Thursday, February 21, 2013

መንግሥት የፓትርያርክ ምርጫውን እድል ለ50 ሚሊዮኑ ምእመን ይሰጥ!!

  •       መንግሥት እንደፓርቲ ሹም ራሱ ያስቀምጥበት፤ አለበለዚያም ምእመኑ የፈለገውን እንዲመርጥ ጳጳሳቱን አደብ ያስገዛ!!
  • አሁን በተያዘው መንገድ ሄዶ አንዱ ቢመረጥ፤ መንግሥት የፈገለውን ሾመ መባሉ ወይም በቡድን ዘመቻ የተደረገ ምርጫ መሰኘቱ አይቀርም!!
  • ጳጳሳቱ ወደየ ሀገረ ስብከቶቻቸው ተበትነው ሕዝቡ ራሱ ተወያይቶ ይምረጥ!!
አንዳንዶች የአዲስ አበባውን የፓትርያርክ ምርጫ ከእርቅ በፊት መደረጉን ይቃወማሉ። እንደገና ተመልሰው እነ አቡነ እገሌ ወደምርጫው መግባት አይገባቸውም ነበር ይላሉ። ምርጫውን መቃወም አንድ ነገር ነው። እነ አቡነ እገሌ መመረጥ የለባቸውም ማለት ደግሞ ሌላ ነገር ነው። « በማንኪያ ሲፋጅ፤ ሲቀዘቅዝ በእጅ» የሚባለው ይሄ ነው።  እንኳን ሰው ዝንጀሮም ቢሾም ከምርጫ በፊት እርቅ ይቅደም ባዮችን አይመለከታቸውም። በምርጫው ላይ እነማን ይታጫሉ ብሎ ወደመከራከር ከተገባ የምርጫውን አስፈላጊነት እንዳመኑ ያስቆጥራልና። አለበለዚያም ቀድሞውኑ እርቅ ይቅደም ማለት የተፈለገው ለማምታት ነበር ማለት ነው። በአጭር ቃል ሲነገር እርቅ ይቅደም ባዮች በሀገር ቤት ውስጥ ያለውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ከመቃወም በስተቀር እነማን ይወዳደራሉ ብሎ ሚዛን ላይ ማስቀመጥ የለባችሁም።
በሌላ መልኩ ምርጫ መደረግ አለበት ባዮችን የሚያሳስበው ነገር እስከ አሁን ድረስ ከተደረጉ የፓትርያርክ ምርጫዎች ይኽኛው የከፋ ገጽታን የማስተናገዱ ጉዳይ ነው። የአቡነ ሳሙኤል ቡድን በአንድ በኩል፤ የአቡነ ጢሞቴዎስና የመሐመድ ሚስት በሌላ በኩል፤ የማኅበረ ቅዱሳን ቡድን በሦስተኛ ረድፍ፤ የወሎ ማኅበር በዐራተኛ ሰልፍ፤ እንዲሁም ሌሎች በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ቡድኖች ያቺን አንድ ወንበር ለማግኘት ወጥረው ይዘዋል። ገንዘብ ይረጫል፤ ጦርና የጦር ወሬ ይሰበቃል፤ አፋኝና ስለላ ይዋቀራል። ባሎቻቸውን የማስለቀስ የዳበረ ልምድ ያላቸው መበለቶች ቤተ ክህነቱንም ለማስለቀስ ቤት ሽያጭ ድረስ ፉከራ ማሰማታቸው ቤተ ክህነቱ ወደሞት እያዘገመ መሄዱን እንጂ ታታሪ ሰዎች መሰለፋቸውን አያሳይም።
ሐራ ተዋሕዶ እንደዘገበው «በስመ ደኅንነት ያጭበረበሩ 40 ግለሰቦች ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው፤ እነንቡረ እድ ኤልያስ የመራጮች ዝርዝር እንዲሰጣቸው ጫና እየፈጠሩ ነው። ለስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ እየተደረገ በሚገኘው ቅድመ ዝግጅት፣ የየራሳቸውንምርጥይዘው የቡድን እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ያሉ አካላትን ያስተባብራሉ ለተባሉ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳት መንግሥት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተሰማ፡፡ ማስጠንቀቂያው የተሰጣቸው ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ እና የምሥራቅ እና ምዕራብ ሐረርጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው፡፡ በማለት አስንብቦናል።
እንግዲህ ቀደም ሲል እንደቆየው ሁሉ ዛሬ ሁከቱና እሳቱ ተባብሶ ቤተ ክህነት ግቢ እየነደደ ለመሆኑ ማሳያ ነው።ጥንቱንም ቢሆን የቡድን ዘመቻ  እጅ ያልተለየው ቤተ ክህነት፤ ከምርጫ ቦርድ እውቅና በሌለው የጳጳሳት ፓርቲ እየታመሰ መገኘቱ አስገራሚም፤ አሳዛኝም ነው።  ጥቅመኞችና ሥልጣን ፈላጊዎች አባ ሳሙኤልን ይላሉ። ሌቦችና ማጅራት መቺዎች የቤተ ክህነት ችግር በረጂም ጢም የሚፈታ ይመስል አባ ማትያስን ይላሉ፤ አድባዮችና ወላዋዮች ዘክልዔ ልብ አባ ገብርኤልን ይላሉ። ዘረኞችና ነገር ጠምጣሚዎች አባ ማቴዎስን ይላሉ። መንታ መንገድ ላይ የቆሙ አስመሳዮች ደግሞ አባ ሉቃስ ይሁኑልን ይላሉ። ከሥር ደግሞ ፍልፈሎች፤ አይጦችና ወሮበሎች የየድርሻቸውን ሲጥ ሲጥ ይላሉ። ቤተ ክህነት በእንደዚህ ዓይነት ሰዎች ተከባለች። «ከነማን ጋር እንደምትውል ንገረኝና ማንነትህን ልንገርህ» የሚባለው ለዚህ አይደል? እየታየ ያለው የሰዎቹ ግብር፤ ማንነታቸውን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መስታወት ነው።

Wednesday, February 20, 2013

ሰላም ለተዋሕዶ እምነት ተከታዮች

በይትባርከ ገሠሠ

 (ይህ ጹሑፍ በሰንደቅ ጋዜጣ 8 ዓመት ቁጥር 389 ረቡዕ የካቲት 13/2005 ታትሞ የወጣ ነው)

በመጀመሪያ የጠራ እምነትና ቃልን መሠረት ማድረግ ይገባል። ስለ እምነት ስንናገር የቁልምጥ ቃላትን ልንጠቀም አይገባም። ዘወትር የክርስቶስ ትምህርት 4 ወንጌላትን ማንበብ ይገባል። ፈሪሳዊያንና ሰዱቃዊያን በስሕተት ጥያቄ ሲዳፈሩት ክርስቶስ ኃይለ ቃል ያለበትን መልስና ትምህርት ያቀርብ ነበር።
በቴክሳስ የተደረገው ጉባኤ እንደ እምነት ወግ የዘገየ ቢሆንም ሙከራው መልካም ነበር ማለት ይቻላል። መሠረተ ይዘቱ ስንመረምር ግን የተጣላች ቤተ ክርስቲያን አይደለችም፡ አንድ ናትና። የተጣላ እምነት አይደለም። እምነት ወይም አምላክ አንድ ነውና። እኔ ልሾም እኔ ልበልጽግ በማለት የተጣሉት መነኮሳት ናቸው እንጂ። ህዝበ ክርስቲያኑ በማያውቀው ምሥጢር እርስ በራሱ ተለይቶ ይኖራል። ምንኩስና ሥርዓት ለሥልጣኑ ሲል በሚፈጥረው ሰበብ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ህዝበ ክርስቲያኑ ሲጨፈጨፍ ሲጣላ ኖሮአል። እንዲህ ሊሆን የቻለውም የምንኩስና ሥርዓት ያለ ታሪኩ፡ ያለ መደቡ፡ ያለ ቦታው፡ ያለ ውሉና……የመሳሰሉትን ሁሉ ረግጦ ከቤተ ክርስቲያንዋ ቁንጮ ወጥቶ ስለ ተከመረ ነው። አሁንም የሚነታረኩ ለራሳቸው ሥልጣን እንጂ ለቤተ ክርስቲያን ክብርና ለምእመናን አንድነት እንዳይደለ በድርድራቸው ኂደት ማወቅ ይቻላል። መነኩሴና መነኩሴ ተደራድረው የሚፈይዱት ውጤት እንደማይኖር አስቀድሞ ማወቅም ብልህነት ነው። ለዚህ መድኀኒቱ ሌላ ነው። እሱም ሊቃውንት፣ ካህናትና ህዝበ ክርስቲያን አንድ ኃይል ፈጥረው ተዋሕዳዊ መሠረተ ሕግ ካልጣሉበት በቀር እየተድበለበሉ፡ ህዝበ ክርስቲያኑን እያሳዘኑና በነጣቂዎች እያዘረፉ መኖር ነው።
ለመሆኑ አቡነ መልከጼዴቅ ማን ናቸው?
በኢትዮጵያ ኪነ ጽሑፍ ሥርዓት ጽሑፉ ቦታ እንዳያጣ የቀድሞ የክብር ስማቸው ተቀምጦአል። የተዋሕዶ እምነትና የንጉሡም ክብደት ተጨምሮበት ሊሆን ይችላል፡ አንድነትዋንና ክብሯን ሊጠብቁላት የመጨረሻው የክብር ቦታዋ አንድ ደረጃ በቀረው ላይ ሰየመቻቸው፤ አከበረቻቸው። ይሁን እንጂ አገር ውስጥ ሳሉም ለግላቸው ይጠቀሙባት እንደ ነበሩና ለተዋሕዶ እምነት አስተዳደር የማይታዘዙ እንደነበሩ ሕይወት ታሪካቸውን መመልከት ያስፈልጋል። አሁንም ውጪ ሀገር ኄደው ከመጀመሪያ ግንጠላው ጀምሮ የግንጠላው ተጠያቂ እሳቸው ራሳቸው ብቻ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይገባል። ለክብራቸው ለኑሮአቸው ሲሉ ቤተ ክርስቲያንዋን የከፈሏት እሰቸው ናቸው። አቡነ መርቆሬዎስ በፍጹም በዚህ ጉደይ ተጠያቂ ሊሆኑ አይገባም። ግንጠላው ሲከናወን አልነበሩምና። አገር ውስጥ ነው የነበሩ። ኋላ ከጥቁሩ ባሕር ኄደው ተቀላቀሉ እንጂ። አዘጋጁ እንደሚያውቀው አቡነ ይስሐቅም በእሳቸው ተገፋፍተው ፈጸሙት እንጂ አላሰቡበትም ነበር።
ወደ መሠረታዊ አጭር ታሪክ እንግባ። 1983 . የውጪው ተደራዳሪ ሲኖዶስ ነኝ የሚለው ሲገነጠል በመጀመሪያ የዘመኑ ምስክር አዘጋጁ እንደ ሆነ ማስቀደም ይገባል። ሐምሌ ወር 28 ሐሙስ ቀን ኒውዮርክ ከተማ ውስጥ ሰሚናሪ ኮሌጅ ከሚባል ቦታ ስብሰባ ተጀመረ። በየዓመቱ የአሜሪካ ርክበ ካህናት በአቡነ ይስሐቅ መሪነት ስንሰበሰብ ነበርንና ነው። በየዓመቱ የማይቀሩ የነበሩ በጣም የሚመለከታቸው ካህናት ቄስ አስተርአየ ጽጌና መምህር ፍሥሐ ጽዮን ካሣ የሚባሉ የዋሺንግቶን ዲሰ. ኑዋሪዎች ኢንፎርሜሽን ሳይኖራቸው አይቀርም ፤አንኄድም ብለው ቀሩ። አዘጋጁ ግን ከሥራው ያለ ክፍያ የሳምንት ፈቃድ ወስዶ ከዋሽንግቶን ዲሲ ወደ ኒው ዮርክ ከተማ ኄደ።
ከላይ እንደ ተጠቀሰው ስብሰባው የተጀመረው ሐሙስ ቀን ነበር። ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ ስብሰባው ሲከሃኄድ ተሠውሮበት ነው መሰል የሰማው ነገር አልነበረም። ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከኢትዮጵያ ሲኖዶስ እንገነጠላለን የሚል ሐዲስ ሐሣብ ሰማ። ሀላፊነቱ የአቡነ ይስሐቅ የነበረ ቢሆንም ተገንጣይ ስብሰባውን የመሩት ሊቀጳጳስ መልከጼዴቅ ነበሩ። ለግንጠላው ትልቅ ምክንያት ሆኖ የቀረበውም አባ ጳውሎስ ፓትርያርክ ሆነው (በነሱ አቀራረብ ሆኖ) ከኢትዮጵያ ሲኖዶስ ኅብረት አይኖረንም ነበር። ከዚህ ችግር የደረሰው የሰሜን አሜሪካ፣ የደቡብ አሜሪካና የኢሮፕ ሀላፊ ሊቀጳጳስ የነበሩት አቡነ ይስሐቅ ሳያስቡትና ሳይፈልጉት በአቡነ መልከጼዴቅ ግፊት ግንጠላው ተፈጽሞአል። እኛ ራሳችን ጠንቅቀን የምናውቀው ቢሆንም ኋላ ራሳቸው አቡነ ይስሐቅ ሳላስበው አሳስተውኛል ብለዋል። በመጀመሪያ በዚሁ ግንጠላ የተቃወሙት 1. አባ ሐዲስ ግደይ ከኒውዮርክ አሁን ሲያትል። 2. ስም ዘነጋሁ የቤርሙዳ ተወካይ ካህን። 3. ታናሹ አባ ይስሐቅ ከሚኒሶታ የመጡ። 4. ራሱ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ከዋሺንግቶን ዲሲ ነበርን። ደጋፊዎች፡ 1 አቡነ ይስሐቅ 2. ሊቀጳጳስ መልከጼዴቅ 3. ሊቀ ካህናት ምሳሌ ከካናዳ 4. ቄስ ከበደ ከምዕራብ ስቴቶች 5. ስማቸውን የረሳሁት ከኒውዮርክና ከሌላም። እነዚህ ሁለቱ ሊቃነ ጳጳሳት 5ኛው ፓትርያርክ እንዲመረጥ በቅድሚያ ኢትዮጵያ ውስጥ ተስማምተው ፈርመው እንደ ነበሩ በብዙ የቤተ ክርስቲያን ሰዎች ይታወቃል።
ግንጠላው ሲፈጸም አቡነ መርቆሬዎስ አገር ቤት ስለነበሩ የግንጠላው መሪ ወይም ተባባሪ ሊባሉ አይገባም።