Wednesday, November 4, 2015

የመጽሐፍ ሕግ ይከበር!!!


ልሳን በሚነገርበት ጊዜ መጽሐፍ ቅዱሱ “በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር” እያለ (1ኛ ቆሮ 14፡28)፤ ፓስተር ዳዊት ደግሞ ያውም በመንፈስ ተመስጦ ሳይሆን ሰዓቱን እያየ በተናገረው ልሳን ላይ “እጅ ለእጅ ተያያዙ” እና “አንዴ ለሁለት ደቂቃ ሁሉም ሰው በልሳኑ ይጸልይ” በማለት ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ ሁሉም በማልሰማው ልሳን ይጮሁ ጀመር፤ ፓስተር ዳዊት እና መጽሐፍ ቅዱሱ የሚሉት ለየቅል ሆኖብኛል፡፡ ለመሆኑ በማኅበር መካከል ዝም ይበል እያለ የሚያዝዘው ትእዛዝ በእኛ ጉባኤ መቼ ነው የሚከበረው? ? ?
በመጽሐፍ ቅዱስ የሚነገር ልሳን እየተነገረን ከሆነ፤ እስቲ የፓስተር ዳዊትን ልሳን በ1ኛ ቆሮ 14፡27 “በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም” ይላልና ትተረጉሙልኝ ዘንድ በትሕትና እጠይቃችኋለሁ ልሳኑ እነሆ፡-


1. አሞላቫንቶስሳክራቶሊያ
2. ሂላሞሪያማሳንቶኮትራቫሎዣንታ
3. ዚንትሮቪዲያሎማንቴስቴኬፕላዶራስ
4. ማዶሎሎስ ሲያማማንዶስሶኮዶጆኖሎሞስ
5. ኢንሞሎዲያናማሳንቶ
6. ኦላሪያማሴንታዲያካላቫሶንታ
7. ማርዶሎሞሲያናታኪቫ
8. ሃሊቮሪያማሳንቶ … ናሚያኖራሳንታ ….
9. ማትራቫዶላማንሳ
10. ሜሮቫንዶሶትራቮላ
11. አሪዞሞሜንቶኮትሬጅሪዮማንዴ
12. ዚልቮንቶቶድጄኔስቫፓሮዳ
13. አጉልቮኖንቴስቴቮዶሞሞንዶ
14. ሳልቬርኖማንቶሴትራዲያቮላ
15. ሀሞራማሺንዶሎሮሪያማንዳ
16. ዚላቮታካሮማንዲያላማሳ
17. አማሎናንቴኤልቬሌንቶስቶትሮቮሎኮዛ
18. አሙላዢቫዚያንዴ
19. ሪቫልዶሎትሮኮሎዞማንዳ
20. ኬልፕሮቫዶስ

መጽሐፍ ቅዱስ “አንዱም ይተርጉም” በሚለው መሠረት፤ ትርጉሙን በቁጥር በቁጥር ለሚተረጉምልኝ፤ አስቀድሜ ስለ ትብብሩ አመሰግናለሁ፡፡