Showing posts with label ሥነ ግጥም. Show all posts
Showing posts with label ሥነ ግጥም. Show all posts

Tuesday, August 14, 2012

ሃሌ ሉያ

የሕይወታችን ባለቤት፤ የመዳናችን ዋስትና፤ የዘላለማዊነት ርስት ለሆነው ለእግዚአብሔር ብቻ የተገባ ይህንን የግጥም ምስጋና ስለወደድነው ከቤተ ጳውሎስ ብሎግ ላይ ወስደን አካፍለናችኋል። ለመዳናችን ሌላ ምስጋና ለማን? ዳዊትም ያለው ይህንን ነው።

መዝ 44፤20-21
የአምላካችንን ስም ረስተንስ ቢሆን፥ እጃችንንም ወደ ሌላ አምላክ አንሥተንስ ቢሆን፥
እግዚአብሔር ይህንን አይመረምርም ነበርን? እርሱ ልብ የሰወረውን ያውቃልና።

ቤተ ጳውሎስ ማክሰኞ ሐምሌ 8/2004 ዓ.ም.

ሃሌ ሉያ ለአብ
ሃሌ ሉያ ለወልድ
ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ
ሃሌ ሉያ በአርያም ላለኸው
ሃሌ ሉያ በልቤ ለነገሥከው
ሃሌ ሉያ ለጥልቁ መሠረት
ሃሌ ሉያ ለምጥቀቱ ጉልላት
ሃሌ ሉያ ለዳርቻዎች ወሰን
ሃሌ ሉያ ከአድማስ ወዲያም ላለኸው
ሃሌ ሉያ ዓመታትን ላስረጀው
ሃሌ ሉያ ሕዝቡን ለታደግኸው
ሃሌ ሉያ ብርሃናትን ለፈጠርከው
ሃሌ ሉያ ስሜን ለለወጥከው
ሃሌ ሉያ ለድካሜ ምርኩዝ
ሃሌ ሉያ ለምስኪንነቴ ሞገስ
ሃሌ ሉያ ለተጨነቁት ዕረፍት
ሃሌ ሉያ ለታወኩት ፀጥታ
ሃሌ ሉያ ሸክም ለተጫናቸው ወደብ
ሃሌ ሉያ ስንጥቁን ልቤን ገጥመህ ለያዝከው
ሃሌ ሉያ በመጽናናትህ ለጎበኘኸኝ
ሃሌ ሉያ ከጥልቁ ስጮህ ለሰማኸኝ
ሃሌ ሉያ ከደጅ ስፈልግህ በውስጤ ላገኘሁህ
ሃሌ ሉያ በማይቻለው ቀን ለቻልኩብህ
ሃሌ ሉያ ለባልቴቲቱ ዳኛ
ሃሌ ሉያ ለሙት ልጅ ሰብሳቢ
ሃሌ ሉያ ለበረሃ ጥላዬ
ሃሌ ሉያ ለምድረ በዳው ጓደኛዬ

Thursday, May 10, 2012

የሰናዖር ማበር



በትልቅ ቸርነት ሌሊቱን አንግቶ
በጽልመቱ ቦታ ፀሐይን አብርቶ
ጨለማን በብርሃን ለለወጠ ጌታ
ምስጋና ሊያቀርቡ፤ ሊያደርሱ ሰላምታ
ወፎች እንኳን አውቀው ሲያሰሙ እልልታ
ክፉ ማኅበር ክፉ  ያነሰ ከእንስሳ
ጠዋት ከመኝታው ከእንቅልፉ ሲነሳ
በስመ አብ ብሎ ማመስገን ሲገባው
መርዝ ሃሳብ ያወጣል ጠማማ ልቡናው
ከደካሞች ጋራ እንዳይኖር ተስማምቶ
ተንኰል የሚዘራ ከመካከል ገብቶ

Sunday, April 22, 2012

«የዘመኑ ምዕራፍ»


*የዘመኑ ምዕራፍ*
                    (by dejebirhan)
ከህይወት ጎዳናወጥቶ ከመንገዱ
ከወደላይ ትቶ - የምድሩን መውደዱ
ነፍስያውን ሽጦ - ውረድ መዋረዱ
ነፍሱን ከሞት ገደል - ሰቅሎ በፈቃዱ።
                  እረፍት የለሽ ኀፍረት - ተከትሎት ኋላ
                  ከጥልቁ ሰጠመሞኝ ሆኖ ተላላ
                  ብራሪው በረረ - ጥልማሞት አጠላ
                   በሀጢአት ፓራሹትበበደል ዣንጥላ።
 አረፈ በማለፍ - አለፈ በማረፍ
 ሲብከነከን ኖሮ - ሲበርና ሲከንፍ
 ኑረቱ ጨለመ - አንዳችም ሳያተርፍ
 እስከዚያው ነበረ - የዘመኑ ምዕራፍ።

Friday, April 20, 2012

ምን አለበት?

አዳምና ሔዋን

***********

አንተ አዳም ራስ ነህ

ብሏል ቅዱስ ቃሉ፤

አንቺ ሔዋን አንገት ነሽ

ብለው ያወራሉ

እንግዲህ ተስማሙ

አንተ ራስ፤

እርሷ አንገት፤

ብታሽከረክርህ …..

ታዲያስ ምን አለበት?
**********
ከደረጀ በላይነህ

Wednesday, April 18, 2012

ከፈጣሪ አይደለም

        እግዚአብሔር ፍቅር ነው!
ሲለጉን ተደፋን፣ ሲገርፉንም ጮኽን
ሲስቡን ተሳብን፣ ሲገፉን ተገፋን
ሲመቱን አመመን፣ ሲጥሉን ወደቅን
ሲሰብሩን፣ደቀቅን፣ሲገድሉንም ሞትን
እንደሆነው ሆነ፣ የሆነው ሆነብን፣
 ከቶ ምንም የለም፣ ያልሆነው የሚሆን።
                 ከሆነውም ሁሉ፤ የሆነብን ነገር፣
                ሥረ መሠረቱ፣ የኩነቱ ምስጢር
               የክስተት እንግዳ፣ ድንገት የሚፈጠር
               ከፀሀይዋ በታች ከቶ አዲስ ነገር
             አምላክ ያላወቀው የለም በዚህ ምድር።