Sunday, May 13, 2012

የነገው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በቅዱስ ፓትርያርኩ ሰብሳቢነት ይቀጥላል!


                (የሊቃነ ጳጳሳቱ  ገመና በዜና ቤተክርስቲያን ተጋለጠ፤ ጳጳሳቱም ስለ ገመናቸው መጋለጥ ተቃጥለዋል!)                       
                                   የጽሁፍ ምንጭ፦ ዐውደ ምሕረት
በትናንትናው ዕለት የዜና ቤተክርስቲያን ጋዜጣ ርዕሰ አንቀጽ ሰፊውን ጊዜ ወስዶ ሲያወያይ ነበር ሰኞም ይቀጥላል

(የማሕበረ ቅዱሳን ብሎጎች ይህን መርዝ ሳንረጭ አያስተኛን አያሣድረን በማለት /ሲኖዶስ ሌላ ሰብሳቢ መርጦ ጉባኤውን ለመቀጠል ወሰነ የሚል ነጭ ውሸት በሰበር ዜናነት አስነብበውናል፡፡ ሲኖዶሱ እንዲህ ያለ ውሳኔ እንዳልወሰነ የተረጋገጠ ሲሆን እነዲያውም ቀኑ ያልታሰበና ያልተጠበቀ አጀንዳ የተስተናገደበት ቀን ነበር፡፡ ዝርዝሩን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡)
በትናንትናው ዕለት የነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በጠዋቱ ውሎ አጀንዳቸው ተቀባይነት እንዲያገኝ የከረረ አቋም ይዘው የሚገኙት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ሲኖዶሱ ሃሳባቸውን ይቀበል ዘንድ ግድ እያሉ የነበረ ቢሆንም የአብዛኛው ጳጳሳት ፍላጎት አጀንዳዎቹን አለመቀበል ስለሆነ ጉዳዩ መክረር ጀምሮ ነበር። ከሰዓቱን ግን የዜና ቤተክርስቲያን ዘገባ እጃቸው ላይ በገባ አባቶች ጉዳዩ ይታይልን ተብሎ ስለተጠየቀ ሲታይ ሁሉን አጀንዳ አስጥሎ ፊታውራሪ ሆነ።

አሁን ያሉት የሲኖዶስ አባላት ቤተክርስቲያንን ከውድቀት አያድኑም!

 
እኛ ጠቅልለን የምንናገረውን «ደጀ ሰላም» ከፋፍሎ በማስቀመጥ የጳጳሳቱን ማንነት ይነግረናል።ባልተለሳለሰው አማርኛችን ሲዘረዘሩ  እንቅልፋሞች፤ አድርባዮች፤ ሆዳሞችና ሰራተኞች  መሆናቸው ነው። ደጀ ሰላም ብሎግ የጳጳሳቱን ማንነት ሲተነትን፤
«ሊቃነ ጳጳሳቱ “ሰማዕታት፣ ነውረኞች፣ ዘገምተኞች እና ጥቅመኞች” በሚል በአራት ተከፍለዋል» ይልና…የጠ/ቤተ ክህነቱ ሠራተኞች “የዳኛ ያለህ! ለቤተ ክርስቲያኒቱ ዳኝነት ይታይላት” የሚል ጽሑፍ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አሰራጩ» በሚል ርዕስ በ10/9/2012  ጽሁፉ ማንነታቸውን ይተነትናል።
ዞሮ ዞሮ በአንድ ነገር እንስማማለን።አራት ቦታ ከተከፈሉትና በዘገባው ከተመረጡት  ውስጥ አንዱ እጅ ብቻ «ሰማዕታት» ወይም ሰራተኛ ናቸው ያላቸውን እነማን እንደሆነ ባናውቃቸውና እኛ የምንመርጠው ምንም እንደሌለ ብናምንም «ነውረኞች፣ ዘገምተኞችና ጥቅመኞች» ባላቸው የሲኖዶሱ ¾ ው  አባላት  የቤተክርስቲያኒቱ የጥፋት  ኃይሎች መሆናቸውን በገለጸው ድልድል ላይ እጃችንን አጨብጭበን መስማማታችን እንገልጻለን። ድንቅ ዘገባ ነው ደጀ ሰላም!!
እንግዲህ እንደ ደጀ ሰላም ዘገባ 75% የሆነው የሲኖዶስ አባል ለቤተክርስቲያን ችግርና ውድቀት ኃላፊነት ያለበትና ሆኖ  ለአዲስ የአስተዳደር ትንሣዔ ምንም ለውጥ ማምጣት የማይችል፤ እንኳን የቤተክርስቲያንን ሸክም ሊያቀል ይቅርና እራሱ ሸክም የሆነባት ኃይል መሆኑን ነው። «ከነውረኞች፤ ጥቅመኞችና ዘገምተኞች» የሚመጣ ምንም ለውጥ የለም።  ደጀ ሰላም! እውነት ለመናገር ብለህ በውዴታህ የተናገርከው ባይሆንም በመንፈስ ቅዱስ ተጸፍተህ የተናገርከው ግን እውነት ነው እንላለን። 

የኔን ዓይን ሌላኛው ለምን አያምንም?

ለፈገግታ