Saturday, November 26, 2011

ይድረስ ለቀሲስ ደጀኔ!!


«እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው»በማለት በብሎግዎ ላይ ጽፈዋል። ገረመኝና አንዳንድ ጥያቄዎችና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎችን አቀረብኩልዎ!!
ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው- ይህንን ከየትኛው መጽሐፍ ላይ አገኙት? ሚካኤል ነው የሚል ተጽፏል? ወይስ ነገረ ሥራው ሚካኤልን ይመስላል ብለው ያልተገለጸውን አቅኚ ሆነው ነው? እግዚአብሔር ሚካኤል ስለመሆኑ ያልገለጸው ረስቶ ወይም ተሳስቶ እርስዎ ግን በትርጉም ፈትተውት ያገኙት እውቀት ነው?
መቼም እንደማይቀበሉኝ አውቃለሁ፣ እኔን ሳይሆን ለዚያውም መጽሐፍ ቅዱስን።
ዘፍ  21፥17
    31፥11
     48፥16
ዘጸ  3፥2
    14፥19
    33፥1-3
ዘኁ  22፥22 - 22፥23 - 22፥24 - 22፥25 - 22፥26 - 22፥27 - 22፥31   -  22፥32    22፥34   22፥35  
አንድም ቦታ ሚካኤል የሚል ስም ተጠቅሶ አይገኝም። እግዚአብሔር ስሙን ያልጠቀሰው ለምን ይመስልዎታል? እኛስ ስሙን መጥቀስ ለምን ይገባናል? የኛ መጥቀስ እግዚአብሔር ያልጠቀሰውን ጉድለት ለመሙላት ነው ወይስ ስውር  የሆነውን ሚካኤል በትርጉማችን ገልጸን በማውጣት መልአኩን ለማክበር?
ለዚያውም ስሙ ባልተገለጸ መልአክ እጅ እግዚአብሔር ያደረገውን ድንቅና ተአምራት ለሚካኤል ለመስጠት «እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው» ማለት በፍጹም ትልቅ ስህተትና ክህደት ነው።
 እርስዎ እግዚአብሔር ያለውን ለምን መተው ይወዳሉ?
 ዘፍ 28፣15 «እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና»
 ዘጸ 6፣6 «ስለዚህም ለእስራኤል ልጆች እንዲህ በላቸው። እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከግብፃውያንም ባርነት አወጣችኋለሁ፥ ከተገዥነታቸውም አድናችኋለሁ በተዘረጋ ክንድ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ»

ዘጸ 6፣7ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ፥ አምላክም እሆናችኋለሁ እኔም ከግብፃውያን ባርነት ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።

ዘጸ 6፣8 «ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም እሰጣት ዘንድ ወደ ማልሁባት ምድር አገባችኋለሁ እርስዋንም ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘጸ 10፣3 «ሙሴም አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ አሉትም። የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በፊቴ ለመዋረድ እስከ መቼ እንቢ ትላለህ? ያገለግሉኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ»
ዘጸ 13፣21 «በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ፥ ሊያበራላቸውም ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ»
ዘጸ 14፥24
ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ ሆኖ የግብፃውያንን ሠራዊት ተመለከተ፥ የግብፃውያንንም ሠራዊት አወከ። 25 የሰረገሎቹንም መንኰራኵር አሰረ፥ ወደ ጭንቅም አገባቸው ግብፃውያንም። እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ይዋጋላቸዋልና ከእስራኤል ፊት እንሽሽ አሉ»
ዘጸ 15፥3 «እግዚአብሔር ተዋጊ ነው፥ ስሙም እግዚአብሔር ነው»
ዘጸ 16፥15
የእስራኤልም ልጆች ባዩት ጊዜ ያ ምን እንደ ሆነ አላወቁምና እርስ በእርሳቸው። ይህ ምንድር ነው? ተባባሉ። ሙሴም፦ ትበሉት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣችሁ እንጀራ ነው»
ከብዙ በጥቂቱ እስራኤል ዘሥጋን የመገባቸው፣የጠበቃቸው፣ያሻገራቸው፣ የጋረዳቸው እግዚአብሔር እንጂ እርስዎ እንዳሉት ሚካኤል የሚባል መልአክ አይደለም።  
ዘሌ20፥24 ነገር ግን እናንተን፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ። እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘዳ 26፣8 እግዚአብሔርም በጸናች እጅና በተዘረጋ ክንድ፥ በታላቅም ድንጋጤ፥ በተአምራትም፥ በድንቅም ከግብፅ አወጣን
ዘዳ 26፣9 ወደዚህም ስፍራ አገባን፥ ወተትና ማር የምታፈስሰውንም ይህችን ምድር ሰጠን።
ቀሲስ- እርስዎ ግን በድፍረት በእግዚአብሔር ላይ ዐምፀው ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ሰጥተው፣ ያሻገራቸው፤ መናን የመገባቸው፣ ወተትና ማር የምታፈሰውን ሀገር ያወረሳቸው ሚካኤል ነው ይላሉ። እግዚአብሔር እኔ ነኝ እያለ እርስዎ ግን የለም ሚካኤል ነው ማለትዎ ለምን ይሆን? ላልተገለጠ መልአክ ክብሩን ከእግዚአብሔር ላይ ወስደው ሲሰጡ ለእኔ እንደተደረገ ይቆጠራል የሚል ይመስልዎት ይሆን? ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ክብሩን ሁሉ መስጠትዎ ሳያንስ ሌሎችም ይህንኑ ስህተትዎን እንዲቀበሉና ፊታቸውን ወዳልተነገረውና እግዚአብሔር ወዳልገለጸው መልአክ እንዲመልሱ ማስተማርዎ ያሳዝናል !! በዘለበ ምላስ የሚናገሩትና የሚጽፉትን ለራስዎ እንዲመች ተርጉመው የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ማጣመምዎ ለምንድነው?
ምናልባት እግዚአብሔር ይቅር ቢልዎ ንስሐ ይግቡበት!! ምክንያቱም እኔ ሰራሁ ያለውን ላልተጻፈ መልአክ ሰጥተው፣ አስቀንተውታልና!!
እርስዎ እግዚአብሔር ያደረገውን ተአምራት ሁሉ ለሌላ አውለው እንዳስቀኑት ሰዎች ሆነዋል።
ዘኁ 14፣22-23 በግብፅ ምድርና በምድረ በዳ ያደረግሁትን ተአምራቴንና ክብሬን ያዩ እነዚህ ሰዎች ሁሉ አሥር ጊዜ ስለ ተፈታተኑኝ፥
 ነገሬንም ስላልሰሙ፥ በእውነት ለአባቶቻቸው የማልሁላቸውን ምድር አያዩም ከእነርሱም የናቀኝ ሰው ሁሉ አያያትም» ይላልና ያስቡበት!!!!!!

Friday, November 25, 2011

እሬት የተቀባ ጡት ማን ይጠባል?



 ሁላችንም ህጻን ልጅ ሆነን አድገን አሁን ካለንበት መድረሳችን እርግጥ ነው። ህጻናትን በተመለከተም ህጻናት ወንድሞችና እህቶችም ይኖሩን ይሆናል። ምናልባትም ህጻናት ልጆች ይኖረንም ይሆናል። ባይኖረን እንኳን ስለህጻናት ያለን እውቀት ትንሽ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ስለህጻናት ማንሳት የወደድኩት «ምርጥ ምርጡን ለህጻናት» የሚል አስተምህሮ ለመስጠት አይደለም። አእምሮአችሁን ለአፍታ ስለህጻናት እንዲያስብና ላነሳ ስለፈለኩት ጉዳይ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ነው።
ጥያቄ ላቅርብላችሁ? ህጻናት ጡት የሚተዉት እንዴት ነው? ጡት የሚጠባ ህጻን ጡት ሲያጣ ወይም ጡት ሲከለክሉት እንዴት ያደርገዋል? መቼም እንደማይስቅና እንደማይፍለቀለቅ አናጣውም። ይነጫነጫል፣ያለቅሳል፤ በአቅሚቲ እናቱን ይቧጥጣል፣ጡት አምጪ ብሎ ይማታል ብንል እውነት ነው። ሲያገኝና ሲጠግብ ደግሞ ጤነኛ እስከሆነ ድረስ ይስቃል፣ይጫወታል። እንዲህ እንዲህ እያለ ሁለትና ሶስት ዓመት ሲሞላው ደግሞ ደግሞ ጡቱን ያስጥሉታል።አራትና አምስት ድረስ የሚጠባ ልጅ እንዳለ ሳይዘነጋ መሆኑን ልብ ይሏል? ጡት የምታስጥል የገጠር እናት ያንን የለመደውን ነገር ለማስጣል ከባድ ይሆንባታል። እንዲጠላው ለማድረግ እሬት ይቀቡታል። ይቆነጥጡታል። ሌላም ነገር እያደረጉ ይከለክሉታል። ይሁን እንጂ የህጻኑ ለቅሶ ሲበረታ ልምድ አደገኛ ነውና እንደገና ያጠቡታል። እንደዚያ እንደዚያ እያደረጉ ምግብ እያቀረቡ፣ጡት እየነፈጉ ከህጻንነት የጡት መጥባት ዓለም ያወጡታል።

Monday, November 21, 2011

የሚያድን ዕይታ


የዘመኑ መስታወት.......



by Dagnu Amde on Friday, November 18, 2011 at 7:11pm

አቤቱ÷ እኔን ለማዳን ተመልከት
አቤቱ÷ እኔን ለመርዳት ፍጠን
(መዝ.69÷ 1)::

በሕይወታችን ብዙ ነገሮችን ዐይተናል፡፡ ዐይተናቸው በውስጣችን የቀሩ፣ ዐይተናቸው የረሳናቸው፣ ዐይተናቸው ደግመን ለማየት ያልፈቀድናቸው፣ ዐይተን እንዳላየ ያለፍናቸው፣ ዐይተን የታዘብናቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ጽጌረዳን ዐይተን እሾህን እናያለን፡፡ የተንሰራፉ አበቦች በአሜከላዎች ላይ ተጐዝጉዘው እናያለን፡፡ ዐይናችን ሁለቱንም ታያለች፡፡ ኅሊና ግን አጥርታና መርጣ ታያለች፡፡ በዐይናችን ብዙ መልካምና ክፉ ነገሮችን እናያለን፡፡ ላየነው ሁሉ ምላሽ መስጠት አያስፈልገንም፡፡ ምላሻችንን የሚፈልጉ ዕይታዎች ግን አሉ፡፡ ማየት ከመስማት በላይ ነው፡፡ ሰምቶ ምላሽ ያልሰጠ ሲያይ ግን ምላሽ ይሰጣል፡፡ ማየት የተግባር አዛዥ ናት፡፡