Friday, October 17, 2014

ካሕናቱና ማኅበሩ…እንዴት ተጃመሩ(ተጀማመሩ)???…

 ( በአማን ነጸረ )

 - ልክ የዛሬ አመት በተካሄደው አመታዊው የሰበካ ጠቅላላ ጉባኤ የምዕራብ ሸዋዎቹ አቡነ ሳዊሮስና ስ/አስኪያጆቻቸው “ማኅበሩ በሀገረ ስብከታችን ጣልቃ እየገባ አላሰራን አለ” የሚል ሪፖርት አቀረቡ፡፡ጉባኤው ለሪፖርቱ ያለውን ድጋፍ በእጁ ብቻ ሳይሆን በእግሩ ጭምር መሬት እየደበደበ በድምድምታ ታግዞ ገለጸ፡፡የዚህ ትርጉም ‘መናገር ፈርተን እንጅ በሁላችንም ሀገረ ስብከት ጣልቃ እየገባ ነው’ የሚል ነበር፡፡መፍትሄውም የራሱን የማኅበሩን አካሄድ መፈተሽ ነበር፡፡ማኅበሩ ያደረገው ግን በኅቡዕ ሚዲያዎቹ ጳጳሱንና ስ/አስኪያጆቹን ማብጠልጠል ሆነ፡፡የእነሱ ኃጢኣት የማኅበሩን ጥፋት ይሸፍነው ይመስል ጳጳሱን ‘ሺበሺ’፣መነኩሴውን ‘ዘማዊ’፣ካሕኑን ‘ካንድ በላይ ያገባ’ እያለ በኅቡዕ መዝለፉን ቀጠለ፡፡

2 - በሂሳብ ሙያ 25 አመታት ልምድ አለን ያሉ የጠቅላይ ቤተክሕነቱ ሰዎች ማኅበሩ በቤተክሕነት ስር እስከሆነና ተጠሪነቱም ለኛ እስከሆነ ድረስ በራሳችን ሰዎች ኦዲት ይደረግ፣የራሳችንን ደረሰኝ ይጠቀም የሚል ጥያቄ አቀረቡ፡፡ጉባኤው አሁንም ድጋፉን ገለጸ፡፡የማኅበሩ ተወካዮች ግን ጉባኤውን ረግጠው ወጡና በተለመዱት ኅቡዕ ሚዲያዎቻቸው የቤተክሕነቱን የአቅም ውሱንነትና የደረሰኞቹን ለሂሳብ አያያዝ ምቹ አለመሆን በመግለጽ ጥያቄውንና ጠያቂዎቹን ለማንኳሰስ ተሽቀዳደሙ፡፡ ‘እንዲህ አይነቱን አሰራር እኮ ማስተካከል የሚቻለው ከአስተዳደሩ በመራቅና እሱን በማራከስ ሳይሆን ውስጥ ገብቶ ራሱን ተቋሙንም አግዞ ከችግሩ ለመውጣት ያብሮነት ተጋድሎ በማድረግ ነው’ ብሎ ለመናገር ይቅርና ይሄን ሀሳብ ማሰብም ኑፋቄ ነው ተባለ፡፡

3 - ቀጠሉና ቤ/ክ ትዘምናለች፤አስተዳደሯ ይስተካከላል የሚል መፈክር አነሱ፡፡መፈክሩ ሁላችንንም አማለለን፡፡በገዳማውያን ጸሎት በመታገዝ 3 ሚሊዮን የፈጀ ጥናት አቅርበናል ‘ወንዶች በጭብጨባ ሴቶች በእልልታ’ ተባልን፡፡ከማኅበራዊ ሚዲያ እስከ ዐለማዊ ጋዜጦችና የዲያስፖራው ሚዲያ ተቀባበለው፡፡ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ጥናቱ ለሚመለከተው አካል ደርሶ ገና አልጸደቀም፤ካሕናቱም አልመከሩበትም፡፡ቀጠለ፡፡ካሕናቱና ምዕመናኑ ስለ ጥናቱ ስልጠና ተብሎ አራት ኪሎ ላይ ከተሙ፡፡ጉዳዩ ግን ስልጠና ሳይሆን ራስን መስበኪያና ጥያቄዎችን ማፈኛ ወደ መሆን አዘነበለ፡፡

4 - ከአጥኚው ክፍል ውስጥ ከ12ቱ 8ቱ የማኅበሩ አባላት ሲሆኑ በቋሚ ትክለኛ አገልጋይ ደረጃ ደግሞ አንድ ጸሐፊ መሀላቸው ጣል ተደርጓል፡፡ካሕናቱ እዚህ ላይ ጥያቄ አነሱ “በጥናቱ ውስጥ እኛን የሚወክል ሰው የታለ?” አሉ፡፡ “ጉዳያችሁ ከጥናቱ ጠቀሜታ ነው ወይስ ከአጥኚው?” እየተባለ ትርፍ ንግግርና አፈና ተጀመረ፡፡ነገርየው “እኛ ስለናንተ ጥቅም ስለምናውቅ ባትሳተፉ ምን ቸገራችሁ--እናውቅላችኋለን” በሚል እንደሚተረጎም ማን አስቦት!!እነሱ እንደሆነ ቀናኢነታቸው ከማንም በላይ ነው!!ጥያቄው ቀጥሏል!! “ያጠናችሁት ጥናት የቤ/ክ የበላይ ሕግ በሆነው ቃለዐዋዲ የታቀፉ ነባር የስራ መደቦች ላይ ሽግሽግ የሚያደርግና የተወሰኑ ኃላፊነቶችን ጨምሮ እንደ አዲስ የሚደለድል ስለሆነ ቃለዐዋዲውን ቀድሞ መመሪያው መምጣቱ ከፈረሱ ጋሪው (በሐጋጊዎች አነጋገር against hierarchy of law) ሆነሳ?” ቢባል!! እረ ወዲያ!!ማን ሰምቶ!! አማሳኝ፣ ዘረኛ፣ ተሐድሶ፣ ካድሬ፣ ወያኔ፣ ሌባ፣ ሙሰኛ፣ምንደኛ፣ተላላኪ፣ደደብ፣ምቀኛ፣ሸረኛ…..የስድብ ሜኑ ተደረደረ!!

5 - አሁን ፅዋው ሞላ!!የአድባራትና ገዳማት አለቆችና ፀሐፊዎች መጋረጃውን ገልጠው ወጡ!!በይፋ ተሰባስበው በቤ/ክሕነቱ አዳራሽ አጀንዳቸውን ቀርጸው ፊርማ ማሰባሰብ ጀመሩ፡፡ገና በጠዋቱ መንገዳቸው ላይ ያለውን ፈተና ተገንዝበውት ነበር፡፡የማኅበሩ ኅቡዕ ሚዲያ የ30 እና 40 አመት አገልግሎታቸውን አፈር አስግጦ ዛሬ እሱ ላይ ጥያቄ ስላነሱ ብቻ ስማቸውን ጭቃ ከመቀባትም አልፎ በራሳቸውና በሚቀርቧቸው ሰዎች ጭምር እንደሚመጣባቸው እንደሚጠብቁ በአደባባይ ተናገሩ፡፡እነ ፋክት መጽሔት፣እነ ‘ቀናኢ ነን’ ብሎጎች የአደባባዩን አቋም “ጥብቅ ምስጢር” እያሉ ቲፎዞ ማንቀሳቀሳቸውን ቀጠሉ፡፡አልገረመንም!!ብሎግን ከግል ኅትመት ሚዲያ አቀናጅቶ በማኅበሩ አካሄድ ጥያቄ ባነሱ ሁሉ መዝመት ከሚሊኒየሙ ማግሥት ጀምሮ እንደ መልካም ትውፊት ስለተያዘ!!

6 - የካሕናቱ በአለቆችና በፀሐፊዎች መያዝ ባሰጋው ማኅበር ቀስቃሽነት ጉዳዩን የምዕመናንን መብት የማስከበር አስመስሎ ከ40 አመት በፊት በሰበካ ጉባኤና በልማት ኮሚቴ እየተመረጠ ከካሕናቱ ጎን ለጎን በቤ/ክ ጉዳይ ውሳኔ ሰጭ የሆነውን ምዕመን ሆድ ለማስባስ ተሞከረ፡፡ “መሬት አንቀጥቅጥ ሰልፍ እንጠራለን፣የአማሳኞችን ገመና እናወጣለን” ተባለ!!ተፎከረ!! ‘እረ ቀስ’ የሚል አልነበረም!! ‘ገመና-ገመና የሚባለው አካሄድ የሚሰራው ሰዎቹ ያጠፉ እለት እለቱን እንዲታረሙና ማስረጃውም ገና ትኩስ እያለ ቢሆን እንጅ ማኅበሩን ሲያነሱ ብቻ ከሆነማ ማኅበሩን ሳያነሱ ስለሚያጠፉት ሰዎች ደንታ የላችሁም፤ስለዚህ እናንተ ቤ/ክ ተጎዳች ምትሉት ማኅበሩ ላይ ጥያቄ ከተነሳ ብቻ ነው’ ያሰኝብናል የሚል ይሉኝታ እንኳ የለም!!ወደ ፊት ብቻ!!በዚህ መሀል ካሕናቱ በጥናቱ ይዘት፣በአጥኚው ስብጥር፣በጥናቱ የስልጠና ሂደት ያላቸውን ቅሬታ በመጠኑ ፈንገጥ ካለና ስሜታዊነት በታከለበት አኳኋን የማኅበረቅዱሳንን ሥም እየጠሩ አስረዱ--ለቅ/ፓትርያርኩ፡፡

7 - ‘የለውጥ አራማጅ ነኝ፣ተነቃናቂ ኃይል አለኝ፣ተወደደም ተጠላም ጥናቱ ሳይሸራረፍ ይተገበራል’ የሚለው ቡድንም በጋዜጣና በብሎግ ተጠራርቶ ፓትርያርኩ ላይ ገብቶ አጀንዳውን አስረዳ፡፡ፓትርያርኩም “ጥናቱ በሊቃውንት ክለሳ ተካሂዶበት ለቤ/ክ በሚበጅ መልኩ ይተገበራል፤ቀደም ሲል የመጡት ካሕናትም ጉዳያቸውን ማስረዳት መብታቸው ቢሆንም ዳኅፀ - ቃል (የምላስ ወለምታ) አድርገዋል” ብለው በአባታዊ መንገድ አስተናገዱ፡፡እዚህ ላይ ጨዋታው ፈረሰ!! ‘ጥናቱ አሁኑኑ’ የሚለው ኃይል የጭቃ ጅራፉን ያጮኸው ጀመር!!ጮኸ-ጮኸ-ጮኸ!!ይሄን ጩኸት ከኋላ ሆኖ ይዘውረው የነበረው ማኅበርም በጩኸቱ ተበረታቶ ነው መሰለኝ መጋረጃውን ገልጦ ወጣና ልሳኔ-የግሌ በሚል ስሜት ሐመር መጽሄቱን መዶሻ፣አቤቱታ አቅራቢዎቹን ካሕናት ደረቅ የማገዶ ግንድ አድርጎ አማሳኝ፣ተሐድሶ…እያለ ፈለጣውን ቀጠለ!!

8 - ካሕናቱ ግን ወይ ፍንክች!!ከነብር ተፋዞ (ተፋጦ) ማን እንቅልፍ ያበዛል!!እስከ በታች ሰራተኛ ወርደው 5ሺህ የሚገመት ፊርማ አሰባሰቡ፣ኮሚቴ አዋቀሩ፣መንግሥት እንዳይገላምጣቸው አሳወቁ (በመንግሥትም ተሰግስግንበታል እየተባለ ማስፈራሪያ ሆኗላ)፣ዐላማቸው ማኅበሩ ቤ/ክ ባሰመረችለት ልክ ከመጓዝ አልፎ ጣልቃ መግባቱን እንዲያቆም እንጅ ማኅበሩን ለማፍረስ አንዳች ፍላጎት እንደሌላቸው ተናገሩ፣የተላተምነው አድማሳትን የሚያቋርጥ የሚዲያ መረብ ከዘረጋ አካል ነውና በአስተዳደር ላይ ያላችሁ ራሳችሁን ካላስፈላጊ ምግባርና ከተበላሸ አስተዳደር ጠብቁ፣በተቻለ መጠን አባቶችን ሰድቦ ለሰዳቢ ከሚሰጠው የተሐድሶዎች እንቅስቃሴ አጀንዳችንን እንጠብቅ…የሚሉ መርሆዎች ተቀመጡ፡፡

9 - እንቅስቃሴው ከላይኛው የቤተክሕነት አካልም ቀላል የማይባል ድጋፍ አገኘ፡፡በፓ/ኩ ዕለተ - ሲመት የካቲት 24 በተደረጉ ቅኔያት ይሄው ሀሳብ…ወቤቴል አሀቲ ኢትኩን ዝርውተ፣አኃዝ ማኅበራተ፣መዋግደ ብዙኅ ፀጋከ ወአስተናድፍ ሥርዓተ…በሚሉ የሊቃውንት ቅኔያት ተንፀባረቀ፡፡ማኅበሩ ግን ይሄንን ከቅርቡ ያሉ ሊቃውንት ውትወታ ከመስማት ይልቅ ለሚመለከተው መምሪያና ላሉበት ሀገረ ስብከት ሳያሳውቅ የጠረፎቹን እየጠራ “ለማናውቀው ስብሰባ ኃላፊነት አንወስድም” ሲባል….የኛ ቤት እንደምታውቁት…እያለ የአዞ እንባውን መርጨት ጀመረ፡፡ታዲያ ሚዲያው አልሰነፈም!!ጉዳዩን ሲፈልግ ከወያኔ አነሳስ፣ሌላ ጊዜ ደግሞ ከተሐድሶ እንቅስሴ ጋር እያገናኘ ማኅበሩ ራሱን የሚያይበትን ውስጣዊ ዐይን ዐውሮ በትምክሕቱ እንዲጀቦን የውዳሴ ከንቱ ቡልኮ አጎናጸፈው፡፡ “አንድ ለእናቱ” እያሉ የቤተክርስቲያኒቱን የ2ሺህ አመት ታሪክ ለ20 አመቱ ማኅበር አሸክመው አንገዳገዱት፡፡ውስጡን እንዳይመለከት ጋረዱት!!

10 - እናም ይሄው አባላቱ ማኅበሩን የበጎነት እና የክፋት፣የጽድቅና የኩነኔ መለኪያ አድርገው ኮሽ ባለ ቁጥር ፡- ራሳቸውን መድኅን ቅሬታ አቅራቢዎችን ሰቃልያነ - እግዚእ፣ራሳቸውን ድመት ሌላውን አይጥ፣እነሱ ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊ ሌላው መናፍቅ፣እነሱ ለነፍስ ያደሩ ሌላው ለሆዱ….እያሉ እያስመሰሉ የልዩነት መስመር ሲያሰምሩ ይውላሉ፡፡የሚበዙት አባላቱም ማኅበራቸውን ከመፈተሸ ይልቅ ዕቡያን ክሶቹን ተቀብው አሜን-አሜን ይላሉ!!ይህ የማኅበሩ ከመዋቅር እና ከማዕከላዊ አስተዳደር የማፈንገጥ ዝንባሌ፣ስሙን ባነሱ የቤ/ክ ልጆች ላይ ሁሉ ከቅ/ሲኖዶስና ከፍርድ ቤት ውሳኔ በፊት የሚያደርገው “የተሐድሶ እና አማሳኝ” የውንጀላ ዘመቻ ለቀሳጥያን ተሐድሶዎችና የእነሱ ልሳናት ለሆኑ ብሎጎች ምን ያህል መንገዱን ጨርቅ እንዳደረገላቸው አልተረዱም!!እነዚህ በቁም ያሉትን፣እነዛ ደግሞ በቅድስና ያረፉትን ክብር በማጉደፍ ምዕመኑ ላይ የእጓለማውታነት ስሜት ለመፍጠር ይታትራሉ!!ከንቱ መታተር!!ፍኖተ ሐኬት--የክፋት መንገድ!!

Wednesday, October 15, 2014

«እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሳ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት!» ያሉት አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ወይስ የሞት መንፈስ?



ዋና ሥራ አስኪያጁ ‹‹ውድቀት እንዳይደረስብዎ አማካሪዎችዎ ሊያዝንልዎ ይገባል፤›› ማለታቸውን የገለጹት የስብሰባው ተሳታፊዎች አያይዘውም ‹‹ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎቻቸው ክፋት ከዕድሜያቸው ዐሥር ዓመት አሳጥረዋል፤ እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሣ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት፤›› ሲሉ መምከራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ( ሐራ)

«እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሳ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት!» ያሉት አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ወይስ የሞት መንፈስ ናቸው?

የሁላችንም ዕድሜ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነው። ማንም የማንንም ዕድሜ አያውቅም። ነገር ግን የሰውን ዕድሜ እናውቃለን የሚሉ ጠንቅ ዋዮችና መናፍስት ጠሪዎች ቢኖሩም አታላዮችና አጭበርባሪዎች ናቸው። ታዲያ አባ ማቴዎስ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስን እድሜ በዐሥር ዓመት ማሳጠር የሚችሉት በምን ጥበባቸው ነው? ደግሞስ ነፍስ ኄር አቡነ ጳውሎስ ሊቆዩ ከሚችሉበት ዕድሜ በዐሥር ዓመት ያሳጠሩትስ በምን ኃይል ነው? አባ ማቴዎስ ስለሟቹ ፓትርያርክ አሟሟት የሚያውቁትን ምሥጢር በፓትርያርክ ማትያስ ላይ ለመድገም እንደሚችሉ «እርስዎም ዕድሜዎ በዐሥር ዓመት እንዳያጥር ያስቡበት!» ሲሉ ማስጠንቀቃቸው የሚነግረን አንድ ምሥጢር አለ። እግዚአብሔር ማኅበረ ቅዱሳንን የማይወደውን ሁሉ ይገድላል እያሉን ነው ወይም ማኅበረ ቅዱሳንን የማይወደውን ሁሉ እኛ እንገድላለን ማለታቸው ነው። እንደዚያ ካልሆነ ማኅበረ ቅዱሳንን ባለመውደድና በሞት መካከል ምን ግንኙነት አለ?

    አባ ማቴዎስ በግልጽ ቋንቋ የተናገሩት ዐረፍተ ነገር እንደሚያስረዳው ስለፓትርያርክ ጳውሎስ አሟሟት በትክክል እንደሚያውቁ ነው። ይህንኑ ዕውቀት በፓትርያርክ ማትያስ ላይ እንደሚደግሙት ማስጠንቀቂያቸው ያስረዳናል።
«የአቦን ግብር የበላ ይለፈልፋል» እንዲሉ በማኅበሩ ላይ የደረሰው የማኅበረ ካህናቱና የፓትርያርኩ ግልጽ አቋም ያበሳጫቸው ሸዌው እጩ ፓትርያርክ አባ ማቴዎስ በንዴት ሳያውቁት ድብቁን አደባባይ ላይ አዋሉት። «አቡነ ጳውሎስን የገደልናቸው እኛ ነን» ሲሉ ራሳቸው መሠከሩ። እኛም በመጠየቅ ጨምረን እንዲነግሩን የምንፈልገው እንዴት አድረገው እድሜአቸውን ማሳጠር እንደቻሉ ምስጢሩን ከቻሉ በጀመሩበት መንገድ በፈቃዳቸው እንዲነግሩን፤ እምቢ ካሉ ደግሞ በሕግ ፊት እንዲዘከዝኩልን ለሚመለከታቸው ክፍሎች እናሳስባለን። 

በአንድ ከፍተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ላይ «ዕድሜህን በዐሥር ዓመት እናሳጥራለን!» የሚለው ዛቻ «ልብስ አጥበን እንተኩሳለን» እንደሚባለው የሠፈር ማስታወቂያ ተነቦ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም። በተዘዋዋሪ «እንገድልሃለን» ማለት ነው። የግድያ ዛቻ ደግሞ በምድራዊው ሕግ ወንጀል ነው።  በሰማያዊውም ቃል ዐመጻና ክፋት ነው።

«አስበው ክፉ ነገርን ተናገሩ። ከፍ ከፍ ብለውም በዓመፃ ተናገሩ» መዝ 73፤8 

አስበው የተናገሩት ቃል ከፍ ያለ የግድያ ዐመጻ ነው። አባ ማቴዎስ ቀድመው እንደማይሞቱ ያረጋገጡ ይመስል የአቡነ ማትያስን በፍጥነት በሞት መወገድ በአደባባይ እንደማወጅ ነውረኛና የከፋ አነጋገር ይኖር ይሆን? እግዚአብሔር አምላክነቱ ለአባ ማቴዎስና ለማኅበረ ቅዱሳን ብቻ የሆነ ያህል አቡነ ማትያስን ቶሎ እንደሚገድል መናገር አሳፋሪ ነው። እንግዲህ እነዚህ ናቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩት!

በማኅበረ ካህናቱ ስብሰባ ላይ የነበሩ አንድ ካህን ከተናገሩት አንድ ቃል እዚህ ላይ ልዋስ። « እነዚህ እኮ መንግሥትን ከአንድ ክ/ሀገር ወደሌላ ክ/ሀገር ያመጡ ሰዎች ናቸው እኮ፤ በዚያን ዘመን እንዲህ ማድረግ የቻሉ ዛሬ «አቢሲዲ ቆጥረውማ ማን ይችላቸዋል?» ማለታቸው አንድ ነገር ያሳስበናል። ለሥልጣን ሲሉ ሰው እስከመግደል ሊደርሱ መቻላቸውን ይገልጻል። እንደዚያ ካልሆነ አባ ማቴዎስ እስከዕድሜ ማሳጠር እብደት ቀመስ ንግግር ባልደረሱም ነበር። ምንም እንኳን የሰው ልጅ ዕድሜ በእግዚአብሔር እጅ ያለ ስለሆነ ሁሉም ሰው መሞቱ ባይቀርም አሟሟቱ ግን ልዩ ልዩ ነው።

 በጎርፍ፤ በመሬት መንቀጥቀጥ፤ በመኪና አደጋ፤ ገደል በመውደቅ፤ ውሃ ውስጥ በመስመጥ፤ በሕመም፤ በሰው እጅ በመገደል ወዘተ መንገድ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችላል። የአቡነ ማትያስ አሟሟት በእነ አባ ማቴዎስ እጅ ይፈጸም ዘንድ ከፈጣሪ የታዘዘ ካልሆነ በስተቀር ካልጠፋ ወቀሳና ሌላ የማሳሰቢያ ንግግር «እንደአቡነ ጳውሎስ ዕድሜዎት በዐሥር ዓመት ያጥራል» ባለሉም ነበር። እግዚአብሔር የነፍሳት ሁሉ ጌታ ስለሆነ  አሟሟታቸውን ልዩ ልዩ አድርጓል።  በእርግጥም የሰውን ነፍስና ሥጋ ይለዩ ዘንድ ምክንያት ከሚሆኑት መካከል ክፉ መናፍስቶች አንዱ ናቸው። አባ ማቴዎስን ከክፉው መንፈስ እንደአንዱ እንቁጠራቸው? ሞትን ያህል ዜና በአደባባይ ያወሩት የክፉው መንፈስ መልዕክት ቢደርሳቸው ይሆናል። እውነታው ግን እግዚአብሔር ለአባ ማቴዎስና ለማኅበራቸው ብቻ የቆመ አምላክ አይደለም። ኃጢአተኞችን ሁሉ በመታገስ ዕለትን በዕድሜአቸው ላይ የሚሰጥ ሁሉን ቻይ አምላክ ነው።
ነገር ግን አባ ማቴዎስ እንደጻድቅ ራሳቸውን ቆጥረው በሌላው ሰው ላይ ሲፈርዱ ለዚህ ክፉ አሳባቸው የሞት መልአክ ቀድሞ ወደእርሳቸው ቢመጣስ?

«ክፉ ሰው ዓመፃን ብቻ ይሻል ስለዚህ ጨካኝ መልአክ ይላክበታል» መዝ 17፤11 ይላልና መጽሐፉ።

አቡነ ማትያስም ከክፉ ሰዎች እጅ እንዲድኑ አብዝተው መጸለይ የሚገባቸው ይመስለናል። ዳዊት በዝማሬው እንዳለው

 « አቤቱ፥ ከክፉ ሰው አድነኝ፥ በልባቸውም ክፉ ካሰቡ ከዓመፀኞች ሰዎች ጠብቀኝ ቀኑን ሁሉ ለሰልፍ ይከማቻሉ» መዝ 140፤1

የዕድሜ ወሰን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

«የሰው ዕድሜ የተወሰነ ነው፥ የወሩም ቍጥር በአንተ ዘንድ ነው፥ እርሱም ሊተላለፈው የማይችለውን ዳርቻ አደረግህለት» ኢዮ 14፤5
አባ ማቴዎስ ማኅበረ ቅዱሳንን የሚነካ ሁሉ ይሞታል እያሉ ይናገራሉ።  ታዲያ አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ናቸው ወይስ የሞት መንፈስ???? የምታውቁ ንገሩን!!

Saturday, October 11, 2014

ፓትርያርኩም፤ ካህናቱም ስለማኅበረ ቅዱሳን በአንድ ድምጽ ተናገሩ!

ቤተ ክርስቲያን ግልጽ የሆነ መዋቅር ያላት ቢሆንም በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራት፣ ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ በመንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት ያከማቹና እያከማቹ በመሆናቸው፣ ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠራቸው ከሆነ አሸባሪ የመሆን ዕድላቸው የሰፋ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስታወቁ፡፡