Wednesday, February 13, 2013

ኢትዮጵያን ወደ እስልምና ሀገር ለመቀየር ከሃሳብ ያለፈ እንቅስቃሴ አለ!

                                         የዐረብ ሊግ ሀገራት ካርታ
(ክፍል አንድ )
ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ከፊውዳላዊ ወደ ሶሻሊስታዊ፤ ከዚያም የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መርህ  በመረከቡ  ሀገሪቱ በአዙሪት ቅብብሎሽ እየተናጠች በመዝለቋ የተነሳ ሕዝቡ የኖረበትን የዝብርቅርቅ ፖለቲካ አመለካከት ባለቤት ሆኖ መገኘቱ የሚካድ አይደለም። ከዚህም ውስጥ አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን የኢህአዴግ «የአብዮታዊ ዴሞክራሲን» ጽንሰ ሃሳብ  ብዙዎች የማይቀበሉት ፍልስፍና መሆኑም እውነት ነው። ይህ ሲባል አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለራሱ ጥቅም ይሁን ተጨቁኗል ለተባለው ወገን ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት የፖለቲካ ትረካው ለጊዜው ይቆየንና በዚህ በአብዮታዊ ፍልስፍና ተጠቃሚ የሆኑ ክፍሎች መኖራቸውን ግን አሌ ልንለው የማንችለው ሐቅ ነው።  ከእነዚህ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ፍልስፍና ግንባር ቀደም ተጠቃሚ ከሆኑት የሀገሪቱ ዜጎች መካከል የእስልምና ሃይማኖት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ይህ መብትን የመጠቀም መርህ መልካምነቱ እንዳለ ሆኖ የመብት አጠቃቀም ልዩነቱ የሚነሳው አብዮታዊ ዲሞክራሲ ይህን በሃይማኖት የመጠቀም መብትን ለእስላሞቹ የሰጠበት ስልትና ጥበብ፤ መብታቸውን ገቢር ለማድረግ አጋጣሚውን ከተጠቀሙበት ከእስላሞቹ ዓላማና ግብ ጋር ሰፊ ልዩነት ያለው የመሆኑ ጉዳይ ነው። የአብዮታዊው ዲሞክራሲ ስልት በተረጋገጠው የእስላሞች መብት የተነሳ እስላሞቹን በዚህ ፍልስፍና በማጥመቅ የኃይል ድጋፍ የማግኘት ጥበብ ሲሆን እስላሞቹ ደግሞ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ፍልስፍና ውስጥ መብትን እየተጠቀሙ የሚገኙት አብዮታዊውን ወደ እስልምናዊ ፍልስፍና የመቀየር መንገድ እንደነበራቸው የተጓዙባቸው የሁለት አሥርት ዓመታት ጉዞዎች ፍንትው አድርጎ የሚያሳየን ሁለቱም ሄደው ሄደው አሁን የደረሱበት የመጠጋገብ የእድገት ደረጃ ነው። ዛሬ እየታየ ያለው የአክራሪዎችና የመንግሥት እሰጥ አገባ መሠረቱ የሁለቱ ፈላስፋዎች የጉዞ መቋጫ «የደረስኩብህና የነቃህብኝ» ዓይነት ድብብቆሽ ከመነሻው ዲሞክራሲን በመስጠትና ዲሞክራሲን በመተግበር ሁለት የተለያዩ ቡድኖች እንደነበሩ የሚያረጋግጥልን ነው።

 ሌላው ነጥብ ፖለቲካዊ ጥቅሙን በማስላት ይሁን ለሃይማኖቶች መከበር ከሃይማኖተኞቹ  በላይ ሃይማኖተኛ  የመሆን ያለመሆኑ የመንግሥት  አቋሙ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ የማይካደው ነገር ቢኖር ኢህአዴግ እንደማንኛውም እምነት ለእስልምናው ሃይማኖት መከበር ትልቅ መብት የመስጠቱ ነገር ጉዳይ ነው። እንዲያውም እስልምናውን ከማንም በላይ በመሸከም በአክራሪዎች የግድያ፤ የማቃጠልና የማሳደድ እርምጃ በኦርቶዶክሱና በሌላው ላይ ሲወሰድ ዝምታን የመረጠበትና ጉዳዩን በማለዘብ ሌሎቹን ዝም እያሰኘ ሲያረግብ መቆየቱም መንግሥት ሲነቀፍበት ቆይቷል።  ሌላው ቀርቶ የመንግሥት ሹመኛው አሊ አብዶ የተባለው የእስልምና አክራሪዎች አባት በአዲስ አበባ ከንቲባነቱ የሕዝብን የልማት ሥራ ወደጎን በመተው በመስጊድ ልማት ላይ ጊዜውን የመፈጸሙ ነገር ኢህአዴግ የእስላሙን ልብ ለማግኘት የተጓዘበት መንገድ ተደርጎ መቆጠሩም መዘንጋት የለበትም።  በአሁኑ ወቅት  በአክራሪዎችና በኢህአዴግ መካከል ያለውን የዓይጥና የድመት ሩጫ ተከትሎ ፤በመግቢያችን ላይ ለመጠቆም እንደወደድነው ለዓመታት በተለያየ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተናጠው ትውልድ የአብዮታዊ ዲሞክራሲን ፍልስፍና በመጥላቱ ብቻ «የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው» ከሚል ስንኩል እሳቤ የተነሳ እስልምናው እንደተጨቆነና አብዮታዊ ዲሞክራሲ መብቱን እንደጨፈለቀው በመቁጠር ድጋፍን ለማሳየት የመሞከሩን ነገር ስንመለከት እጅግ ያስገርማል። ያሳዝናልም። ኢህአዴግን መጥላት አንድ ነገር ነው። በእስልምና ፍቅር መቃጠል ደግሞ ሌላ ነገር ነው። በኢህአዴግ የሥልጣን ዘመናት ሁሉ ከኢህአዴግ ጋር ቆሞ የነበረው የእስልምናው አክራሪ ክፍል የእድገቱን ደረጃ በጨረሰበት ወቅት ላይ ወደመላተም ሲደርስ በመመልከት «የጠላትህ ጠላት ወዳጄ ነው» የሚለው ያረጀ ፈሊጥ የትም አያደርስም። እውነታውንም አይለውጥም።  እውን የእስላሞች የሃይማኖት መብት በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፍልስፍና አልተከበረም?  የእስልምና መብቶች ከሌሎች ሃይማኖቶች መብት ያነሰ ነበር?  ኢህአዴግን ከሌሎቹ በተለይም ከኦርቶዶክሶች በላይ በተለጠጠ መብት ሲያባልገው አልቆየም? ኢህአዴግ ለእስላም ኢትዮጵያውያን የሰጠው ወሰን አልባ መብት ከሚያስነቅፈው በቀር የእስላሞችን መብት በመደፍጠጥ እንደጨቆነ አድርጎ መናገር ያስተዛዝባል።  ኢህአዴግ አንባገነን ይሁን ወይም በእስላሞች ጉዳይ እጁን ያስገባ፤ አያስገባ አንድ ነገር ሆኖ  ከሌላው ሃይማኖቶች በተለየ እስልምና ተጨቁኗል የሚለው አባባል ሚዛን የሚደፋ አይደለም። እንደእውነቱ ከሆነ ምዕራብ አፍሪካን እያመሰሰ ያለው አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ ውስጥ የጦርነት ዘመቻውን አልጀመረም ካልሆነ በስተቀር ሃይማኖታዊ መብቱ ተረግጧል በማለት የፖለቲካ ኅብረት ለማድረግ መስማማት የሚያሳየው የኢህአዴግን ብልግና ሳይሆን ፖለቲካ የሚባለው የሀሰት ፍልስፍና እየቆሸሸ መምጣቱን ነው። በምድር ላይ ያለው እውነታ ግን ከዐረብ ሀገራት እስከ ኢትዮጵያውያ ድረስ የአክራሪ ሙስሊሞች እንቅስቃሴውና የትስስሩ ዘመቻ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያን የ«ዲን አልኢስላም» ሀገር ለማድረግ እርግጥ የመሆኑ ጉዳይ ብዙ የተባለለት ስለሆነ ፖለቲካ ሀቁን አይለውጠውም።

በኢትዮጵያ ውስጥ ኢስላማይዜሽን እየተገለጠባቸው ያሉትን መንገዶች መመልከት ይቻላል፤ ዋና ዋናዎቹ፤

1/ የክርስትናውን ሃይማኖት በመንቀፍ፤ በማንቋሸሽ፤ በመተች መጻሕፍትን ማሳተም፤ ማሰራጨት

2/ የወሀቢዝም መፈልፈያ መድረሳዎችን በሀገር ውስጥ መክፈትና ማሰልጠን

3/ በአክራሪ ሀገራት በሚሰጠው የአክራሪነት ትምህርት መጠመቅ፤ የማስፋፊያ የወታደራዊ ስልትን መማር፤

4/ በተለያዩ ስፍራዎች ትንኮሳዎችን በመፍጠር፤ አጋጣሚዎችን መጠቀም

5/ ባያምኑበትም ባለው ፖለቲካዊ ተቋም ውስጥ አማኞቻቸውን በመሰግሰግ መብትና ጥቅምን ለማስከበር ስልጣን መቆጣጠር

6/ ኢኮኖሚያዊ አቅም የሌላቸውን የሌላ እምነት ሰዎችን በጥቅም መለወጥ ወይም በጋብቻ ምክንያት ማስለም

7/ ግልጽ የሆነ ጫና እስካልመጣ ድረስ መንግሥትን በመደገፍ ስልታዊ እንቅስቃሴን ማስፋፋት

8/ የእስልምናው ቁጥር ከክርስቲያኑ እንደሚበልጥ የተሳሳተ መረጃ በማውጣት፤ ሸሪአን ለኢትዮጵያ ማወጅ

የመሳሰሉትን መንገዶችን በመተግበር በዲሞክራሲው ሽፋን ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሰራ ቆይቷል።

Monday, February 11, 2013

ምንኩስናና ወንጌል ይተዋወቃሉ?

በድንግልና ሕይወት እግዚአብሔርን ስለ ማገልገል መጽሐፍ ቅዱስ በሚገባ ያስተምራል። ማቴ 19፤10-  1ቆሮ 7፤25-39   ጥያቄው ግን «ድንግልናና ምንኩስና አንድ ናቸውን?» የሚለው ጥያቄ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በድንግልና የኖሩና በድንግልናም ስለመኖር የተናገረበት መንፈስ መነኩሴ ስለመባሉ ምንም ያለው ነገር የለም። ምንኩስናን ደናግላን ብቻ ሳይሆኑ መአስባንም /ባለትዳሮችም/ የሚከተሉት ህግ ነው። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ስለደንግልና ከሚናገረው ሃሳብ ጋር የምንኩስና ህግ ምንም ግንኙነት እንደሌለው ነው።  ምንኩስና በጫካና በበረሃ ኑር የሚልን ልምምድ የሚያስተምር ሲሆን ወንጌል ግን ለእግዚአብሔር ቃል መስፋፋት ያለጋብቻ በድንግልና መኖር ጠቃሚ እንደሆነ እንጂ ወደጫካ መሄድ አስፈላጊ ስለመሆኑ አያስተምርም። 
ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ድንግልናን የሚደግፈው፤


1/ በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ጥሪ መሠረት ለአገልግሎት ራሳቸውን የለዩ ማለትም እግዚአብሔርን ለማገልገል ብለው ሃሳባቸውን በዚህ ዓለም የትዳር ፈተና /ሚስትና ልጆችን በመውለድ/ ምክንያት ልባቸው ተከፍሎ የእግዚአብሔር መንግሥት መስፋፋት ሥራ እንዳይተጓጎል የሚያደርጉት ውሳኔ ነው። /እንደሐዋርያው ጳውሎስ ማለት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ለወንጌል አገልግሎት የተለየና በድንግልና የኖረ ሰው እንጂ መነኩሴ አልነበረም/

2/  በተፈጥሮ ጃንደረባ የሆኑ ወይም ሰዎች ጃንደረባ ያደረጓቸው ከትዳርና ልጅ ከመውለድ ሕይወት ጋር የተራራቁ ስለሚሆኑ ራሳቸውን በድንግልና ሕይወት ውስጥ መኖር እንደሚችሉ ሲያገነዝበን ይታያል።


እንደመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ከዚህ ውጪ ሰዎች በድንግልና እንዲኖሩ የሚገደዱበት መንገድ የለም። ይሁን እንጂ ምንኩስና የሚባለው ሕግ ለደኅንነት፤ ለጽድቅና መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ተብሎ በድንግልና መኖርን የሚሰብክ መንገድ ነው። ይህ መንገድ የሰዎች ህግ እንጂ የእግዚአብሔር ቃል መሠረትነት የሌለው ለጽድቅና ለመዳን የሚደረግበት የትግል መድረክ በመሆኑ በልዩ ልዩ ፈተናና ውድቀት ውስጥ የሚታለፍበት መንገድ መሆኑም እርግጥ ነው።  ይህም «የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም» ያለው ቃል እንደተፈጸመ ያሳያል። ሮሜ 10፤3 ምክንያቱም ጽድቅ በክርስቶስ ደም የተሰጠንና በእምነት የምንቀበለው ስጦታ እንጂ እኛ በምናደርገው ተጋድሎ የሚገኝ አይደለም። በእምነት የተቀበለውን ጽድቅ  ሥራ ከመጠበቅ ውጪ በጥረት የሚመጣ አይደለም። ሮሜ 5፤16 ኤፌ 4፤24

 በኢትዮጵያ ውስጥ ይሁን በዓለም አቀፍ ሃይማኖቶች ውስጥ እየታየ ያለው የምንኩስና አስነዋሪና የፈቲው ውድቀቶች እየጎሉ በመምጣታቸው የተነሳ በትግል የማይወጡት መሆኑን መነሻም በትግል ጽድቅ ለመስራት የመሞከር ውጤት ነው። 
ዓለማውያኑን በመፈወስና ከእውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል በማገናኘት ወደዘላለማዊው መንገድ መምራት የሚገባቸው ሰዎች ለመጽደቅ የተመረጠው መንገድ ምንኩስና ነው በማለታቸው ሰባኪና መምህር ጠፍቶ ዓለማውያኑ ከእውቀት ማነስ የተነሳ በኃጢአት ውስጥ በመኖር በመነኮሳቱ የጽድቅ ስራ ላይ የመዳን ተስፋ እንዳላቸው እንዲያስቡ ተደርገዋል። ዛሬም በመነኮሳቱ የቀደመ ሥራ ላይ ተስፋን በማድረግ አማልዱኝ የሚሉ ድምጾች የመብዛታቸው ምክንያት ይሄው ነው። ክንፍ የበቀለበት ቀን፤ እግር የተቆረጠበት እለት፤ መሬት የቀደዱበትና ሱራፌል የሆኑበት መዓልት እያሉ በየገዳማቱ እየዞሩ በጸሎትዎ ያስቡኝ፤ ጻድቁ አይርሱኝ የሚለው ልመና መሠረቱ መነኮሳቱ በሥራቸው ጸድቀው፤ያጸድቃሉ፤ እኔ ግን ኃጢአቴ ብዙ ስለሆነ የመዳን ተስፋዬ የመነመነ ነው ከሚል አስተሳሰብ የመነጨ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል። የክርስትና ጽድቅ ክርስቶስ እንደሆነ የዝንጋዔ ልቡና በሕዝቡ ውስጥ ያሰረጸው ይህ ምንኩስና የሚሉት ፍልስፍና ነው። «ወንጌል ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ» ሲል የክርስቶስን የማዳን መንገድ የሚከተሉ ማለቱ እንጂ በመነኮሳት ተጋድሎ ላይ የሚንጠላጠሉ ማለቱ አልነበረም። ጽድቅ በሰው ልጆች ትግልና ውጣ ውረድ የሚመጣ ቢሆን ኖሮ ሐዋርያው « እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ» ሮሜ 5፤18 ባላለም ነበር። 


የምንኩስና መስራቾች የ4ኛው ክ/ዘመን ግብጻውያን ሰዎች መሆናቸው እርግጥ ነው። እነዚህ ሰዎች ጀምረውታል ከመባሉ ከ4ኛው ክ/ዘመን በፊት በቤተክርቲያን ውስጥ እንዳልነበረ ይታወቃል። ድንግልናን በመከተል ይሁን መአስብነትን በመተው ከምንኩስና ሕግ ጋር የመስማማት መሠረቱ በአንዳንዶች በኩል የዓለማዊ አስተሳሰብ ወደቤተክርስቲያን በመግባቱ የፈጠረባቸውን ሃዘን ለመሸሽ፤ አንዳንዶቹም ዓለማዊው ኑሮ አስቸጋሪ ሲሆንባቸው ከዚህ ለመገላገል፤ ሌሎቹም የመኖር ተስፋቸው ሲሟጠጥ «ሄጄ እዚያው ልሙት» ከሚል አስተሳሰብ የተነሳ እንደሆነ ከምንኩስናው መጽሐፍ ስንረዳ ሰው ሰራሽነቱን ያጎላዋል።  ሥርዓቱን ቤተኛ ያደረጉት ሰዎች ተዋጽዖ «አባ በእንተ ነፍሱ፤ አባ በእንተ ከርሱና አባ በእንተ ልብሱ» ናቸው። የምንኩስና የሕይወት መገለጫዎች መሆናቸውን መናገሩ የምንኩስናን መሠረት ሰዋዊ ሥርዓት መሆኑን እንደማሳያ መውሰድ ይቻላል። ምንም እንኳን «አባ በእንተ ነፍሱ» የተባለው እጸድቅበታለሁ ብሎ ቢገባበትም ጽድቅ የሰው ልጆች ትግል ገጸ በረከት ስላይደለች ዓላማው መንገዱን የሳተ ከመሆን አያልፍም።

በመሠረቱ ምንኩስና የመጽሐፍ ቅዱሱ ድንግልናዊ ሕይወት መገለጫ  አይደለም። ከላይ እንደጠቆምነው ምንኩስና ባለትዳሮችም ትዳር በኋላ ሊከተሉት የሚችሉት መንገድ ስለሆነ ግንኙነት የለውም። ምንኩስና ከመጽሐፍ ቅዱሱ ቃል ጋር ራሱን በማስጠጋትና መንፈሳዊ ምስል በመቀባት ቤተክርስቲያን ውስጥ የተተከለ ሰው ሰራሽ ስርዓት ነው። የተፈጠረበት ዓመተ ምህረት እንደሚያስረዳው አመጣጡ ከቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል ይልቅ የግኖስቲኮች ጋር ሲስማማ ይገኛል። ውርርሱም ከሂንዱይዝም፤ ቡድሂዝምና ዞሮአስተራኒዝም ጋር ነው።  ምንኩስና የሚባለው ስርዓት በ4ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ ሳይተከል ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረ ስርዓት ነው። ወንጌል ደግሞ አዲስ የሕይወት መንገድ እንጂ የቡድሂዝምን የምንኩስና ስርዓት አስፈጻሚ ባለመሆኑ አንድም ቦታ የዚህን ስርዓት ጠቃሚነትና አስፈላጊነት አልተናገረም። ስለሆነም ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረው ይህ ሥርዓት የክርስትናን መልክና ቅርጽ ይዞ በግብጽ በኩል ወደ ዓለም ሊሰራጭ በቅቷል።
 ይህች ግብጽ ለዓለም ያበረከተችው ይህንን ብቻ አይደለም። የእስላሙን መስራች መሐመድን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አጣምመው ያስተማሩት መነኩሴ ግብጻዊ እንደነበሩ ታሪክ ይናገራል። የቶማስ ወንጌል፤ የማርያም መግደላዊት ወንጌል፤ የባርናባስ ወንጌል፤ የይሁዳ /ሰያጤ እግዚኡ/ ወንጌልን ጽፈው ለዓለም አበርክተዋል። እነዚህ መጻሕፍት እንደቤተክርስቲያን ቅዱሳት ባይቆጠሩም ለብዙዎች መሰናከያ ሆነዋል። ግብጻውያኑ ብዙ የክህደትና የፍልስፍና መጻሕፍት ምንጮችም ነበሩ። ከዚህ የተነሳ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የነበረውን የምንኩስና ሥርዓት ጎትተው በማምጣት ክርስቲያናዊ መልክ ቀብተው በዓለም ቢያስፋፉት ብዙም አያስገርምም። አሳዛኙ ነገር ዓለሙ ሁሉ ይህንን ስርዓት መጽሐፍ ቅዱሳዊ አድርጎ በመቁጠር የወንጌል ዘመን አዲስ ግኝት አድርጎ በህግ መተግበሩ ነው።  
 የምንኩስና ሕግጋት የምሥራቃውያንን ሃይማኖቶች የተከተለ ስርዓት ነው። ቢጫ መልበስ፤ መቁጠሪያ መቁጠርና መሬት ላይ እየወደቁና እየተነሱ መስገድ ከክርስትና መምጣት 500 ዓመት በፊት ሲደረግ የመቆየቱ ነገር ዛሬም ይኼው ስርዓት ከክርስትናው ጋር በተመሳሳይ መልኩ ይከናወናል። እንጨት አለዝቦ፤ ቅርጽ ቀርጾ፤ በሚያስቡት የኅሊና ፍላጎት መልኩ መላእክትን፤ የሚያመልኩትን ጌታ ስእል ስሎ፤ እጣን ማጠንና ለእነሱም መስገድ የቡድሂዝም ቀደምት እምነት መሠረቶች ናቸው። ይህንኑ ድርጊት በክርስትናው ዓለም ያስፋፉት እነዚሁ የቡድሂዝምና ሂንዱይዝም ቅጂ ግብጻውያን መነኮሳት ስለመሆናቸው የድርጊቱ ተወራራሽነት አመላካች ነው። ቅድመ ክርስትና ሲመለክ የነበረው የሂንዲዎቹ የሎርድ ሺቫ ወይም ቪሽኑ ስእል ከክርስትና ብዙ ስእሎች የሚለየው የመስቀል ምልክት አለመያዙ ብቻ ነው።
                           የቡድሂዝም የሎርድ ቪዥኑ ስእልበቅዱሳን አማልክቱ ተከቦ

 ነገሮችን ለማስረዳት ወይም ለማስገንዘብ አንድን ቅርጽ ወይም ምስል መጠቀም ጥሩ ቢሆንም ወደአምልኮና ስግደት ቀይሮ አንዳች ነገር በእሱ በኩል እንዲከናወንልን መጠበቅ ግን የክርስትና ትምህርት አይደለም።

ጉዶ ሪኒ የተባለው ካቶሊካዊ ሰዓሊ በ1636 ዓ/ም በኅሊናው ቀርጾ በስእል ያስቀመጠው፤ አንድ የዘመኑን ባለጡንቻ ስፖርተኛ የሚመስል፤ ራሰ በራ ሰው እሱ ይሆናል ብሎ ያሰበው ሚካኤል መልአክ በላዩ ላይ ቆሞበት  የሳለው ስእል ዛሬ በገበያ ላይ በጣም ተፈላጊ ነው። ተፈላጊነቱም ክርስቲያን ነን የሚሉቱ ሰዎች ከፊት ለፊታቸው አስቀምጠው እየወደቁ በመነሳት በመስገድ ከምስሉ የመልስ ተስፋ መጠበቅ ሚካኤል ለሚሉት የራሳቸው ስሜት የሚያቀርቡት ልመና  እጅግ አሳዛኝ ነው። ይህ ሁሉ ሰባኪ የመጥፋቱና የእግዚአብሔር ቃል ለሰዎች ሁሉ በእውነት ያለመገለጡ ችግር መሆኑን ማንም አይክድም።  ሪኒ ራሱ ስእሉን የሳለው የችሎታውን ውጤት በማስመሰል ለማሳየት እንጂ እንዲሰገድበት ወይም ያየው እውነተኛ ነገር ሆኖ አልነበረም።

ጉዶ ሪኒ በ1636 ዓ/ም የሳለው ስእል

Thursday, February 7, 2013

ሰበር ዜና፦ የ6ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ቀን ተወሰነ!



የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የ6ኛውን ፓትርያርክ ምርጫ የካቲት 21/2005 ዓ/ም ለማካሄድ  መወሰኑን ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።


ቅዱስ ሲኖዶሱ ዛሬ ጥር 30/2005 ዓ/ም ባደረገው  አስቸኳይ ጉባዔ ላይ ያሳለፈው ውሳኔ እንደጠቆመው ለምርጫው ሂደት የተሰየሙት አስመራጮች በሚያቀርቡት ተመራጮች ላይ ድምጽ በመስጠት የ6ኛውን ፓትርያርክ ምርጫ ለማከናወን እንዲቻል አስፈላጊው ሁሉ ከወዲሁ እንዲደረግ ትእዛዝ መስጠቱም ታውቋል።

ከሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል የሚያጉረመርሙና ባለተራዎች ነን እስከሚሉቱ ድረስ የተወሰነ መሳሳብ ውስጥ ውስጡን የነበረ ቢሆንም ይህንን ክፍተት ለመሙላት ምንም እንዳልተፈጠረ ለማድረግ በተወሰኑ የነጻ ሚዲያ ዘገባዎች ላይ የክስ ፋይል በመክፈት ዝም የማሰኘቱ ሂደትና መረጃዎች እንዳይሾልኩ ለመከላከል የተወሰዱት እርምጃዎች በተወሰኑ መልኩ ውጤታማ መሆናቸው ታይቷል። አንዳንዶቹ ጳጳሳት ለቤተክርስቲያኗ ከማሰብ ይልቅ እኔ ወይም እኛ እያለን፤ እነ እገሌ ፓትርያርክ ሊሆኑ ነው? ከሚል የቅናት መሰል በትር የተነሳ ስብሰባ በመርገጥ ወይም በስብሰባው አንገኝም ከሚል የደጋፊ  ፍለጋ እምቢታ ድረስ ቢጓዙም ያሰቡትና የተመኙት ሊሳካ ሳይችል ቀርቶ የምርጫው ሂደት አይቀሬ ስለመሆኑ የተሰጠው ውሳኔ አረጋግጧል።

ሲኖዶሱ ያቋቋመው የአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 30 ቀን 2005 .. በመንበረ ፓትርያርክ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ የካቲት 21 ቀን ለሚፈጸመው የፓትርያርክ ምርጫ የሚቀርቡት አምስት ዕጩ ፓትርያርኮች የካቲት 18 ቀን ለሕዝብ ይፋ ይሆናሉ፡፡