Tuesday, May 22, 2012

"ማኅበረ ቅዱሳን" የሚታዘዘው ለማን ነው?

                             http://awdeselam.blogspot.com
ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ሁኔታና የወደፊት ዕጣ የሚነጋገር ሁሉ የሚስማማበት አንድ ነገር አለ። ይኸውም "ማኅበረ ቅዱሳን" የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በአንድም በሌላም መንገድ በመከፋፈል እራሱን ብቸኛ የቤተ ክርስቲያንዋ ነጻ አውጪ አድርጎ የመመልከቱ ነገር ነው። አንዳንድ ጊዜማ ከማኅበሩ መመሥረት በፊት በቤተ ክርስቲያን ሥራ እንዳልተሠራ፣ እንዳልተደከመባት አድርጎ በድፍረት በመናገር የወጣቱን ክፍል ለማሞኘት ይሞከራል። 
ይህ ማኅበር ፊት የማያሳዩትን በስደት ውጪ ሀገር የሚኖሩትን አባቶች በማቃለልና ሃይማኖት ለዋጮች እንደሆኑ አስመስሎ በማቅረብ፣ ለብዙ ክብር የበቁትን፣ እያንዳንዳቸው ለቤተ ክርስቲያን ከሃምሳ ዓመታት በላይ የደከሙትን አባቶች በመናቅና በማዋረድ፣ ወጣቶች ለአባቶቻቸው አክብሮት እንዳይኖራቸው ሰድቦ በማሰደብ በስደት ባሉባቸው ቦታዎች ሲያሳድዳቸው ተስተውሏል አሁንም እየተስተዋለ ነው። በቅዱሳን ስም ራሱን ለሚጠራ ማኅበር የከበሩትን ማዋረዱ የተመረጡትን መናቁ ስሙ እንደማይገባው የሚያሳይ ነው።
ይህ ብቻ አይደለም። ይኸው ማኅበር በስደት ያለችውን ቤተ ክርስቲያን ሲያሳድድ “ከአዲስ አበባ ሲኖዶስ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ሥር የምተዳደር ነኝ” … “ሲኖዶስ አንዲት ናት” … “ከእናት ቤተ ክርስቲያን ጋር መደባለቅ ያስፈልጋል” በማለት በውጪ ያለውን ሕዝብ በመደለል ነው። ሙከራው እንዳሰበው ባይሳካለትም በቂ ጥፋት ለማጥፋት ያገኘውን አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሟል።

ማኅበሩ እራሱን በአዲስ አበባ ሲኖዶስ ሥር እንደሆነ አድርጎ ቢያቀርብም በምግባሩ ግን እዚያም ያሉትን አባቶች መከፋፈሉና አልታዘዝ ባይነቱ ዓይን እያወጣ ከመጣ ቆይቷል። እስከ አሁን አንዳንዶች በጠቅላይ ቤተ ክህነት የሚገኙ መምሪያ ኃላፊዎችንና አንዳንድ አባቶችን በገንዘብ፣ ሌሎችንም ደካማ ጎናቸውን አሰመልክቶ ምስጢር እንደሚያወጣ በማስፈራራት አፋቸውን ለጉሞ ቆይቷል። የወደፊቱን እግዚአብሔር ያውቃል። እንደሚታወቀው ይህ ማኅበር “አጥፍተሃል” … “ተሳስተሃል” ... “አሁንስ በቃ! ... አልበዛም እንዴ?” የሚለውን ሁሉ “ተሐድሶ ናቸው” በማለት ወይም “ኑፋቄ አስተምረዋል” ብሎ ስም በማጥፋትና አመጽን በማስተባበር ቅን የቤተ ክርስቲያንዋን አገልጋዮች ስም እያጎደፈ ነው። ብዙዎች ጭንቅ ሆኖባቸው የማኅበሩን ድክመት እያወቁ ተሸክመው ባልተማሩ ልጆች እየታዘዙ “ስቀሉ ሲባሉ እየሰቀሉ” “አውርዱ ሲባሉ እያወረዱ” ማኅበሩ ሊያገኝ ከሚገባው በላይ ሥልጣን እንዲኖረው ምክንያት ሆነዋል።
ያም ሆነ ይህ “ይህቺ ባቄላ ያደረች እንደሆነ አትቆረጠምም” እንደተባለው ወይም “ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቆመን ማውረድ እንዳያቅተን” ተብሎ እንደተተነበየው ዓይነት ነገር እንዳይመጣ ሁሉም ሊያስተውል ይገባዋል።
የወቅቱ የቤተ ክርስቲያን ችግር ማለትም የአባቶች መለያየትን ማኅበሩ የጥፋት ተልእኮውን ለመፈጸም ተጠቅሞበታል እየተጠቀመበትም ነው::  እንዲያውም ሁለቱንም ሲኖዶሶች በማቃለልና ባለመታዘዝ የማኅበሩን አጀንዳ የሚያካሂዱ ጥቂት አባቶችን እያታለለ ራሱን እንደ ሦሰተኛ አማራጭ እያቀረበ ነው:: ለዚህም ነው በሁለቱ ሲኖዶሶች መካከል ሰላም እንዲወርድ የማይፈልገው የተጀመረውን የሰላም የእርቅ እንቅስቃሴ ለማምከን የሚንቀሳቀሰው። በአባቶች መካከል ሰላምና እርቅ መምጣቱ ለቤተ ክርስቲያን የሚበጅ ሆኖ ሳለ በቤተ ክርስቲያን ሥር ነኝ ለሚለው ለ"ማኅበረ ቅዱሳን" አልዋጥ ማለቱ ማኅበሩ ድብቅና መሠሪ ተልእኮ እንዳለው በግልጽ የሚያሳይ ነው::      

ማኅበረ ቅዱሳን ከዳላስ ሚካኤል የዛሬ 2 ዓመት የቦጨቀው 120 ሺህ ዶላር የት ደረሰ?

ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ!!!!
የሚካኤልን ታቦት የከሰሱ ሰዎችን በማስቀደም ቤተክርስቲያኑን ለማፍረስ የሚታገሉት የወያኔ ተስፈኞች የጠሩት ስብሰባ መክሸፉን እንደሰማችሁ እናውቃለን። ህዝቡ እንደማይፈልጋቸው
፩ኛ፦ በምርጫ
፪ኛ፦ በጠሩት ስብሰባ ላይ ባለመገኘት እንደተፋቸው በድጋሚ አረጋግጦላቸዋል።

የሚካኤል ቤተክርስቲያን ከተቋቋመ ጀምሮ አንድ ጊዜ እንኳን በቦርድ አባልነት ተመርጠው  አገልግሎት ሰጥተው በማያውቁት በአቶ ጌታቸው ትርፌና ቤተክርስቲያኑ ከተመሰረተ ከቦርድ ወጥተው በማያውቁት በአቶ እዩኤል ነጋ አማካኝነት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የተሰገሰገውና የተሰባሰበው የፖለቲካ ድርጅት በቦርድ አባላት ምርጫ ላይ ተሳትፎ መሸነፉን ሁላችሁም የምታውቁት ነገር ነው።

ይህ ቡድን የሰላምና የአንድነት አስተባባሪ ኮሚቴ በመባል ይታወቃል። በውስጡም፦
፩ኛ፡- የሽማግሌዎች ኮሚቴ
፪ኛ፦ የአባላት ኮሚቴ እና
፫ኛ፦ የቀሳውስት ኮሚቴዎች አሉበት።
ለክፉ ቀን ያዋቀሩት ሽምቅ ድርጅት ነው። ይህ ሁሉ ደባ የሚፈጸመው ቤተክርስቲያናችንን ተገን በማድረግ ነው። ከላይ ስማቸው የተጠቀሰው ግለሰቦች ባለፈው ምርጫ ላይ ያቀረቧቸው ተወዳዳሪዎች ከዚህ ቡድን ድጋፍ በማግኘት ስልጣን ላይ አንዲቆዩና ደግመው እንዲመረጡ የተደረገው ሙከራ መክሸፉ ይታወሳል። በምርጫው ሲሸነፉ በመደናበር ሮጠው ከወያኔ እግር ስር ተደፉ። ወያኔም በገንዘብ ኃይል ድምጽ ገዝቶ ቢለግስም የምርጫዉን ዉጤት ግን መለወጥ አልቻለም።

የህዝብን ድምጽ አክብሮ መቀበል የተሳናቸው አቶ ጌታቸውና አቶ እዩኤልም ቀደም ሲል ምርጫውን እንዲያሸንፉ ሊረዳቸው ሞክሮ አቅም ወዳነሰው ቡድን ተመልሰው በውስጡ የተዋቀሩትን ኮሚቴዎች እንዲያንቀሳቅስ ትእዛዝ አስተላለፉ። ሁለቱ ግለሰቦች ደግሞ ቀደም ሲል ፕሮግራም በተያዘለት አመታዊ የምእመናን ስብሰባ ላይ ዶክተር ግርማንና አቶ አበራን ለማስወጣት የተንኮል ስራ ለመስራት ወስኑ። በምርጫ ያጡትን ወንበር ሁለቱን ተመራጮች በማባረር ዙረው ለመያዝ የተጠነሰሰ ሤራ ነበር። በዚህ መሰረት የወያኔ ተወካዮችም ከተቋቋመው ኮሚቴ ጋር ለመስራት ተስማሙ። በተደረሰው ስምምነት መሰረት ተስፈኛ ባለ ሃብቶች ሰብሰባውን እንዲጠሩ ተወሰነ። በጉባኤው ላይ የወያኔ ካህን መጋበዛቸው ይፋ ሲወጣ አቶ ጌታቸውና አቶ እዩኤል ከነተከታዮቻቸው ራሳቸውን ከስብሰባው አገለሉ። ወያኔወችም ብቻቸውን ቀሩ። ስብሰባውም ከሸፈ።

ግንባር ቀደም የስብሰባው መሪዎች የነበሩትም ከዚህ የሚከተሉት ናቸው፦
፩ኛ፦ አቶ ኃይሉ እጅጉ-

ቅዱስ ሲኖዶሱና ዘጠነኛ ቀኑ!


                                   ምንጭ፦ ዓውደ ምሕረት ብሎግ
  •  አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን /ቤት ላለማስረከብ አስቂኝ መከራከሪያ አቀረቡ
  •     ማኅበሯ ሌላው መንገድ ሁሉ አላስኬድ ሲላት አይመጥንም በሚል የሰንበት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊነትን ከመምህር እንቍባህርይ ላይ ለመንጠቅ የምታድረገው ሙከራ አልተሳካላትም።
  •     ማኅበረ ቅዱሳንን የመፍረስ ስጋትን ጥሎበት የነበረው የማኅበራት መተዳደሪያ ደንብ እንደገና ውድቅ እንዲሆን እንቅልፍ አጥቶበት የነበረ ሲሆን ድጋሚ እንዲጠና ታዟል።  

አባ አብርሃም ርስት ጉልቴ ነው ያሉትን የሀገረ ስብከቱን /ቤት እንዲያስረክቡ የታዘዙትን ትዕዛዝ ለመቃመም ከተነሳው ጥያቄ ጋር የማይሄድ እኔ ከእርስዎ እሻላለሁ የሚል መከራከሪያ አቀረቡ። እኔ ምን አለኝ እና ነው መልስ የምባለው? ሲሉ የነበሩት ሰው አሁን በራሴ ወጪ አጣሪ ተልኮ ከእኔ እና ከእርሰዎ ማን ጥሩ ስራ እንደሰራ ይጣራ? ሲሉ ጠይቀዋል። ይህም ጥያቄ አሜሪካ ለመመለስ ያላቸውን ከፍተኛ ጉጉት ያሳያል ተብሏል። ስውየውን የሚያስጨንቃቸው የቤተክርስቲያን ልጆች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተገኝተው አባትነትን ማሳየት ሳይሆን ጥቅምና ምቾት ባለበት ቦታ ላይ መንቀባረር መሆኑንም አሜሪካ ለመመለስ ያላቸው ከፍተኛ ፍላጎት ያሳያል።
አሁን በቅርቡ እንኳ ወደ ሐረር ሀገረ ስብከት እንደ ደረሱ ለኔ የተመደበችው መኪና የትኛዋ ነች? ብለው ሲጠይቁ ከእሳቸው በፊት ነበሩት አቡነ ዮሴፍ ይሄዱበት የነበረቸውን መኪና ሲያሳዩዋቸው ከት በለው ስቀው!  እኔ በዚህ መኪና ልሄድ? ብለው ጠይቀው ይህ መኪና ስለማይመጥነኝ በአስቸኳይ «ከሞኤንኮ» አዲስ መኪና ይገዛ ብለው አዲስ መኪና አስገዝተው በእስዋ መንፈላሰፍ ጀምረዋል። ድንቄም አባትነት።