Thursday, May 24, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን ተላላኪ ጳጳሳት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ባልተከተለ መንገድ መወገዝ የሌለባቸውን የቤተ ክርስቲያን ልጆች “አወገዝን” አሉ

                 ምንጭ፦ አባ ሰላማ ብሎግ
              ( ለፒዲኤፍ ንባብ እዚህ ይጫኑ )
ነውራችን ተሸፈነልን ብለውና ከማኅበሩ የሚከፈላቸውን ረብጣ ብር ከግምት በማስገባት፣ እንዲሁም ከማኅበረ ቅዱሳን ጎን ብንቆም ፓትርያርክነቱ ለእኛ ይሆናል በሚል ክፉ ምኞት ተይዘው ለአንድ ወንበር እርስ በርስ እየታገሉ፣ የቤተክርስቲያንን ሳይሆን የማኅበሩን አላማ ለማሳካት በግንቦቱ ሲኖዶስ ከመጠን በላይ ሲፋንኑ የነበሩት አባ አብርሃም፣ አባ ዲዮስቆሮስና አባ ሳሙኤል፣ እንዲሁም አባ ጢሞቴዎስ፣ “ምንም ቢሆን ማኅበረ ቅዱሳን የከሰሳቸውን ሰዎችና ማኅበራት ሁሉ ሳናወግዝ አንበተንም፤ ማኅበረ ቅዱሳን ያጠናው በቂ ነው፤ እነርሱን ጠርቶ ማነጋገር አያስፈልግም” በሚል የማኅበረ ቅዱሳንን ክስ ብቻ በመቀበልና ተከሳሾቹን ሳያነጋግሩ ፍትሀዊነት የጎደለውን ፍርድ በመፍረድ “አውግዘናል” ማለታቸው ተሰማ። እነዚህ በስም የተጠቀሱ የሰሙኑን የሲኖዶስ ስብሰባ ማኅበረ ቅዱሳን በአቡነ ጢሞቴዎስ ቤት ያገባላቸውን ግብር በምሳ ሰአት እየበሉ፣ የቀኑን ውሎ ለማኅበሩ አመራሮች ሪፖርት እያቀረቡና በቀጣዩ ስብሰባ ላይ ማድረግ ስለሚገባቸው መመሪያ ከማኅበሩ አመራሮች እየተቀበሉ ሲኖዶሱን ሲያውኩ መሰንበታቸው ይታወሳል።በተለይም አባ አብርሃም ከአሜሪካው ሀገረ ስብከት መነሳታቸው ጥቅማቸውን ስላስቀረባቸው በግላቸውም በማኅበረ ቅዱሳንም በኩል አልተወደደምና፣ ይህን ቂም ለመወጣት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ “ክስ የቀረበባቸው ግለሰቦች ተጠርተው ሳይጠየቁ እንዴት ይወገዛሉ? ስለዚህ ተጠርተው ይጠየቁና ውሳኔ ይሰጥ” ሲሉ ያቀረቡትን ሐሳብ ለጊዜው ተቀብለው የነበረ ቢሆንም፣ በዚህ እጅግ የተከፋው ማኅበረ ቅዱሳን “ሰዎቹማ ካልተወገዙ ጤና አይሰጡንም። ስለዚህ ስብሰባው ከመዘጋቱ በፊት አውግዛችሁ መለያየት አለባችሁ ሲል ተላላኪ ጳጳሳቱን ባዘዘው መሰረት ተልእኮዋቸውን ተወጥተዋል። አንዳንዶቹ አረጋውያን ጳጳሳት ግን ውግዘት የተባለውን ህገወጥነት “ኧረ ተዉ ምንድነው ለውሳኔ መቸኮል? ተጠርተው ያልተጠየቁ ሁሉ ተጠርተው ይጠየቁ። አሊያ ይህ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔ አይደለም” ቢሉም ለቤተክርስቲያን ሳይሆን ለግል ምቾታቸውና ለሥልጣናቸው ብቻ የቆሙት አባ አብርሃም፣ አባ ሳሙኤል፣ አባ ዲዮስቆሮስና አባ ጢሞቴዎስ አሻፈረን በሚል ማውገዛቸውን አውጀዋል። እነዚህ በቀሚሳቸውና በቆባቸው ካልሆነ በቀር አንድም የጳጳስ ሰብእና የሌላቸውና ሊወገዙ የሚገባቸው “ጳጳሳት”፣ መጽሐፍ ቅዱስንም ሆነ ህገ ቤተክርስቲያንን እንደማያውቁ ካስተላለፉት ህገወጥ ውግዘት መረዳት ተችሏል። እንደክርስቶስ ትምህርት ቤተክርስቲያን ያጠፋውን ሰው ጠርታ መምከርና እንዲመለስ ማድረግ የመጀመሪያ ሥራዋ ነበር። ተመለስ የተባለው ሰው አልመለስ ብሎ ከጸና ግን ታወግዘዋለች። አሁን እነ አባ አብርሃም አስተላለፍን ያሉት ውግዘት ግን ይህን ስርአት ያልተከተለ፣ ከቤተክርስቲያን ፈጽሞ የማይጠበቅ፣ በእነርሱ መለኪያ የተሳሳተን ሰው ከስህተቱ ለመመለስ ሳይሆን በዚያው ጠፍቶ እንዲቀር ለማድረግ የተላለፈ የ“ጥፋ” አዋጅ ነው። በእውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያንና በደጋጎቹ አባቶች አይን ሲታይ “ውግዘት ዘበከንቱ” ነው። መጽሐፍ ቅዱስም “እንደሚተላለፍ ድንቢጥ ወዲያና ወዲህም እንደሚበርር ጨረባ፥ እንዲሁ ከንቱ እርግማን በማንም ላይ አይደርስም።” (መጽሐፈ ምሳሌ 26፡2) ሲል የገለጸው አይነት ከንቱ መሆኑን ይናገራል።

Wednesday, May 23, 2012

ሲኖዶሱ የሚመራው በማን ነው? በፓትርያርኩ ወይስ?


                                          ምንጭ፥ ዓውደ ምሕረት
የሰሞኑ የሲኖዶስ ስብሰባን ሂደት ላየ ሊለው የሚችለው ብዙ ነገር ይኖረዋል። በተለይ በስብሰባ ላይ በተነሳ ሀሳብ ሁሉ ላይ ከውጭ ካለው አየር ምክር የሚሹ አንዳንድ ጳጳሳት አካላቸውን ሲኖዶሱ ላይ አድርገው ልባቸው ማኅበረ ቅዱሳን ቢሮ ውስጥ አስቀምጠው በማቅ ሳንባ ነው የሚተነፍሱት።  የሚተነፍሱበት አየር ደግሞ በልዩ ሁኔታ ማንያዘዋል በሚባል ኬሚስት የተሰራ ነው። ይህ ታዋቂ ኬሚስት የሚቀምመው ኬሚካል  በመጀመሪያ የሚሞክረውም አባ ሳሙኤል የሚባሉ ባለመንታ ችግር ጳጳስ ላይ ነው። እሳቸው ላይ በትክክል እንደሰራ ሲያውቅ እሳቸውን አስጨብጦ በእለቱ  የሚተነፍሱት አየር ለሚያጥራቸው ሌሎች ጳጳሳት ይልከዋል።
ከዚያማ ገበርዲኑን ለብሶ ቤተ ክህነት ግቢ ላይ መዞር ነው። ጋሻ ጃግሬዎቹ ሲከቡት የዛሬ አጀንዳ ይህ ይህ ነው፤ የሚወሰነውም ይሔ ነው እያለ ራሱን በመንፈስ ቅዱስ ቦታ አስቀምጦ ያወራል። ማታ ላይም የኮሌጁ ምሩቃን ቢሮ ላይ መብራት አጥፍቶና መጋረጃ ጋርዶ ሰው የሌለ አስመስሎ ይቀመጣል እንዲህ እንደሚያድርግ የሚያውቁ የኮሌጁ ተማሪዎች ታድያ ማንያዘዋል የሚባል የሌሊት ሰይጣን አለ ብለውበመፍራትወደ ምሩቃኑ ቢሮ አካባቢ አይሄዱም።

ይህ ሰው  መሸት ሲል ሶስት ወይም አራት ሰዓት ላይ በአባ ሳሙኤል ስልክ ጥሪ መሰረት ወደ አባ ሳሙኤል ሄዶ ስብሰባው እንዴት ነበር? ብሎ ይጠይቃል። ታድያ አባ ሳሙኤልም በተለመደው ጀብደኛ ባህሪያቸው እንዲህ ተብሎ፤ እንዲህ ተደርጎ እንዲህ ተወሰነ ብለው ይነግሩታል። አጅሬም 6ሰዓት ወይም 7 ሰዓት ላይ ወጥቶ ይሄዳል። አንዳንዴም እዛው ያድራል። ያደረም ቀን፤ ወጥቶ የሄደም ቀን ተማሪ ያየዋል። ተማሪ ለጥናት ማታን ይመርጣልና ሹክክ ብሎ ከአባ ሳሙኤል ቤት ሲወጣ ያዩታል። ቀን ለደጀ ሰላም ብሎ አስቀድሞ ያዘጋጀውን ሪፓርት ያወጣና እሳቸው ካሉት ጋር ያስተያየዋል። የሚሻሻል ካለ አሻሽሎ፣ ቅመም መጨመር ካለበትም ጨምሮ «ደጀ ሰላም» ላይ ፖስት እንዲደረግ ለአሉላ ይልካል። አንዳንዴም ለአሉላ በስልክ ይነግረውና እሱ የራሱን ቅመም ጨምሮ ያወጣዋል። ታድያ ይህ ሁሉ ቅንጅት እያለ ደጀ ሰላም እውነት የማታወራው ብሎ ለሚጠይቅ ጠያቂ እንዲህ የሚል መልስ እንሰጠዋለን። ብዙ ጊዜ ደጀ ሰላም የተሳሳተ ዘገባ የምታወጣው በሶስት ዋና ዋና  ምክንያቶች ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን የፓትርያርክነቱን ወንበር ሊጨብጥ የቀረው ትንሽ ነው!


  • በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ማኅበረ ቅዱሳን ከተራ ማኅበርነት ወደ ሀገረ ስብከትነት  አደገ።
  • ሲኖዶሱ ሙሉ በሙሉ በማኅበረ ቅዱሳን እጁን ተጠምዝዞ እንደሚሰራ አስመሰከረ።
  • ማኅበረ ቅዱሳን ከእንግዲህ የቀረው ፓትርያርክነቱና ቤተመንግሥቱ ነው!
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ሆኖ  የየሀገረ ስብከቶቹ  ጠቅላይ ጽ/ቤት ሆኖ ያገለግላል። ይህ ጽ/ቤት ደግሞ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ በየ3 ዓመቱ በሚያደርገው ምርጫ በሚመድበው ሊቀጳጳስ ነው። እንግዲህ ማኅበረ ቅዱሳን ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና አሥኪያጅ ሆነ ማለት ራሱን የቻለ ሀ/ስብከት  ሆነ ማለት ነው። የጠቅላይ ቤተክህነቱ መምሪያዎች ሊያዙት አይችሉም። ከዚያም በላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሊያዙት፤ ሊናገሩትና ሊቆጡት አይችሉም ማለት ነው። በቀጥታ በቅዱስ ሲኖዶስ በሚመደበው ሊቀጳጳስ በኩል ግንኙነቱ ከቅዱስ ሲኖዶሱ ጋር ብቻ ይሆናል ማለት ነው። እንዲህ ነው እንጂ ሹመት፤ መሾም ካልቀረ!! አንድ ማኅበር ባንድ ጊዜ እመር ብሎ አናት ላይ ፊጢጥ ብሎ ከመቀመጥ ወዲያ ሹመት ከወደየት ይገኛል? ከእንግዲህ  ከተቀመጠበት ደረጃ አንጻር ማኅበር መባሉ ዝቅ የሚያደርገው ስም ስለሆነ የቅዱሳን መምሪያ ወይም የወጣቶች ሀ/ስብከት እንዲባል ሲኖዶሱ በነካካው እጁ ስሙንም ማሻሻል ይገባዋል። ከዚያም አያይዞ ለዚሁ አዲስ ሀ/ስብከት አንድ ሊቀጳጳስ እንዲመድቡለትም ጥቆማውን እናቀርባለን።
አንድ ነገር ታዘብን። ቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ የሚባል አካል እንደሌላት ተረዳን። በአንድ ተራ ማኅበር እየተመሩ የእሱን ጉዳይ ብቻ ሲያነሱና ሲጥሉ ሦስትና አራት ቀናት ስብሰባ መወዘፍን ምን ይሉታል? ስንት ስራ መስራት እየቻሉ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ማውረድ እስኪያቅታቸው ድረስ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን አጀንዳ ይዞ መከራከርን እውነት ሰዎቹ በመንፈስ ቅዱስ ነው የሚመሩት እንድንል ያደርገናል።
 በመሰረቱ እኰ ማኅበረ ቅዱሳን አሸባሪ አመራር እንደሚነዳው መንግሥት በድብቅ ሳይሆን በግልጽ አውጆ እያለ ስለማኅበሩ አጀንዳ መያዝ ትልቅ ስህተት ነው። ቅዱስ ፓትርያርኩ ከፈጸሙት ስህተት ሁሉ ይህኛው ይከፋል። መንግስት ያስጠነቀቀውን ማኅበር ጉዳይ ለክርክር ማቅረብ አልነበረባቸውም። ከሽብር ተግባር ነጻና ትክክለኛ ማኅበር ስለመሆኑ በህግ አግባብ ከመንግስት ማረጋገጫ ሊያቀርብ ሲገባው ጭራሹኑ ከማኅበርነት ወደ ሀ/ ስብከትነት ማሳደግ እብደት ካልሆነ ጤንነት አይደለም። ቅዱስ ፓትርያርኩ አሁንም ደግመው ሊያስቡበት ይገባል እንላለን። ከየጎዳናው እየጠሩ ድስት የደፉለት ሁሉ አንድ ላይ አድሞ ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር በጥቅም ሲተሳሰር እንዴት አሜን ብለው ሊቀበሉ ቻሉ? ብለን ፓትርያርኩን አጥብቀን እንጠይቃለን።
ይህ ማኅበር እስካሁን እየታዘዘ እንዳልቆየ የተጻፉለት ደብዳቤዎች አረጋጋጮች ናቸው። እሱ ራሱ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ አረጋግጧል። አንዴ ከኢህአዴግ፤ አንዴ ደግሞ ከተቃዋሚ ነኝ እያለ፤ ሌላ ጊዜ ከሀገር ቤቱ ሲኖዶስ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ገለልተኛ እየመሰለ የተጓዘበትን ሁላችንም እናውቃለን። የወንድሞች ከሳሽና አሳዳጅ ስለመሆኑም ግፉን የቀመሱ ሁሉ ይመሰክራሉ። የተጓዘባቸውን ስልቶች ሁሉ ያጠናው መንግሥት ከሽብር አቀንቃኝ  ከሰለፊያ ጋር በአንድ ረድፍ አንዳስቀመጠው ነግሮናል። ስለሆነም አቡነ ጳውሎስ ይህንን የአድማና በጥቅም የተሳሰረ ውሳኔ አልፈርምም በማለት ውድቅ ሊያደርጉት ይገባል። ማኅበሩ አስቀድሞ ከሰለፊያ ተግባር ነጻ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ማምጣት ይጠበቅበታል። ደጋፊዎቹ ጳጳሳትን በማስረጃና በሰው ምስክር ተጠንተው ብቁ ሆነው ያልተገኙ ካሉ ከማእረጋቸው መሰናበት አለባቸው።  ቄስ የነበሩ፤ ልጆች የወለዱ፤ ቅምጥ ያላቸው እንዳሉ ይወራል፤ የአንዳንዶቹም ይታወቃል። ለዚሁም ማሳያ የሚሆነው አባ ሚካኤል በፍርድ ቤት ባለልጅነታቸው መረጋገጡ ነው። እየተሸፋፈነ መቀመጡ ለቤተክርስቲያን ጠንቅ የሆነ ውሳኔ ለማስወሰን ያልተመለሱ ሰዎች ስብስብን አስገኘ። ስለዚህ አባ ገብርኤል፤ አቶ ኢያሱ ተብለው እንደነበረው፤ ማንነታቸው እንደገና ተመርምሮ ውሳኔ ሊሰጥባቸው ይገባል።ጨከን ያለ የሥርዓት ማስከበር አካሄድ መውሰድ ካልተቻለ ነገ ፓትርያርክነቱን አስቀድሞ ከዚያም ቤተመንግሥቱን እንደሚረከብ የሚጠራጠር ካለ ምንም የማያውቅ ብቻ ነው። አመኑንም አላመኑም ፓትርያርክ ጳውሎስ፤አንድ ነገር አስረግጠን እንነግርዎታለን። በማኅበረ ቅዱሳንና በደጋፊዎቹ ጳጳሳት ግብዓተ መሬትዎ ሊፈጸም የቀረው ጥቂት ነው። ከሆነለት ፓትርያርክነቱን ለሚታዘዝ የወሎ ጳጳስ ወይም ለሸዋ ሰው ብቻ ሰጥቶ ወደ ቤተመንግሥት ሰተት ብሎ ለመግባት ከጽዋ ማኅበርነት ወደ መምሪያ ተገዳዳሪነት፤ አሁን ደግሞ ወደ ሀገረ ስብከትነት ማደጉ ከምንም በላይ ማሳያ ነው።  ታዲያ ከእንግዲህ የቀረው ምንድነው? ይህ ሁሉ ለጽድቅ ነው እንዳይሉንና እንዳንስቅ። ነጋዴና ሸቃጭ፤  ጻድቅ ማኅበር አራት ኪሎ የለም እንልዎታለን። እያየነው የወጣው ይህ ሀረግ ተክሉን አንቆ ወዳሰበበት መጓዝ ብቻ ነው። እግዚአብሔር ለዚህ ክፉ ማኅበር አሳልፎ ከሰጠን በእውነትም ቤተክርስቲያኒቱ ለፈተናና ለውድቀት ተመርጣለች ማለት ነው።
ሰውዬው «ኵሉ ንምርዓይ ምቅናይ» ያለው ወዶ አይደለም ለካ! ሁሉ ቢገርመን ሁሉን ለማየት መቆየት ብለናል።