Thursday, March 7, 2013

«ጉዞው»


መንፈሳዊ ልቦለድ

የሀገርህን እወቅ ጉዞ ደስ ይለኛል። ባለኝ ትርፍ ጊዜ ወይም ዓመታዊ የሥራ ፈቃድ ያላየኋቸውን ታሪካዊም ይሁን ከባቢያዊ መልክዓ ምድሮች፤ የኅብረተሰብ አኗኗርና ባህል መጎብኘት በጣም ስለሚያስደስተኝ እነሆ ተሰናዳሁ። አዲስ አበባ አምስት ኪሎ ባለችው ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መግቢያ በር አካባቢ በተለጠፈ አንድ ማስታወቂያ ላይ ባገኘሁት አድራሻ መሠረት በዓመታዊው የመርጦ ለማርያም የንግሥ በዓል ላይ ለመታደም ከተጓዦች ጋር እነሆ ታድሜአለሁ።
 
አውቶቡሱ በተቀጠረለት ቦታና ሰዓት ቆሟል። እኔም ሰዓቱን አክብሬ ከቦታው ተገኝቻለሁ። ተጓዦችም ተሰብስበዋል። ግማሹ ሀገሩን ለቆ የሚሄድ እስኪመስል ድረስ የሚያመላልሰው ጓዝ የት የለሌ ነው። ጧፉ፤ ሻማው፤ጥላው ይጫናል። ግማሹ ለስለት፤ ግማሹም ለሽያጭ ነው። ነጋዴው የሚሸቅጠውን እቃ ይጭናል፤ ያስጭናል። ከየአድባራቱ በተንሸዋረረ ጨረታ የሚገዙ ነጋዴዎች በዓላትን እየቆጠሩ ይሸቅጣሉ። የሥራ ፈጠራ ይሁን በተፈጠረው ሥራ የማትረፍ ክህሎት፤ ገንዘብ ለዋጩና ሻማ ሻጩ ብዙ ነው። ግርግሩ ለብቻው ነው። ዓለማየሁ፤ ዓለሚቱ፤ መንግሥቱ.........ከዚህም፤ ከዚያም የሰዉ ስም ይጠራል።  «ስሟ ስንቅ ነው የእመቤቴ» የሚል መዝሙር በትልቁ የከፈተ አንድ ተጓዥም ሲንቅ ሲጭን አይቻለሁ። ጆሮው ላይ ማዳመጫውን የወተፈና በመዝሙር ምርቃና ውስጥ የሰጠመ ሌላው ተጓዥም ምናልባት መንግሥቱ፤ ሀብታሙ....... እየተባለ ሲጠራ ያልሰማው በምናቡ መንግሥተ ሰማይ የገባ መስሎት ይሆናል። ቢሆንስ? ማን ያውቃል።

የንጋት ብርድ አጥንት ሰርስሮ ስለሚገባ የለብስኩትን ጋቢ እጥፋት ዘርግቼ ወደአንድ ጥግ ቆምኩኝ። ከእጄ የቪዲዮ ካሜራ በስተቀር የያዝኩት ምንም ጓዝ ስለሌለ ራሴን ከዚህ ግርግር የሰወርኩ እድለኛ አድርጌ ቆጠርኩት።  ሲፈጥረኝ ግርግር አልወድም። በሰርግና በበዓላት ድግስ ላይ ሰዎች ሲዋከቡ ሳይ ይገርመኛል። ግርግሩ ካለፈ ወደነበረ ማንነት መመለስ ስላለ ያንን መዘንጋት መስሎ ስለሚሰማኝ ምንም አይመስለኝም።  ትንሹን ነገር አዋክበው የተዋጣለት ግርግር መፍጠር የሚችሉ ሰዎችን ሳይ ይገርመኛል። መርጦ ለማርያም ለዓመታዊ ክብረ በዓል ለመሄድ መንፈሳዊነቱ ማድላት ሲገባው ይሄ ሁሉ ግርግርና አታሞ ይገርማል።

Wednesday, March 6, 2013

የይሖዋ ምስክሮች መሠረት ምንድነው?


ይህንን መረጃ ለማውጣት መነሻ የሆነን አንድ ጠያቂያችን ባቀረበው ጥያቄ ሲሆን ሌሎችም ስለይሖዋ ምስክሮች አነሳስ የበለጠ ግንዛቤ እንዲያገኙ በማለት እንዲያነቡ ወይም ዳውንሎድ እንዲያደርጉ አቅርበነዋል።በቀኝ ጠርዝ ያለውን ምልክት ተጭነው ገጹን ማስፋት ይችላሉ።

Monday, March 4, 2013

«ያዘዝሁህንም ቃል ኪዳኔንና ሥርዓቴን አልጠበቅህምና መንግሥትህን ከአንተ ቀዳድጄ ለባሪያህ እሰጠዋለሁ»

ከኒቆዲሞስ

 የተወደዳችሁ ደጀብርሃኖች እንደስማችሁ ብርሃንናሰላም ሊያመጣ የሚችል ጽሑፍ እያወጣችሁ እያስነበባችሁንና እንድንረዳላችሁ እየሞከራችሁ ነውና እግዚአብሔር ይስጥልን::በተቻለ መጠን በተለይ በተከፋፈልችው ቤ/ክርስቲያናችን ውስጥ ሰላም እንዲሆን የምትጽፉት ጽሑፍና ጥረታችሁ ያስመሰግናችኋል::ግን አንድ ነገር አስተውለን ይሆን?መለያየትና መከፋፈል መልካም ጎን የለውም እንደምንል ሁሉ መለያየት በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱ ያደረገበትን የእስራኤል ነገድን ሕዝብ ታሪክ በማን ልናላክክ ነው?በሰይጣን ወይስ በሰው?ታውቃላችሁ በ1ኛ ነገሥት ምዕራፍ 11:9-13 እና 29-40 ድረስ ያለውን ስናነብ የምናየው የማንን ሥራ ነው?ታዲያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ብትከፋፈል ምን ያስደንቃል?እኔ ፈራጅ ባልሆንና ባልናገር እውነቱንና ሐቁን ግን ለማሳየት እሞክራለሁ!!
 ( ቀሪውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ )