Sunday, May 27, 2012

ሰባ ስምንት ነፍስ የገደለው ሰው [በላኤ ሰብእ]በጥርኝ ውሃና በማርያም ጥላ ዳነ

ምንጭ፤ አባ ሰላማ ብሎግ፤ Friday, February 24, 2012
እኔ መንገድ እውነት ሕይወትም ነኝ በኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም [መጽሐፍ ቅዱስ ዮሐ 146]
ታምረ ማርያም የተባለው ጉደኛ መጽሐፍ ድንግል ማርያምን ያከበረ የሚመስል ነገር ግን ስድብ እና ክህደት የሞላበት መጽሐፍ መሆኑን ደጋግመን ለማሳየት ሞክረናል። መጽሐፍ ቅዱስ ከተጻፈ 1400 ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ ንጉሥ በዘርዓ ያዕቆብ የተደረሰ ሲሆን በወቅቱ የነበሩ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት እና ምእመናን ይህ ልዩ ወንጌል ከሐዋርያት ትምህርት የወጣ ስለሆነ አንቀበለውም በማለታቸው፣ እስከ አንገታቸው በጉድጓድ ተቀብረው በጭንቅላታቸው ላይ የፈረስና የከብት መንጋ እንደተነዳባቸው ምላሳቸውንና አፍንጫቸውን እንደተቆረጡ እራሱ ታምረ ማርያም ይመሰክራል። [ታምር 24 እና 25 ገጽ 112- 121]

ታምረ ማርያምን ቁጭ ብለን በማስተዋል ብንመረምረው መጽሐፍ ቅዱስን ለመቃወም የክርስትናን ትምህርት ለመበረዝ በጠላት ሆን ተብሎ የተቀመመ ይመስላል። አጼ ዘርዓ ያዕቆብ እስራኤላዊ ነኝ ስለሚል ምን አልባት አይሁዶች መሲሐዊ እምነታችንን ለማጠፋት የፈጸሙት ሴራ ይሆን? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል። ዘራ ያዕቆብ አይሁዳዊ ነኝ እያለ ይመካ ነበር፤ ከዚያም አልፎ የይሁዳ ነገድ ነኝ ይል ነበር። አባ እስጢፋኖስ ግን ኢትዮጵያዊ ነህ አትዋሽ ከአይሁዳዊነት ይልቅ ክርስቲያን መሆን ይበልጣልና በዚህ አትመካ በማለት እንደተከራከረው ገድለ እስጢፋኖስ ይናገራል [በሕግ አምላክ በፕሮፌሰር ጌታቸው]


መጽሐፉን ዛሬ መመርመር ለምን አስፈለገ? የሚል ጠያቂ ሊኖር ይችላል፣ መልሳችን አብዛኛው የዋሕ ምእመን እምነቱን የመሠረተው በታምረ ማርያም ላይ ነው የሚል ሥጋት ስላለን ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄድ ታምሯን ሰምቼ ልምጣ እንጂ ወንጌል ሰምቼ ልምጣ ብሎ አያስብም፣ እሑድ እሑድ ታምር የሚያነብ እንጂ ወንጌል ለማስተማር የሚያስብ ቄስም የለንም። 400 000 ካህናት እንዳላት የሚነገርላት ቤተ ክርስቲያናችን ታምረ ማርያም አንብቦ ከማሳለም ያላፈ አገልግሎት የሚሰጥ አይደለም። በተለይም ታምሯን ሰምቶ የሄደ ሥጋውና ደሙን እንደተቀበለ ይቆጠርለታል የሚለው ባዕድ ወንጌል ብዙ ሕዝብ ወደ ስጋውና ደሙ እንዳይደርስ ስላደረገው ይህም የስሕተት ትምህርቶች ውጤት ሆኖ ስላገኘነው፣ ሲኖዶሱ ከተኛበት እስኪነቃ ድረስ ጩኸታችንን አናቆምም። ወደ ተነሳንበት እርስ እንመለስ፥

መጽሐፉቅምርበሚባል አገር አንድ ሰው ነበር በማለት ታሪኩን ይጀምራል

ወኢየበልዕ እክለ ወኢ ሥጋ ላሕም ወኢ ካልአ እንሥሣ አላ ይበልዕ ሥጋ ሰብእ

ትርጉም እህል፥ የላም፥ ሥጋ የሌሎችንም እንሥሳ ሥጋ አይበላም ነበር የሰው ሥጋ ይበላ ነበር እንጂ 68

Saturday, May 26, 2012

ቁም ነገር በፈገግታ

«ወሶበሂ ይነብብ ሐሰተ እምዚአሁ ይነብብ….ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል»


 በመምህር ፈንታ
የማኅበረ ቅዱሳን አፈቀላጤ የሆነው ደጀ ሰላም በወርሃ መጋቢት መጨረሻ ላይ የሚከበረውን የመድኃኔዓለም ዓመታዊ በዓል አስታኰ በዛሬማ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን የመንግሥት የስኳር ልማት ለማጥናት ሳይሆን ለሽብር ፍጆታ የሚሆን መረጃ ለመሰብሰብ የማኅበሩን አባላት በተሳላሚ ሽፋን ወደ ገዳሙ ከላካቸው አባላቶቹ የተገኘውን ዘገባ ደጀ ሰላም በገጹ አውጥቶ ነበር።
የስኳር ልማቱን ለማስቆም ሕዝቡ ለጦርነት ተመመ፤ መንግሥት አካባቢውን ለቆ ወጣ፤ ፖሊሶች አለቁ፤ ሬሳ ቆጠራው ቀጥሏል …..ወዘተ የብስጭት ማስተንፈሻ ስሜቶቻቸውን ከልካይ በሌለበት ድረ ገጽ ውሸቱን በቆርጦ ቀጥል ጥበባቸው  እንቶ ፈንቶአቸውን አስነብበውናል።
አሁን ደግሞ ጉዳዩ በወሬ የማይቆም መሆኑን ሲያረጋግጡ ለጫወታ ወግ ፍለጋ ጥቂት ጊዜ እረፍት የወሰዱ መስለዋል። አንድ ነገር ፈጥረው የሽብር ዜና እስኪያሰሙን ድረስ የሚያስተምሩት የወንጌል ቃል ስለሌላቸው ጥሩ የእረፍት ጊዜ ይሁንላችሁ ብለናቸዋል።
ይህንን ያህል ለመግቢያ ካልን የጽሁፋችን ርእስ ወደ ሆነው ጉዳይ እናምራ። ከሁከት ውጪ ነገረ መለኰትን የማያውቁ ሽፍቶች» በሚለው ጉዳይ ተንተርሰን ወደ ርእሳችን ስንገባ ደጀ ሰላም በተሳላሚ ሽፋን በማቅ አባላቶቿ ያስጠናችው  የጥናት አንዱ ክፍል በዋልድባ ገዳም «የዘጠኝ መለኰት አማኞች» መኖራቸው መዘገብ ነበር።   ስለዋልድባ መነኰሳት መናፍቅነትና ክሃዲነት ያገኘሁት ውጤት ነው በማለት  በስኳር ጥናቱ ለውሶና ስኳር አድርጎ በማቅረብ ስለዘጠኝ መለኮት አማኞች ሊያስነብበን ፈልጎ ይህንኑ በኢንተርኔት ላይ ሰቅሎት አግኝተናል።
ከጽሁፏ የተወሰደው  ዘገባዋ ይህንን ይመስላል።

ይሁን እንጂ እነ በጋሻውን፤ እነ አባ ሠረቀ ብርሃንንና ሌሎችንም ሁሉ በአንድ ሙቀጫ አስገብታ በተሐድሶ ስም የምትወቅጠው ይህች ብሎግና ማኅበር ድሮውን በፈጠራና ስም በማጥፋት ላይ ተመስርታ እንጂ የሃይማኖት እውቀት ስላላት በዚያ ላይ ተመስርታ ወይም የመናፍቃን ጉዳይ የሚያሳስባት ሆኖ አይደለም።