Saturday, April 19, 2014

«አሮጌውን እርሾ አስወግዱ፤ ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና»



ዕብራውያን     פֶּסַח «ፔሳኽ» ይሉታል። ፋሲካ ማለት ነው።  በወርኀ ኒሳን በዐሥራ ዐምስተኛው ቀን ይከበራል። ሥርዓቱ የሚጀመረው በዐሥራ አራተኛው ቀን ዋዜማ ሲሆን በፋሲካው ሳምንት እርሾ የገባበት ምንም ዓይነት ምግብ መመገብ ክልክል ነው።ዕለቱን ተቦክቶ ወዲያው የሚጋገር እንጂ የኮመጠጠ ወይም የቦካና የዋለ፤ያደረ መመገብ በሕጉ እንደተቀመጠው ከእስራኤል አንድነት ያስወግዳል። ከማንኛውም እርድ ላይ ጥሬ መብላት ወይም ከበሉትም አስተርፎ ማሳደር አይፈቀድም። ለመስዋዕት የሚቀርበው የበግ ወይም የፍየል መስዋዕትም እድሜው ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ጤናማና የተመረጠ መሆን ይገባዋል። በዐሥራ ዐራተኛው ቀን ምሽት መስዋዕቱ ይታረዳል።ሥጋውን ደግሞ ሌሊት  ከመራራ ቅጠል ጋር ቀላልቅለው ይበሉታል። 
ደሙን ደግሞ  የበሩን ሁለት ረድፍ «መቃንና ጉበኑን» ይቀቡታል።  ሁለቱን ቋሚ መቃንና የላይኛውን ጉበን ሲቀቡት ይህንን ቅርጽ ይይዛል።


ይህ ቅርጽ የዕብራውያን ስምንተኛውን ፊደል «ኼ» የተባለውን ይወክላል። (እንደአማርኛው በጉሮሮ ሳይሆን በላንቃ የሚነበብ ነው) «ኼ» ማለት በዕብራውያን ትርጉም «ሕይወት» ማለት ነው። ዕብራውያንም በፊደላቸው በ«ኼ» ቅርጽ በሚቀቡት ደም የተነሳ ወደፈርዖናውያን ሠፈር የሚያልፈው ሞት አይነካቸውም። ምክንያቱም ሕይወት የሚል ማኅተም በራቸው ጉበንና መቃን ላይ ታትሟልና። ፋሲካ ማለት ይህ ነው። በደሙ ምልክት የተከለሉ በሕይወት ለመቆየት ዋስትና የያዙ ሲሆን ይህንን ማኅተም ያላገኙና ምን እየሆነ እንዳለ የማያውቁ ደግሞ  በሞት የሚወሰዱበት  የፍርድ ምልክት ነው። ደሙ የሞትና የሕይወት መለያ ምልክት ሆኖ አገልግሏል።
ይህ ሥርዓት እስራኤላውያንን ከባርነት፤ ከጠላት አገዛዝና ከመገደል የታደገ የዋስትና መንገድ ነበር። እንደዚሁ ሁሉ የአዲስ ኪዳኑ ፋሲካ ሕዝብና አሕዛብን ከሰይጣን ባርነትና ከዘላለም ሞት የታደገ በመሆኑ ሐዋርያው ጳውሎስ «እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና» 1ኛ ቆሮ 5፤7 በማለት የሚነግረን።  አሮጌውን እርሾ ካላስወገድን ፋሲካችን የሆነውን ክርስቶስ መቀበል አይቻልም። የክርስቶስን ፋሲካ እካፈላለሁ በማለት የበዓሉን አከባበር ማድመቅ፤ እንኳን አደረሰህ/አደረሰሽ መባባል ልምድ እንጂ የመለወጥ ምልክት አይደለም። የክፋት እርሾ የተባሉትን ሐዋርያው ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ ሲነግረን እንዲህ ይለናል። «ሴሰኛ፤ ገንዘብን የሚመኝ፤ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ፤ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ» ከመሆን መታቀብ ብቻ ሳይሆን ከሆኑትም ጋር አብሮ ባለመብላት ጭምር በመከልከል ከአሮጌው እርሾ ሆምጣጣነት መራቅ እንዲገባን ያስፈልጋል። (1ኛ ቆሮ 5፤11) የእስራኤል ዘሥጋ ፋሲካ መጻጻና የቦካ ይከለክል እንደነበረው ሁሉ የአዲስ ኪዳኑ ፋሲካም እንዲሁ ይከለክላል። በኃጢአትና በዐመጻ የቦካ የውስጣችንን ሆምጣጣ እርሾ ካላስወገድን በስተቀር በፋሲካው የሚገኘውን ሕይወት በፍጹም  አናገኝም።  የቀደመው ፋሲካ እርሾ ያለውን ነገር ከቤቱ ያላጠፋ «ከእስራኤል ጉባዔ ተለይቶ ይጥፋ» የሚል ሕግ ነበረው።  ምድራዊው ፋሲካ ይህንን ያህል ከከበረ ሰማያዊውማ እንደምን የበለጠ አይከብር? ፋሲካን መናገርና ፋሲካን አውቆ መኖር የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ስለፋሲካ ብዙ ማስተማርና መናገር ይቻል ይሆናል። ስለፋሲካ የመልካም ጊዜ መግለጫና ስጦታም መለዋወጥ ይቻል ይሆናል። ፋሲካን ማክበር ማለት 2 ወራት በጾም አሳልፎ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታልህ/ፈታልሽ» ተብሎ ልጓም አልቦ የመሆኛ ሰዓት ደረሰ በማለት የሰላምታ መሰጣጣት ፕሮግራም አይደለም። ጾሙ ሲፈታ እንደፈለገን ልንበላ፤ ልንጠጣ፤ ልንናገር የልጓም አጥራችን ተከፈተ ማለት ከሆነ በአሮጌው እርሾ ብቻ ሳይሆን ከሰው የልማድ ስርዓት ጋር እንኖራለን ማለት ነው። የክርስቶስ ፋሲካ ግን በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ አይገኝም። ፋሲካ በስግደትና በወይራ ቅጠል በመጠብጠብ የሚገኝም ጸጋ አይደለም።  ፋሲካ የአንድ ወቅት ራስን ማስገዛትና በጽኑ እሳቤና ጭንቅ ማለፍ ውስጥ የሚመጣም አይደለም።
ፋሲካ በልባችን መቃንና ጉበን ላይ የደሙን ምልክት በመያዝ ዕብራውያን ከሞት እንዳመለጡበት የ «ኼ» ምልክት ማኅተም በመያዝ ብቻ ነው የምንድነው። ያን ጊዜ ብቻ ነው ሞት በራችን ላይ ያለውን የአዲስ ኪዳኑን «ፔሳኽ» አይቶ የሚያልፈው። ይህንን የደም ማኅተም ለመያዝም ከክፋት፤ ከሀሰት፤ ከግፍና ከዐመጻ እርሾ መለየት የግድ ነው። ከዝሙት፤ ከስርቆት፤ ከጉቦ፤ ከምኞትና ከኃጢአት ሁሉ እርሾ ሳንለይ ውስጣችን የሞላውን መጻጻ ተሸክመን የፋሲካ ሕይወት የለም። እስራኤላውያን መዳን የቻሉት የፋሲካቸውን የበግ ደም ምልክት በመያዛቸው ብቻ ነው።  እኛም የአዲስ ኪዳኑ የእግዚአብሔር በግ የክርስቶስን ደም ምልክት ካልያዝን በማንም በሌላ ምልክት ወይም ጻድቅ ዋስትና ልንድን አንችልም። ሁሉም ይህንን የደም ምልክት የመያዝ ግዴታ ስላለበት ማንም ለማንም ዋስትና ሊሆን እንደማይችል ጳውሎስም «ልዩነት የለም፤ ሁሉም የመዳን ጸጋ ያስፈልገዋል» አለን። 

«እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ» ሮሜ 3፤22-24
እንግዲህ  ከፋሲካው ተስፋ የምናደርግ ሁላችን እስኪ ራሳችንን እንመርምር። እንደመጽሐፍ ሊያነበን በሚቻለው ከፋሲካችን ክርስቶስ ፊት እስኪ ራሳችንን እናንብበው። በእውነት እነዚህ እርሾዎች በውስጣችን ከሌሉ ከ2000 ዓመት በፊት ለሕይወት የፈሰሰውን ደም ይዘናል ማለት ነው። ያኔም ሞት በኛ ላይ ምንም ሥልጣን እንደሌለው አረጋግጠናል። እስራኤላውያን የበራቸውን ጉበንና መቃን በቀቡ ጊዜ ሞት እንደማይነካቸው እርግጠኞች እንደነበሩ ሁሉ እኛም የበለጠውንና የተሻለውን የሕይወት ደም በእምነት ስለያዝን ለዘላለማዊ ሕይወት እርግጠኞች መሆን እንችላለን። ከዚያ ባሻገር በየዓመቱ በሚመጣ በዓል የሚገኝ የደም ምልክት የለም። በጥብጠባና በስግደትም የሚገኝ የሕይወት ዋስትና እንዳለ ካሰብን የፋሲካውን ምስጢር በልምድ ሽፋን ስተነዋል ማለት ነው። የተደረገልንን ማሰብ አንድ ነገር ሆኖ ሰው ግን ዓይኑን በዚያ በዓል ላይ ተክሎ የዓመቱ ኃጢአት ወይም ሸክም እንደሚወድቅ ማሰብ ስህተት ነው። ዓመቱን ሙሉ ከክፋትና ከግፍ እርሾ በመላቀቅ፤ ለአንድም ሰከንድ የማይለይ ምልክት ልባችን ጉበንና መቃን ላይ ደሙን በእምነት ይዘን መገኘት የግድ ይሆንብናል። ያኔ ነው ፋሲካችን ታርዷል የምንለው። ያኔም ነው ሁልጊዜ በሕይወት መንገድ ላይ እንዳለን የምናውቀው። መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን፤ መንፈሳዊ ጉዞ እንዲሰምርልን ዕለት፤ ዕለት መታደስ መታደስ ይገባዋል።
«ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል» 2ኛ ቆሮ 4፤16 ንስሐ እንግባና እንታደስ።
ፋሲካችን የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ያደረገልንን ውለታ እያሰብን ውስጣችንን መፈተሽ የግድ ነው። በአምናው እኛነታችንና በዘንድሮው እኛነታችን መካከል የሕይወት ለውጥ ከሌለን ሞት በመጣ ጊዜ ምንም የመዳን ምልክት እንደሌላቸው ፈርዖናውያንን ወደዘላለማዊ ሞት መሄዳችን እውነት ነው። በወይራ በመጠብጠብ 30 እና 40 ለመስገድ ከመሽቀዳደም ይልቅ፤ ከሞት የማምለጫ የፋሲካው ዓርማ ክርስቶስን ከኃጢአት በጸዳ ማንነታችን ውስጥ ዘወትር ይዘነው እንኑር። ዝሙት፤ ውሸት፤ስርቆት፤ ሃሜት፤ ነቀፋ፤ ምኞትና ገንዘብን መውደድ ሁሉ ሳንተው ፋሲካን ማክበር አይቻልም። ከቦታ ቦታ በመዞርም ፋሲካ አይገኝም። ፋሲካ በልባችን ላይ አንዴ የተሰራው የክርስቶስ የእምነታችን ከተማ ነው። በዚያ ላይ የማይጠፋ ብርሃን አለ። ክርስቶስ ባለበት በዚያ የልባችን ከተማ ውስጥ ማስተዋል፤ ደግነት፤ በጎነትና ቅንነት አለ። ከዚያ መልካም ከተማ የሚወጣው ሃሳባችን የተራቡትን ያበላል፤ የታረዙትን ያለብሳል፤ የታመሙትን ይጠይቃል። ኑሮአችን፤ አነጋገራችንና አካሄዳችን በልክ ነው። ዕለት ዕለት በምንኖረው ሕይወት እንጂ በዓመት አንድ ቀን በሚከበር ፋሲካ ክርስቶስን መምሰል አይቻልም። ሞት የደሙ ምልክት የሌለባቸውን እስራኤላውያንን ሁሉ ይገድል ነበርና። እኛም በሰማይ የተሰጠንን ተስፋ እስክናገኝ ድረስ ሞት ከተጠበቀልን ተስፋችን እንዳያስቀረን ፋሲካችን ክርስቶስን ዕለት ዕለት በልባችን ይዘን እንኖራለን። ያኔም በክርስቶስ ያለ ተስፋችን ምሉዕ ስለሆነ ስለመዳናችን አንጠራጠርም። አብርሃም ልጅ ሳይኖረው «ዘርህ ዓለሙን ይሞላል» ሲባል በእምነቱ ተስፋውን ተቀበለ። በክርስቶስ ትንሣዔ ያመንን እኛ ደግሞ እንደምንድን ካመን የተሰጠን የመዳን ተስፋ በሰማይ እውነት ሆኖ ይጠብቀናል።  ምክንያቱም የመዳናችን የእምነት ተስፋ ክርስቶስን በልባችን ዕለት ዕለት ይዘን እንዞራለንና!!

Monday, April 14, 2014

«ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ከሆነ እኔም አክራሪ ነኝ» የሚሉ ድምጾች ምነው በዙሳ?



የሚያከሩ እስኪበጠስ ያክርሩ፤ የማያከርና ተግባብቶ የሚኖር የት ይድረስ?
 
በአንድ ወቅት ዳንኤል ክብረት የተባለው ሰውዬ በእንቁ መጽሔት ላይ እንደተናገረው «ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ሆኖ የገደለው ሰው የለም!» ብሎ ነበር። በዳንኤል አስተሳሰብ «አክራሪ» ማለት በሃይማኖተኝነት ሰበብ ሰው የመግደል ደረጃ ላይ ሲደረስ መሆኑ ነው። ከመግደል በመለስ ያለው ኃይልና ዛቻ፤ማሳደድ ተፈቅዷል ማለት ነው? ሌላው የማኅበረ ቅዱሳን የሜሪላንድ አፈቀላጤ ኤፍሬም እሸቴ ደግሞ «አክራሪ ሃይማኖተኛ መሆን ጥሩ ነው» ሲል ተመራጭነቱን በማሳየት የማኅበረ ቅዱሳንን የማክረር እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ሲታትር ታይቷል።  አክራሪ በባህሪው እኔ ትክክል ነኝ ከሚል ጽንፍ ተነስቶ፤ የምለውን ተቀበሉኝ፤ እምቢ ካላችሁ ወግዱልኝ፤ አለበለዚያ እኔው በኃይል አስወግዳችኋለሁ በሚል ድምዳሜ የሚያበቃ አስተሳሰብ ነው።  አንዳንዶች አክራሪነት በዚህ ዘመን የተከሰተ አድርገው ሲመለከቱ ይታያል። ትርጉሙና የተግባራዊ እንቅስቃሴው ስፋትና ጥልቀት ተለይቶ ታወቀ እንጂ አክራሪነት ጥንትም ነበረ።  በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 9 ላይ እንደተመለከተው ኢየሱስ ለሐዋርያቱ እንደነገራቸው «አስቀድማችሁ ወደሰማርያ ከተማ ሂዱና፤ ጌታ ይመጣል ብላችሁ አስናድታችሁ ጠብቁኝ» ብሎ ባዘዛቸው ጊዜ የከተማይቱ ሰዎች መልዕክቱን እንዳልተቀበሉ ሐዋርያት ስለተመለከቱ «ጌታ ሆይ፥ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን?» ብለውታል።  ጌታ ግን፤ «የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም» ብሏቸዋል።  አክራሪዎች ራሳቸውን የእግዚአብሔር ብቸኛ ወታደሮች አድርገው ራሳቸውን ያስቀምጣሉ። ስለዚህ እኛን ያልመሰለ ይጥፋ ባዮች ናቸው። አስተምሮ፤ ተከራክሮ መመለስ ስለማይችሉ አጭሩ መፍትሄ ማስወገድ ነው።
እንደዚሁ ሁሉ በፖለቲካው ከተሰማሩት ድረ ገጾች አንስቶ እስከጥቃቅኖቹ ብሎጎች ድረስ አንዱ ከአንዱ እየተቀባበሉ የማያውቁትን ማኅበር ለማሳወቅና ለሃይማኖት ማክረር እጅግ ጠቃሚ እንደሆነ የሚገልጹ ጽሁፎችን እስከማራገብ ድረስ ዘልቀዋል።  በፌስቡክና በትዊተር ገጾች «ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ከተባለ እኔም አክራሪ ልባል» ከሚለው ድምጽ አንስቶ የማኅበረ ቅዱሳንን ዓርማ የሚያሳይ ግለ ስእል በመለጠፍ አጋርነታቸውን ለማሳየት የሞከሩ ብዙዎች ናቸው።  ሁሉንም ስንመለከት «አክራሪ ሃይማኖተኛ» መሆን አስፈላጊ እንደሆነና «እኛም የዚሁ ሰልፍ አባሪ ሆነን ለሃይማኖታችን አክራሪ ነን» የሚል ይዘት ያለው አቋም እየተንጸባረቀ መገኘቱን መገንዘብ ይቻላል። ሃይማኖተኛ ነን የሚሉቱ ወገኖች ያሉበትን ምክንያት ከማየታችን በፊት ፖለቲከኞቹ ነገሩን ለማስጮህ የፈለጉበትን ምክንያት እንመልከት።

1/ ፖለቲከኞች ማኅበረ ቅዱሳንን የመደገፍ ምክንያት፤

ፖለቲከኛ ሃይማኖት የለውም ማለት ባይቻልም ሃይማኖተኛ ግን ፖለቲከኛ መሆን አይችልም። ፖለቲከኛ ሃይማኖት ሊኖረው የሚችለው ስለሃይማኖቱ አውቆና አምኖበት በመከተሉና እምነቱ የሚያዘውን ለመፈጸም እንደእግዚአብሔር ቃል ለመኖር ለራሱ ኪዳን የገባ ሳይሆን በውርስ ከቤተሰቦቹ የተረከበው ወይም በልምድ ሲከተለው ስለኖረ ራሱን ሃይማኖት እንዳለው አሳምኖ ሲያበቃ ከፖለቲካ የሚገኘውን የምድራዊ ሳይንስ ጫወታ የሚጫወት ሰው ነው።
 ምክንያቱም ፖለቲካ ባላጋራህ የሆነውን የሌላኛውን ሰው አመለካከትም ሆነ ተግባር በምትችለው መንገድ በልጠህ ወይም ጠልፈህ በመገኘት ምድራዊ ሥልጣንን መቆጣጠር ማለት ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ የሰውን ልጅ ጠላትነት የማይቀበል፤ ባላጋራውም ሰይጣን ብቻ መሆኑ አምኖ ለእግዚአብሔር መንግሥት ሲል ሃይማኖታዊ መመሪያውን በመከተል ለማይታየው ሰማያዊ ሕይወት ሲል ከሚታየው ጠልፎ የመጣልና የመዋሸት ዓለም የጸዳ ማለት ነው። የዲሞክራሲ ጣሪያ ነክተናል ከሚሉት አንስቶ የነሱኑ መንገድ ተከትለናል እስከሚሉቱ ድረስ ሁሉም ፖለቲከኞች በፖለቲካል ቲዎሪ ከሚነገረው ታሪክ ባሻገር ማስመሰል፤ መዋሸት፤ ማታለል፤ ጠልፎ መጣል ወይም እውነተኛ መስሎ መታየት፤ ሀቀኛ፤ የህዝብ ወገንተኛ መሆንን መደስኮር በሁሉ ዘንድ መኖሩ በማስረጃ አስደግፎ መናገር ይቻላል።  በግርድፉ የተቀመጠውን የፖለቲካ ትርጉም ብንመለከት ለምድራዊ ስልጣን መታገል የመጨረሻ ግብ መሆኑ እውነት ነው።
« Politics is the activities associated with the governance of a country or other area, esp. the debate or conflict among individuals or parties having or hoping to achieve power»
« ፖለቲካ ከሀገራዊ ወይም ከክልላዊ የሕዝብ አስተዳደር ክንዋኔዎች ጋር በተዛመደና በተለይም በተቃርኖአዊ የእርስ በእርስ የሃሳብ ፍጭት የተነሳ ተስፋ በሚሰጥ የፓርቲዎች ስነ ሞገት ብልጫ አግኝቶ የስልጣን ኃይልን የመጨበጥ ግብ ያለው ነው»
ፖለቲካዊ ስልጣን ማለት ግን ለሃይማኖተኛ ጥቅም አይሰጥም፤ ወይም አይጎዳም ማለት አይደለም። እንደሚመራበት የፖለቲካ ርእዮት /አመለካከት/ ይወሰናል። ሃይማኖታዊ መንግሥት ባለበት ሀገር መንግሥቱ ለተመሰረተበት ሃይማኖት አብላጫውን ወይም ዋናውን አገልግሎት ይሰጣል። ሌሎች ሃይማኖቶች እንደመንግስታዊው ሃይማኖት እኩል መብት ሊኖራቸው አይችልም።  ሃይማኖት የለሽ መንግሥት ከሆነ ደግሞ ሁሉም ሃይማኖቶች የመንግስቱ ጠላቶች ነው። ሴኩላር/ ገለልተኛ/ የመንግስት አወቃቀር ባለበት ሀገር ደግሞ መንግስት በሃይማኖቶች ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ ይደነግጋል። ጣልቃ የማይገባው ለሴኩላር መንግሥታዊ አወቃቀሩ ስጋት እስካልሆኑ ድረስ ብቻ ነው። እንደመንግሥታዊው የፖለቲካ አወቃቀር ሥርዓቱ ሃይማኖትን ሊጠቅም ወይም ሊጎዳው መቻሉ እርግጥ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ በአፄዎቹ፤ በደርግና በኢህአዴግ መካከል ባለው የፖለቲካ ርእዮት የተነሳ ፖለቲከኞቹ ሃይማኖትን የሚመለከቱበት መነጽር የተለያየ ነው። ሃይማኖትን በተለያየ መነጽር የሚያዩ ፖለቲከኞች፤ ሃይማኖተኞች ሊሆኑ አይችሉም።  ፖለቲከኞች የቆሙለትን የተለያየ የፖለቲካ ስርዓት ያገለግላሉ።  ፖለቲከኛ ሆኖ ሃይማኖተኛ ለመሆን ከባድ የሚሆነው ለዚህ ነው። ሃይማኖተኛ ሆኖ መዋሸት አይቻልም። ፖለቲከኛ  ስርአቱን እስከጠቀመ ድረስ ይዋሻል፤ የሌለ ተስፋ ይሰጣል።  አላስፈላጊ ወይም ጠቃሚ ካልሆነ ደግሞ ማስተባበያ ወይም ይቅርታ ሊጠየቅ ይችላል። ለሃይማኖተኛ ንስሀ እንጂ ማስተባበያ ወይም ይቅርታ የሚል የአደባባይ ዲስኩር የለም። ፖለቲከኛ ሃይማኖት ሊኖረው ቢችልም ሃይማኖተኛ ግን በጭራሽ ፖለቲከኛ መሆን አለመቻሉ እርግጥ ነው። ታዲያ የልምድ ሃይማኖት ያላቸው ነገር ግን ሃይማኖተኛ መሆን የማይችሉ ፖለቲከኞች ማኅበረ ቅዱሳን ሲነካ የሚጮሁት ለምንድነው? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት። ዋናው ነጥብ «የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው» ከሚል የፖለቲካ ፍልስፍና የተነሳ ነው። 

 ሃይማኖት የሌላቸው /እምነት የለሾች/ ይሁኑ ማኅበረ ቅዱሳንን በልምድ የሚመሳሰሉ ባለሃይማኖቶች እና «ማኅበሩ ተነካ ማለት የእግዚአብሔር መንግሥት ተነካ» ባይ የዋሆች ሁሉም በአንድነት ውጥንቅጡ በወጣ አቋም ውስጥ ሆነው ለማኅበሩ ለመጮህ ሞክረዋል። የሚገርመው ደግሞ የማኅበረ ቅዱሳንን መጥፋት የሚመኙ እስላሞች ሳይቀሩ «የሃይማኖት ነጻነት ይከበር» በማለት ለማኅበሩ ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት መሞከራቸው ነው። ዋነኛ ዓላማቸው የሃይማኖት መከበር ስላሳሰባቸው ሳይሆን በእስልምና ጎራ ያሉ ታሳሪዎችን ድምጽ ከማኅበረ ቅዱሳን ጎራ ካሉት ጋር በማስተሳሰር ጉዳዩን ለማጦዝ ከመፈለግ የተነሳ ነው።  በዘመነ ኢህአዴግ እስልምና ተጨቁኗል ቢሉ ለሰሚው ግራ ነው።  በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ብቻ የእስላም መስጊድ ከቤተ ክርስቲያን ቁጥር የበለጠው በዘመነ ኢህአዴግ መሆኑ በጭራሽ ሊስተባበል የሚችል አይደለም።  ከአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ 16% ለሆነው የእስልምና ተከታይ 180 በላይ መስጊዶች ሲኖሩት 74% ከመቶው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ያሉት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር 150 ገደማ ብቻ ነው። በኦርቶዶክስ ተጨቁነን ነበር የሚሉትን አቤቱታ እንደኢህአዴግ ያካካሰላቸው መንግስት ለእስላሞች የለም ማለት ይቻላል። በዘመነ ኢህአዴግ የተሰራው መስጊድ በሺህ ዘመናት ውስጥ ከተሰራው ይበልጣል።
 እንዳላት ተከታይ ብዛትና ሊኖራት እንደሚችለው የድርሻ ስፋት ድምጿ ያልተደመጠው ኦርቶዶክስ ናት ማለት ይቻላል። ከመንግሥታዊ ክፍል ያሉ፤ ፕሮቴስታንቱም፤ እስልምናውም፤ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ የሚለው አሮጌ ፖለቲከኛው ሁሉንም ስንመለከት በግልጽም ይሁን በስውር ይህች ቤተ ክርስቲያን ለሀገሪቱ ባበረከተችው ከመጠቀምና በስሟ ከመነገድ በስተቀር ያደረጉላት አንዳችም ድጋፍ የለም። ላበረከተችው በጎ አስተዋጽኦ ዋጋ መስጠት በራሱ ትልቅ ነበር።

ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን «ልጠፋ ነው» እያለ ለሚያሰማው ጩኸት ፖለቲከኞቹን ያስተባበራቸው ኢህአዴግን እንደጋራ ጠላት ለመፈረጅ እንጂ በሃይማኖት ስለተሰሳሰሩ አይደለም። ኦርቶዶክስ እንድትጠፋ ሲሰሩ የቆዩ የቀድሞ መንግስት ፖለቲከኞች፤ የተለያዩ የሌኒናዊ ፓርቲ አባላትና ርዝራዦች ሳይቀሩ ለማኅበረ ቅዱሳን ሲጮሁ እያየን ነው። እውን ለኦርቶዶክስ አዝነው ነው? የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖታዊ መሪዎች ከመግደል አንስቶ፤ ጣልቃ ገብቶ በመሾም፤ ሲኖዶሱን በመከፋፈልና በማዳከም ትልቅ ድርሻ ያላቸው እነዚህ ጮኸው የማይሰለቹ ፖለቲከኞች ትልቁን ድርሻ ይወስዳሉ። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳንን ለመደገፍ መሞከራቸው ቤተ ክርስቲያኒቱን የማዳከም ቀጣይ ተግባራቸው ማሳያ ተደርጎ ከሚወሰድ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኒቱ ከማኅበሩም ሆነ ከፖለቲከኞቹ ያተረፈችውም ምንም ነገር የለም።

2/ ሃይማኖተኞች የማኅበሩ ደጋፊዎች፤

ማኅበሩ ራሱ እንደሚለው ከሆነ 35,000 መደበኛ አባላትና 500,000 ተከታይ አባላት እንዳሉት ይነገራል። ያለውን የፋይናንስ አቅም በትክክል ባይናገርና ባናውቅም ቅሉ ከልዩ ልዩ የንግድ ተቋማት ገቢ ምንጮቹ የሚያገኘውን ካፒታል ሳንጨምር ከ35,000 አባላቱ ላይ ብቻ በግርድፉ ብንገምት በወርሃዊ መዋጮ መልክ 10 ብር ቢሰበስብ 350,000 ብር ወርሃዊና ከ500,000 ተከታይ አባላቱ ላይ ደግሞ ለልዩ ልዩ የማኅበሩ ልማታዊ ስራዎች ሰበብ በዓመታዊ ድጋፍ 10 ብር በነፍስ ወከፍ እንዲሰጡት ቢጠይቅና ካሉት ተከታይ አባላቱ መካከል 400,000 ያህሉ ለ10 ብር የድጋፍ ጥያቄው ምላሽ ቢሰጡ 4,000,000 ብር ያገኛል ማለት ነው። ከወርሃዊ  የአባልነት መዋጮ ገቢው ጋር በዓመት ሲሰላ ከ8 እስከ 9 ሚሊዮን ያላነሰ በዓመት ይሰበስባል ማለት ነው። ይህ ስሌት በመንፈሳዊ ጉዞ ሰበብ፤ በመጽሔት፤ በሆቴልና በሱቅ ሽያጭ፤ በካሴት፤ በሲዲ፤ በእርዳታ ጥሪ፤ ከበጎ አድራጎት፤ ከለጋሽ፤ ከቤት ኪራይ ወዘተ የሚገኘውን ግዙፍ ገቢ ሳይጨምር መሆኑ ታሳቢ ይደረግ።  ጆርጅ በርንስ እንዲህ ይላል። « Don't stay in bed, unless you can make money in bed»  «አልጋህ ላይ ሆነህ ገንዘብ ካላገኘህ በቀር አልጋህ ላይ አትቆይ» እንደማለት ነው። ይህ ብሂል የገባው ቅዱስ ማኅበር «መኒ» ይሰራል። «መኒ» የማይገዛው ስልጣን፤ ጉልበትና እውቀት በሌለበት ዘመን የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር አይባልም።

ይህ ማኅበር ከአንታርክቲካ በስተቀር በሁሉም ዓለማት ላይ ቢሮዎች አሉት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ባለችበት ቦታ ሁሉ አለ። በሳንባዋ ይተነፍሳል፤ በደም ስሯም ይዘዋወራል። ነገር ግን መዋቅሩና የመዋቅሩ መረብ ማኅበረ ቅዱሳዊ ነው። አብዛኛው አባላቱና ደጋፊዎቹ አብረው የተሰለፉት ቤተ ክርስቲያኒቱን የደገፉና የረዱ እየመሰላቸው መሆኑ እርግጥ ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ከዘመኑ ጋር መዘመን ባይችልና ባንቀላፋበት ቦታ ሁሉ ማኅበሩ እየተገኘ ከበሮ እየመታ፤ እየዘመረ አለሁልሽ እያለ ማኅበሩንና ቤተ ክርስቲያኒቱን ለይቶ የሚያይ ተከታይ ባይኖር አያስገርምም።  የሚገርመው እንመራሃለን የሚሉቱ የማኅበሩ ተመሪ ሆነው መገኘታቸው ነው።

ሀ/ ሊቃነ ጳጳሳቱ፤

ሊቃነ ጳጳሳቱን ማኅበሩ እንዴት አባል አድርጎ እንደሚይዝ ዝርዝር ውስጥ አንገባም። ነገር ግን ሊቃነ ጳጳሳቱ የሲኖዶስ አባልና በቤተ ክርስቲያኒቱ የአንዱ ሀገረ ስብከት ወይም ክፍል ተጠሪ ሆነው ሲያበቁ የማኅበሩን ዓላማ ተቀባይ፤ የማኅበሩ ጠበቃና ተከራካሪ ሲሆኑ ግርምት ይፈጥርብናል። ዋናው ጥያቄ የሚነሳውም ማኅበሩ የሲኖዶሱ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ነው ወይ? ሊቃነ ጳጳሳቱ በሀገረ ስብከታቸው መሥራት ያልቻሉትን የሚሰራላቸው ወኪላቸው ነው ወይ?  ምን መስራት ያልቻሉትን፤ ምን መስራት እንዲችልላቸው፤ የትኛውንስ ጉዳይ እንዲያስፈጽም ውክልና ተሰጥቶታል?
 በማኅበሩ ስያሜና ቁመና እንዲሁም በሲኖዶስና በሊቃነ ጳጳሳት መካከል ያለው የሥልጣን፤ የደረጃ ክፍተት የሚለካው በምንድነው? የሚሉ ጥያቄዎች ግራ የሚያጋቡና ምላሻቸውንም በውል የሚያውቅ አለመኖሩ ጉዳዩን አስደማሚ ያደርገዋል።  ስለዚህ ጥርት ያለ መልስ የሌለው የአንድ ማኅበር ዓላማ በአእምሮአቸው የሰረጸ ነገር ግን የሲኖዶስ አባል ነን የሚሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአንድም፤ በሌላ መንገድም የማኅበሩ ጉዳይ ፈጻሚ ሆነው መገኘታቸው እርግጥ ነው።

ለ/ ወጣት የሰንበት ት/ቤት አባላት፤ የጥምቀት ተመላሽ ማኅበር፤ የጉዞና መንፈሳዊ ማኅበራት፤

እነዚህ ወጣት ክፍሎች ከማኅበሩ ሰፊና ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ አንጻር በቁጥጥር ስር መዋላቸው የግድ ነው። ደግሞም አስፈላጊ መሳሪዎች ናቸው። በአንድ በኩል በችግር ወቅት ለማንቀሳቀስ፤ በሌላ መልኩም በችግር ቀን ለመደበቅ ሊያገለግሉ ይችላሉ። መሰረታዊ የትጥቅ መሳሪያቸው ደግሞ «ቤተክርስቲያንን ከልዩ ልዩ ኃይሎች መጠበቅ» የሚል መንፈሳዊ መሰል ትጥቅ ሲሆን ወጣቶቹ ዓይናቸውን በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ በእምነት እንዲጥሉ በማድረግ ማኅበሩ ለሚፈልገው ዓላማ ማገልገል እንዲችሉ ተደርገው ይቀረጻሉ። ወጣቶቹ በእርግጥም ከልባዊ እምነት ተነስተው የሚከተሉ ስለሆነ ቤተ ክርስቲያንን እንደማገልገል እንጂ ማኅበሩን እንደመታዘዝ አይቆጥሩም ወይም ማኅበሩን ማገልገል የቤተ ክርስቲያኒቱን ፈቃድ እንደመፈጸም አድርገው እንዲያስቡ ተደርገዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ ሰንበት ተማሪዎች፤ የጥምቀት ተመላሽ ቡድኖችና የጉዞ ማኅበራት የማኅበሩ ታዛዥና ተጠባባቂ ኃይሎች ናቸው። የእነዚህ ማኅበራት አባል ሆኖ ማኅበረ ቅዱሳንን ማውገዝ ወይም መቃወም በጭራሽ አይታሰብም።

ሐ/ የመንግሥት ተቋማት አባሎቹ፤

ማኅበሩ ከሚያገኘው ሰፊ የፋይናንስ አቅም አኳያ አባላትን ለመመልመል መጠቀሙ እንዲሁም ከሚጓዝበት አደገኛ የስብከት ዘዴው አንጻር አእምሮአቸውን የመጠምዘዝ ስልት ረገድ በመንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ ብዙ አባላትን ማደራጀት ችሏል። የማኅበሩን አቅም ማደራጀት ብቻ ሳይሆን አንድ አቅጣጫ ማየት እንዲችሉ ተደርገው የተቀረጹ የመንግሥታዊ ተቋማት አባላቱ በጣም ጠቃሚ ክፍሎቹ ናቸው።  በመንግሥት ጉዳይ እንደማይገቡ ማሳያዎቹ ናቸው። በሌላ መልኩም የመረጃ ምንጭ ሆነውም ያገለግላሉ። የየትኛውም የመንግሥት ተቋማት ሰራተኛ በየትኛውም ማኅበርና የእምነት ተቋም ውስጥ አባል የመሆን መብት ያለው መሆኑ ባይካድም የያዘውን የመንግስት ስራ ለማኅበሩ አገልግሎት ማዋል ግን ወንጀል ነው። ፖሊሳዊ ስልጣናቸውን በመጠቀም ለማኅበሩ አገልግሎት ተሰማርተው ያላግባብ ያሰሩ፤ የደበደቡ አሉ። ቤተ ክርስቲያኒቱ ስትጠይቃቸው ከመተባበር ይልቅ ማኅበሩ ሲጠራቸው አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጡ የመንግሥታዊ ስልጣን አካላት መኖራቸው ማኅበሩ የቱን ያህል ስር እንደሰደደ ያሳያል። እነዚህ አካላት ከማኅበሩ ጎን በግልጽም፤ በስውርም መቆማቸው ነገሩን ከባድ ያደርገዋል።

3/ ማኅበሩ ራሱን ለማዳን የሚቀያይራቸው ስልቶች፤

ማኅበሩ የልዩ ልዩ ሰዎች ተዋጽኦ መሆኑ እንዳለ ሆኖ አመራሩ ራሱን ከወቅቱ የፖለቲካ ሙቀት ጋር በማስማማት የሚያደርጉት የጉዞ ስልት እጅግ የሚደነቅ ነው። ማኅበሩ ሃይማኖታዊ ድርጅት እንዳይደለ ይታወቃል። የድርጅት/ Organization/ ቅርጽ ያለው ነገር ግን በተቋምነት/ Institution/ ደረጃ የተደራጀ ይመስላል። ደግሞም በቤተ ክርስቲያን ስር ያለ የሰንበት ተማሪዎችም ማኅበር ለመምሰልም ይሞክራል። ምሁራን አመራሩ በሳል ስለሆኑ ከሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ስር ያወጡት አለምክንያት አይደለም። የሰንበት ት/ቤት በመባልና የሚንቀሳቀስበት ቅርጽ ተመሳሳይ ስላይደለ እንዳይበላሽበት ከመፈለግ የተነሳ የተዘየደ መላ መሆኑ ነው። ዛሬም ያ የማኅበሩ አመራር ኢህአዴግ ከገባበት የሙስሊሞች እንቅስቃሴ፤ ከምርጫ 2007 ዝግጅት እና የጥላቻ ፖለቲካ ካሰባሰባቸው ኃይሎች ጋር ያለበትን ክፍተት በመጠቀም ከመንግሥት ጋር ያለውን ልዩነት ለመጠቀም እየሰራ ይገኛል። በአንድ ወገን ስለማኅበሩ ጉዳይ እያስጮኸ ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ ከጩኸቱ በሚገኘው የስውር ድምጽ ብዛት መንግሥት ወደያዘው ፤ልቀቀው እሰጥ አገባ እንዳይሄድ ባለበት በማስቆም ለመንግስት ፈቃዳት ሁሉ ታማኝ መሆኑን ለማሳየት በመሞከር ራሱን በማዳን ስልት ላይ ተጠምዷል። የቅዱሳን ማኅበር ሳይሆን ጠንካራ የፖለቲካ ቅዱሳን ያሉት ማኅበር ስለሆነ ሊደነቅ ይገባዋል።

4/ ማኅበሩና የመጨረሻ ውጤቱ፤

በትግርኛ የሚተረት አንድ ተረት አለ። «ወጮስ እንተገምጠልካዮ ወጮ» ይላሉ። «ብርድ ልብስን ብትገለብጠው ያው ብርድ ልብስ ነው» እንደማለት ነው። ያውም የደብረ ብርሃን ብርድልብስን ብትገለብጠው ያው ዥንጉርጉሩ  የደብረ ብርሃን ብርድ ልብስ ነው። የሰንበት ት/ቤት?/Sunday school/  ድርጅት? /organization/ ተቋም? /Institution/ የቱ እንደሆነ ማኅበረ ቅዱሳን እስካሁን የለየለት አይደለም። ነገር ግን ቅርጹንና መልኩን እንደእስስት እየቀያየረ 22 ዓመት ቆይቷል። ቤተ ክርስቲያኒቱ ለማኅበሩ ምኑ እንደሆነች ሲኖዶሱ በእርግጥ አያውቅም። ማኅበሩ ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን እንዴት እንደሚጠቀምባት አሳምሮ ያውቃል። በጣም አደገኛና ስልታዊ ጉዞ የማድረግ ብቃት ያለው አመራር እንዳለው በጉዞው ላይ የሚያጋጥመውን ሳንካ ካለፈበት ተነስቶ መናገር ይቻላል። እውነተኛና ቅን የቤተ ክርስቲያን አባላት የሱም አባል መሆናቸው ሳይዘነጋ ማለት ነው። ነገር ግን ማኅበሩ  ቢደግፉት፤ ቢከተሉት፤ ቢጮኹለት፤ ቢታገሱት እንደ«የደብረ ብርሃን ብርድ ልብስ ቢገለብጡት ያው ብርድ ልብስ» ከመሆን የሚያልፍ አይደለም!!


Tuesday, April 1, 2014

አንዳንድ “ማኅበራት” ራሳቸውን «ቅዱስ» ሲሉ በጣም ያስቁኛል...





 (an article by Tedy Sih) በመጠነኛ መሻሻል የቀረበ
መቸም ለጽድቅ የሚሰሩ ፖለቲከኞች እንደሌሉት ሁሉ ፖለቲካን ስራየ ብለው የሚሰማሩበትና በሱም ለፅድቅ የበቁ ቅዱሳን የሉም፡፡ ለፖለቲካ ሲሉ ተደራጅተው ራሳቸውን ‹‹ቅዱሳን›› ብለው የሚሰይሙ ደፋሮች ግን አይጠፉም፡፡ የፖለቲካ ግባቸውን ለማሳካት የሚከተሉት እኩይ የትግል ስነ ዘዴንም ጭምር ‹‹ቅዱስ ጦርነት›› ብለው የሚጠሩ ነፈዞዎችም ሞልተዋል፡፡ እኛ ሀገር ወስጥ በእንዲህ ያለ ፖለቲካ ላይ የተጣዱ ‹‹ቅዱሳን ፖለቲከኞች›› እንደምናየው ሁሉ ‹‹ቅዱሳን›› ገጣምያን፣ ጋዜጠኞች፣ ምሁራን፣ ጥላቻ ቀስቃሾች፣ ጠብ ተንኳሾች፣ አመጽ ናፋቂዎች፣ ጦር አውርድ ባዮች ወዘተ መታዘብ ከጀመርን ሰነባብተናል፡፡ አሁን ደግሞ እነዚህን ሁሉ የሚያገናኘውን የሚስጥር ቋጠሮ ሊገልፅልን ፈልጎ በትጋት የተነሳ የሚመስል አንድ ‹‹ቅዱሳን ማኅበር»ኢህአዴግ ሊያጠቃኝ ተነስቷልእያለን ነው። ከስሞታው ዜና እንደምንረዳው ይህ ማኅበር ራሱን እንደፖለቲካ ፓርቲ እንደሚቆጥር እማኝነት ይሰጣል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ከፖለቲካ የለሁበትም ማለትም ይከጅለዋል። ባለህንጻ፤ ባለሆቴል፤ ነጋዴና ገንዘብ የሚሰበስብ ቅዱስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አልተሰማም። ተቋም ነኝ ወይም ድርጅት ነኝ ማለት አንድ ነገር ነው። ነገር ግን «ቅዱስ ማኅበር» እባላለሁ ቢለን «ቅዱሱ ማኅበር» ለማለት የሚያስችለን ምክንያት የለውም። ሲጀመር ብላቴ የጦር ካምፕ ተነሳ፤ ሲጨረስ በስመ ክርስትና ባለቢዝነስ መሆን ቻለ፤ እውነታው ይህ ነው። ማኅበሩና ቅድስና ከመነሻው እስካሁን  ድረስ አይተዋወቁም። በስምም ሆነ በግብር ከማኅበሩ ጋር የሚመሳሰሉ የቅዱሳን ታሪክ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አልነበረም።
ከሁለት ዓመት በፊት ዲያቆን መልከጸዴቅ የተሰኘ የማኅበሩ አባል እንዲሁም የማኅበሩ መስራችና መሪ የነበረው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በጻፏቸው እማኝነቶች ማኅበሩየቄሳርን ለቄሳርየሚለውን ህግ በደፈጠጡ ህቡእ ፖለቲከኞች እንደሚመራ በስፋት ጽፈው አስነብበው ነበር። እስቲ ለዛሬ ከመልከጸዴቅ ጽሁፎች ቀነጫጭቤ ላቅርብላችሁ። በቀጣይ ክፍሎች ሙሉ ጽሁፎቻቸውን በተከታታይ አቀርባለሁ።
“...አዎ! ፖለቲካና ቅዱስነት ለየቅል ናቸው። ሰዎች ራሳቸውን በጀማ ቅዱሳን የሚል መጠርያ ሰጥተው በይፋ መንቀሳቀሳቸው ራሱ ችግሮች አሉበት። በጥላቻ የሚመራ ጽንፈኛ ዓለማዊ አጀንዳ ለማስፈጸም በፖለቲከኞች ሲደረግ ደግሞ ችግሮቹ የከፉ ናቸው። ቅድሚያ ነገር «ስም ይመርኆ ኅበ ግብሩ» ቅድስና ላይ አይሰራም። ቅዱስ ስም ፍጹም እምነትንና ቅዱስ ምግባርን ተከትሎ የሚመጣ ነገር ነው እንጂ ስምህን ቅድስት ወይም ቅዱስ ስላልክ ቅዱስ ትሆናለህ ማለት አይደለም። በተጨማሪም ጥቂቶችም ሆኑ ብዙሃን ተደራጅተው ራሳቸውን በወል ቅዱሳን ብለው መሰየማቸው የግብዝነታቸውና የትእቢታቸው መጠን ከፍ አድርጎ ከወደ ቤተ ሳጥናኤል እንደመጡ ይነግረን እንደሁ እንጂ ከእግዚአብሔር ቤት እንዳልሆኑ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። በይበልጥም በአስተምህሮተ ቤተክርስቲያን ይህ ድርጊት መንፈስ ቅዱስን እንደመሳደብም ይቆጠራል። የቄሳርን ለቄሳር ቁም ነገር ያስተዋሉ የሚመስሉት የዘመናችን ፖለቲካዊ አስተሳሰቦችም ይህንን አይደግፉም። ከየትኛውም ቲዮሎጂያዊም ሆነ ዓለማዊ ፍልስፍና እና አመክንዮ አንጻር ሲታይም ድርጊቱ ርኩሰት ነው።
በስሙ በአመሰራረቱና በግብሩ ይህን መሰል ርኩሰት የተሸከመ ወገን በሃገራችን ስለመኖሩም ተጨባጭ ማስረጃ እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያለ የለም። የማኅበሩ አባላት ሙሉ በሙሉ ፖለቲከኞች ባይሆኑም አመሰራረቱ፣ መስራቾቹና እስካሁንም እየመሩት ያሉት ፖለቲካኞች እንጂ ሃይማኖት መሪዎች አልነበሩም።አሁንም አይደሉም። እርግጥ በመንፈሳዊ ሰናይ ምግባር ቤተክርስቲያኗን ሊያገለግሉ ማኅበሩን የተቀላቀሉ ብዙ ቀና ወጣቶችና አባቶች ነበሩበት።አሁንም አሉ። እነሱም ስላሉ በጎ ገጽታ እንዲኖርው ስለማድረጋቸውም በማንም አይካድም። ቢሆንም እስትንፋስ ዘርተው ይዞት እንዲጓዝ የፈለጉትን ፖለቲካዊ ተልእኮ በማሸከም ማኅበሩን ያቆሙትና የሚመሩትታላላቅ ወንድሞችየሚል የኮድ ስም ያላቸው ፖለቲከኞች ናቸው።አሁንም ድረስ አመቺ ሽፋን በሚሰጥ ተቋም ውስጥ አድፍጠው ማኅበሩን ይመሩታል። ቆምኩለት ከሚለው መንፈሳዊ ተልእኮው ተጻራሪ ለሆኑ የጥላቻና የጥፋት እንቅስቃሴዎች መፈናጠጫ ፈረስ እድርገውታል።.....”
“...ማኅበሩ ስለ ፖለቲካዊ ስነፍጥረቱ እና ብላቴ ስለመመስረቱ አንዳችም ትንፍሽ አይልም። ስለ አመሰራረቱና ተልእኮው በማኅበሩ ድረ ገጽ የሚነበበውም የሚስጥራዊነቱና የአደናጋሪነቱ ተቀጽላ ሊባል የሚችል ነው። በአምላክና በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ 1984 .. በኢ... ሰንበት /ቤቶች ማደራጃ ስር መንፈሳዊ አገልግሎትና ምግባረ ሰናይ ለማስፋፋት እንደቆመ ይገልጻል። ግቡም በከፍተኛ ትም/ተቋማት ያሉ ወጣት ተማሪዎች ወንጌል በማስተማር ኃላፊነት የሚሰማቸው የቤተክርስቲያንና የሃገሪቱ አባላት ማድረግ ነው ሲል፤ ጥናት ተኮር ስራዎች በመስራትም የቤተክርስቲያናን ችግሮች ለመፍታት እንደሚጥር ይናገራል።...
እርግጥ በጎ አደራጎታዊ ስራዎቹንይበል! እባክህን እነሱን ብቻ አጠናክረህ ቀጥል፤ ቤተክርስቲያኗንም አገልግል!” ይሰኝባቸዋል እንጂ ማንም አይከፋባቸውም። ችግሩ ይሄኛው ገጹ የሚያምር ሽፋን ሁኖ ሌላኛውን ገጹ መደበቂያ መሆኑ ላይ ነው። ምስረታው ለፖለቲካ ሲባል ነበር። መስራቾቹም ፖለቲካኞች ናቸው። አንቀሳቃሽ ሞተሩ የሆነውን ፖለቲካዊ ተልእኮውንም ሆነ ተግባሩን እስካሁን በኅቡእ እየመሩ የሚያሽከረክሩትም በማኅበሩ ይፋዊ መዋቅር የማይታዩ ነገር ግን ወሳኝ ስልጣን ያላቸውታላላቅ ወንድሞችናቸው።...”
ከመልከጸዴቅ ዘማኅበረበኩር ጽሁፍ የተቀነጨበ

Saturday, March 29, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን የሚፈርሰው በራሱ ተግባር ነው፤ ኢሕአዴግ ላለፉት 22 ዓመታት መቼ ነካው?



ይህ ህንጻ የማነው? የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን? የመንበረ ፓትርያርክ? የኢንቨስተር? የነጋዴ? የአስመጪና ላኪ?

የሀገሬ ሰው «ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮኻል» ይላል። ይህ አባባል ለሰሞነኛው የማኅበረ ቅዱሳን የጅቡ በላኝ ጩኸት ይስማማል። ኢህአዴግ ሊያጠፋኝ ነው ሲል በየግል ጋዜጣው ማስወራቱ 22 ዓመታት ኢህአዴግ በሚመራት ሀገር ውስጥ ያልነበረ ይመስላል። ሲነግድ፤ ሲያስነግድ፤ ሲሸጥ ሲለውጥ፤ከግብርና ታክስ ተከልሎ በሚሊዮኖች ብር ህንጻ ሲገነባ በሀገሪቱ ኢህአዴግ ያላየው ወይም የማያውቀው ይመስላል። ኢህአዴግ ማኅበረ ቅዱሳንን በአስማት ይሁን በምትሃት እስከዛሬ ሳያየው ቆይቶ አሁን ለማየት ዓይኑን ሲከፍት ማኅበረ ቅዱሳንን አገኘውና ሊበላው ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ኢህአዴግ ሊያጠፋኝ ለምን ፈለገ ሲል ለመጠየቅ የተገደደ ይመስላል። በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያለው ተግባሬ ከማኅበረ ካህናቱ ጋር አጋጨኝ፤ በማያገባኝ አስተዳደር ውስጥ እጄን ሳስገባ ተገኘሁ እንዳይል ከመሬት ተነስቶ ኢህአዴግ ሊውጠኝ ነው ወደሚል ቅስቀሳ መግባቱን  ከመምረጡ በስተቀር በምድር ላይ ያለው እውነታ ግን የምርጫ ዘጠና ሰባት ውጤትና ተከትሎ የመጣው ፖለቲካዊ ቀውስ ስንቱን ፓርቲና የተቃዋሚ መሪዎች እየደፈጠጠ ሲያልፍ ማኅበረ ቅዱሳን ግን በቤተ ክርስቲያኒቱ ታዛ ተጠልሎ አልፏል። ኢህአዴግ ቢያጠፋው ኖሮ ያኔ ባጠፋው ነበር።
ከዚህ በፊት ማኅበሩ እንደጥራጊ አውጥቶ የጣለው ዳንኤል ክብረት ይህን ኢህአዴግ ሊበላኝ ነው የሚለውን የማኅበረ ቅዱሳንን ዘፈን እንዲህ ሲል በደጀሰላም ብሎግ ላይ አውጥቶ ነበር።
«እኔ እንደምገምተው የማኅበሩ አባላት መንግሥትን እንዲፈሩ እና እንዲጠሉ የሚፈልጉ አካላት በአመራሩ ውስጥ ሳይኖሩ አይ ቀርም፡፡ ምንጊዜም አንዳች ከባድ ነገር ሲነሣ መንግሥት እንዲህ ብሎናል፣ በዚህ ስብሰባው እንዲህ ብሏል፣ ሊዘጋን ነው፣ ሊያስረን ነው፣ ሊጨርሰን ነው ከማለት ያለፈ አንድም ቀን በጎ ነገር ስለ መንግሥት የማያነሡ አካላት አሉ»
 ስለዚህ ከዚህ አባባል ተነስተን ልንል የምንችለው ነገር ይህ መንግሥት ሊበላን ነው የሚለው ዜማ እንደስልት የተያዘና መንግሥት በአባላቱ ዘንድ እንዲጠላ የተዘየደ መሆኑ ነው። ከዚያም ባሻገር መሰሪ ስራውን ለመደበቅ ራሱን ጻድቅ አድርጎ በሌሎች ሰዎች ዘንድ ለመሳል የታቀደ ጥበብ ሲሆን ጻድቁ ማኅበረ ቅዱሳንን ኢህአዴግ ሊያጠፋው ስለሆነ ኦርቶዶክሳውያን የሆናችሁ ሁሉ የዚህን መንግሥት መሠሪነት ተመልከቱ ብሎ ክፉ ስዕል ለመስጠት የተፈለገ ብልጠት ነው።
እውነቱ ግን ማኅበረ ቅዱሳን ነጋዴ ድርጅት መሆኑ ማንም ያውቃል። የግል ይሁን የአክሲዮን ማኅበር መሆኑ ያልታወቀና የራሱን ሀብት የፈጠረ ተቋም ስለመሆኑም ስራው ምስክር ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ከንግድ ተቋማቱና ከልዩ ልዩ የገቢ ምንጮቹ ባሻገር የራሱ የሆኑ አባላት ያሉትና የአባልነት መዋጮ የሚሰበስብ ድርጅት ነው። ከዋናው ማዕከል ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኒቱ ቁመት የራሱ የሆነ መዋቅርና  ራሱን የቻለ አደረጃጀት ያለው ነገር ግን አደረጃጀቱ በየትኛው የሀገሪቱ  የአደረጃጀት ፈቃድ ላይ እንደቆመ ያልታወቀ መሆኑም እርግጥ ነው። ይህንን የራሱ ተቋማዊ ኅልውና ያለውን ማኅበር በሀብቱ፤ በንግድ ተቋማቱ፤ በመዋቅራዊ አካላቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመቆጣጠርና የማዘዝ ምንም ሥልጣን የላትም።  በአንጻሩም ማኅበሩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስር ተሸፋፍኖ እንደመጠለሉ መጠን ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ ላይ የመቆጣጠርና የማዘዝ ሥልጣን እንዳላት ግምት ያለው በመሆኑ መንግሥት ይህን ድርጅት ነክቶት አያውቅም። ስለዚህ ይህንን ማኅበር ቤተ ክርስቲያኒቱም፤ መንግሥትም ሳይመለከቱት ከሁለት ወገን ቁጥጥር ነጻ ሆኖ 22 ዓመት ዘልቋል።
 «ለሁሉም ጊዜ አለው» እንዲሉ ሆኖ ማኅበሩን ማነህ? ምንድነህ? የት ነህ? ምን አለህ? ምን አገባህ? የሚሉ ካህናትና የአመራር አካላት ተባብረው በመነሳት መጠየቅ ሲጀምሩ ጥቂት ሟሳኞችና አሟሳኞች ወደሚል ሃሳብ ለመውረድ ተገዷል።  በምንም ደረጃ ያሉ ሰዎች ማኅበረ ቅዱሳንን መክሰስ መቻላቸው የማኅበሩን ማንነት ማሳያው ተግባሩ እንጂ ክሱ አይደለም።  እየተከሰሰ ያለው ማኅበር በተግባሩ ያልታወቀ ማኅበር ባለመሆኑ በሟሳኞችና አሟሳኞች የቃላት ጫወታ እየፈጸመ የቆየውን ሸፍጥ ሸፍኖ ማስቀረት አይቻልም።
ማኅበረ ቅዱሳን በተግባር በሌለው ሥልጣንና መብት መናፍቃን ናቸው ያላቸውን ኢትዮጵያውያንን በራሱ ጥቁር መዝገብ አስፍሮ አስደብድቧል፤ ሰልሏል፤ ስም አጥፍቷል፤ አስፈራርቷል፤ እንዲሰደዱ አድርጓል። ማኅበረ ቅዱሳን በቤተክርስቲያኒቱ ስም መጽሔትና መጻሕፍትን፤ ካሴትና ቪዲዮ፤ አልባሳትና ንዋየ ቅድሳትን ከታክስና ከቀረጥ ነጻ ሆኖ ነግዷል። የማኅበረ ቅዱሳን አቋም የሚቃወሙ ሁሉ ጠላቶቹ ናቸው። የሚደግፉት ደግሞ ጳጳሳቱ ሳይቀሩ ወንጀል ቢኖርባቸው እንኳን የቤተ ክርስቲያኒቱ ታማኝ አገልጋይ ተደርገው ዜና ይሰራላቸዋል፤ ሙገሳ ይሰጣቸዋል። አባ እስጢፋኖስን ማንሳት ይቻላል። ጠላቶቼ ከሚላቸውና ስማቸውን ሌሊትና ቀን ሲያጠፋቸው ከቆዩት ጳጳሳት ውስጥ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ደግሞ የጥላቻ የአፍ መፍቻው ናቸው። ሌሎቹም ፈርተው አንገታቸውን ደፍተውለታል። የተገዳደረውን አንገት ያስደፋል፤ አለያም ቀና ካለ አንገቱን ይሰብራል።  ሌላው ቀርቶ ሲያመሰግናቸው የነበሩትን አዲሱን ፓትርያርክ ጠላቶቼ የሚላቸውን ሰዎች ሲቀጣ በቆየበት መልኩ በስም ማጥፋት ቅጣት ናዳውን እያወረደባቸው ይገኛል። ለራሱ ኅልውና ብቻ የሚጨነቅ፤ ካልመሰለው ደግሞ ሲያወድሳቸው ለነበሩት ሳይቀር ግድ የሌለው ማኅበር ስለመሆኑ ከድርጊቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።  ወትሮውንም ሸፋጭ ነጋዴ ገንዘቡን እንጂ ወዳጅና እውነት በእሱ ዘንድ ዋጋ የሌላቸው ስለሆኑ የሚያስበው ጊዜያዊ ትርፉን ብቻ ነው። በዚህ ዙሪያ ማኅበሩ አሸንቅጥሮ የጣለውና ለተቀበለው የእጅ መንሻ በውጪ እንዳለ የሚለፈልፈው ዳንኤል ክብረት ማኅበሩ ስለግለሰቦችና ስለቤተ ክርስቲያኒቱ ደንታ ቢስ እንደሆነ ያጋለጠው እንዲህ ሲል ነበር።
«ዲያቆን በጋሻው ማስተማር የጀመረው መቼ ነው? ማኅበሩ በነዲያቆን በጋሻው ላይ ሃሳብ ዛሬ መሠንዘር ለምን ጀመረ? በጋሻው ለቤተ ክርስቲያን አደጋ ነው ብሎ ስላሰበ አይደለም፡፡ በጋሻው ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ስለ ተናገረ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ምንም ያልተናገረው ማኅበር ስሙ ሲነሣ ቤተ ክርስቲያን ተነካች ብሎ ተነሣ፡፡ ማኅበሩ አቡነ ጳውሎስን በተመለከተ የተለየ አቋም መያዝ የጀመረው መቼ ነው? «እርሳቸው ማኅበሩን ሊያፈርሱ ነው» ብሎ መሥጋት ከጀመረ በኋላ፡፡ አባ ሠረቀንም ቢሆ ንኮ ዛሬ ዛሬ በእምነት ችግር ይከሳቸዋል እንጂ፣ ከእርሳቸው ጋር ያለው ዋናው ችግሩ ማኅበሩ መነካቱ ነው፡፡ አባ ሠረቀ ማኅበረ ቅዱሳንን ሳይነኩ የፈለጉትን ቢሆኑ ኖሮ አይናገራቸውም ነበር፡፡ ባለፈው ጊዜ በቅዱስ ሲኖዶስ ላይ ችግር ሲፈጠር፣ ዝምታን መርጦ የነበረው አመራር የመንግሥት አካላት ከቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት ጋር ሆነው ስለ ማኅበሩ ሲያወያዩት ግን አገር ይያዝልኝ አለ፡፡ የአዋሳ ምእመናንን ችግር በዝምታ ያለፈው አመራር አባ ሠረቀ አንዳች ነገር ተናገሩ ብሎ ድምፁን አሰምቶ ተናገረ፡፡ እነዚህ እና መሰል ሁኔታዎች አመራሩ የሚቆረቁረው ማኅበሩ ሲነካ እንጂ ቤተ ክርስቲያኒቱ ስትነካ አለመሆኑን ያመለክታሉ» ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ከራሱ በላይ ማንንም እንደማይወድ እርግጥ ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን በፖለቲካው ዙሪያ ከምርጫ 97 በፊትም ሆነ በኋላ ስላለው ሁኔታ መንግሥት በቂ መረጃ እንዳለው ይሰማል። በዚህ ዙሪያ መንግሥት ያለውን መረጃ እስኪያወጣ ድረስ የምንለው ነገር የለም። ነገር ግን ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያኒቱን ሲያምሳት መቆየቱን፤ እጁን እያስገባ ሲኖዶሱን ሳይቀር እንደሚጠመዝዝ እናውቃለን። ማኅበሩ ደፋርና የልብ ልብ የተሰማው አንዳንድ የሲኖዶስ አባላት ተጠግቶ የጉባዔ ሃሳብ በራሱ መንገድ እስከመጠምዘዝ የመድረሱን አቅም እየለካ በመሄዱ ነው። ዛሬ ላይ ያ ነገር የለም። ፓትርያርክ ማትያስ ለዚህ የማኅበሩ ሃሳብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ገና አንድ ዓመት ሳይሞላቸው ከኢህአዴግ ጋር ተመሳጥረው ሊያጠፉኝ ነው እያለ ስም ወደማጥፋት ወርዷል። በተቃራኒው ደግሞ ማንም እንደማያጠፋው በሚገልጽ ጀብደኝነቱ ፓትርያርክ ጳውሎስም እንደዚሁ ሊያጠፉኝ ሞክረው እንደማያዋጣቸው አውቀው አጃቸውን ከእኔ ላይ ለማንሳት ተገደዋል በማለት ለፓትርያርክ ማትያስ የማስጠንቀቂያ ማስታወቂያ እየሰራ ይገኛል። እጅዎን ከእኔ ላይ የማንሳትን ጉዳይ ችላ ሳይሉ ከቀድሞው ፓትርያርክ ትምህርት ውሰዱ በማለት ማሳሰቢያ እየሰጠ መሆኑ ነው። የሚፈራው ከተገኘ ጥሩ ጀብደኝነት ነው፤ ነገር ግን ባለቀ ጊዜ ማላዘን ዋጋ የለውም። ማኅበረ ቅዱሳን ቤተክርስቲያኒቱ ስንት ችግር ባለባት ሰዓት ራሱ ችግር ፈጣሪ ሆኖ ካለቦታው የተገኘ ማኅበር ስለሆነ ተገቢ ቦታውን መያዝ ካለበት ሰዓቱ አሁን ነው። ማኅበረ ካህናቱና የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር አባላት ጠንክሮ መታገል የሚገባችሁ ወቅት ቢኖር ዛሬ ነው። ማኅበሩ ቁጭ ብሎ አዋጭ የሆነውን መንገድ መቅረጽ ካለበት ቶሎ ብሎ ይህንኑ እንዲፈጽም ምክር እንለግሰዋለን። የአክሲዮን ማኅበር፤ የሃይማኖት ተቋም፤ በጎ አድራጊ ድርጅት ወይም የተሻለ ነው ብሎ የደረሰበትን ውሳኔ ወደተግባር መቀየር ካለበት ቀኑ ሳይመሽ በብርሃኑ ይሆን ዘንድ ልናሳስበው እንወዳለን። ሲሆን ዘንድሮ፤ ካልሆነም በቀጣዩ ዓመት፤ ቢረዝም፤ ቢረዝም አንድ ቀን ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጉያ እንደመዥገር የተጣበቀበት ቀን እንደሚያበቃ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ምክንያቱም ማኅበሩና ተግባሩ፤ ካህናቱና አስተዳደሩ መቼም ቢሆን አሁን ባለው መንገድ አብረው መጓዝ አይችሉምና ነው።  ከዚህ ሁሉ ፓትርያርኩም፤ ካህናቱም፤ አመራሮችም፤ መንግሥትም ይህንን ማኅበር ቦታ የማስያዙን ጉዳይ ችላ ሊሉት አይገባም። ማኅበረ ቅዱሳን ሳይኖር ቤተ ክርስቲያን ነበረች፤ ማኅበረ ቅዱሳን ሳይኖርም ትኖራለች!!!  «ማኅበረ ቅዱሳን ከሌለ ቤተ ክርስቲያን ትጠፋለች» የሚለው ራሱ ማኅበረ ቅዱሳን ብቻ ነው።

Monday, March 24, 2014

አዲሱ ፓትርያርክ ብዙ ሥራ ይጠብቃቸዋል! ( በድጋሚ የቀረበ )

ይህንን ጽሁፍ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በተሾሙ ማግስት በመካነ ጦማራችን ላይ አውጥተነው ነበር፤ እነሆ አንድ ዓመት አለፈው። ከተናገርናቸውና ይፈጸሙ ዘንድ ከምንጠብቃቸው ተስፋዎች ውስጥ ምን ያህሉ ተግባራዊ ተደርጓል የሚለውን ወደኋላ መለስ ብለን ለማየት እንዲቻል ደግመን አቀረብነው። ቤተ ክርስቲያኒቱ እንደጥንቱ ዛሬም በልምድና በግምት እየተጓዘች ነው ወይስ የተሻለ የአስተዳደር ማዕከል መገንባት ችላለች? የሚለውን ጥያቄ አሁንም ማንሳታችንን አልተውንም። ከወቅቱ ሰሞነኛ ዜናዎች መካከል በማኅበረ ቅዱሳን ላይ እየቀረቡ የሚገኙት የማኅበረ ካህናቱ አቤቱታዎች (በማኅበሩ ዘንድ በጣት የሚቆጠሩ እየተባሉ ይናቃሉ) እንዲሁም ፓትርያርኩም እያመረሩ የመገኘታቸው ጉዳይ ብዙ እየተባለለት ነው። ( የፓትርያርኩ ለመታዘዝ ፈቃደኛ አለመሆንም ማኅበሩ እያናደደው ነው)  በዚህ ጽሁፍ ውስጥ ማኅበሩን ቦታ ካላስያዙት የፓትርያርኩ የስራ ሂደት አስቸጋሪ እንደሚሆን የዛሬ ዓመት ጠቁመን ነበር። አጠቃላይ የመዋቅር ለውጥና የአዲስ ሕግ አወጣጥ የፓትርያርኩ አዲስ የስራ ጅማሮ እንዲሆን አሳስበን የነበረ ቢሆንም ማኅበሩ ግን ፓትርያርኩን አስቀምጦ በአባ እስጢፋኖስ በኩል ራሱ ፓትርያርክ የሆነበትን ሂደት ለመታዘብ መገደዳችንንም እንድናስታውስ አድርጎናል። ለሁሉም ሊሆን ይገባል ብለን በግላችን ያሳየንበትን ሁኔታ መታዘብ እንዲቻል ለአንባብያን በድጋሚ አቅርበናል። መልካም ንባብ!!

በዚህም ተባለ፤ በዚያ አቡነ ማትያስ ፮ኛው ፓትርያርክ ሆነው ተሹመዋል። ባለፈው ግድፈትና እውነት ላይ  እያነሳንና እየጣልን ጊዜ አናጠፋም። ይልቅስ ብዙዎች የታገሉለት የምርጫው ስኬት እንዳሰቡት ጥሩ የሥራ ጊዜ ይዞ ይመጣላቸው  እንደሆነ የምናይበት፤  ገሚሶቻችንም የምናያቸው የቤተ ክህነት ተግዳሮቶች የሚቀረፉበት፤ ሰናይ የአስተዳደርና መንፈሳዊ ዘመን ናፍቆታችንን ተስፋ በማድረግ እንደዚህ በፊቱ አስቀድመን አንዳንድ ነገሮችን ለማመልከት ወደድን።
የአዲሱ ፓትርያርክ አዲስ የሥራ ዘመን ቀላል እንደማይሆን ይገመታል። የተጠራቀሙ የቤተ ክህነቱ ችግሮችና ብዙ እንከኖች  ከፊታቸው ይጠብቋቸዋል። የችግሮቹ ዓይነቶች፤ ደረጃና ጥልቀት የተለያዩ እንደመሆናቸው መጠን የተለያየ ውሳኔና እርምጃንም የሚጠይቁ ናቸው። ለዚህ የተዘጋጀ የአእምሮ ዝግጁነት፤ የእውቀት በሊህነት፤ ድፍረትና ማስተዋል እንደሚጠይቁም አይጠረጠርም።  ያንን ዓይነት ሰው ከየት እናገኛለን ብለን አናሳብም። ምክንያቱም ምርጫው /ከተባለ/ ትልቅ አባት ሰጥቶናልና። ስለዚህ ወደችግሮቹ እንንደርደር።

1/ የቤተ ክህነቱ ላዕላይና ታህታይ መዋቅር ማሻሻል

የቤተ ክህነቱ ቀዳሚው ችግር ሥራና ሠራተኛ የተገናኘበት ተቋም አለመሆኑ ነው። ሥራና ሠራተኛ ካልተገናኘ ደግሞ  በየትኛውም መልኩ የቤተ ክህነቱ የሥራ አፈጻጸም «ከርሞ ጥጃ» መሆኑ አይቀርም። ሥራና ሠራተኛ ማለት ለተገቢው ሥራ ተገቢ ባለሙያ ወይም ተቀራራቢ ችሎታ ያለው ሰው ማለት ነው። እንደዚህ ባለው ሰው ላይ የተቋሙን ዓላማና ግብ በደንብ ካስጨበጡት ከችግሮቹ ብዛት አንጻር ባንድ ጊዜ ፈጽሞ ባይወገድም፤ ከየትኛውም ጊዜ የተሻለ ለውጥ ሊመጣ ይችላል። በዘመድ አዝማድ የተለጣጠፉና የተደረቱ ክፍሎችን ይዞ መቀጠል ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ይሆናልና አሁን ያለን የሥራና ሠራተኛ አቋም የችግሩ ዋና ምንጭ ነው ባይባልም የችግሩ አካል ነውና ከጥገናዊ ለውጥ ወይም ከማስመሰል /pseudo/ የራቀ ለውጥ ያስፈልገዋል። ከአቅም በታች ለመሥራት የእድሜ ጣሪያ የገደባቸውም  በየመልኩ ቦታቸውን መያዝ  ካልቻሉ ቤተ ክህነት የዘመዳ ዘመዶች የጡረታ ተቋም ሆኖ ይቀጥላል እንጂ የሥራ ብቃት መለኪያ ስፍራ ሊሆን አይችልም። 

ሀገር አቀፍ ተቋም የሆነው ቤተ ክህነት ሀገር አቀፍ አደረጃጀት ሊኖረው የግድ ነው። ከላይ እስከታች አደረጃጀቱ መሻሻል አስፈላጊ ከሚባልበት ጊዜ ላይ ተደርሷል ብለን እናምናለን። በአንድ ወቅት በአሁኑ ሰዓት የአንበሳ አውቶቡስ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ በድሉ አሰፋ የቤተ ክህነቱን የአቅም ግንባታ ክፍል ሆነው ጥናት አቅርበው እንደነበር አስታውሳለሁ። ቤተ ክህነትና የዘመኑ ጥናት ሊግባቡ ባለመቻላቸው ቤተ ክህነትም በአሮጌ ልምዷ ስትቀጥል፤ አቶ በድሉም አሮጌው ጎዳና አላሰራ ስላላቸው ትተውት የተሻለ ቦታ ሄደዋል። ስለዚህ ቤተ ክህነትን ከአሮጌ መዋቅር ወደዘመነ ሥርዓት ለማስገባት አዲሱ ፓትርያርክ ትልቁ ሥራቸው መሆን አለበት  እንላለን። የተደረተውን በመጠገን  ላይ ካተኮሩ ግን ልባቸው ወልቆ እርጅናቸውን ከማፋጠን በስተቀር ለእርሳቸውም ይሁን ለቤተ ክህነቱ ቀጣይ አስተዳደር አንዳችም  ነገር ጠብ ሳይል ይቀጥላል ማለት ነው። ይህን ማስተካከል የአዲሱ ፓትርያርክ ፈታኝ ሥራ ነው ብለን እናስባለን።


2/  እርምጃ አወሳሰድ፤ የሥራ ብቃት መለኪያና አፈጻጸሙን የመቆጣጠሪያ ስልት፤

 ቤተክህነትን በብቃት የሚመራ ሕግ፤ መመሪያና ደንብ የለውም። ያለውንም በሥራ የሚያውል አካል አልነበረም። ነገሮች ሁሉ በልምድና በስምምነት የሚሰራበት ሆኖ ቆይቷል። ሥልጣንና ተግባር ለክቶ የሚሰጥ መመሪያ ባለመኖሩ ሥራና ኃላፊነት ተደበላልቀው በባለሥልጣን ይጣሳል፤ ወይም በመሞማዳሞድ ይሸፈናል።  መመሪያው ሕግ ሳይሆን ሹመኛው ራሱ ሕግ ሆኖ ያገለግላል። የአድርግና አታድርግ፤ የጌታና የሎሌ አስተዳደር እንጂ የ21ኛው ክ/ዘመን የተጠያቂነት አሠራር በቤተ ክህነት  የለም። ባለሥልጣናቱ ከፈለጉ ከአፈር ይቀላቅሉሃል፤ ከወደዱም ጣሪያ ላይ ይሰቅሉሃል። ሰው  የሚያድገውም  ይሁን  ድባቅ የሚመታው ተጠያቂነት በሌለው ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ቆይቷል።  ለሠራው ሥራ ብቃትና ጉድለት መለኪያ  ሚዛን የለም። ሌላው ይቅርና የፓትርያርክ የምርጫ ሕግ እንኳን ከእንከን የጸዳ ባለመሆኑ በነቶሎ ቶሎ ቤት ጥበብ  ተለክቶ የተሰፋው በቅርቡ መሆኑን ልብ ይሏል።  እንግዳነቱ ብዙ ጭቅጭቅና ክርክር ማስነሳቱም  አንዱ የቅርብ ጊዜ ትዝታ መሆኑ አይዘነጋም።  ነገም ይህ ችግር ላለመደገሙ ዋስትና የለም። ስለዚህ ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ  ወጥነት ያለው ሕግ፤ መመሪያና ደንብ ሊኖር ይገባል።  ይህንን ችግር አጥንቶ የተሻለ መፍትሄ በማምጣት ላይ አዲሱ ፓትርያርክ ትልቅ ሥራ ይጠብቃቸዋል።

3/ መንፈሳዊ ሲመት/ሹመት/ በተገቢው መለኪያ ማከናወን

ከጵጵስናው ጀምሮ እስከ እልቅና ድረስ ያለው የሲመት አሰጣጥ ሲባል እንደቆየውና እንደምናውቀው ወይ ገንዘብ ያለው፤ ወይ ዘመድ ያለው እንጂ በችሎታና በብቃት ልኬት የሚገኝ አልነበረም።  ጉልበት ስር መንበርከክን ዝቅ ሲልም ትቢያ መላስን እንደመስፈርት ሲሰራበት ቆይቷል። መከባበር ተገቢ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ያይደለ ሥጋዊ ክብርን ከመፈለግና ለሹመት ሲባል ወደአምልኮ የተቀየረ ስግደት የመስጠት ትእቢታዊ  ግብር ማላቀቅ ተገቢ ነው። ጵጵስናውንም እንደሲሞን መሰርይ ሽጡልኝ ወደሚባልበት ደረጃ ማውረድ ወይም በአማላጅና በሽማግሌ የሚረከቡት ንብረት መሆኑ መቆም አለበት።   መሪው በተመሪው የተመሠከረለት ቢሆን እንዴት ባማረ ነበር? ጳውሎስም የመከረን ይህንኑ እንድናደርግ ነበር።  ብዙ ጊዜ እንደሚታየው መሪውን ገንዘብ ይመርጥና ወደተመሪው ሕዝብ ይላካል። እዚያም እንደደረሰ መሪው ለሚመራው ሕዝብ ሳይሆን አገልጋይነቱ ለመደቡት ክፍሎች ይሆናል። ሕዝቡም በሚወርድበት የዐመጻ ሥራ የተነሳ እምነቱን እንዲጠላ፤ እንዲያፍርና እንዲሸማቀቅ ብሎም እንዲኮበልል ይገደዳል። ሕገ ወጥነት የሰለጠነበት የቤተ ክህነት ሥልጣን እንደገና መበጠር ይገባዋል።  ሕዝቡ መጣብን ሳይሆን መጣልን የሚል መንፈሳዊ መሪ ይፈልጋል። በመጡበት ተላላኪዎች እስከዛሬ መሮታል። እናም አዲሱ ፓትርያርክ ይህንን ሁሉ ችግር ተረክበው የጣፈጠ ሥራን ሊያሳዩት ይጠበቃል።  ያለፈውን ችግር ተሸክመው በምን ቸገረኝነት ይቀጥላሉ ወይስ ይህንን የሚሸከም ጀርባ የለኝም ይሉ ይሆን? እሳቸውንና ደጋፊዎቻቸውን የምንጠይቃቸው  መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ትልቁ ፈታኝ ሥራቸው እንደሆነ ግን በበኩላችን አስምረንበት እናልፋለን።


4/  የመንፈሳዊ ሀብት ጥበቃና ልማት አንጻር፤

ቤተክህነት ጥንታዊ የመንፈሳዊ ሀብት ባለቤት ብትሆንም አሁን ያለችበት ደረጃ ግን በተገቢ ሥፍራዋ ላይ አይደለም።  ግእዝ ቋንቋ የሀገሪቱ ሀብት መሆኑ ቀርቶ ዛሬ በዱርና በበረሃ ተደብቆ የሚገኝ በመጥፋት ላይ ቅርስ ሆኗል። ይህንን ቋንቋ በሕይወት ለማቆየት የአብነት መምህራን ግሱን እያስገሰሱ፤ ቅኔውን እያስዘረፉ በጥቂቶች እጅ ብቻ የሚገኝ ቋንቋ ሀብት ከማድረግ ባሻገር የብዙዎች ለማድረግ ቤተ ክህነት አቅሟ ተሰልቧል።  ሐምቡርግ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ኢንስቲቲዩት ግእዝን ሲያስተምር የቋንቋው ባለቤት ግን ለዚህ ነገር እንግዳ ናት።  መምህራኖቹ ከውሻ ጋር እየታገሉ ከተማሩት ውጪ ቤተ ክርስቲያኒቱ በወጥ የትምህርት ሥርዓት ለማስተማር ጊዜ አላገኘችም። ወይም ጊዜውን ለመጠቀም አልፈለገችም።  ትውልዱ እንግሊዝኛ፤ ዐረቢኛና ፈረንሳይኛ ሲማር የራሱ የሆነውን ግእዝን እየፈለገ አላገኘውም። ከመንፈሳዊ ቀጣይ ልማት ውስጥ የግእዝ ቋንቋን እንደሙሉ ቋንቋ ለትውልድ ማስተላለፍ ይጠበቅባታል። ከጥቂት የአብነት መምህራን እጅ ወደ ሁሉን አቀፍ ቋንቋ እንዲቀየር በኮሌጅ ደረጃ ማስተማር ይጠበቅባታል።  ሌሎቹንም የአብነት ትምህርቶች ደረጃና ብቃት በማሻሻል ቀጣይነቱን ማረጋገጥ የቤተክህነቱ ድርሻ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የቴኦሎጂ ኮሌጆችም ካለው የቤተ ክርስቲያኒቱ የሰው ኃይል ብዛት ጋር ፈጽሞ እንደማይመጣጠን  ይታወቃል። ሁለት ጡት ሆኖ መቅረቱ ያሳዝናል።/እንደምን?/ ሌላው ቢቀር የላምን ጡት ቁጥር ሞልቶ የምሁራን ወተት የሚታለበው መቼ ይሆን?  እያንዳንዱ ሀገረ ስብከት የኮሌጅ ባለቤት መሆን በሚገባው ሰዓት፤ አንድም የሴሚናሪ/ ት/ቤት የሌለው መሆኑ ያስከፋል።  ጳውሎስ መንፈሳዊ ት/ቤት እንኳን ባለበት መርገጥ ከጀምረ ሦስት መንግሥታት አለፉት። ለዚያውም እስከነ ግዙፍ ችግሩ። እያንዳንዱ ሀገረ ስብከት የካህናቱን ብቃትና ችሎታ ማሳደግ  በሚገባው ወቅት በዲያቆን ቅጥርና ማባረር ጊዜውን ማጥፋቱ አሳዛኝ ነገር ነው። የአጫጭር፤ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የትምህርትና የስልጠና መስኮች መከፈት ይኖርባቸው ነበር። የእድሜአችንና የስፍራችንን  መራራቅ ቢያንስ ማቀራረብ ተገቢ ነው።

 በመንፈሳዊ ሃብት ጥበቃና ልማት አንጻር ሌላው የሚነሳው ነገር ማን እንደጻፋቸው የማይታወቁ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ የሚጻረሩ፤ ተረት፤ ቧልት፤ ቀልድና ክህደት የሚያስፋፉ መጻሕፍትና ትምህርቶች ሁሉ በሊቃውንቱ እንዲታረሙና እንዲመረመሩ መደረግ ይገባዋል።  በተሀድሶ መጣና በመናፍቃን በላህ ዘመቻ እንከኖቻችንን ተሽከመን መዝለቅ ችግሩን ከሚያባብስ በስተቀር መፍትሄ አይሆንም። ገሚሱም ከእውቀት ማነስ የተነሳ ሲመቸው ከሚነቅፍ፤ ገሚሱም ባልዋለበት ቦታ ሊቅ ሆኖ ጠበቃና ተከራካሪ ከሚመስል ምሁራኑ የተሳሳተውን አርመው፤ የጎደለውን መልተው ሊያስተካክሉ ይገባል።  ቤተ ክህነት የማታውቀውን ጠልሰም ሁሉ በይፋ ማውገዝ ይገባታል። ዝምታ በራሱ ወዶ እንደመቀበል ይቆጠራልና።  የተሻለ የህትመትና የሚዲያ ዘመን ላይ ብንገኝም ማንም ተነስቶ እኔ ጠበቃ ነኝ በሚል ዲስኩር ኑፋቄን ሲያሰራጭ፤ ሲያሳትም፤ ሲዘፍን/ ሲዘምር?/ ቤተ ክርስቲያኒቱ ዝምታዋ አስገራሚ ሆኗል። የቤተ ክርስቲያኒቱን ስርዓትና ደንብ  የተከተለ በሚል ሽፋን መድረኳን  የርግብ ለዋጮች ገበያ ሲያስመስለው ዝምታው ያስገርማል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ሊቃውንት ጉባዔውን ሊቃውንት ስላልመሩት ወይም ሊቃውንት መሰኘት በምንም ልኬታ እንደሆነ ትርጉሙ ጠፍቷል ማለት ነው። እነዚህን  ሁሉ ችግሮች የመለየት፤ የማስወገድና የማረም መንፈሳዊ ልማት ከአዲሱ ፓትርያርክ የሚጠበቅ ሥራ ነው።
እንደዚሁም ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያላትን ቅርስና ሀብት በአግባቡ መዝግባ፤ በዘመነ የመረጃዋ ቋት አስገብታ መያዝ ይገባታል። የፈረሰውን በመጠገን፤ ያረጀውን በማደስ ልትሰራው የሚገባት አንገብጋቢ ጉዳይ ሞልቷታል። በጉብኝትና ጎብኚ /Tour & Tourism operation / ረገድ የሰራችው ምንም ነገር የለም። በሀብቷ የሚበለጽጉት ሌሎች ናቸው። «ከሞኝ በራፍ፤ ይቆረጣል እርፍ» እንዲሉ አስጎብኚዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ ስንፍና፤ ጉብዝናቸውን በቤቷ ውስጥ እያሳዩ ያሉት ያተርፉባታል ። ስለሆነም በመንፈሳዊ ሀብት ልማትና ጥበቃ አዲሱ ፓትርያርክ ብዙ ይጠበቅባቸዋል።

5/ ማኅበራዊ ልማትና እንቅስቃሴ

ከኋላዋ የመጡ አብያተ እምነቶች በተሻለ ደረጃ በሕብረተሰብና በመንግሥታዊ የልማት ተሳትፎ ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው። እያንዳንዷን የምጽዋት ገንዘብ በልማትና ልማቱን ተከትሎ በሚደረገው ስብከት ላይ ያውላሉ። የቤተ ክህነት ሙዳየ ምጽዋት ግን ሌላ የልማት ገቢ ስለሌለ የካህናት ደመወዝ ከመሆን ወጥቶ የሕብረተሰብ ልማት ላይ መዋል አልቻለም። ለኃጢአት ማስተስረያ የሚሰጥ ገንዘብ ተመልሶ ሕይወት ወዳለው ልማት የመዋል እድል አላገኘም። አድባራትና ገዳማት በልማት ሥራ ላይ ጉልበታቸውን እንዲያውሉ ማስቻልና  ይህንንም በገንዘብና በሙያ ቤተ ክህነት ማገዝ ሲገባት የልመና ደብዳቤ በመስጠት ወደጎዳና ትልካቸዋለች። በየአድባራቱ የልማት ክፍል እንዲስፋፋ የገንዘብ ዘረፋንና ብክነትን መቆጣጠር መቻል በራሱ ልማት ነበር። ይሁን እንጂ ያንን ገንዘብ ወደተሻለ  ልማት ማዋል በሚል ሰበብ  ገንዘብ የሚዘረፍበት ዘዴ ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ማስቆም ካልተቻለ አዲሱ ፓትርያርክ ስኬታማ እንዳይሆኑ ያደርጋቸዋል። መራጮቻቸውንም በመምረጣቸው መመካት የማይችሉ ድኩማን ሆነው ያፍራሉ። ስለዚህም ሁሉም ወገን የሚጠብቀው ልማት በሰው ኃይል ብቻ ሳይሆን በገንዘብ አጠቃቀም፤ በማኅበራዊ እንቅስቃሴ፤ በሕብረተሰብ አቀፍ ልማት ውስጥ ተሳትፎ ማድረግን ያጠቃልላል። እነአቡነ ቴዎፍሎስ ያስገነቡትን ህንጻዎች እያከራዩ የጳጳሳት ደመወዝ በየሁለት ዓመቱ መጨመር ሳይሆን በየሁለት ዓመቱ ደመወዝ የሚያስጨምር ልማት ሰርቶ ማስረከብ ይጠበቃል። የተሻለ ደመወዝና ሥራ ፍለጋ የሚጎርፈው ቄስና አባ የትየለሌ ነው። ቤተ ክህነት ሁሉንም ማርካት የሚችል ቅጥር በመፈጸም ጊዜዋን ማጥፋት የለባትም። ሥራ በመፍጠር የተጨማሪ ባለሙያ ባለቤት ማድረግም ትችላለች። አድባራት /በተለይም/ አዲስ አበባ የቅጥር ሁኔታ ሞልቶ ወደመፍሰስ/ saturated/ ወደ መሆን ደረጃ ደርሷል። ካህን ሁሉ የግድ መቀደስ ወይም ማኅሌት ብቻ ካልቆመ መኖር አይችልም የሚል ህግ የለም። ስለዚህ በልዩ ልዩ ሙያ ማሰልጠን፤ ትርፋማ ልማትን መፍጠር ይጠበቅባታል። በመቅጠርና በማዘዋወር ዘመኗን መፈጸም የለባትም።

በሌላ መልኩም ቤተ ክህነት  እመራዋለሁ በምትለው ሕዝብ ውስጥ በጤና፤ በአካባቢ ጥበቃ፤ በንጹህ የመጠጥ ውሃ፤ ወዘተ ልማት ውስጥ መኖሯን ማሳየት አለባት።  የአባልነት መዋጮ እያለች  ከተከታዮቿ ላይ በፐርሰንት መልቀም ብቻ ሳይሆን  የተለቀመውን ገንዘብ መልሳ በልማት ውስጥ ለተከታዮቿ ማፍሰስ ይገባታል።  የቤተ ክህነቱ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን በስሩ እስካሉት መምሪያዎች ጭምር ባለፉት ዓመታት ያልተወራረደ የእርዳታ ገንዘብ ተሸክሞ መቆየቱ ይነገራል። ቀጣዩ የልማት ኮሚሽኑ የቡድን ተሿሚው አባት ይህንን ያብሱት ይሆን ወይስ ያርሙት?  ጊዜው ሲደርስ የምናየው ሆኖ ለአሁኑ ግን አዲሱ ፓትርያርክ ቀጣይ ብዙ ሥራ እንደሚጠብቃቸው እንጠቁማለን።

5/  ማኅበራት፤ ቡድኖችና ግለሰቦች እንደ ቅልጥም ሰባሪ አሞራ ማኮብኮባቸውን ማስቆም፤

ቤተ ክህነት ከቅዱስ ሲኖዶስ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ አንድ ወጥ መዋቅር አላት።  በዚህ መዋቅር ውስጥ ሥፍራ የሌለው ነገር ግን የሚጠጋበትን ጥግ እየቀደዱ ወይም እየቦረቦሩ ባዘጋጁለት ቦታ ሆኖ በእንቅስቃሴው፤ ቤተ ክርስቲያኗን አክሎ፤ እሷን መስሎ የራሱን  የሀገረ ስብከት ተቋም በሀገር ውስጥና በውጪው ያደራጀው ራሱን «ማኅበረ ቅዱሳን» እያለ የሚጠራውን ክፍል አዲሱ ፓትርያርክ ተገቢውን ቦታ ሊሰጡት ይገባል። በሲኖዶሱ፤ በሀገረ ስብከቱ፤ በአድባራትና ገዳማቱ ሁሉ ያልታጠበ እጁን እያስገባ መቀጠል የለበትም። ሰንበት ተማሪ ነኝ የሚል ከሆነም የሰንበት ተማሪዎችን ሕግና ደንብ አጥብቆ የሚይዝበት ምክር ሊሰጠው ተገቢ ነው። ራሴን የቻልኩ ማኅበር ነኝ ካለም ራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ  ይኑር እንጂ ከቤተ ክህነት ጀርባ ላይ እንደትኋን ተጣብቆ ሲመቸው አዛዥና ናዛዥ፤ ሳይመቸው ደግሞ ትሁት መስሎ ነጣላውን እያጣፋ ከበሮ መደብደቡን ያቁም።  ከእሱ ጋር ሲነፍስ የሚነፍሱ ጳጳሳትም ያሉበትን ተቋምና ደረጃ እንጂ የቡድን ዋሻ አድርገው መጠቀማቸውን ማቆም አለባቸው። ይህ ሃሳብ የብዙዎች ሃሳብ ስለሆነ እንደቀላል ነገር መታየት የለበትም። ከሁሉም በላይ የአዲሱ ፓትርያርክ የሥራ እንቅፋት አንዱ ይኸው በቅዱሳን ስም የተሰባሰበው ማኅበር ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቤተ ክህነቱን የወረሩ የቀን ጅቦችና ወሮ በሎች የቤተ ክህነቱን ዓርማና መለያ ለብሰው በጨዋ ደንብ ተቀምጠዋል። እነዚህም ቤተ ክህነቱን እንደቅንቅን የበሉ ምንደኞች ቦታ ቦታቸውን መያዝ ይገባቸዋል። ትዳር አልሆን ያላቸው፤ እድሜአቸውን ለንስሐ ያልተጠቀሙ አሞራዎችም ሲኖዶስን እስከመበጥበጥ ልምድና ችሎታ ያላቸው ስለሆኑ ከአዲሱ ፓትርያርክ ጋር ክንፋቸውን እያማቱ ሰላማዊ ርግብ ለመመስል መሞከራቸው አይቀርምና ለእንደዚህ ዓይነቶቹም ቤተ ክህነት ሥፍራ እንደሌላት ማሳየት የአዲሱ ፓትርያርክ ሌላው ፈታኝ ሥራ ነው። እንዳለፈው  ሁሉ አዲሱም ተመሳሳይ ድርጊትን ካራመዱ  ራስን ወደእሳት ውስጥ ማስገባት ይሆንባቸዋል። እኛም ብለን ነበር፤ የሚሰማን ጠፋ እንጂ ማለታችንን አንተውም።  ችግሮች ተባባሱ ከማለት ይልቅ መፍትሄ አገኙ የሚል የምስራች የምናወራ እንድንሆን እንሻለን።  አሁንም የሦስት ረድፍ ቡድኖች ይታዩናል። ራሳቸውን አሸዋ ውስጥ ከተው የተደበቁ ቢመስሉም ዓመላቸው ስለማያስችላቸው ብቅ ብለው በቅርቡ ቦታ ቦታቸውን ሲይዙ እናገኛቸዋለን።   የሆኖ ሆኖ  ቤተ ክርስቲያኗን ብቻ ማዕከል አድርገው የመሥራት ድርሻው በአዲሱ ፓትርያርክ ጫንቃ ላይ ወድቋል።

6/ ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋር ኅብረትና ስምምነት ማድረግ

ይህንን ሁሉ ሥራ ለመሥራት የሲኖዶሱ ኅብረትና ስምምነት አስፈላጊ ስለመሆኑ ምንም ጥርጣሬ የለንም። አንዱን በማቅረብና ሌላውን በማራቅ የሚሰራ ሥራ ውጤታማ አይሆንም። በሁሉ ነገር ነገር ሙሉ ስምምነት መኖር ባይችል እንኳን ሰፊ ውይይትና አብላጫ ድምጽ መኖሩ በራሱ እንደሙሉ ስምምነት ያስቆጥራልና ይህንን ማዳበር ካለፉት የሲኖዶስ ጉባዔዎች እንደተሻለ ተሞክሮ መጠቀም ተገቢ ነው እንላለን። መከፋፈል፤ መምታት፤ መነጠል፤ ማሳደም፤ መግፋት የመሳሰሉት ከዚህ በፊት ተሞክረው የትም አላደረሱምና ከዚህ ዓይነቱ ጥቃቅን የሚመስል ግን አደገኛ አካሄድ መጠበቅ ይበጃልም ጥቆማችን ነው። ሥልጣንን ሰብስቦ ሳይሆን በየደረጃው ከፋፍሎ  ነገር ግን አስረክቦ ያይደለ ጠብቆ የመሥራት ጥበብ ጠቃሚ ነው።  ወደታች ወርዶ ቄስ እስከመቅጠርና እስከማዛወር መሄድ ግን የፓትርያርክ አንባ ገነንነት መገለጫ ነው። አሞራዎች  ማንዣበባቸው የፍቅራቸው ጥግ ሰማይ ስለደረሰ ሳይሆን የሹመት ጥንብ የት እንዳለ ለማየት ሲሉ እንደሆነ ወደ ላይ መሰቀላቸውን ማጤን ይገባል።  ጣል ጣል ይደረግልን ማለታቸው እንደማይቀር ከዓመላቸው ተነስተን ብንገምት ግምታችን ከእውነታው የራቀ አይደለም። ይህንን ይፈልጋሉና አዲሱ ፓትርያርክ በቅጥር ላይ ተጠምደው እጃቸውን ማድከም የለባቸውም።  መንፈሳዊ የተባለው ሥልጣን ወዳጅ መጥቀሚያ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኗን ችግር መፍቻ ማድረጉ ይበጃል። የቀድሞውን በነቀፉበት አፍ ራስን እዚያው ውስጥ ማስገባት በሰውም ያስተዛዝባል፤ ፈጣሪንም ያስቀይማል።  ቢሞቱ ምን የመሰለ አባት ሞተብን እንጂ እንኳንም ተቀሰፈልን ከሚል ክፉ ስም ለመጠበቅ ቢያንስ ራስንና የተናገሩትን ቃል መጠበቅ መልካም ነው።  ጠቢቡ በመጽሐፉ «ከመልካም ሽቱ መልካም ስም፥ ከመወለድ ቀንም የሞት ቀን ይሻላል» እንዳለው።  በተቻለ መጠን ከመልካም ሽቱ ለተሻለው መልካም ስም መሥራት ብልኅነት ነው።  ስለዚህ ከሲኖዶስ አባላት ጋር ተስማምቶ መሥራት ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት ጠቃሚ መሆኑን እየገለጽን ሲኖዶሱን ለመጠምዘዝ ወይም ለማሽከርከር የሚፈልጉ ሰንጎ ያዢዎችንም  እያስታገሱ  መጓዝ ተገቢ መሆኑንም ሳንዘነጋ ነው።

7/ አቤቱታዎችን፤ እሮሮዎችንና  ጩኸቶችን መስማት መቻል፤

ቤተ ክህነት የእሮሮና የአቤቱታ ፋብሪካ መሆኗ ይታወቃል። በአንድ ወቅት ምሬት ያንገሸገሸው የልጆች አባት፤ አንዱን ጳጳስ በሽጉጥ እስከማስፈራራትና አንዱን ሹም  እስከ መግደል ያደረሰው ጉዳይ ምሬትና እሮሮን የሚሰማ ሰው በመጥፋቱ የተነሳ ነው። ይህ እሮሮና የምሬት ጩኸት እስከዛሬም ከቤተ ክህነቱ ግቢ አላባራም። የቤተ ክህነቱ ቢሮ ይዘጋል። ባለሥልጣኑ ጩኸት አልሰማ  ይላል። በዘመድ ወይም በገንዘብ ድምጹ የሚታፈን ወገን ብዙ ነው።  ልቅሶ እና ወይኔን ይዞ እንዲመለስ ይደረጋል። የፓትርያርክ ቢሮ ለመድረስማ እንዴት ይታሰባል? መንግሥተ ሰማይ በእምነትና በጥቂት ሥራ መግባት ሲቻል ለመንበረ ፓትርያርክ በር ግን እምነትና ምግባር ዋጋ የላቸውም። በእነሱ ፋንታ ገንዘብና ዘመድ በሩን ሁሉ ከፍተው ደንበኛቸውን ይጋብዛሉ። ይህ አባባል የሚያቅለሸልሽ ቢሆንም የተገለጠ እውነት ነው። አዲሱ ፓትርያርክ ከዚህ ጋር ብዙ ትግል ይጠብቃቸዋል። የእሳቸው ቢሮም  ወፍ እንዳያሾልክ ተደርጎ ካልተጠረቀመ በስተቀር ቤተ ክህነት በአቤቱታና በመብት ጥሰት እሮሮ ከመሞላቱ የተነሳ  ባለጉዳይን እንዴት እንደሚያስተናግዱ ስናስበው ግራ ይገባናል።  ከላይ እስከታች ድረስ የአቤቱታ አቀራረብና የመፍትሄ አሰጣጥ መንገድ ካልተዘረጋ በስተቀር አዲሱ ፓትርያርክም ያለፈውን ደግመው በአዳራሻቸው ጥቂት ወፋፍራሞችንና ጉንጫቸው ሊፈነዳ የደረሰውን ብቻ የሚያስተናግዱ የዘመነኞች ፓትርያርክ ሆነው እንዳይቀሩ እንሰጋለን።
ፍርድ የመስጠት ሥልጣኑ የነበራት ቤተ ክህነት በፍርደ ገምድል ሰዎች በመሞላቷ ከደረጃው የወረደ፤ ከሥራ የተባረረ፤ እድገት የተከለከለ፤ ደመወዙን የተቀማ፤ በሀሰት ምስክሮች ወህኒ የማቀቀ ብዙዎች እንዳሉ እናውቃለን። ከዘበኛው ጀምሮ በየደረጃው ባለጉዳይን እንደ ልጅነት ልምሻ በሽታ የሚያማቅቅ ሞልቷል።   ለዓመታት የተከማቸውን ችግር ባንድ ሌሊት ማስወገድ እንደማይቻል ቢታወቅም ችግሩ የት እንዳለ አውቆ ለማስተካከል መነሳቱ በራሱ የፍጻሜው መጀመሪያ ነውና በዚህ ዙሪያ ብዙ እንጠብቃለን። በየፍርድ ቤቱ የቤተ ክህነት የክስ ፋይል እና በየከርቸሌው የቤተ ክህነት ተያያዥ ሰዎች ውሳኔ ዓለማውያኑን ሳይቀር በሚያሳፍር ደረጃ ላይ መገኘቱም የአደባባይ ሐቅ ነው። ይህንን ሁሉ የቆየ እንቅፋት ለማስወገድ አዲሱ ፓትርያርክ ረጅም መንገድ ይጠብቃቸዋል።

የከተማ አወደልዳዩን እና በባህል መድኃኒት ሰበብ በየሰፈሩ ያለውንና  በቤተክህነቱ ዓርማ  የሚዘርፈውን አጭልግ ሁሉ አንድ ፈር ማስያዝ የወቅቱ ተግዳሮት ነው። እንደዚሁም ሁሉ የሴቶች መብት የተከበረ እንደመሆኑ መጠን በተገቢ ሙያቸው ማሰራት አግባብ መሆኑ ባይካድም ባለሙያ ካህናት ሊሰሩ የሚችሉትን ሥራ ሁሉ ምክንያቱ በታወቀና ባልታወቀ መንገድ ቤተ ክህነቱን የሴቶች ማኅበር አድርጎ መሰግሰጉም አንዱ ችግርና ሰሚ ያጣ እሮሮ ነው።  ያዝ ለቀቅና የአንድ ሰሞን ግርግር አድርጎ መተዉ የቤተ ክህነቱን ስምና ክብር ሊጠግን አይችልም። ይህ ሁሉ ውዝፍ ሥራ አዲሱን ፓትርያርክ  የሚጠብቅ ነው። ቀድሶ ማቁረብና ቡራኬ መስጠት አባታዊ ተግባር መሆኑ ባይዘነጋም በየአድባራቱ በዓላትን ጠብቆ በመሄድ ፈጣን ምላሽ የሚያሻቸውን ፋይል ጠረጴዛ ላይ እንዲወዘፍ ያደርጋልና «በሉ ተነሱ»  በሚል ቀጭን ትእዛዝ መሄድ ጠቃሚ አይደለም።  በታቀደና በተያዘ መርሐ ግብር ብቻ መመራትም እሮሮዎች እንዳይበዙ ያግዛልና ይኼም ሊታሰብበት የሚገባ ይመስለናል። 

ይህ ሁሉ የርእሰ መንበሩ ሰርቶ የማሰራት ኃላፊነት ነው። በባሌ ይሁን በቦሌ ስልጣንን በእጅ ማድረጉ ብቻ ለቤተ ክርስቲያን ምንም አይጠቅማትም። ካለፈው ተምሮ፤ ያለበትን የአሁኑን ተንትኖ የወደፊቱን የሚያይ ባለርእይ መሪ እንጂ ቤተ ክህነት የሹመኛ ችግር የለባትም። ስንወቃቀስ ሳይሆን ስንነጋገር ብቻ ነው ለችግራችን መፍትሄ ማምጣት የሚቻለው። አለበለዚያ በመጫጫህ አንድም ነገር ሳንሰራ ዘመናችን ያልፋል። እንግዲህ ቢሰራ የምንመኘው፤ ካለፉት ሂደቶች ወደዚህ የተሻገሩ ናቸው የምንላቸውን ችግሮች በጥቂቱ አንስተናል። አጠቃላይ ጥናት ቢደረግ ደግሞ የገዘፈ ነገር እንደሚኖር ይገመታል። ይህ የግል ምልከታ ነው። ከዚህ የግል ምልከታ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይሁን በከፊል ደስ የማይላቸው ወገኖች ይኖራሉ። ደስ የማይላቸው ከራሳቸው ጥቅም አንጻር ሊሆን ይችላል ወይም ከማንም የተሻለ ጠቃሚ ርእይ አዘጋጅተው ይሆናል። እኛ ግን እያየን ስንለው የቆየነውን ፤ ያዩትም ሲሉት የኖሩትን፤  ብዙዎችም ሲሉት የደከሙበትን አጠራቅመን  በትንሹ  ማለት ያለብንን እነሆ ብለናል። ወደፊት ችግሮቹ እዚያው ሆነው ስናገኛቸው ደግሞ ዳግመኛ ብለን ነበር እንላለን።ችግሩ  ሲቀረፍ ደግሞ እሰየው ማለታችን የግድ ነው።  ችግሮቹ ካልተቀረፉም  የሁሉም ሃሳብ ወደመሆን መሻገሩ አይቀርም።  ያኔ ደግሞ አዲስ ፊት አይተን ምን አተረፍን፤ ምንስ አጎደልን? ማለታችን አይቀርም። « ለዚሁ ነው በሬዬን ያረድኩት» ማለትም ይመጣል። ከዚያ በፊት ያለንበትን እና የምንሄድበትን ማየት እስካልተቻለ ድረስ «ጉልቻ ቢለዋወጥ….» ከመሆን አይርቅም።

በስተመጨረሻም  ብዙ ሥራ ከፊታቸው ለተደቀነው ለአዲሱ ፓትርያርክ  ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ መጪው ዘመን የሰላም፤ የፍቅር፤ የአንድነት፤ የእድገትና የመንፈሳዊ ብልጽግና ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

Friday, March 21, 2014

የአቶ ግርማ ወንድሙ የማጭበርበር ጥምቀት የተፈቀደ አይደለም!



  

ግርማ ወንድሙ አጠምቃለሁ፤ ሰይጣንም አስወጣለሁ እያለ ማጭበርበርና ገንዘብ መዝረፍ ከጀመረ ሰነባብቷል። ማታለል በሀገሪቱ ህግ ወንጀል ቢሆንም ይህንን አታላይ የሚዳኝ ህግ እስካሁን አልተገኘም።  ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ ሊቃነ ጳጳሳቱም ከእነዚህ ዓይነቶች አጭበርባሪዎች ጋር ግንባር ፈጥረው ቤተ ክርስቲያኒቱ እመራበታለሁ ከምትለው የሥልጣነ ክህነት የአሰጣጥ ሂደት በተቃራኒው ግርማ ወንድሙ ለተባለው ነፍሰ በላ ወታደር  የቅስና ማዕርግ ሰጥተውት «ይፍታህ» እያለ ኃጢአት ሲደመሰስ እንደሚውል መዝጊያ የሚያክል መስቀል ጨብጦ እያየን ነው። ከስጋ ለባሽ መካከል ኃጢአትን የሚያስተሰርይ ቢገኝ ኖሮ የክርስቶስ ሰው መሆን ባላስፈለገም ነበር። 
  ዳሩ ግን እንኳን የሌሎችን ኃጢአት ሊያስተሰርይ ይቅርና ከማጭበርበር ዓለም ወጥቶ ራሱን መግዛት ያልቻለው ግርማ ወንድሙ መውጊያ በሚያክል የብረት መስቀል «ይፍታሽ፣ ይፍታህ» እያለ እንዲደበድብ ጳጳሳቱ ቅስና ሰጥተውታል። ጳጳሳቱ ገንዘብና የሚቀበላቸው ካገኙ እንኳን ቅስና ጵጵስናም ከመስጠት አይመለሱም። የትም ሳይማሩ የክብር ዶክተሬት ዲግሪ እንደሚሰጠው ሁሉ «ፈቀደ እግዚእ» ብለው የሰኞ ውዳሴ ማርያምን መዝለቅ ለማይችሉ ሁሉ የክብር የቅስና ማዕርግ ሲሰጥ እያየን ነው።  እስካሁን በአደባባይ የክብር የቅስና ማዕርግ እንደምትሰጥ ከቤተ ክርስቲያኒቱ በኦፊሴል ባንሰማም በተግባር ግን የማይሰራበት የክብር የቅስና ማዕርግ ይዘው ያሉ እንዳሉ እናውቃለን። ማኅበረ ቅዱሳን ደግሞ በዚህ መልኩ ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። የሚያገለግሉበት ወይም ያገለገሉበት ደብርና ገዳም ሳይኖር ወይም ለማገልገል የሚያበቃ ሙያ ወይም ትምህርት ሳይኖራቸው ቅስናና ዲቁና አለን ብለው በእጃቸው ትላልቅ መስቀል ጨብጠው መንገድ የሚያጣብቡ ሁሉ ለወደፊቱ መለየት አለባቸው።
 ይህንን የዲቁና፤ የቅስናና ሌሎች ማዕርጋት ልክ የንግድ ፈቃድ እድሳት እንደሚደረገው የእድሳት ዘመን ተደርጎለት ማዕረጉን ከየት እንዳገኘው? የት እንደሚያገለግልበትና ምን እንደተማረ? እየተመረመረ ተገቢ ሆኖ ያልተገኘው ሁሉ እንዳጭበረበረ ተቆጥሮ ወዳቂ ካልተደረገ በየሜዳው «ቀሲስ» የሚባሉ ጩልሌዎችን አደብ ማስገዛት አይቻልም። ከእነዚህም የክብር የቅስና ማዕርግ ተሸካሚ አንዱ አቶ ግርማ ወንድሙ ነው። ሌሎቹም ቢሆኑ ሙያውና እውቀቱ እያላቸው ነገር ግን ሥነ ምግባርና ለተመደቡበት ማዕርግ የሚያበቃ ማንነት የሌላቸው ዲያቆናት፤ ቀሳውስትና መነኮሳት ከዚሁ ጋር ተያይዞ ካልታየ በስተቀር የዝቅጠትና የውርደት መለያ ሆኖ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ውድቀት አስተዋጽኦ ማድረጉ አይካድም። ምዕመናንና ምዕመናት በእንደዚህ ዓይነቶቹ ተቆጣጣሪ አልባ ባለማዕርጋት ስርዓተ አልበኝነት የተነሳ በሀፍረት ተሸማቀው  እንደሚገኙም ይታወቃል።

   ከእነዚህኞቹ አንዱ የሆነው አቶ ግርማ ወንድሙ በስመ ማጥመቅ የሚሊዮን ብሮች ባለቤት መሆኑ ሳያንስ ከዚህ ዓይነቱ ተግባር እንዲላቀቅ ቤተ ክርስቲያኒቱ ብትመክረውም ለመስማት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ( እሱ ይሁን ወዳጆቹ) ማን እንዳስጻፈው ያልታወቀ የማጥመቅ ፈቃድ አውጥተው እንደነበር አይዘነጋም። ( ደብዳቤውን ለማንበብእዚህ ይጫኑ )

  ይሁን እንጂ በአባ ገሪማ ፊርማ ቅዱስ ፓትርያርኩ የማጥመቅ ፈቃድ ሰጥተውታል የተባለበት ደብዳቤ ከቤተ ክህነቱ ደርሶ ኖሮ ሲመረመር የሀሰትና የማጭበርበር ተግባር መሆኑ በመረጋገጡ ቤተ ክህነት ይህንኑ ለማሳወቅ ተገዷል። በዚሁ መሠረት ለአቶ ግርማ ወንድሙ የማጥመቅ ሥራ ምንም ዓይነት ፈቃድ እንዳልተሰጠና ፈቃድ የተሰጠው በማስመሰል የተበተነው ወረቀት የማጭበርበር ውጤት እንጂ የቤተ ክህነቱን የፕሮቶኮል ቁጥር የያዘ እንዳይደለ በጻፈው ደብዳቤ ላይ ገልጿል። በአባ ገሪማ የተጻፈውን ደብዳቤ ለማንበብ  ( እዚህ ላይ ይጫኑ ) 

አቶ ግርማ ድሮም አጥማቂ አልነበረም፤ አሁንም አጥማቂነት እንዳልተፈቀደለት ተረጋግጧል።  ግርማ ወንድሙ ከእጁ በምን ዓይነት ተአምር ሊለያት በማይፈልጋት መቁጠሪያ ሰይጣናዊ አስማት የሚጠቀም አስመሳይ እንጂ አጥማቂ አይደለም። ስለዚህ አፍቃሬ ግርማ ወንድሙ የሆናችሁ ሁሉ እርማችሁን አውጡ።

 ዳሩ በማስመሰል የሚያጠምቀው ግርማ ወንድሙ ይቅርና «እኔ ጥቁሯ ድንግል ማርያም ነኝ» እያለች ስታጭበረብር የነበረችው ሴት እንኳን ብዙ ተከታዮች ማፍራቷን አይተናል፤ ከእሷ አታላይነትም የበለጠ «ጥቁሯ ድንግል ማርያም» እንደሆነች አምነው የሚከተሏት ሰዎች ያስገረመን ጉዳይ ሆኖ አልፏል። ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን እንጂ የወንጌልን ቃል ስለማይመረምር ለእንደዚህ ዓይነት ትንግርቶች ተጋላጭ ነው።  

«በዚያን ጊዜ ማንም እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፤ ወይም ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ። እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ»    ማቴ 24፤23-25

Saturday, March 15, 2014

«ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መጽሐፍ” ቤተ ክርስቲያን እንድትቀበል ተጠየቀ»

 (ምንጭ፤አዲስ አድማስ)
መጽሐፉ ለአቡነ ማትያስና ለጠ/ሚ ኃይለማርያም እንዲደርሳቸው ተደርጓል
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታናሁ እና ለተመድ ተልኳል

       ከተፃፈ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል የተባለውንና ስለ ቅዱስ ኤልያስ መምጣት ምስጢር የሚተነትነውን መጽሐፍ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀብላ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በማስተርጎም ምዕመናኖችን እንድታስተምር፣ “ማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ለቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጻፈው ደብዳቤ ጠየቀ፡፡
ማህበሩ፤የመጽሐፉን ኮፒዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ለብፁዕ አቡነ ማትያስ  ህዝቡን እንዲያስተምሩበት ከሚያሳስብ ደብዳቤ ጋር መላኩን አስታውቋል፡፡
አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ሥላሴ፤“ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ለሁለት ሺህ ዘመን ስትጠብቀው የቆየችውን ምስጢራዊ መጽሐፍ በአደራ የመረከብና ለዓለም ሁሉ የማሳወቅ ፅኑ ኃላፊነትን ይመለከታል” በሚል ርዕስ ለፓትርያርኩ፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲሁም ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔትናሁ እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት በፃፈው  ደብዳቤ “ማህፈድ ብርህት ዘዲዮስቆሮስ አንበሳ” በሚል ርዕስ በግዕዝ ቋንቋ የተፃፈውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኗ ሊቃውንት ተቀብለው ምእመናኑን ስለ ቅዱስ ኤልያስ እና ትክክለኛይቱ ሰንበት እንዲያስተምሩበት አሳስቧል፡፡
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር የተላከው ኢትዮጵያና እስራኤል በመንፈሣዊ አሰራር አንድ ስለሚሆኑበት ሁኔታ ለማመልከት ነው ያሉት የማህበሩ አመራሮች፤ለተባበሩት መንግሥታት የተላከውም መልእክቱ ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ስለሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡
ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት እንደተፃፈ የሚነገርለት መጽሐፉ፤ ስለ ቀዳሚት ሰንበት ምንነትና ዘለዓለማዊነት በግልፅ እንደሚያብራራ እንዲሁም የኢትዮጵያና የእስራኤልን አንድነትና ትንሳኤ ምስጢር ተንትኖ እንደሚያስረዳ ተጠቁሟል፡፡
ማህበሩ በላከው መልዕክት፣ ቅዱስ ኤልያስ ከብሄረ ህያዋን ይዞት የመጣውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እንዲመረምሩት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲተረጎምና እንዲታተም፣ ምዕመናንም እንዲያነቡት የማድረግ ግዴታ ፓትርያርኩ እንዳለባቸው ያሳስባል፡፡ “ይህ ሳይሆን በእንቢተኝነትና በቸልታ ለዘመናት በተስፋ የተጠበቀውን ይህን መጽሀፍ እንዳይቀርብ ቢያደርጉ፣ ከብሄረ ህያዋን የመጣው ቀናኢ ነቢይ ዓለምን ሁሉ እየገሰፀ ባለበት ኃያል፣ ስልጣኑ ፅኑ ፈራጅነቱና ቁጣው የሚፈርድ መሆኑን አረጋግጠን እንነግርዎታለን” ብሏል፡፡ “ለቤተ-ክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ እና ካህናት ጥፋትና የመጨረሻው ውድቀት ነው” ሲልም ለመፅሃፉ ትኩረት እንዲሰጥ ማህበሩ  አበክሮ አሳስቧል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ የፓትርያርኩን ጽ/ቤት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጽ/ቤት በስልክ አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

Wednesday, March 12, 2014

የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የሰንበቴ ማኅበራት ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተወከለውን ኦዲተር የኦዲት መርኃ ግብር በመቃወም ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

በአዲስ አበባ የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የሰንበቴ ማኅበራት ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተወከለውን ኦዲተር የኦዲት መርኃ ግብር በመቃወም ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ፡፡ በተለያየ መጥፎ ሥነ ምግባርና ድርጊት ከካቴድራሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የተባረሩ ሁለት አባላትን ይዘው በካቴድራሉ ሁለተኛ ሰንበት ትምህርት ቤት ለማቋቋም ከጉርድ ሾላ እና አካባቢ የሰበሰቧቸው ወጣቶች ስለ ሰንበት ትምህርት ቤት አመሰራረት ግንዛቤ የሌላቸው በመሆናቸው የአዲሱ ሰንበት ትምህርት ቤት ምስረታ አልተሳካም፡፡  ቀደም ሲል የሰንበቴ ማኅበራቱ ከሀገረ ስብከቱም ሆነ ከካቴድራሉ አስተዳደር እውቅና ውጪ የሚሸጡትንና በወር እስከ 300.000.00 (ሦስት መቶ ሺህ ብር) ገቢ የሚያገኙበት የቀብር ፉካ ሽያጭ እና የአዳራሽ ኪራይ ንግድ ወይ ለቤተክህነቱ ፈሰስ እንዲያደርጉ አልያም ንግድ ፈቃድ አውጥተው ለመንግሥት ግብር እንዲከፍሉ በሀገረ ስብከቱ የቀረበውን ሐሳብ አልተቀበሉትም፡፡ እናም በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ከጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ፤ የቅዱ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በተገኙበት ተመርጦ ሥራ የጀመረውን ሰበካ ጉባዔ አይመራንም፤ እነርሱ ባቀረቡት ጥቆማ መነሻነት ከመንግሥት እና ከገለልተኛ አካላት የተዋቀረው የኦዲት  ኮሚቴ እኛን (የሰንበቴ ማኅበራቱን እና እንደ አቶ ወልዴ የሺጥላ አይነት በሕንጻ አሰሪ ኮሚቴ ገንዘብ ጉድለት የተገኘባቸውንና በቤተክርስቲያኑ ግቢ በቤተልሔሙ ጎን 26 ፉካ በመስራት መናፍቅ ልጆቻቸውን ወራሽ በማድረግ ሕገ ወጥ ሰነድ ያዘጋጁትን) ኦዲት ሊያደርጉ አይገባም በሚል ነጻና ገለልተኛ ቤተክርስቲያን እንመሰርታለን የሚል ፖስተር በመያዝ  እሑድ የካቲት 2 ቀን ጠዋት በቅዳሴ ሰዓት የቅዳሴ ሥነ ሥርዓቱን ለማስተጓጎል ሞክረዋል፡፡
በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የሴት ሰባኪ የሆነችውና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሕጋዊ ባሏን ጥላ   ወልዴ የሺጥላ የተባለውን የቀድሞ የህንጻ ኮሚቴ ሊቀ መንበር የወሸመችው እራሷን የዘመኑ የወንጌል አብሳሪ በመንፈስ ቅዱስ የተቀባሁ ጳውሎሳዊት ነኝ በማለት ጸሎተ ፍትሐት አያስፈልግም እኔ በፍትሀቱ ፋንታ ጸሎት አድጋለሁ አስተምራለሁ በማለት ምንፍቅና የምታስፋፋው  ቅድስት አሳልፍ ወደ ቤተክርስቲያኑ ድንጋይ እንዲወረውሩ ተሰብሳቢዎቹን ስታግባባ ነበር፡፡
ከካቴድራሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ሴት አባላትን በመተናኮልና ወሲባዊ ጥቃት በማድረስ በሕግ ተከሶ የተቀጣውና ከሰንበት ትምህርት ቤት በዚህ ቅሌት የተባረረው ሰለሞን አጥሌ የተባለው የታክሲ ሾፌርና የሰንበት ትምህርት ቤቱን ገንዘብ በተለያየ ወቅት በመውሰድ በሌብነት ወንጀል ተከሶ ከሰንበት ትምህርት ቤት የተባረረውና ዲቃላ ልጁን ደብቆ ሁለተኛ ሚስት በተክሊል ያገባው የሰለሞን አጥሌ ወያላ የሆነው ሲሳይ አፈወርቅ የተባሉት ሁለት ግለሰቦች መናፍቃንን በማሰባሰብ ሁለተኛ ሰንበት ትምህርት ቤት ለማቋቋም ያደረጉት እንቅስቃሴ አልተሳካላቸውም፡፡
ከዚህ ቀደም በዋነኛነት የሰንበቴ ማኅበራቱንና በመንግሥት ላይ ያኮረፉትን እንደነ ታዋቂውና ጨካኙ የደርግ የምስራቅ  ጎጃም ክፍለ ሀገር አስተዳዳሪና የደርጉ አባል አንሙት ክንዴን አይነት ሰዎችን በማሰባሰብ የደርግ ሥርዓተ ማኅበርን በቤተክርስቲያን ለመመስረት የሚታገለው የደርግ የስለላ ሹም የመቶ አለቃ አባቡ ታከለው በአጣዳፊ ህመም ከሰልፉ ላይ ወጥቶ ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን ህመሙ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ እለቱን ኦፕራሲዎን መደረጉንና እስካሁን ከሰመመን እንዳልነቃ ታውቋል፡፡
የካቴድራሉ አስተዳደር በሰንበቴ ማኅበር ስም ተደራጅተው የሚነግዱትን አንዳንድ የደርግ ጡረተኞችና የሰንበቴ አላማ ጠላ ማንቃረርና ቆሎ ማሸርደም የሚመስላቸው ሥራ ፈት አባወራዎችንና የሚገስጻቸው ያጡ ባሎቻቸው የዘነጓዋቸውን እንደነ ቅድስት አይነት መናፍቃንን በቅጡ በመቃወሙና በፍርድ ቤት በተወሰነ ቤተክርስቲያኒቱ  ባወጣችው ሕግ ሕገወጥ ንግድ እና የቦታ ወረራ በመቃወሙ በመረጃ ባልተረጋገጠ ሙስና እና ስም ማጥፋት ሆ ብለን በመጮህ  ከሰን እናስወግዳለን ከሚመጣውም ጋር በመደራደር የፉካ ንግዳችንን እንቀጥላለን በማለት  ለሀገረ ስብከቱ ቅሬታቸውን በሕጋዊ ሽፋን ቢያቀርቡም ሀገረ ስብከቱ በቦታው ያለውን ችግር በዘላቂ ሁኔታ ለመፍታት ከመንግሥትና ከገለልተኛ አካላት  የተመደበው አጣሪ ግን በተጨባጭ በደረሰው መረጃ  እና በተለያዩ ጊዜያት በሰንበቴ ማኅበራቱ በቤተክርስቲኗ የድንጋይ  መአድን ሽያጭ  ባገኙት ገንዘብ በገዟቸው የቢራ አክስዮኖች ባለቤትነት ጉዳይ እንዲሁም እነ ወልዴ የሺጥላ የህንጻ ኮሚቴ ሊቀመንበር መሆናቸውን ሽፋን በማድረግ በሌሎች አብበያተክርስቲያናት ባልተለመደ መልኩ በቤተክርስቲያኗ ግቢ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ለግላቸው 26 ፉካ በመገንባት ለፈጸሙት ምዝበራ ከ1994 ዓ.ም ጀምሮ ኦዲት ለማድረግ በማሰብ ያዘጋጀውን የጊዜ አጠቃቀም መመሪያ በመቃወም ሰልፉን አደራጅተዋል፡፡
 ቁጥራቸው 60 የሚደርሱት እነዚሁ ሰልፈኞች ከያዟቸው መፈክሮች መካከል መንግሥትን የሚተቹ እና አመጹን በማስፋፋት ልክ በእስልምና እምነት በመስኪዶች አካባቢ እንዳለው አይነት ውጥረት ለመፍጠር ቢያስቡም ፖሊስ ደርሶ ሰልፉ እንዲበተን አድርጓል፡፡ በቅርቡ ከአሜሪካ የመጣውና የደህንነት አባል ነኝ በማለት አመጹን የሚያስተባብረው አለማየሁ ከልል  ክሰ ቢመጣ አዘጋላችኋለሁ በማለት ቃል እንደገባላቸው የሰንበቴ ማኅበራቱ አመራሮች አስታውቀዋል፡፡ በዚህ ድርጊት ውስጥ የተሳተፉት ዋናዎቹ ግለሰቦች የተለያየ ችግር ያለባቸው ሲሆኑ አንዳንዶቹ በአጫሽነት ፤ ሰካራምነት ፤ በቃሚነት የሚታወቁ እና በአካባቢ ማኅበረሰብ የእንጨት ሽበት ተብለው የተናቁ ሽማግሌዎች ናቸው፡፡ ይህን አጋጣሚ እንደ መልካም የቆጠሩት አንዳድ ፖለቲካ ኃይሎች ሰልፉን ለማጠናከርና ወደ ውጪ በመውጣት ህዝብን ቀልብ ለመሳብ ቢያስቡም ፖሊስ ግን ይህንን ሊፈቅድ አልቻለም፡፡ ከትግራይ የተመረጠ ፓትርያርክ ቤተክርስቲያኗን ሊመራ አይችልም መንግሥት እጁን ከቤተክርስቲያናችን ላይ ያንሳ ትግሬ ተወላጅ ሰራተኞች ይውጡ በማለት በዋናነት መፈክር ሲያሰሙ የዋሉት አንሙት ክንዴ፤ አስማረ ዋሴ ፤ ባዬ ባዘዘው፤ወልሴ የሺጥላ፤ አበበ ደስታ ፤ መልአከ ኃይሌ ፤ ታደሰ  ፤ ቅድስት አሳልፍ፤ ደሳለኝ ፋንታቢል፤ ወልደኢየሱስ በሻህ ፤ሙሉ በለጠ ሲሆኑ ከወጣቶቹ ደግሞ ሴሰኛው ታክሲ ሾፌር  ሰለሞን አጥሌ እና ሌባው ሲሳይ አፈወርቅ ሲሆኑ እነዚህ የግል ጥቅም ያሳወራቸውና እምነትና ፖለቲካ የተቀላቀለባቸው ግለሰቦች በፖሊስ ክስ እንደተመሰረተባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሰአሊተ ምህረት ያለው የሰንበቴ አካሄድ ገና ከጅምሩ በ34ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ሰበበካ ጉባዔ ታላቅ ተቃውሞ የገጠምውና ሲኖዶሱ እልባት እንዲሰጠው በተሰብሳቢዎቹ አቋም የተያዘበትቤተክርስቲያን የምትመዘበርበት መንገድ ነው፡፡ የሰንበቴ ማኅበራቱ ወደ እድርነትና እክስዮን ማኅበርነት በመለወጣቸው እና ከቀብር ፉካና ከአዳራሽ ኪራይ ያገኙትን ገቢ የቢራ አክስዮኖችን በመግዛት ከመንፈሳዊ ተግባት ውጪ የሚያውሉት ሲሆን ለረፈደበት የፖለቲካ ዓላማ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚያንቀሳቅሱ ማወቅ ተችሏል፡፡ የዚህ ድርጊት ዋነኛ መሪ ወልዴ የሺጥላ በኢትዮ ቴሌኮም ሲሰራ በጽዳት ሰራተኞች ላይ በፈጸመው የወሲብ ትንኮሳ በአስተዳደር ተከሶ ከቅርንጫፍሥ አስኪጅነት ወደ ሽያጭ ሰራተኛነት የወረደ ግለሰብ መሆኑ ስለርሱ የሚያውቁት ሁሉ ይመሰክራሉ፡፡
በካቴድራሉ ጉብኝት ያደረጉት ቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁአን ሊቃነጳጳሳት በሰንበቴ ማኅበራ የተወረረውንና ለብዝኃኑ ጥቅም መስጠት ያለበትን ቦታ እና ግንባታ ተመልክተው ማዘናቸው ታውቋል፡፡ የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰፊ የልማት ቦታና በሰንበቴ የተወረረ የቀብር ስፍራ እንዲሁም በሰንበቴ ማኅበራ ቁጥጥር ሥር የሆነ በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመት የድንጋይ ማእድን ሐብት እና ከ100.000 በላይ አማንያን ያሉበት ሲሆን በሰንበቴ የጥቅም ሰንሰለት የተደራጁ ከ60 የማይበልጡ ግለሰቦች ምክንያት ሰላሙን አጥቶ የቆየ ደብር ነው፡፡