Wednesday, April 17, 2013

'ማሪያም ነኝ` ባዩዋ ተፈረደባት


በአሸናፊ ደምሴ
ሰንደቅ ጋዜጣ ረቡዕ 9/8/2005 ዓ/ም
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በመንቀሳቀስ ሰዎችን በማታለልእኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌያለሁ፤ ከሞትም ተነስቻለሁ፤ የወለድኳቸውንም ልጆች ያገኘሁት በመንፈስ ነውስትልና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል በሚል የሰዎችን የግል ሀብት ለራሷ ስታደርግ ደርሼባታለሁ ሲል ክስ የመሰርተባት 34 ዓመቷ ትዕግስት ብርሃኑ /ጊዮርጊስ፤ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6 ወንጀል ችሎት ፊት ቀርባ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ 2 ዓመት 4 ወራት ፅኑ እስራትና በአንድ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ወሰነ።
እንደአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ከሆነ ግለሰቧ በአራት የተለያዩ ክሶች የተወነጀለች ሲሆን፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትለሰው ህይወት ማለፍ ሳቢያ ነችሲል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ ያልተሟላ ነው ሲል ውድቅ ሲያደርገው በተቀሩት ሶስት ክሶች ግን ጥፋተኛ ነች ብሎ እንድትከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር።
ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባለችበት አንደኛ ክስ በየካቲትና በመጋቢት ወራት ውስጥ 1999 . የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት አስባ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 21 ልዩ ቦታው ኪዳነምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 300 በላይ ሰዎችን በመሰብሰብእኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌ፤ ከሞትም ተነስቼያለሁየሚል የሀሰት ወሬ በመንዛትና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል ንብረት አያስፈልግም በሚል ያላችሁን ንብረት አምጡ ስትል ከተለያዩ የግል ተበዳዮች ጥሬ ገንዘብና ወርቅ የተቀበለች ሲሆን፤ በአጠቃላይም 40 ብር ለግል ጥቅሟ አውላለች ሲል በክስ መዝገቡ ያስረዳል።

Monday, April 15, 2013

የካናዳዋ፤ ዊኒፔግ ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከገለልተኝነት ወደአሜሪካው ሲኖዶስ ተቀላቀለች።





በካናዳ፤ ዊኒፔግ ከተማ፤ 353ኛው Mountain Ave መስቀለኛ መንገድ ላይ የምትገኘው የደብረ ገነት ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን ለብዙ ጊዜ ከየትኛውም ሲኖዶስ ነጻ ሆና በገለልተኝነት መቆየትዋ ይታወቃል።  ይሁን እንጂ  የቆይታ ጊዜዋን በማጥናትና በአዲስ አበባ ያለውን የሲኖዶስ የምርጫ ሂደት በመገምገም፤ ከእንግዲህ በአንዱ ሲኖዶስ ስር መጠቃለል እንደሚገባት በማመን ካሉት ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት በአቡነ መርቆሬዎስ በሚመራው ሲኖዶስ ስር ለመጠቃለል ወስናለች።

በዚሁ መሠረት እስካሁን እውቅና ሳይሰጡት ለቆዩት የአሜሪካው ሲኖዶስ ሕጋዊ እውቅና በመስጠትና እንደትክክለኛው ሲኖዶስ በመቁጠር መንፈሳዊ ግንኙነቷን እንደምታደርግ በኦፊሴል በመግለጽ መጠቃለሏን የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
የኢትዮጵያውን ሲኖዶስ ሽኩቻና የፓትርያርኩን ምርጫ ሂደት የመንግሥት እጅ አለበት በሚሉ ብዙ ገለልተኛ የዳያስፖራ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ቅሬታ በማሳደሩ እውቅና ወደከለከሉት የአሜሪካው ሲኖዶስ ቀስ በቀስ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። ወደፊትም ይህ ሁኔታ በሌሎቹም ገለልተኛ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ሊኖር እንደሚችል ይገመታል። የአሜሪካው ሲኖዶስም አብያተ ክርስቲያናትን በመንፈሳዊ አገልግሎት የመድረስና ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በየአኅጉረ ስብከቱ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ የማስተማርና የማሳመን የእቅድ መርሐ ግብር ነድፎ የነበረ ሲሆን እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ወደአሜሪካው ሲኖዶስ ቀስ በቀስ መቀላቀል መጀመራቸው የዚህ እቅድ የሥራ ውጤት ይሁን አይሁን ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም።
በደብረ ገነት ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን ውስጥ የገብርኤልም ጽላት በደባልነት እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።
ዊኒፔግ በሀገረ ካናዳ፣ በማኒቶባ ክፍለ-ሀገር የምትገኝ ስትሆን የአየር ንብረቷ ቀዝቃዛና በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ከተማ ናት።