ልሳን ምንድን ነው
ሀ . ልሳን ምንድን ነው፤ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰቸው ቦታዎችሰ1.ልሳን ቋንቋ ማለት ነው።
ልሳን ማለት ቋንቋ ማለት ነው። በአዲስ ልሳን መናገር ማለትም በአዲስ ቋንቋ መናገር ማለት ነው። በአዲስ ቋንቋ መናገር ሲባልም ተወልደው ባላደጉበት፤ ባልተማሩት ቋንቋ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት መናገር ማለት ነው። የመጀመሪያውና ትክክለኛው ልሳን የተገለጸው በጰራቅሊጦስ እለት ነው። ታሪኩም በሐዋርያት ስራ ምዕራፍ ሁለት ተገልጿል። ሐዋርያትም ሆነ በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖች የተናገሩት በሚሰማና ሊተረጎም በሚችል ቋንቋ ነበር። ሐዋ 2፡ 6 ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ሐዋርያት በልሳን ሲናገሩ የተሰበሰቡት አይሁድ በራሰቸው ቋንቋ ሲናገሩ ሰምተዋቸዋል። ሐዋርያት የሚያወቁት የራሳቸውን ቋንቋ ብቻ ነበር ነገር ግን እነዚህ ሰዎች የተሰበሰቡት ከዓለም ሁሉ ነበር። ሐዋርያትም የተናገሩት የአለምን ቋንቋ ነበር።ጌታችንም በማር 16፤ 17 በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ ሲል በሚሰማ ቋንቋ ማለቱ ነው።
1ኛቆሮ 14፡ 9-11 እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል ? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና። በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤ እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
ብሎ ቋንቋ ሁሉ ሰሚ እንዳለውና እናንተም የምትናገሩት ቋንቋ ሰሚ ባለው ህዝብ መሐከል መሆን አለበት ብሎ ያብራራል።
2.ልሳን መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩና ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ጸጋዎች አንዱ ነው።