«በአርባምንጭ የመድኃኔዓለም
ሕንፃ ቤተክርስቲያን ግንባታ ላይ በብፁዕ አቡነ ኤልያስና በምዕመናን መካከል ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በዕርቅ ተደመደመ»
(
http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com)
በአርባምንጭ ከተማ በመሠራት ላይ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የሰሜን ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ሕዝብን ሳያማክሩ የዲዛይን ለውጥ በማድረጋቸው ምክንያት አለመግባባት ተፈጥሮ ግንባታው መቋረጡን ቀደም ሲል November 16, 2012 ባወጣነው ዘገባ መግለጻችን ይታወሳል፡፡
ለውዝግቡ መነሻ የሆነው የዲዛይን ለውጥ የመነጨው ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሲሆን "ማኅበሩ" አባሉ የሆነ አንድ ኢንጂነርን ከአዲስ አበባ ልኮ የሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ዲዛይን ባለ አንድ ጉልላት ክብ ሕንፃ እንዲሆንና ቀደም ሲል በሕዝብ ምርጫና ስምምነት ግንባታው ተጀምሮ የነበረው ባለሦስት ጉልላት ሕንፃ ቤተክርስቲያን እንዲቀር በመወሰኑ ነው፡፡