Showing posts with label ለፈገግታ. Show all posts
Showing posts with label ለፈገግታ. Show all posts

Friday, June 29, 2012

«የታማኝ ወዳጆች መከዳዳት»


 ባንድ አገር የሚተማመኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ። ከነዚህም አንደኛው በሀብቱ የገነነ በሽምግልናው የተከበረ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ እየሠራ ከሚያፈራው ከዕለት ምግቡ ካመት ልብሱ የሚተርፈው ገንዘቡን እየወሰደ ባደራ ስም አኑርልኝ እያለ ለባለጸጋው የሚሰጥ ነበረ። ያም ታማኝ መሳዩ ሽማግሌ ያደራውን ገንዘብ እየተቀበለ ሲያስቀምጥለት ቆይቶ አንድ ቀን ባለ ገንዘቡ ለዕለት ችግሩ ካኖረው ሒሳብ ላይ ጥቂት እንዲሰጠው ቢጠይቀው ምን ሰጠኸኝና ትጠይቀኛለህ አላየሁም ብሎ ጨርሶ ካደው፤ እየተመላለሰ በማሳዘን ቢለምነውም አላዘነለትም፣ አልራራለትም። ቁርጡን ካወቀ በኋላ ላገሩ ዳኛ ክስ ለማቅረብ ሄዶ አመለከተ፤ ዳኛውም ስትሰጠው ያየህ ምስክር የሚሆን ሰው አለህን ብሎ ቢጠይቀው ከኔና ከሱ በቀር ማንም ሰው አልነበረም አለው። እንግዲያስ እኔ እጠይቅልሃለሁና ከሦስት ቀን በኋላ ተመልሰህ እንድትመጣ ብሎ አስታወቀው።
ብልኁ ዳኛ አደራ አስቀማጩን ሰው ጠርቶ፣ አሁን ያስጠራሁህ እኔ በድንገት ከዚህ አገር ከሹመቴ ተሽሬ መሄዴ ነው፤ ብጠይቅ ባስጠይቅም ታማኝ ሽማግሌ ባገር ያለኸው አንተ መሆንህን ሰማሁ፡ ስለዚህ ዕቃዬንና ያለኝን ገንዘቤን በሙሉ አንድ ጊዜ አንሥቼ ለመሄድ ስለማይቻለኝ አንተ ዘንድ እንድታስቀምጥልኝና በየጊዜው ሰው ስልክ እንድትሰጥልኝ እለምንሃለሁ አለው።
ሽማግሌውም እንግዲህ ይህ ያገር ዳኛ ትልቅ ሰው ስለ ሆነ ባደራ የሚያስቀምጠው ገንዘብ በብዙ የሚቆጠር ዕቃውም ካይነቱ ብዛት ጋራ የበረከተ ይሆናልና ይኸን ተቀብዬ አላየሁም ብዬ ባለሀብት ባለገንዘብ እሆናለሁ ብሎ ደስ አለውና ለዳኛው እሺ ጌታዬ ሲል መልስ ሰጠው።
ከሦስት ቀንም በኋላ ባለገንዘብ ለዳኛው በቀጠሮዬ መጥቻለሁ ብሎ አመለከተው። እንግዲህ ሂድና አንዳችም ነገር ሳትጨምር ባገሩ ዳኛ ልከስህ ነውና ገንዘቤን ስጠኝ በለው፤ በዚያም ጊዜ ገንዘብህን በሙሉ አንድም ሳያስቀር ጨርሶ ይሰጥሃል አለው። እንደ ተባለውም ሁሉ ሄዶ ቢጠይቀው ይህን አልሰጥም ያልኩት እንደ ሆነ ለዳኛው ሲነግረው ከሓዲነቴን ያውቅብኝና የሱን ብዙውን ገንዘብና ዕቃ ያስቀርብኛል ሲል ገንዘቡን በሙሉ አውጥቶ ሰጠው ይባላል።
እንቅልፍ ለምኔ፣ 3 እትም። ከብ/ጌታ ማኅተመ ሥላሴ። 1960 አርቲስትክ ማተሚያ። /አ። ገጽ 184-185

Friday, June 8, 2012

ቁም ነገር በፈገግታ!

 ቸልተኝነት እና አስተዋዩ ውሻ!

ከውል ውጩ በሚደርስ ኃላፊነት ህግ ውስጥ የቸልተኝነት ጥያቄ ከተነሳ ምላሹ ለብዙ ፍርድ ቤቶች ብዙውን ጊዜ አስቸጋሪ ነው፡፡ በብዙ የህግ ስርዐቶች ውስጥ ተቀባይነት ያገኘው የቸልተኝነት መለኪያ “የአንድ አስተዋይ ሰው ሚዛን” ሲሆን ይህም አንድ አስተዋይ ሰው በተመሳሳይ ሁኔታዎች ውስጥ ቢሆን ኖሮ ምን እንደሚያደርግ በመላምታዊ ፍሬ ነገር ላይ ተመስርቶ ማሰላሰልና ድምዳሜ ላይ መድረስን ይጠይቃል፡፡ እንግዲህ ቸልተኝነትን በአንድ አስተዋይ ሰው እይታ መዝኖ መወሰን አስቸጋሪ ከሆነ ይህን መለኪያ ለአንድ አስተዋይ ውሻ ተፈፃሚ ማድረግ ደግሞ በጣም ፈታኝ ብቻ ሳይሆን አስገራሚም ጭምር ነው፡፡

በአሜሪካም ኢሊዮኒስ ግዛት በኪርካም እና ዊል (Kirkham Vs. Will) መካከል በታየ አንድ የይግባኝ ክርክር ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በጉዳዩ የተነሳው ጭብጭ የአንድ አስተዋይ ውሻ መለኪያ በመጠቀም እልባት ሰጥቶበታል፡፡ ክሱ የተጀመረው “የተከሳሽ ውሻ በንክሻ ላደረሰብኝ ጉዳት የውሻው ባለቤት የሆነው ተከሳሽ ካሳ ሊከፍለኝ ይገባል፡፡” በሚል ከሳሽ ባቀረበው ክስ ሲሆን ተከሳሹም በበኩሉ ከሳሽ የተነከሰው ውሻውን በመተናኮሉ ስለሆነ በራሱ ጥፋት ለደረሰበት ጉዳት ልጠየቅ አይገባም በማለት ተከራክሯል፡፡ ክሱ በስር ፍርድ ቤት ውድቅ ከተደረገ በኋላ በይግባኝ ክርክሩ ላይ በዋነኛነት የተነሳው ጭብጥ “መተናኮል አለ ወይስ የለም?” የሚለው ጥያቄ ነበር፡፡ ውሳኔውን የሰጡት ዳኛ ይህንን ጭብጥ ለመወሰን እንደመመዘኛ ወይም መስፈርት የተጠቀሙት የተለመደውን የአስተዋይ ሰው ሚዛን ሳይሆን የአንድ አስተዋይ ውሻ መለኪያ ነበርር፡ በዚህ ሚዛን ወይም መለኪያ መሠረት መተናኮል አለ ወይስ የለም የሚለውን ጥያቄ ለመወሰን በተመሳሳይ ሄኔታዎች ውስጥ አንድ አስተዋይ ውሻ ተከሳሽ ካሳየው እንቅስቃሴ አንጻር ምን ዓይነት ምላሽ ይሰጣል? የሚል መላምታዊ ጥያቄ አንስቶ ድምዳሜ ላይ መድረስን ይጠይቃል፡፡ ፍርድ ቤቱ ተፈጻሚ ባደረግው መለኪያ መሰረት የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ አጽንቶታል፡፡

source:  http://abookmedhin.wordpress.com/

Wednesday, May 2, 2012

ባለጭድ

በጮራ ቊጥር 3 ላይ የቀረበ 
from chorra blogger

ለፈገግታ


ገበሬው ባለው አንድ በሬ ከሌሎችም አቀናጅቶ ማረሱ ከፍተኛ ችግር ይፈጥርበትና ያንን ሸጦ ሁለት መለስተኛ በሬዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ በሬው ለዐይን ሞላ ብሎ ጥሩ ዋጋ እንዲያወጣለት በማሰብ ጭድ በገፍ ሲያበላው ይሰነብትና ለገበያ ያቀርበዋል፡፡ 

በሬውን ሊገዛ የመጣ ነጋዴም የበሬው አቋም ከሩቅ ይስበውና ጠጋ ብሎ ተዟዙሮ በደንብ ይመለከተዋል፤ በመጨረሻም ከወደ ሆዱ ጐሸም እያደረገ፤ «ባለ ጭድ ዋጋውስ?» ይለዋል በሽሙጥ፡፡ 

ነገሩ የገባው ገበሬም «ለጠንቋይ አይሸጥም» በማለት አጸፋውን መለሰለት ይባላል፡፡