Saturday, May 4, 2013

ለብርሃነ ትንሣዔው በዓል እንኳን አደረሳችሁ!


«ደብዳቤ ከመጻፍ መነጋገር፤ ወደሌላው ጣትን ከመጠቆም ቅድሚያ ራስን ማየት፤ ማኅበራትን ተስፋ ከማድረግም በሥራ ማሳየት ይሻል ነበር»


 
ቅዱስ ፓትርያርኩ ለአቡነ አብርሃም ሰሞኑን የንብረት አስረክብ ደብዳቤ መጻፋቸው ይታወሳል። ቅዱስ ፓትርያርኩ ከዚህ ቀደም የተጻፉትንና የተደረጉትን የጽሁፍ ልውውጦች መነሻ በማድረግ ደብዳቤውን ለመጻፍ መቻላቸውን እንጂ በእርሳቸው ደረጃ አቡነ አብርሃም ለምን እስካሁን እንዳላስረከቡ ወይም ለማስረከብም ይሁን ላለማስረከብ ያበቃቸውን ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ለማወቅ ያደረጉት ውይይትም ይሁን ንግግር ስለመኖሩ በተጻፈው ደብዳቤ ውስጥ ምንም አልተገለጸም። ደብዳቤውን ለመጻፍ የሚያበቁ አሳማኝ ምክንያቶች መኖራቸው ቢታመንም እንኳን አቡኑን አስጠርቶ በአካል በማወያየት እሺታቸውን ይሁን እምቢታቸውን መረዳቱ የበለጠ ተቀራርቦ የመሥራት ምልክት መሆን በቻለ ነበር። የፓትርያርኩም  አዲስ የሥራ መንፈስ መሆኑን ለመረዳትም እድል እናገኝበት ነበር። ከዚህ አንጻር ፓትርያርኩ ነገሮችን በማርገብ ተወያይቶና አወያይቶ ለችግሮች የቅድሚያ መፍትሄ አምጪ መንገዶችን ለመከተል ገና ብዙ ይቀራቸዋል ብለን እንገምታለን።

Thursday, May 2, 2013

ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአል!





ዕብራውያን     פֶּסַח» ፔሳኽ» ይሉታል። ፋሲካ ማለት ነው።  በወርኀ ኒሳን በዐሥራ ዐምስተኛው ቀን ይከበራል። ሥርዓቱ የሚጀመረው በዐሥራ አራተኛው ቀን ዋዜማ ሲሆን በፋሲካው ሳምንት እርሾ የገባበት ምንም ዓይነት ምግብ መመገብ ክልክል ነው።ዕለቱን ተቦክቶ ወዲያው የሚጋገር እንጂ የኮመጠጠ ወይም የቦካና የዋለ፤ያደረ መመገብ በሕጉ እንደተቀመጠው ከእስራኤል አንድነት ያስወግዳል። ከማንኛውም እርድ ላይ ጥሬ መብላት ወይም ከበሉትም አስተርፎ ማሳደር አይፈቀድም። ለመስዋዕት የሚቀርበው የበግ ወይም የፍየል መስዋዕትም እድሜው ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ጤናማና የተመረጠ መሆን ይገባዋል። በዐሥራ ዐራተኛው ቀን ምሽት መስዋዕቱ ይታረዳል።ሥጋውን ደግሞ ሌሊት  ከመራራ ቅጠል ጋር ቀላልቅለው ይበሉታል።