Friday, May 25, 2012

ፋሲካ

             ምንጭ፦http://bethelhemm.blogspot.com
በሚያስፈራው ሌሊት ጩኸት ሲበረታ
ግብጽ ተሸበረች ጌታ በኩሯን መታ
ሞት መግባት አልቻለም ወደ እስራኤል ቤት
ታትሞ ስላየ የደም ምልክት
ደጃቸውን ዘግተው ፋሲካ አደረጉ
በደም ተከልለው ሌሊቱን አነጉ
ባሕሩን ተሻግረው ከነዓን ሲገቡም
የልጅ ልጆቻቸው ፋሲካን አልረሱም
ይህ ሥርዓት አልፎ የእግዚአብሔር በግ መጣ
ሰውን የገዛውን የሞት ኃይል ሊቀጣ
የሰው ፍቅር ስቦት ከሰማያት ወርዶ
ጠላትን ረታው ፋሲካችን ታርዶ 

በመስቀል ተሰቅሎ ስለሆነ ቤዛ
ወገኖቹን ዋጅቶ በራሱ ደም ገዛ
ንጉሡ እንዲገባ ደጆች አይዘጉም
ሌሊቱ አልፏልና የሚያሰጋን የለም
የሕይወታችን ጉበን በደም ታጥሯልና
ሞት እያየ አለፈን ኃይሉን አጥቷልና
ለምሕረት በሚጮኸው የደሙ ምልክት
ባሕሩን ከፍለን አልፈን እንገባለን ገነት
የዘላለም አምላክ የምስጋና ጌታ
ምርኮን የማረከ ማኅተሙን የፈታ
ሞትን ድል የነሳው የናዝሬቱ ኢየሱስ
በዙፋኑ ያለው የአርያም ንጉሥ
ከፍ ከፍ ይበል ይድረሰው ምስጋና
መከራን ታግሶ ለእኛ ታርዷልና
ፋሲካን ስናደርግ ኖረን በእድሜ ጸጋ
ክርስቶስ ፋሲካ መሆኑን አንዘንጋ፡፡

Thursday, May 24, 2012

በፍርድ ፈንታ ደም ማፍሰስ በጽድቅ ፈንታ ጩኸት(ኢሳ. 5÷7)


                      ምንጭ፦ቤተ ጳውሎስ ብሎግ  

አንዲት ሕጻን ልጅ ሞታ የጎጃሟ አልቃሽ፡-
                         ምን ዓይነት ቄስ ናቸው የማይጠብቁ ዕቃ
                      እበተስኪያን ጓሮ እጣኒቱ ወድቃ
በማለት የሀዘን ቅኔ (ሙሾ) አሰምታለች፡፡ የቄሱ አንዱ ሥራ ዕጣን መጠበቅ ሲሆን ዋነኛው ሥራቸው ግን ሕጻናትን መጠበቅ ወይም ማሳደግ ነው፡፡ ሕፃናት ከቤተ ክርስቲያን አደባባይ ሊቀመጡ አባቶቻቸውን እያዩ ሊማሩ ሲገባ ከቤተ ክርስቲያን ጓሮ ከመቃብር ውስጥ ሲወድቁ ማየት አሳዛኝ ነው፡፡ አልቃሿ በሕፃናት ማለቅ ቀሳውስቱ ለምን አይጸልዩም ማለቷ ሲሆን ከዚያ ባሻገር ግን ትውልድን ለምን ይቀጫሉ? ማለቷ ነው፡፡ አባቶች አደራቸውን ባለመወጣታቸው ትውልዳችን የሞት ልጅ ሆኗል፡፡ ራሱን በራሱ እየመራ የዘመን ምርኮኛ፣ የኃጢአት ግዞተኛ ሆኗል፡፡ ይልቁንም በአባቶች ፈንታ እንዲተኩ ከዐውደ ምሕረቱ ሊቀርቡ የሚገባቸው ወጣቶች እየተገፉ ወደ መቃብር ስፍራ መውረዳቸው ዛሬም ልብ ያለውን የሚያስለቅስ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስም፡- “አሁን ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ ቅኔ እቀኛለሁብሏል (ኢሳ. 5÷1)፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ለእግዚአብሔር አዝኖ ወዳጅነቱን ለመግለጥ የሀዘን ሙሾ አሰምቷል፡፡ ስለ ወዳጅ ይለቀሳል፡፡ ወዳጅ በሞት ስለተለየ ብቻ ሳይሆን የጠበቀው እንዳልጠበቀው ሲሆንበት ይልቁንም ልጁን በሞት ሲያጣ ለወዳጅ ይለቀሳል፡፡ እግዚአብሔር ሕያው ወዳጅ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሞትን ስለመረጡት ትውልዶች ነው፡፡ እግዚአብሔር መንግሥቱ የማይነካ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ከእግዚአብሔር ፍቅር ለተፈናቀሉት ነው፡፡ እግዚአብሔር የማይጎድልበት ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሰላማቸውን ስላላወቁ ሕዝቦች ነው፡፡ በእውነት ካጣ ሰው ይልቅ አግኝቶ ያላወቀበት እጅግ ሊለቀስለት ይገባል፡፡ እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ለገፉ፣ ገነትን ታህል ቦታ ችላ ላሉ ልቅሶ ይገባል፡፡ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ለሟቾቹ ሳይሆን ለወዳጁ ለእግዚአብሔር ነው፡፡ የሰው ልጆች እንዳፈቀራቸው አለመገኘታቸው፣ እንዳደረገላቸው አለማመስገናቸውን ባሰበ ጊዜ ለወዳጁ አለቀሰ፡፡

አፍ በእነሱም ዘንድ አለ!


ማቅ( ማቅ፤ ማለት ጥቁር የሀዘን ልብስ ማለት እንደሆነ ልብ ይሏል?) ማቅ  ቅድመ ሲኖዶስ ለማሳካት ካወጣችው እቅድ ውስጥ በተወሰነ ደረጃ ማሳካቷን ሰምተናል። እግረ መንገዱንም ሲኖዶስ በምን በምን ጉዳዮች ላይ ሊወያይ እንደተዘጋጀና ምን ምን ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ለማወቅ የፈለገ ካለ ከማቅ ማእከላዊ ቢሮ በቂ መረጃ ሊያገኝ እንደሚችል ከበቂ በላይ አረጋግጦ አልፏል።እነ ማንያዘዋል በታክሲው ውስጥ የቀደዳ ወጋቸው ሲኖዶሱ ገና ሳይሰበሰብ «ሁሉም ነገር በኛ እቅድና መንገድ እንዲፈጸም ተመቻችቷል፤ ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም» ሲል ለኤፍሬም ካጽናናውና የድኅረ ሲኖዶስን  ውጤት ስንመለከት  በእርግጥም ሲኖዶሱ አስቀድሞ በተጠናቀቀ ውሳኔ ላይ መሰብሰቡን እና ማቅ ከማኅበርነት በላይ ሲኖዶሱን ለአስፈጻሚነት የሰየመችው ስብስብ እንደሆነም  ደረት የሚያስነፋ ንግግሩ አስረጂያችን ሆኗል ። በአጭር ቃል ስምዓ ጽድቅንና ሐመር መጽሔትን በማንበብ ወይም ቱባ የማቅ ሹመኛን በመጠጋት ብቻ ከእንግዲህ ወዲያ ባለው የሲኖዶስ ስብሰባ ላይ መወያያ የሚሆነውን አጀንዳ አስቀድሞ ማወቅ እንደሚቻል ተረድተናል። አባ ጳውሎስም አስቀድሞ የተዘጋጀላቸውን  ውሳኔዎችን ለማንበብ አሁን ከሚጠቀሙበት በተሻለ ደረጃ ፊደላትን የሚያጎላ መነጽር እንዲገዙ ብንመክራቸው የምናየው ነገር ሁሉ ለምክሩ አመላካች ነገር ነው። ፓትርያርክነቱን ፈንግሎ 7 ኰሚቴ በማዋቀር እሰጥ አገባ ውስጥ ከመግባት ፓትርያርኩን ባሉበት አስቀምጦ የ7 ቱን ኰሚቴዎች ውሳኔ እንዲያነቡ ማድረጉ አዲሱ የተዋጣለት የማቅ ስልት ነው። እኛም ይበል ብለናል! ግን እስከመቼ?
ማኅበሯ በተወሰነ ደረጃ የተሳካላት ነገር ያለ ቢመስልም በወሬ ሊደሰኰር ከሚችል ባለፈ  ምንም የሚጨበጥ ነገር አይታይም።
ለምሳሌ ብናነሳ፤ አባ ኅሩይን ከውድቀት ማዳን ወይም ወደነበሩበት ማስመለስ ብዙ ታግላለች። ይህም ማቅን ከኅሊና መላላጥ አውጥቶ ያሰበችውን ታዛዥ ሰው መታደግ ያስቻላት ሳይሆን ቀርቷል። ይህ ትልቁ ኪሳራዋ ነው። መፈንቅለ እንቍ ባህርይ ለማድረግ ያደረገችው ኩዴታም አልተሳካም። ይህም ኪሳራ ቁጥር ሁለት ነው።
 አባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤልንና መ/ሐዲስ በጋሻው ደሳለኝን ለማስወገዝ ያልፈለቀለችው ድንጋይና ያልቆፈረችው ጥልቅ ጉድጓድ አልበረም። ማን እንደሚገባበት እግዚአብሔር ብቻ የሚያውቀው የማኅበሯ ጥልቅ ጉድጓድ አፉን እንደከፈተ ህልሟ  ለወዲያኛው ዓመት ተሸጋግሯል። ሁሉን ለማየት የዚያ ሰው ይበለንና ለጊዜው ማቅ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ የደከመችበትና የለፋችበት የኃጢአትና የዐመጻ ስብስብ ጩኸቷ አልተሳካላትም። ይህም ሦስተኛው ኪሳራዋ ነው።
ተወግዘዋል ወይም ማእረገ ክህነታቸው ተገፎ «አቶ» ተብለዋል፤ በማለት የምታላዝነውን  ውሳኔ ስንመለከት፤ ከሚስተጋባ የገደል ማሚቱ ጩኸት በስተቀር የሚያዝ፤ የሚጨበጥ እውነተኛ ነገር አይታየንም። ምክንያቱም የወንጌሉ መምህር ጽጌ ስጦታውም ሆነ ወንጌልን በመተንተን ድንቅ ጽሁፎችን ያበረከተው ዲ/ን አግዛቸው ተፈራ ከቤተክርስቲያኒቱ በግፍ ከተባረሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል። እንዲያውም መምህር ጽጌ ስጦታው ነፍስና ስጋውን ለመለየት በደረሰ ድብደባ ነበር የደህና ሰንብት አሸኛኘት የተደረገለት። አሁን ያንን ድብደባ ለመድገም ካልሆነና አግዛቸውንም ሳንደበድበው አመለጠን ለማለት ካልሆነ በስተቀር የሌሉትን ሰዎች ማእረገ ክህነታቸውን ገፈን አውግዘናል በማለት የምታገኘውን ጥቅም  የምታውቀው የሀዘን ሸማ የሆነችው ማቅና ተላላኪ ጳጳሶቿ ብቻ ናቸው። እኛ ግን የሚገባን ነገር ቢኖር የግለሰቦቹን እንደኢትዮጵያዊ የመኖር መብታቸውን ለመግፈፍና፤ «ባልሰብክ ወዮልኝ» ያለውን ቃል እንዳይናገሩ አፋቸውን በመዝጋት፤ የማስተማር ነጻነታቸው ለመቀማት የተደረገ ጩኸት መሆኑን ነው። ስለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ከሊቃውንቱና ከመጻሕፍቱ ውጪ ያስተማሩት ነገር ካለ ስህተቱን በመጻህፍትና በሊቃውንቱ ወግ መልስ መስጠት እንጂ ማቅ በነዳችው ስብሰባ ላይ የሌለ ክህነት ቀምተናል፤ በዚያ ላይ አውግዘናል ማለት ቤተክርስቲያኒቱ በአላዋቂዎች መከበቧን ያመላከተ ስለመሆኑም ያረጋገጠ ሆኗል። የተባረሩት ቀድሞ አይደለም እንዴ? የዛሬው ስለምን ይሆን? ማውገዝ ያስፈለገው ብለን እንጠይቃለን።
እነ መልዓከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ በነበሩባት ቤተክርስቲያን ስለግብረ ሰዶም ከመጻፍ ያልዘለሉ ሰዎች ሞልተውባት ስናይ አውግዘናል የሚለው «እሪ በከንቱ » ጩኸት መታየቱ የግድ ነው። ሊቁ አባት ብጹእ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ብንድራቸው ይሻላል ያሏቸው ሰዎች ከከበቧት ቤተክርስቲያን በእውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ መጠበቅ ያልዘሩትን ለማጨድ ከመሞከር የተለየ አይደለም።