስጥ ሥራ ምን አድርገው ያውቃሉ? እያንዳንዱ ደብር የየራሱ አስተዳደር ያለውና በምእመናን የተቋቋመ እንጂ በብጹእ አቡነ ፋኑኤል  አይፈርስ፤ አይቋቋም!!  ሲኖዶስ የሰጣቸውን ተልእኰ ከመወጣት ውጪ አድባራቱን ምን በድለዋል? ምእመናንስ ቤተክርስቲያናቸው የምትሰጣቸውን መንፈሳዊ አገልግሎት ከማግኘት ውጪ ከዐመጻና ከብጥብጥ ምን ያተርፋሉ? እነዚህንና እነዚህን መሰል ጥያቄዎች ብናቀርብ መልሱ ምንም ይሆናል! ከብጥብጥና ከዐመጻ ምእመናን ምንም አያተርፉም። ይልቁንም ከኋላ ሆኖ ድብቅ አጀንዳውን እንደ ወፍ ጉንፋን/bird flu/ የሚረጨውና የሚበክለው ማቅ፤
1/  የአድባራቱ ተቆርቋሪ ሆኖ ራሱን በመሰየም መድረክ ከተቆጣጠረ በኋላ ገንዘብ መዝረፍ፤ አላስቀርብ ካሉት ደግሞ በጥቅም የሚደልላቸውን መሥፍኖች በመፍጠር መገንጠል፤
2/ አባ ፋኑኤልን በሄዱበት ሁሉ እየተከታተለ ማሳደድ የመጨረሻው ዓላማና ግቡ ስለሆነ ይህንኑ አሽክላ ሥራውን እስከእለተ ሞቱ መተግበር፤
3/ የፖለቲካ ሥራው ከሀገር ቤት ብዙም እያወላዳው ባለመሆኑ ወደውጪው ዓለም ፊቱን በማዞር በየቦታው ማመስ፤ መበጥበጥና ጉንፋኑን ማራባት ሥራዬ ብሎ ተያይዞታል። የሲያትሉ ቅ/ አማኑኤል ቤተክርስቲያንም ህውከት የዚያ ተግባሩ አንዱ ማሳያ ነው።