Saturday, January 18, 2014

የማኅበረ ቅዱሳን የግል ጋዜጦች ዘመቻና የሐራ ተዋሕዶ ጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!





ደጀ ሰላም የተባለችው የማኅበረ ቅዱሳን ብሎግ ከተዘጋች በኋላ የጭቃ ሹምነቱን ሥልጣን የተረከበችው «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግ አንድም ቀን ተሳስታ ነገረ ወንጌል ሳታስተምር በነገረ ወሬ ጫሪነቷ እነሆ አንድ ዓመቷን አከበረች። የሐራ ዘተዋሕዶ ብሎግ አገልግሎት በወሬ ነጋሪነት ላይ ጊዜዋን የማጥፋቷ ምክንያት በማኅበሩና በዙሪያው ስላሉት የመርሃ ስብከት መልእክት በሙሉ «በማኅበረ ቅዱሳን» ዋናው ድረ ገጽ ስለሚተላለፍ «ሐራ» ስለወንጌልና ስለማኅበሩ አዳዲስ ዜና መዘገብ አይጠበቅባትም። ይህ የሚያሳየው የማኅበሩ  አመራር ቁጭ ብሎ እንዴት መተላለፍ እንዳለበትና ምን መተላለፍ እንደሚገባው በደንብ የመከረበት መሆኑን ያሳያል።
 ሰሞኑን ደግሞ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ ለመቸከል ያዘጋጁትን የአፈና እቅዳቸው መግቢያ መንገድ ይሆን ዘንድ የነደፉት የጥናትና ስትራቴጂ መርሃ ግብር በሐራ ዘተዋሕዶ ላይ  ብቻ እየለቀለቁ ዜና መስራት ስላቃታቸው የግል በተባሉ ጋዜጦች ላይ የጥናት ጩኸታቸውን ማስተጋባት ከጀመሩ ሳምንት አልፏቸዋል። ሐራ ደግሞ በማኅበሩ አባላት በጋዜጦች ላይ የወጡትን ዜና ወዲያው እንደ አዲስ ዜና ተከትላ ትለጥፋች።

ማኅበሩ የጳጳሳት አባላት ብቻ ሳይሆን በህክምና ሆስፒታሎች፤ በፌዴራል ፖሊሶች፤ በፍርድ ቤቶች፤ በትምህርት ሚኒስቴር፤ በመንገድ ትራንስፖርትና በመሳሰሉት መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ በግልጽና በስውር የሚሰሩ ምልምል አባላት እንዳሉት እርግጥ ነው።በግል ጋዜጦች ላይ የሚሰሩ አባላቱም በስም ጭምር የሚታወቁ እንዳሉም የአደባባይ ምስጢር ነው። ስለሆነም በፈለገው ጊዜ የፈለገውን መረጃና ዜና በፈለገው ጋዜጣ ላይ ለማውጣት የሚቸገር ባለመሆኑ የመረጃ መረቡን በቂ ሽፋን መስጠት ያቃታትን «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግን ለማስተንፈስ በስመ ነጻ ሚዲያዎች ላይ ያቀረበውን ጥናት ለመተግበር እንዲቻልና  ተፅዕኖ ለማሳረፍ ሲል በስመ አባ እስጢፋኖስ፤ በስመ ሰንበት ተማሪ አለያም ማን እንደዘገበው ስም ሳይገለጽ ጋዜጣ ላይ እንዲለቀለቅ ለማድረግ ውጣ ውረድ የለበትም።


በእርግጥ በስመ ነጻ ሚዲያ የሚታተሙት የኢትዮጵያ ጋዜጦች አብዛኞቹ ይህንን ያህል ትኩስና የአንባቢን ቀልብ በሚስብ መረጃ በቂ ልምድና ብቃት ያላቸው ስላልሆኑ ከጊዜ ማሳለፊያ ዜናነት ባለፈ ለማኅበረ ቅዱሳን ጥረት ውጤታማ ጎን ያስገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም። ግማሾቹ የፕሬስ ህጉን ስለሚፈሩ እንደዱሮው በሬ ወለደ ብለው በመጻፍ ጉድ፤ ድንቅ የሚያሰኝ ፈጠራ ላለማቅረብ ራሳቸውን በራሳቸው ሳንሱር በማድረግ የተቸገሩ ናቸው። ገሚሶቹም «አቶ እንትና ተከሰሰ፤ ወ/ሮ ብሪቱ ቲማቲም ሸጠው ትርፋማ ሆኑ፤ ዓለማየሁ አዲስ ሆቴል ከፈተ » በሚል የተለመደ ዜና የሚውተረተሩ ስለሆነ የማኅበረ ቅዱሳንን የጥናት ወረቀት ተቀብለው ዜና ቢሰሩ ለጊዜ ማሳለፊያነት ማንበብ ከሚቻል ውጪ በዚያ ንባብ ስለጥናቱ የድጋፍ ይሁን የተቃውሞ ሰልፍ የሚወጣ እንደሌለ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ብዙዎቹም /tabloid /ወሬና ጭምጭምታ በመለቃቀም፤ የኮከብ ቆጠራና ታሮት በመተረክ፤ ስሜታዊ ፈጠራ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። society reporting/ ማኅበራዊ ዜና የሚሰሩ፤ ስለምግብ፤ ፋሽን፤ ስለቁንጅና የሚተርኩ ናቸው። comedic 
/ ዋዛና ፈዛዛ፤ ቀልድና ቧልት የሚዘግቡ ሲሆኑ በተወሰነ መልኩ gonzo journalism / የተሻለ ምልከታ አለው። ራሱ የመረጃው ምንጭ ሆኖ በመጀመሪያ ረድፍ የሚዘግብ ሲሆን በያዘው አሳማኝ ጭብጥ ለመረጃው ኃላፊነትን የሚወስድ ነው። አሉ፤ ሰማሁ፤ ሰዎች ነገሩኝ አይልም።  /Investigative journalism/ የምርመራ ጋዜጠኝነትን ባህል የተከተለ ጋዜጣ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ብቻ ሳይሆን አይታሰብም። ታዲያ ከዚህ አንጻር የማኅበሩ ስውር ጋዜጠኞች ጽሁፍ በደረጃ በየትኞቹ ጋዜጦች ላይ የሀ/ስብከቱን የጥናት አስፈላጊነት አከታትለው አወጡ ብለን ብንጠይቅ ግልጽ መልስ አናገኝም።  በቃ ዜና ሆኖ መውጣቱ ብቻ በቂያቸው ነበርና ለማውጣት ማውጣት በቻሉት ጋዜጣ ላይ ሁሉ ዜና ሆኖ እንዲወጣ ደክመዋል። ውጤቱ ድካም ሆኖ መቅረቱ ግን ያሳዝናል።

ምናልባት 50 ሚሊየን ተከታይ አለኝ የምትለዋን ቤተ ክርስቲያን የሚመሩት ሹመኞች «አንድ ለእናቱ» የሆነውና ያውም በየወሩ አንዴ ከሚታተመው «ከዜና ቤተ ክርስቲያን» ውጪ ለጋዜጦች ዜና ባይተዋር ስለሆኑ ዛሬ ምን ተባለ? አዲስ አድማስ ምን ይዞ ወጣ? በማለት እንደአዲስ የመረጃ ምንጭነት የጽሁፉ ስውር ባለቤት የሆነው  ማኅበሩ እንደአዲስ ግኝት ሲነግራቸው በመባነን ተደንቀው ከሚያነቡት በስተቀር ለማኅበሩ የዜና ስራ ድካም አንዳች ትርፍ ለማስገኘት የሚችል ተጨባጭ ነገር እንደሌለው እርግጥ ነው።
«ድከም ያለው ውሃ ይወቅጣል» እንዲሉ ማኅበሩ አንዴ በሐራ ተዋሕዶ፤ አንዳንዴ በግል ጋዜጦች፤ አንዴ በሰንበት ተማሪዎች፤ አንዴ በጥምቀት ተመላሾች፤ ሌላ ጊዜ በጳጳሳት በኩል የሚወጣ፤ የሚወርደው ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ተጨንቆ ሳይሆን የራሱን መዋቅር በሀ/ስብከቱ ችግር አስታኮ ለመዘርጋት ከማለም የመነጨ ስለሆነ እንደታወቀበት ስንነግረው ፈጽሞ አይገባውም። 


አሁን ደግሞ የያዘው አዲስ ስልት ፓትርያርኩን በውዳሴ ከንቱ ጠልፎ በአንድ ጀንበር የጥናቱን ተአምር ለማሳየት ተዘጋጅተዋል የምትል ዜና ደጋግሞ ማሰማት ጀምሯል። ወደኋላ ያፈገፍጉብኛል ብሎ ስለሰጋ ብርታት ሰጪ የምስጋና መርፌ እየወጋ መሆኑ ነው። ቤተ ክህነትን በማኅበሩ ያስወረራት የሚያዥጎደጉደው ውዳሴ ከንቱ፤ ጥቅማ ጥቅምና በስለላ የሚሰበስበው የግለሰቦች የነውር ፋይል ናቸው። ስለዚህ ፓትርያርክ ማትያስ ቤተ ክርስቲያኒቷ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በራሷ ልጆች፤ በራሷ ሊቃውንት፤ ለራሷ የሚሆን ሕግ ማውጣት ትችላለችና ማኅበሩ በግል ጋዜጦች፤ በወጣቶችና በጳጳሳት በኩል ጫና ለማሳደር የሚያደርገውን ዘመቻ እንዳይፈሩ እናሳስባለን። የማኅበረ ቅዱሳን የጋዜጦች ላይ ዘመቻና የሐራ ዘተዋሕዶ የጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በ1994 እና በ1995 ዓ/ም በአንጻራዊነት የተሻለ የአስተዳደር ዘመን ነበረው!



ከመሪጌታ ይኄይስ ተአምኖ፤  ኩቤክ- ካናዳ

እንዲህ እንደዛሬው ሳይሆን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ማለት በሀ/ስብከቱ ውስጥ የፈለገውን ማድረግ የሚችል ሹመኛ ማለት ነው። ከ1992 ዓ/ም  ጥቂት ቀደም ብሎ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሊቀ ካህናት ብርሃኑ ገ/አማኑኤል ሥራ አስኪያጅነትና (ነፍሱን ይማረውና) የዮሐንስ ዋለ ዘመን እንዳበቃ፤ ከቤተ ክህነቱ ሙያ ውጪ የሌላ ሙያ ባለቤት ያልሆኑትና የተለየ ሥራ እንዳላቸው የማናውቅላቸው ነገር ግን በአድዋና በመቀሌ  ትልቅ ኢንቨስትመንት ያላቸው አለቃ መኮነን ገ/መድኅን የሥራ አስኪያጅነቱን ኃላፊነት ከተረከቡ በኋላ ሙስናው ያለማስታወቂያ መደበኛ የስራ መስክ ሆኖ እንደነበር የምናውቅ ሰዎች የምንዘነጋው አይመስለኝም።

  እንደዚያም ሆኖ አለቃ መኮነን ገ/መድኅን ጎበዝ የአስተዳደር ሰው ናቸው። በዚያ ላይም ባመኑበት ጉዳይ ደፋርና ወደኋላ የማያፈገፍጉ ጠንካራ ሰው ስለመሆናቸውም መጥቀሱ ተገቢ ይመስለኛል። በወቅቱ ፀሀፊ የነበረውና አሁን በአሜሪካ በታክሲ ሾፌርነት የሚሰራው ክነፈ ርግብ ሐጎስ ፈጣንና ከዓይን ላይ የሚነጥቅ ቀልጣፋ እንደመሆኑ መጠን የሚበቃውን ገንዘብ መሰብሰብ ችሎ እንደነበር የምናውቅ እናስታውሳለን። እንደዛሬው የጉቦው የጨረታ መነሻ ዋጋው ከፍ ሳይል በፊት ለጉቦው በተሰጠው የሀ/ስብከቱ ምሥጢራዊ መጠሪያ ሥም ማለትም «ሥላሴ ስንት ናቸው? ከተባለ መልሱ «አንድም ሦስትም ናቸው» ማለት ሲተረጎም ክፍያው ከአንድ ሺህ እስከሦስት ሺህ ይደርሳል ማለት ሲሆን «አምስቱ አዕማደ ምሥጢር» ከተባለ ደግሞ «እስከ አምስት ሺህ»፤ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ከተባለ ደግሞ « እስከ ሰባት ሺህ ብር» ጉቦ ይጠየቃል ወይም ይከፈላል ማለት ነበር። ዛሬን ወደኋላ መለስ ብዬ ሳየው በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሽፋን የጉቦ መቀበያ ተመንን በቁጥር የማስቀመጥ መጥፎ ልምድ መነሻው እምነትን ለገንዘብ የማዋል ምሥጢራዊ ክህደትና ማላገጥ እየተስፋፋ የመምጣቱ ምልክት መሆኑን ያመላከተ እንደነበር ነው። እምነት ከሰዎች ውስጥ እየጠፋ በመጣ ቁጥር እምነቱ ለሥም መጠሪያ ይሆንና በተግባር ግን ወደሸቀጥነት ይለወጣል ማለት ነው። ጌታችንንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በቤተ መቅደሱ ደጃፍ ሲሸጡና ሲለውጡ የነበሩትን በሃይማኖት ስም የመጡ ነገር ግን እምነቱን የመሸቀጫ መድረክ ያደረጉትን ሰዎች የገለጸበት መንገድ ተመሳሳይ ነበር። 

«የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ።በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።ደቀ መዛሙርቱም። የቤትህ ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ አሰቡ» ዮሐ2፤13-17 

ዕለተ ፋሲካ ቀርቦ ሳለ የሃይማኖት ሰዎች ሸቀጥ በመቅደሱ ደጃፍ ከትንሿ እርግብ እስከ ትልቁ በሬ ድረስ ሲሸጥ እንደነበር ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል። ዛሬም እንደ ቃሉ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የነዋይ ፋሲካቸውን የሚያከብሩ ሞልተዋል። ከነጋዴውና ሸቃጩ ማኅበረ ቅዱሳን አንስቶ በሥራ አሥኪያጅነት ዘመናቸው ባርከውና ቀድሰው ጉቦውን ያስፋፉት አባ እስጢፋኖስ፤ ታሪክ ራሱን ይደግማል እንዲሉ ዛሬም ቤተ መቅደሱ ደጃፍ ላይ ተኮልኩለው አዋጭ ያሉትን የጥናትና ስትራቴጂ ገበያ ዘርግተው ለመሸጥ እያስማሙ መገኘታቸው ብዙም ላያስገርም ይችላል። በእምነት ሥም በዐደባባይ መሸጥ፤ መለወጥ ሲያያዝ የመጣ ነውና ብዙም ግር አያሰኝም።  ዛሬም ድረስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ ሸቃጮቹ መልካቸውን እየለዋወጡ መነገዳቸውን አላቆሙም። «የቤትህ ቅናት በላኝ» ለማለት በመጀመሪያ የንግድ ሂሳቡን ዘግቶ ወደኋላ የሚጎትተውን ብዙ ሀብት ትቶ ሊመጣ ይገባል እንጂ ስሜትና አፍን አስተባብሮ ነፍስያን በማባበል ማንንም ማታለል እንደማቻል ግን እንነግራቸዋለን።

«እርሱም በመንገድ ሲወጣ አንድ ሰው ወደ እርሱ ሮጦ ተንበረከከለትና። ቸር መምህር ሆይ፥ የዘላለም ሕይወትን እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።ትእዛዛትን ታውቃለህ፤ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አታታልል፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው። እርሱም መልሶ፦ መምህር ሆይ፥ ይህን ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለው። ኢየሱስም ወደ እርሱ ተመልክቶ ወደደውና። አንድ ነገር ጐደለህ፤ ሂድ፥ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መስቀሉንም ተሸክመህ ና፥ ተከተለኝ አለው። ነገር ግን ስለዚህ ነገር ፊቱ ጠቈረ፥ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነም ሄደ» ማር 10፤17-22

ሀብትና ንብረታቸውን እያከማቹ «የቤትህ ቅናት በላኝ» ቢሉ ሁሉን ዐዋቂ ፈጣሪን ቀርቶ በዓይን የምናያቸው እኛን ሊታልሉ ከቶ አይችሉም። የገነቡትን የመኖሪያ ቤት ለቤተ ክርስቲያናቸው ይስጡ፤ ከመቅደሱ ደጃፍ የተገተረውንም ህንጻ የተወደደ መስዋዕት እንዲሆንላቸው ለቤተ መቅደስ መባዕ ይስጡና ስለ ቤቱ ቅናቱ   ይንገሩን። ያኔም ምሳሌ የሚሆነውን ሥራቸውን ዐይተን እንደነዚህ ዓይነቶቹን ቤተ ክርስቲያን ትፈልጋቸዋለች ብለን ምስክርነታችንን እንሰጣቸዋለን።
   ከዚያ ባሻገር የወጣቱን ሀብታም ታህል  «አታመንዝር፤ አትስረቅ፤ አታታልል፤ በሀሰት አትመስክር» የሚለውን ትዕዛዛት ከህጻንነታቸው ጀምረው ማክበር ስለመቻላቸው አፋቸውን ሞልተው ለመናገር የማይችሉ «የቤተ መቅደሱ ቅናት በላኝ» ቢሉ ማን ያምናቸዋል? ሌላው ቀርቶ ማኅበረ ቅዱሳን  የቤተ መቅደሱን ደጃፍ ሰናዖር ህንጻውን መባዕ አድርጎ ሊሰጥ ይቅርና ቤተ ክርስቲያን ሂሳብህን ኦዲት ታድርግህ፤ በቤተክህነቱም ሰነድ ገቢህን ሰብስብ፤ ሲባል በሕጋዊ የውጭ ኦዲተር አስመርምሬአለሁና የምሰጣችሁ ወረቀት በቂያችሁ ነው በማለት አቅሙም፤ ሥልጣኑም የላችሁም በማለት ማናናቁ ብቻ የማንነቱ ምሥክር ነውና ወቅታዊውን ችግር ተመልክቶ የራስን አጀንዳ ማስፈጸም አግባብ አይደለም።
  ወደ ርዕሰ ጉዳያችን ስንመለስ በ1994 ዓ/ም  አለቃ መኮነን ገ/መድኅን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነቱን ጨርሰው ለስድስት ወር ገደማ የወረቀት ራስጌና ግርጌ የማይለዩት፤ የማኅጸንቱ ልጅ ሥራ አስኪያጅነቱ እንደለቀቁ፤ በወቅቱ ከአሜሪካ የተመለሱት አባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል / በኋላም አባ ሳሙኤል ሊቀ ጳጳስ/ መረከባቸው ይታወሳል።  ፀሀፊ የነበረው ክነፈ ርግብ ሐጎስም የዞረ ሂሳቡን በአባ ማኅጸንቱ በማስጨረስና የሚሸመጥጠውን ጨራርሶ በአጋጣሚ ያገኛትን ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊትን አግብቶ ወደአሜሪካ ኮበለለ።
   አባ ተከስተ ብርሃን የወቅቱ ሥራ አስኪያጅ ሆነው በትኩስና ባልተበረዘ ስሜት በሀ/ስብከቱ ውስጥ ተንሰራፍቶ የነበረውን ሙስናና ቤተሰባዊ ተቋም ለመናድ ጊዜ አልፈጀባቸውም። የካህናት አስተዳደሩን መጋቤ ሃይማኖት ጸገየን፤ የትምህርትና ስብከተ ወንጌል ኃላፊውን ርዕሰ ደብር መሀሪን፤ የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊውን (ነፍሱን ይማረውና) ኃይሉ ማርቆስን፤ ከወረዳ ቤተ ክህነት ወደ ፀሀፊነት የተዛወሩት አፈ መምህር ገ/ዮሐንስን፤ ከብዙ ድካምና ጥረት በኋላ ደ,ግሞ ወ/ሮ ሣራ ገ/ሥላሴን፤ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ክፍሌን የመሳሰሉትን የማይገፉ ተራሮች አንድ በአንድ ለመናድ በመቻላቸው ትልቅ ስም ለመገንባትና በበታቾቻቸው ላይም የማይቻሉ ሰው የመሆናቸውን ተፅዕኖ ማሳደር ችለው ነበር።
 ከላይ የተዘረዘሩት ሰዎች በአንድም ሆነ፤ በሌላም ምክንያት ከበላይ ባለሥልጣናት በተለይም (ነፍሳቸውን ይማርና) ከወቅቱ ፓትርያርክ ከአቡነ ጳውሎስ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ስለነበሩ እንደዚህ ዓይነቶቹን ሰዎች ከያዙበት ስኳር ከሆነ ሥልጣን ላይ ማስነሳት የሚታሰብ ባለመሆኑ የአባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ግንባር እድለኛ ስለነበር ይሆናል ወይም በበላይ አካል በኩል ተሰሚነት ያገኙ እንደነበሩ መገመት ይቻላል።  ይህም የስምና የኃይል ግንባታ ብቃት በበታቾቻቸው ላይ ፍርሃት በማንገሱ ትእዛዞቻቸው ሁሉ ተፈጻሚ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል። 
በእርግጥም ቀደም ብሎ ከእነ አባ ኃ/ማርያም ዘመንና ከወዲህም በእነ ሊቀ ካህናት ብርሃኑና ዮሐንስ ዋለ በኋላም በአለቃ መኮንንና ክነፈ ርግብ ሐጎስ አስተዳደር ጊዜያት ውስጥ ሀ/ስብከቱ ተጨመላልቆ ስለነበር የአባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል አዲስ የአወቃቀር መንፈስ ተስፋን መፈንጠቁ የሚጠበቅ ነው።  ደግሞም ከእነድክመቶቹ በወቅቱ የአዲሱ ሥራ አስኪያጅ ቀናና ትኩስ መንፈስ ብዙ ድጋፍ ከካህናቱ ወገን አግኝቶም ነበር።
  መረን የለሽ የግል ጋዜጦች የቤተ ክህነቱን ገመና ሳይዙ የሚወጡበት ቀን አለ ለማለት አይቻልም ነበር። ይህም በብዙ መልኩ ቀንሶ የተገኘው በአባ ተከስተ ብርሃን ሥራ አስኪያጅነት ወቅት ለመሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። በተለይም በ1994 እና በ1995 ዓ/ም በይበልጥም አባ ተከስተ ብርሃን የሊቀ ጳጳስነቱን ሥልጣን ከማግኘታቸው በፊት የነበረው የሀ/ስብከቱ አስተዳደር በአንጻራዊነት ሲታይ በሀ/ስብከቱ ታሪክ ከመቼውም ጊዜ የተሻለ እንደነበር አይካድም። የዚህ ጽሁፍ አቅራቢም ይህንኑ ይመሰክራል።


 አባ ሳሙኤል ሊቀ ጳጳስ ከሆኑም በኋላ ጥቂት ለማስቀጠል ሞከረው ነበር። ነገር ግን ቀደም ሲል የነበራቸውን የመልካም ስራ መንፈሳቸውን ማን እንደቀማቸው ሳይታወቅ፤ በፓትርያርክ ጳውሎስ ፊት የነበራቸውንም ግርማ ሞገስ እየሸረሸረ የወሰደው ነገር ሳይገለጥ ሀ/ስብከቱን ማስተዳደር ትተዋል በሚባል ደረጃ ወደ መርሳት ደርሰው ነበር። ምናልባትም ሥራ የአስኪያጅነቱን ዘመን የተጠቀሙት ወደሥልጣን የመሸጋገሪያ ስልት አድርገውት ይሆን? የሚል ጥያቄ የሚያስነሳው ሥራ አስኪያጅ ሳሉ ከነበሩበት ዘመን የተሻለ ሥልጣን ሲይዙ የበለጠ መስራት እየቻሉ ለመስራት አለመፈለጋቸው ፍንጭ ሊሰጠን ይችላል። ከዚያም በላይ አብረውአቸው የሚውሉትንና የሚወርዱትን ሰዎች ማንነት ስንመለከት በወቅቱ በትክክለኛ የኅሊናቸው መስመር ላይ እንዳልነበሩ ያረጋገጠ ማረጋገጥ ችለናል።

  ከሀ/ስብከቱ ሽያጭ ክፍል ተነስቶ ወደሥራ አስኪያጅነት ያደገው መሪጌታ መኩሪያ ደሳለኝ ከያዘው በኋላ የሀ/ስብከቱ የአስተዳደር ዘመን ሳይሆን የሞት ዘመኑ ሆኖ ተተክቷል። የተገነባው መልካም አወቃቀርና አስተዳደር እምጥ ይግባ ስምጥ ሳይታወቅ በአፍ ጢሙ ተደፋቷል። በተመሳሳይ መልኩ ሊቀ ጳጳስ ሳሙኤል መተንፈሻ እስኪያጡ ድረስ ከረቫት ባሰሩ አሸርጋጅ ፀሐፊዎች፤ ራሳቸውን ባልሰበኩ ሰባኪዎች፤ በሙዳየ ምጽዋት ገልባጭ አስተዳዳሪዎች ተከበው በውዳሴ ከንቱ መከራቸውን ያዩ ነበር። ሃይማኖት የለሹ ዘሪሁን ሙላቱ (ዛሬም በየመድረኩ ሃይማኖት እንዳለው ሰው ያናፋል) ቀኝ እጃቸው ሆኖ አለሁልዎ ሲላቸው መጨረሻውን ለማየት እንመኝ ነበር። የዛሬው የቦሌ መድኃኔ ዓለም ፀሀፊ ሰሎሞን በቀለ የካዝናውን ቀበኛ አይጥ ይዘው ሲጓዙ ለተመለከተ አጀብ የሚያሰኝ ነበር። የባሌ ጎባው አጭበርባሪ ሰሎሞን ቶልቻ (ቄስ ነኝ ይላል)፤  የቅድስት ማርያሙ ሰንበት ተማሪ ሡራፌል ወንድሙ (እሱም አሁን አሜሪካ ገብቶ ቄስ ነኝ ይላል) የመሳሰሉት ሁሉ እንደበረዶ ናዳ የሚሟሙ ወዳጆችን አፍርተው አይተን የሚቀልጡበትን ቀን ስንጠባበቅ ነበር።

  ጉዳይ የሚፈጸመው በስልክ ወደመሆን ተቀይሯል። በጉድ ሙዳዩ አባ አብርሃም በኩል የሚቀርቡ ተቀጣሪዎች ውጤታማ መሆናቸውም የታየበት ወቅት ነበር። ባለ ጉዳይ፤ ጉዳይ የለሽ ሆኗል። የአድባራትና ገዳማት ምዝበራ ከመቼውም ጊዜ በላይ ገኗል። ከስራ የሚባረር፤ አላግባብ የሚዛወር፤ ከደረጃው የሚወርድ በርክቷል። ፍርድ ቤቶችን የቤተ ክህነት አቤቱታ አሰልችቶታል። ብዙ ችግሮችና የሥልጣን ሽኩቻዎች ተበራክተው የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ግብዓተ መሬቱ ሊፈጸም ሲል ከአባ ጳውሎስ ጋር የጠለቀ ክርክር ሲነሳ ጎራው ይለይ ጀመረ። ዘመቻው ሁሉ ፈልቶ፤ ገንፍሎና ቀዝቅዞ የሆነው ሁሉ ሆነ።  በተለያየ ጊዜ ከሀ/ስብከቱ ያስቀየሯቸው ሰዎች አባ ሳሙኤልን መዋጋት ዛሬ ነው በማለት ጦር ሰበቁ። አየር ላይ የተንሳፈፉት እነአባ ዕዝራ በጀት መደቡ። እነኤልዛቤል እጅጋየሁም እንደጉዲት ተፋለሙ። አባ ሳሙኤልም ብቻቸውን ቀርተው፤ ብቻቸውን ተዋግተው ዘለቁ። ሁሉም ጥጉን ይዞ «ያመኑት ፈረስ በደንደስ» እንዲሉ ያመኗቸው ሁሉ ከዱ። አባ ሳሙኤል ሀ/ስብከታቸውን በአግባቡ የአስተዳደር ማዕከላዊነት ይዘውት ቢሆን ኖሮ አንድ ጊዜ ለዐራት፤ ሌላ ላንድ ሲጠቀለልና ሲፈታ ባልኖረም ነበር። እንደጀመሩት ለመጨረስ አልቻሉም።

  ዛሬስ? ዛሬ ያለፈውን ስህተት ሲደገም ማየት የባሰ ያሳምማል። አባ እስጢፋኖስ ያንን ስህተት እየደገሙት ነው። ማኅበረ ቅዱሳንና ተላላኪዎቹ ከኋላ ሆነው ሀ/ስብከቱን እያስተዳደሩት መገኘታቸው እርግጥ ነው። እኛ የምንለው ራሳችሁን ሁኑ ነው። ሌሎችን ተደግፋችሁ የራሳችሁን ገመና ለአጋልጦ ገላጭ አትስጡ ነው። እውነት መናገር ካስፈለገ ካህናቱ የማንንም አባቶች ገመና አደባባይ ማውጣት አይፈልጉም፤ አይወዱምም። ችግሩ ያለው ከራሳቸው ከባለገመናዎቹ ሲሆን ገመናቸውን እንደድመት ሽፍን አድርገው መያዝ ያቅታቸውና ያለቦታቸው ተገኝተው እንዲገለጥላቸው አርፎ የተኛውን ካህን በግድ ይነካኩታል።  አፄ ቴዎድሮስን እልክ ያጋባቸውና እስከሞት ያደረሳቸው የካህን አድማ ነው። አባ እስጢፋኖስም አዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ያለማኅበረ ቅዱሳን ውሻል ማስተዳደር አልቻሉበትም። በእልኽ ቤት አይገነባምና በእልኸኝነት ሁሉን ከግብ አደርሳለሁ ማለቱን ትተው ሀ/ስብከትን ለቀው አንዱን፤ ጅማዎትን ለዚያውም ከቻሉ እስኪ እሱኑ በደንብ ያስተዳድሩ ምክሬ ነው!!

Wednesday, January 15, 2014

ትግርኛ ተናጋሪ ጎንደሬው ሊቀ ጳጳስ እስጢፋኖስ ከጎንደሬዎች ጋር እየመከሩ ነው!!


( ከብሶቴ ተሰማ አዲስ አበባ )
ዘር ለእህል ነው። የእህል ዘር ግንዱ አንድ አይደለም። ዘሩ በየመልኩ ልዩ ልዩ ነው። የሰው ልጅ ግን እንደዚያ አይደለም። መልኩ ቢለያይም ግንዱ አንድ አዳምና ሔዋን ናቸው። ከዚያም በላይ ሁላችንም በክርስቶስ ሞትና ትንሣዔ  አንድ ሆነናል። ይሁን እንጂ ክርስትናን ከስምና ከሹመት በስተቀር የማያውቁ አንዳንዶች ዛሬም  የሰውን ልጅ ከእህል የዘር ዓይነት ቆጠራ ራቅ ብለው ለማየት እንዳልቻሉ እርግጥ ነው።
ከእነዚህም አንዱ አባ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የማኅበረ ቅዱሳን ሊቀጳጳስ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን አንዲት ብትሆንም በአስተዳደር ይዞታዋ የተለያየ በመሆኑ ሊቀ ጳጳሱ በጅማ ሀ/ስብከት ሳሉ ገመናቸው ተሸፍኖ፤ በሰው መሳይ ሸንጎ ተከልለው በሰላም ይኖሩ ነበር።  ኅሊናቸውን አሳርፈው መኖር የሚችሉበትን ሀ/ስብከት ይዘው አርፈው እንደመቀመጥ ከወታደሮች ማኅበር ጋር አብረው በመቆም የእድሜ ልክ መጽሐፋቸው ይነበብ ዘንድ በየቦታው አለሁ ማለታቸው ያሳዝናል።  ደርሶ መንፈሳዊ መስሎ ለመታየት የአበው አጥንት ይወቅሰናል፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይፋረደናል በሚል በአስመሳይ ተቆርቋሪነት የማኅበሩን ዓላማ ለማስፈጸም ደፋ ቀና ማለታቸው ለእርሳቸው የትጉህ ሰራተኛ ትግል ቢመስላቸውም እውነቱን ለሚያዩ ግን ያለቦታቸው በአጉል ሰዓት የተገኙ  ሰው ናቸው። ከአባ ገብርኤል ጋር ከአስመራ ጀምሮ በድሬዳዋ ዞረው፤ አዲስ አበባን አካለው ኮተቤ 02 እስካሳነጹት የመኖሪያ ህንጻ ድረስ ብዙ ጉድ መኖሩን የምናውቅ እናውቀዋለን።
በእርግጥ ሊቀጳጳሱ( ከተባሉ) ዓይናቸውን በጨው የታጠቡ ስለሆነ ስለበደልና ጥፋት ትንሽ ስሜት አይሰጣቸውም። የኅሊና ጸጸትም ፈጽሞ አይነካካቸውም። ከድፍረቱ ጋር የደነደነ ልብ ስለታጠቁ የተባለው ቢባል፤ የተወራው ቢወራ ደንታ የላቸውም። ለዚህም ነው ከበደል ጋር ዕረፍት በሌለው ወዳጅነት እስከ ህይወታቸው ህቅታ ድረስ ቃል በመግባት ዛሬም የአንድ ተራ ማኅበር ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው የመገኘታቸው ነገር  አረጋጋጭ ነው። በመሰረቱ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ለማስተዳደር ራሱ ከሙስናና ከአስነዋሪ ስነ ምግባር የጸዳ መሆን ይገባው ነበር። አፉን ሞልቶ ለመናገር፤ ሌባና ብልሹ አስተዳደር ለማስተካከል የሚችለው ከዚህ የጸዳ ቢሆንም አባ እስጢፋኖስ ግን ለአባ ማትያስ በዋሉላቸው ውለታ የተነሳ በስራ አስኪያጅነት ዘመናቸው በጉቦ የጋጡትን ሀ/ስብከት  በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስነት ስም ተመልሰው ባልያዙም ነበር። በዚህ ዘመን ከሰጪም፤ ከተቀባይም ኅሊና የሚባል ነገር ስለጠፋ እያየነው ያለው ሊሆን ግድ ሆነ።
በአዲስ አባ ሀስብከት ውስጥ መልካም አስተዳደር እንዲመጣ ካስፈለገ ያለው አማራጭ የአባ እስጢፋኖስ ከቦታው ማስነሳት ብቻ ነው። የተባለውም መዋቅር ጥናት እንደአዲስ ከሚታይ በስተቀር በእሳቸው አስፈጻሚነትና በማኅበሩ ገፊነት ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም። /ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ/ ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም።
አባ እስጢፋኖስ የጎንደር ተወላጅ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎችንና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቃነ መናብርትን በደጋፊነት በማሰለፍ በማቅ የተዘጋጀውን የመዋቅራዊ ለውጥ በተግባር ላይ ለማዋልና ከጀርባቸው ያለውን አሳፋሪ ታሪክ ለመደበቅ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡
አቡነ እስጢፋኖስ የአዲስ አበባ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት በ1990ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት በእሳቸው ድጋፍ የድራፍት ቡድን በማቋቋም አዲስ አበባን ሲያውኳት እንደነበር ቀደምት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ ያን ጊዜ ስያሜውን ያገኘው የድራፍት ቡድን አባ እስጢፋኖስን ቤተክርስቲያን ወንበር ላይ በስራ አስኪያጅነት አስቀምጦ በከተማዋ በሚገኙ ዝነኛ ሆቴሎች በመቀመጥ ቅጥር ዝውውርና እድገት በመስተት መላውን የቤተክርስቲያኒቱ ሰራተኞች ሲያበጣብጥ በወቅቱ በጉዳዩ መንግሥት እጁን አስገብቶ እሳቸውንም ከኃላፊነታቸው ድራፍት ቡድኑንም ከጣልቃ ገብነቱ በመግታት በወቅቱ ሰላም ተገኝቶ ቆይቷል፡፡ ታሪክ እራሱን ይደግማል እንደሚባለው ዛሬም ሳይገባቸው ያገኙትን አስኬማ ለዚሁ ሰላም አደፍራሽ ለሆነ ተልእኮ በመጠቀም በመላው አዲስ አበባ በመንግሥት ላይ ካኮረፈው የማቅ ቡድን ጋር በመሆን  ዛሬም ቤተክርስቲያኒቱን እያወኩ ይገኛሉ፡፡
በቅርቡ በማቅ ቡድን ራዕይ መሠረት ቤተክርስቲያኗን ለመቆጣጠር  በተዘረጋው ወጥመድ መዋቅራዊ ለውጥ በሚል የተዘረጋው ስውር እስትራቴጂ በግልጽ የቤተክርስቲያኗ ችግር መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ቅዱስ ፓትርያርኩ በማቅ የተዘጋጀው የመዋቅራዊ ጥናት ውድቅ ሁኖ በቤተክርስቲያኗ ሊቃውንት ሁሉን ያማከለ ሕግ እና መመሪያ እንዲወጣ የማቅን የሽብር ሴራ ቀድመው ለተገነዘቡ አገልጋዮች ቃል ገብተው ነበር፡፡ አቡነ እስጢፋኖስ ከቤተክርስቲያኗ ሕግ ውጪ የወለዷቸውንና በየአብያተ ክርስቲያናቱ በቁጥጥር እና ሒሳብ ሹም የቀጠሯቸው ልጆቻቸው ጉዳይ እንዲጣራም ሐሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ ታድያ ይህ አካሄድ ያሰጋቸው አቡነ እስጢፋኖስ በፖለቲካ ምክንያት የተገለሉና አካላቸው ኢትዮጵያ ሆኖ ልባቸው  የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ  ጋር የሆኑ የጎንደር ተወላጅ አለቆችን በመሰብሰብ ይኸው የልጆቻቸው ጉዳይ ተዳፍኖ እንዲቆይና መዋቅራዊ ጥናቱ በተገባር ላይ እንዲውል የእሳቸው ሥላጣን ቆይታን የሚያረጋግጥ ውሳኔ በቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያስወስኑ አደራ በማለት አሰማርተዋቸዋል፡፡ በየትኛውም ወገን አዲሱ መተዳደሪያ ሕግ ተግባራዊ ቢሆን  በሚፈጠረው አለመግባባት ሐገር ሲታመስ ከዚሁ ብጥብጥ ፖለቲካዊ ጥቅም ለማግኘትና የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ ከብጥብጡ መልካም አጋጣሚ እንዲያገኝ ጥረታቸውን በመቀጠል ፓትርያርኩ ድረስ ዘልቀው የአደራ መልእክታቸውን አሰምተዋል፡፡
የአቡነ እስጢፋኖስ የሀገር ልጅና የጥቅም ተሳታፊ የሆነው የአፍሪካ ኅብረቱ ዋና ጸሐፊ አቶ አብርሃም አቧሀይ የእነዚህ የጎንደር ኃይሎች ዋና አደራጅና መሪ ሲሆን እራሳቸውንም የአርበኞች ግንባር ብለው ሰይመው ፓትርያርኩ ዘንድ በመቅረብ የተሰጣቸውን ተልእኮ ለመፈጸም ሞክረዋል፡፡ የጳሳሳት ልብስ ሰፊው ወርቁ አየለ ፤ የየረር ዑራኤል አለቃ ዘማርያም ሙጬ፤ የጃቲ ኪዳነምሕረት አስተዳዳሪ፤ የደብረሲና እግዚአብሔር አብ ምክትል ሊቀ መንበር፤   እና የሰሚት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ አባ ገብረ ስላሴ ከጎንደር ተወላጅ ሊቃነ መናብርቶቻቸው ጋር በመሆን ብዙ ባሉበት ስብሰባ  የአቡነ እስጢፋኖስ ሥልጣን እንዲራዘም ልመናቸውን ለፓትርያርኩ አቅርበዋል፡፡
ከአቡነ እስጢፋኖስ ተቃዋሚዎች ይቅርታ ጠይቀዋል በማለት  አዲስ ፕሮፓጋንዳ በማናፈስ ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማስበርገግ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ እንደ ሌሊት ወፍ ከዚህኛውም ከዚያኛውም ቡድን አለሁ በማለት በመሀል ሰፋሪነት አንዴ ተቃዋሚ ሌላ ጊዜ ደጋፊ አሁን ደግሞ አስታራቂ የሆነውና የቦሌ መድኃኔዓለምን ጸሐፊነት ላለመነጠቅ በሚባዝነው በቀሲስ ሰሎሞን በቀለ አስታራቂነት ይቅርታ የጠየቁት የሲኤምሲ ሚካኤል አለቃ መ/ር ዘካርያስ ሲሆኑ እሳቸውም ይቅርታ የጠየቁት አዲስ በሚሰራው  ካቴድራል ስም የሚገባ ሲሚንቶ  ከንብረት ክፍል ኃላፊዋ ወ/ሮ ሰርክ አዲስ እና ከምክትል ጸሐፊው ፋንታሁን ከሙጨ ወንድም ጋር በመሆን መሸጣቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ በአቡነ እስጢፋኖስ ሰዎች በመያዙ ይህንን እንደመደራደሪያ በመጠቀም አንተም ተው እኔም እተዋለሁ በሚል በአቡነ እስጢፋኖስ የተደረሰ ድራማ መሆኑን ታውቋል፡፡
ለቤተክርስቲያን ለውጥ የሚያስፈልጋት ቢሆንም ለውጡ ሁሉን አቀፍ የሆነና ከቤተክርስቲያኒቱ ሌሎች ሕጎች ጋር የማይጣረስ አዘገጃጀቱም ሁሉን ያሳተፈ እንዲሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪዎችና ሌሎች ሰራተኞች በግልጽ መጠየቃቸው አይዘነጋም፡፡
ጥያቄው መቼም አይቆምም!!