Saturday, February 23, 2013

ቅዱስ ሲኖዶስ ከታሪክና ከትውልድ ወቀሳ ለመዳን ምርጫውን ሊያዘገይ ይገባል!


አሁን ነገሮች እየጠሩ ወደ መቋጫው ደርሰዋል። ፓትርያርኩ ማን መሆኑም እየታወቀ ሄዷል ከማለት ይልቅ ታውቋል ማለት ይቀላል። ከሁሉም የሚያሳስበውና የሚያሳዝነው በእነ ኑረዲን ኢሊያስ፤ በእነ እጅጋየሁ ኤልዛቤል፤ በእነእዝራ የዐመጽ አለቃ ፤ በእነ ፋንታሁን የከሰረ ዐረብ፤ በእነ ኃ/ሥላሴ ሆድ አምላኩ  በመሳሰሉ የ21ኛው ክ/ዘመን የቤተ ክርስቲያን ሸክሞች ግፊትና ዘመቻ የሚመረጥ ፓትርያርክ ሊኖረን መሆኑን ስናስበው ያሳዝናል፤ ያበሳጫልም። ትልቁ ሃዘናችን  የአቡነ ማትያስን  ድክመትና ጥንካሬ በመመዘን ሳይሆን ባሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንኳን ቀጣዩ ፓትርያርካችን አድርገን እንዳንቀበላቸው የሚያስገድዱን ነገሮች ገና ፓትርያርክ ሳይሆኑ ዙሪያቸውን ተሰልፈው ያሉትን ጎግ ማንጉግ ስንመለከት ነው። መንግሥት ደግሞ በኃላፊነት ስሜት ሂደቱን በማገዝ አድማውን፤ ዐመጹን፤ ዘመቻውን፤ ሰልፉንና ጦርነቱን በማስቆም  የካርድ ምርጫ ከመንፈሳዊ ምርጫ ጋር የሚስማማ ባይሆንም እንኳን አጠቃላይ ምእመናን በነጻና በግልጽ የተሳተፉበት ምርጫ እንዲመስል ማድረግ ሲገባው ከወሮበሎች ጋር ግንባር መፍጠሩ አሳዛኝም፤ አሳፋሪም ነው። የሾለኩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አቡነ ማትያስ በሀገረ ስብከታቸው ሳሉ ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን የስልክ መልእክት እንደተደረገላቸውና መመረጣቸው እርግጥ በመሆኑ ጓዛቸውን ሸክፈው አዲስ አበባ እንዲገቡ መደረጉን ነው።  ምርጫው ላይ መንግሥት ስውር እጅ መስደድ ምን ትርፍ ለማግኘት ይሆን? የተሳሳተ ስሌትና በስሜት የሚነዳ ተግባር ከመሆን አያልፍም።

በሌላ መልኩም ዜግነታቸው አሜሪካዊ ቢሆንም በአሜሪካ ሕግ ሁለት ዜግነት መያዝ ስለሚቻል አቡነ ማትያስም በዚሁ ሁለት ዜግነት እየተጠቀሙ መገኘታቸውን መረዳት ተችሏል።  ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ሕግ ሁለት ዜግነትን ባይፈቅድም ላለፉት በአሜሪካ ኖረው ከደርግ ውድቀት በኋላ  ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ ኢትዮጵያዊ ዜግነትን አድሰው በኢትዮጵያ የጉዞ ዶኩሜንት እንደሚጠቀሙ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። በአሜሪካዊ ዜግነታቸው ደግሞ አሜሪካ ውስጥ የራሳቸው የግል  ቤተክርስቲያን አላቸው። የጡረታ ባለመብት ናቸው።  ይሁን እንጂ ለፓትርያክነት ሥልጣን እርግጠኛ  የሆነ  ዋስትና ካገኙ አሜሪካዊነትን የማይጥሉበት ምክንያት አይታየንም። ምክንያቱም አሜሪካዊ ሆነው አርጅተውበታልና እንደወጣትነት ዘመን አያጓጓቸውም። ይልቅስ ከሰለቹበት አሜሪካዊነት ይልቅ ያላዩት ፓትርያርክነት ይናፍቃልና ዜግነታቸውን መልሰው ለመቅረብ የመቻላቸው ነገር ብዙም አይከብዳቸውም። ደግሞስ ፓትርያርክን ያህል ሥልጣን ለመስጠት ከተቻለ አሜሪካዊ ነህ፤ አይደለህም ብሎ ማንኛው ሰው ይሆን ሀሞት ኖሮት የሚመረምረው?

ይህ ሁሉ ቢሆንም የዘንደሮው የፓትርያርክ ምርጫ አሳዛኝ፤ ታሪክ የሚያበላሽ፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚያቆስል ከመሆን ያለፈ አይሆንም። ከዚህም የተነሳ ለመንግሥትና ለቅዱስ ሲኖዶስ ከታች የተመለከተውን ጩኸት ለትልቁ ጆሮአቸው ማሰማት እንወዳለን።


በተለይ ለኢትዮጵያ መንግሥት፤


መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው የሚል ሕግ ቢኖርም እንደኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ይህንን የአሜሪካውያንን ሕግ ለመተግበር ይቻላል ብሎ ማሰብ ራስን ማታለል ነው። በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት እነዚህ ሁለት ክፍሎች ግልጽም ስውርም ግንኙነት አላቸው። በዚህ ጽሁፍ ያንን ወደማብራራት አንገባም። ነገር ግን ማሳሰብ የምንወደው ነገር እንደዜጋም፤ እንደ እምነት ሰውም የምንናገረውን ሊሰማን ይገባል። ምንም እንኳን የኛ ማሳሰቢያ ሚዛን ባይደፋ፤ ማሳሰቢያችንን  መስማት የሚችልበት እድል ባይኖር  የመንግሥት ጆሮ ትልቅና  ከዝሆን የተሻለ ነው ብለን ስለምንገምት ጥቂት መናገር አስፈልጎናል።

1/ መንግሥት ካለፈው ስህተት ከመማር ይልቅ ስህተትን እንደተመረቀበት ሙያ መደጋገም የለበትም። የፈረንጆቹን አባባል በመዋስ በአጭር ቃል ላስቀምጥ። «በመጀመሪያ ስታልፍ የመታህ የድንጋይ እንቅፋት፤ ዳግመኛ ስትመለስ ቢመታህ ድንጋዩ አንተ ነህ» ይላሉ። ስለዚህ ዳግመኛ ስህተት መሥራት የለበትም።

2/ አሁን ላለው የቤተ ክርስቲያን ቀውስና ምስቅልቅል ሙት ወቃሽ አያድርገኝና የምናከብራቸው አባት አቡነ ጳውሎስ ትልቅ ድርሻ ነበራቸው። ማንን መሾም እንዳለባቸው ያለማወቃቸው፤ ገንዘብና አስተዳደር ላይ የነበራቸው ድክመት፤ ሥርዓተ አልበኞች እየተፈለፈሉና እየፋፉ የሚሄዱበትን ሁኔታ ለማስቆም የሚያስችል  ሥራ  ባለመሰራቱ ይህንን ሁሉ ወዝፈው አልፈዋል። ዛሬ ያንን የተረዳ፤ ማስወገድ የሚችል ብርቱ፤ በሥራው የተመሰከረ፤ ለተግዳሮቶች ራሱን ያዘጋጀ መሪ እንዲኖረን እንፈልጋለን። ስለዚህ መንግሥት ያለፈ ስህተቱን በመድገም እኔን ብቻ የማይቃወም ይሁን በሚል ስሌት ይህችን ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን ማጥፋት የለበትም።

3/ እርግጥ ነው፤ መንግሥት ቤተ ክርስቲያን  ራሷን ችላ በመንፈሳዊ እድገት፤ በልማትና በማኅበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንድትገባ ይፈልጋል። ድጋፍም እንደሚሰጥ ይገመታል። ነገር ግን የእርስ በእርስ መጠላለፋችንን እያየ እጁን ለማስገባት መሞከሩ ነገሩን ከማባባስ በስተቀር ጤና የሚሰጣት አይሆንም። ስለዚህ  መንግሥት ከራሱና ከጥቂት የቤተ ክርስቲያን ሹመኞች ጋር ብቻ የሚያደርገውን ግንኙነት በልክ አድርጎ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ያገባኛል ከሚለው ነገር ግን ቦታ ካልተሰጠው ሕዝብ ጋር ሆኖ የእውቀት፤ የታሪክ፤ የባህል፤ የቅርስ፤ የትውፊት ባለቤት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ወደፊት እንድትሄድ ድጋፍና እገዛ ማድረግ ይገባዋል።

Friday, February 22, 2013

ሰበር ዜና – ለዕጩ ፓትርያርክነት የተመረጡት ሊቃነ ጳጳሳት ታወቁ !!


ከዚህ ቀደም ስንል እንደቆየነው ከብዙ እጩዎች መካከል አምስቱን የመለያው መስፈርት ግልጽ ባለመሆኑ የአስመራጭ ኮሚቴው መልካም ፈቃደኝነት የሚወስነው እንደሚሆን በነበረን ግምት መሠረት ለ6ኛ ፓትርያርክነት የታጩትን አምስት ጳጳሳት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ለቋሚ ሲኖዶስ ማቅረቡ ተሰምቷል። በዚህ መካከል ሌላ አዲስ ክስተት እስካልተፈጠረ ድረስ የአባ ሳሙኤልና የአባ ገብርኤል እጩ ሆኖ የመቅረብ ነገር ውድቅ ሆኗል። በእርግጥም የጭለማው ቡድን ተብሎ የሚጠራው ክፍል የትግሉን ድል እያጣጣመ ወደሚገኝበት እርከን ተሸጋግሯል። በሌላ መልኩም ጥላወጊ የሆነው  ያ ክፉ ማኅበርም የስኬት ደረጃውን አሳድጓል ማለት ይቻላል። ከእንግዲህ የሚኖረው ወሳኙ ፍልሚያ በጥላ ወጊው ማኅበርና በጭለማው ቡድን መካከል ይሆናል ማለት ነው። ያ ማለት ደግሞ በሁለት ሊቃነ ጳጳሳት መካከል ወደሚደረግ ውድድር ተሸጋግሯል ማለት ነው። የሰልፉን ብርታት አይተን ግምታችንን ስንወስድ ሌሎቹ እጩዎች ለማሟያነት የቀረቡ ናቸው። ምናልባትም የእነ ኤልያስ አብርሃ ፓርቲ የሆነው የጭለማው ቡድን  ሥልጣንን መከታ አድርጎና ከኋላ የድጋፍ ኃይሉን አስታኮ ያንን ጥላ ወጊ ማኅበር ሊያሸንፍ እንደሚችል አስቀድሞ መገመት ይቻላል። ረጂም እጅ እንደገባም ዘግይቶ የወጡ መረጃዎች ይናገራሉ። በምርጫው ውስጥ የሰዎች ምርጫ እንጂ የመንፈስ ቅዱስ አሠራር በጭራሽ የለም።

                                                                                                                          

        የእጩዎች የምርጫ ሂደት ሐራ ዘተዋሕዶ እንዲህ ዘግቦታል።

  •     ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል አልተካተቱም
  •     ሁሉም የኮሚቴው አባላት በውሳኔው ስለመስማማታቸው አጠራጣሪ ኾኗል
  •     የፓትርያሪክነት መመዘኛ መስፈርቱ ከዕጩዎች ማንነት ጋራ በአግባቡ ይረጋገጥ
  •     ‹‹ዕጩዎቹን ስታውቅ ፓትርያሪኩን ታውቃቸዋለኽ››› /ሰሞንኛ አባባል/
የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ ለዕጩ ፓትርያሪክነት አጣርቶ የለያቸውን አምስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ለቋሚ /ሲኖዶሱ ማቅረቡ ተሰማ፡፡ ከየካቲት ዘጠኝ ቀን ጀምሮ የዕጩዎች ልየታ ሲያካሂድ የቆየው አስመራጭ ኮሚቴው÷ ለፓትርያሪክነት ለመመረጥ ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ስም ዝርዝር፡-

1)  ብፁዕ አቡነ ማትያስበኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስ

2)  ብፁዕ አቡነ ማቴዎስየወላይታ ዳውሮ /ስብከት ሊቀ ጳጳስ

3)  ብፁዕ አቡነ ዮሴፍየባሌ /ስብከት ሊቀ ጳጳስ

4)  ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤልየከፋ ሸካ ቤንች ማጂ /ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

5)  ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕየሰሜን ጎንደር /ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡

«የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው» ፪ኛ ቆሮ ፲፩፤፳፰


 በዘመኑ የግንኙነት መሣሪያ በሆነው መረጃ መረብ ላይ ተቀምጠን ከውድ ጊዜያችን ላይ ቀንሰን የምናካፍለውን መልእክት አንዳንዶች እነሱን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንድናስተላልፍ  ይፈልጋሉ። ገሚሶቹ ደግሞ የሆነ ስውር ዓላማ አንግበን የተሰለፍን  አስመስለው ይስሉናል። አንዳንዶቹም በእግዚአብሔር መንግሥትና አሁን ባለው ምድራዊው የቤተክህነት አስተዳደር መካከል ያለውን ልዩነት በደንብ ያልተረዳን አድርገውም ይገምታሉ። በተለይም የሰሞኑን የፓትርያርክ ምርጫን በተመለከተ የምናወጣቸውን ዘገባዎች የሚያስከፋቸው ሰዎች እንዳሉ ለማወቅ ችለናል። በዚህም ይሁን በዚያ የእግዚአብሔር እቅድና ዓላማ እንዳይሆን የሚከለክል ምንም ኃይል እንደሌለ እያመንን የእኛ ዓላማና ፍላጎትም ምን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ሥራና ዘመን  እንዲመጣ ከመፈለግ የመነጨ ትግል ለማድረግ ብቻ እንደተሰለፍን ለሚጠሉንም ሆነ ለሚወዱን ማሳወቅ እንፈልጋለን።
ይህንንም አቋማችን ከሐዋርያው ጳውሎስ ቃል ተውሰን በአጭር ቃል ስናስቀምጠው ««የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው» ፪ኛ ቆሮ ፲፩፤፳፰ እንዳለው የቤተ ክርስቲያናችን ነገር ብቻ ያሳስበናል።
አንዳንዶችን ቅር የሚያሰኝ፤ ሌሎችን ደግሞ የሚያሳዝን፤ ለገሚሱም ደስታን የሚሰጥ መረጃ ስናወጣ በእኛ በኩል ያለው ስሌት ግን አንድ ሃሳብ ብቻ ነው፤ እሱም የእግዚአብሔር መንግሥት እንዳይስፋፋ መንገድ ላይ ያሉ ጋሬጣዎችን እየነቀስን በማሳየት ሰው በመረጃና በእውቀት እውነቱን እንዲረዳ ማድረግ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከዓለም ቀደምት ቤተክርስቲያን ተርታ የምትመደብ ቤተክርስቲያን ናት። በእውቀት የበለጸገች፤ በአስተምህሮ የዳበረች፤ በትውፊትና በታሪክ ከፍተኛ ስፍራ የያዘች መሆኗም ለማንም የሚሰወር አይደለም።  ይሁን እንጂ እንደቀደምትነቷ ወደኋላ እየሄደች፤ በአስተምህሮዋ እየደከመች፤ በአስተዳደሯ እየወደቀች፤ በትውፊቷ እየኮሰመነች፤ በታሪኳ እየተሸፈነች መሄዷ በገሃድ የሚታይ እውነት መሆኑንም መካድ አይቻልም።
በቁጥር 75 የእስልምና ሰዎች መካና መዲናን ለቀው ወደኢትዮጵያ ሲሰደዱ ክርስትና የኢትዮጵያ መንግሥታዊ ሃይማኖት ነበር። መንግሥቱንም፤ ጉልቱንም፤ሕዝቡንም ትቆጣጠር የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ከኋላዋ የመጣው እስልምና አንድም የዐረብ ተወላጅ ሳይኖረው የሸሪአ መንግሥት ለማቋቋም የሚያስችል ኃይል አለኝ እስከማለት የደረሰው የቤተ ክርስቲያኒቱ እድገት እንደመሠረቱ ከፍ እያለ መጓዙን ሳይሆን እያቆሽቆለቆለ  የመሄዱ አንዱ ማሳያ ነው ብሎ መጥቀስ ይቻላል። እንደዚሁ ሁሉ ከ16ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ ብቅ ጥልቅ ይል የነበረው የአውሮፓውያን የወንጌል ሰዎች እንቅስቃሴ በስውር የነበረው ስርጭት ዛሬ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አባላትን ማፍራት የቻለው ይህችው ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ቤተ መንግሥቱን፤ ቤተ ክህነቱንና ሕዝቡን እስከጉልተ ርስቱ  የመቆጣጠር አቅም እያላት መሆኑን አይተን ዛሬ ላይ የደረሰችበትን ደረጃ ስንመረምር ሽቅብ ሳይሆን እያቆለቆለች መጓዟን ቢመረንም የሚታየውን እውነታ መቀበል የግድ ይለናል።
በተለይም ቤተ ክርስቲያኗ የነበራትን የክብር ሥፍራና መንፈሳዊ ኃይል ቀስ በቀስ እያጣች በዝናና በስም ብቻ ወደመኖር የደረሰችው ዘርዓ ያእቆብ የተባለውን ሰው ንጉሥ አድርጋ ከተቀበለች ወዲህ ባሉ ዘመናት ውስጥ ስለመሆኑ፤ እውነት በሀሰት ሰርዶ ተሸፍኖ የሌለ ታሪክ እውነት እንዲመስል ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እንደሆነ ታሪክ አፍ አውጥቶ እየተናገረ ይገኛል።  ዛሬ ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ  በአንድ በኩል  ከቅዱሳኖቿ እንደ አንዱ አድርጋ የምትቆጥረው ፤ በሌላ መልኩም በተደለዘው ገድሏ ከሰውነት ተርታ አውጥታ ከውሾች መድባ የምትረግመው ሰማእቱ አባ እስጢፋኖስንና ደቀ መዛሙርቱን እያሳደደች ለ100 ዓመት ባሳረፈችባቸው ሰይፍ የፈሰሰው ደም በዐውደ ምሕረቷ ላይ እየጮኸ እነሆ የሰማይ ክሳት ተለቆባት እየከሳችና እየደከመች በመሄድ ላይ ትገኛለች። የግራኝ ወረራ፤ የድርቡሽ፤ የግብጽ፤ የቱርክ፤ የጣልያን ሰይፍ የወረደው ሳያንስ እርስ በእርስ ስንበላላ ኖረናል።