Monday, March 11, 2013

የአቡነ ኤልያስና የአርባ ምንጭ ምዕመናን ውዝግብ!




«በአርባምንጭ የመድኃኔዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ግንባታ ላይ በብፁዕ አቡነ ኤልያስና በምዕመናን መካከል ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በዕርቅ ተደመደመ» 
                               ( http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com)                                                            
በአርባምንጭ ከተማ በመሠራት ላይ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የሰሜን ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ሕዝብን ሳያማክሩ የዲዛይን ለውጥ በማድረጋቸው ምክንያት አለመግባባት ተፈጥሮ ግንባታው መቋረጡን ቀደም ሲል November 16, 2012 ባወጣነው ዘገባ መግለጻችን ይታወሳል፡፡
ለውዝግቡ መነሻ የሆነው የዲዛይን ለውጥ የመነጨው "ማኅበረ ቅዱሳን" ሲሆን "ማኅበሩ" አባሉ የሆነ አንድ ኢንጂነርን ከአዲስ አበባ ልኮ የሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ዲዛይን ባለ አንድ ጉልላት ክብ ሕንፃ እንዲሆንና ቀደም ሲል በሕዝብ ምርጫና ስምምነት ግንባታው ተጀምሮ የነበረው ባለሦስት ጉልላት ሕንፃ ቤተክርስቲያን እንዲቀር በመወሰኑ ነው፡፡

Thursday, March 7, 2013

ግብጽ በአንበጣ መንጋ ተመታች!




በዘመነ ፈርዖን ግብጽን ከመቷት መቅሰፍቶች አንዱ የአንበጣ መንጋ ነበር። የአሁኑ የአንበጣ መንጋ በምን መቅሰፍትነት እንደተላከ ባናውቅም መንጋው ግን በግብጽ ምድር በዓባይ ውሃ የበቀለውን ብዙ ጋሻ መሬት አትክልትና ሰብል ጋጥ አድርጎታል። በየከተማው ውስጥ የተረፈረፈውን የአንበጣ መንጋ ሰብስቦ በማቃጠል ቅርናቱ አያድርስ ሆኗል።
 የግብጽ ፖለቲካ እየተናጠና ሥልጣኑ የእስልምናውን ጽንፍ በሚያራምዱ ክፍሎች የመውደቁ ነገር ተጋግሞ ረብሻና ሁከት ባስከተለው መዘዝ ዓመታዊ የቱሪስት ገቢዋ መጠን ከ12 ቢሊዮን ብር ወደ 4 ቢሊዮን ገደማ የመውረዱ ችግር ሳይለቃት ሰሞኑን አዝመራዋን እምሽክ ያደረገ በአንበጣ መንጋ መቷታል።

 ከታሪክ እንደምንማረው ግብጾች ኢትዮጵያን እንደስትራቴጂክ ጠላት ማየታቸው ያልተጠቀምንበት ዓባይ ወንዛችን ያመጣብን መዘዝ እንጂ በድንበር ይሁን በጉርብትና የምንዛመዳቸው ሆነን አይደለም። ለኢትዮጵያ የሚደግሱት ስውር  የሁከትና የብጥብጥ እጃቸው ሳይሰበሰብ ምንም ሳንነካቸው እዳቸውን እየከፈሉ መገኘታቸው ያስገርማል። ምንም እንኳን የማንንም ጥፋትና ውድቀት ባንመኝም፤ ሳንደርስባቸው እየደረሱብን በሚመጣባቸው መርገም እኛ ተጠያቂዎች አይደለንም።  
ይህ ግብጽን እየበላና እየበረረ በማቋረጥ ላይ ያለው የሰማይ ላይ ነፍሳት መንጋ ወደእስራኤልም እንዳይዛመት የእስራኤል መንግሥት በድንበሮቹ ዙሪያ የተባይ ማጥፊያ መርዝ እየረጨ ይገኛል። 

ግብጾችም ሳያስቡት የደረሰባቸውን ውርጅብኝ ለመከላከል እየታገሉ ይገኛሉ። አንዳንድ ሚዲያዎች በዓለም ክርስቲያኖች ዘንድ የሚታወቀው «የጌታ ጾም» የተባለው በደረሰበት ሰዓት ይህ መቅሰፍት በግብጽ ላይ መምጣቱ ለምን ይሆን? ሲሉ ይጠይቃሉ።  በእርግጥ እንደመጽሐፉ ቃል የምጥ ጣር የመጀመሪያ ምልክቶች አንዱ ይሆን? የሁላችንም ጥያቄ ነው።